fa
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

رفتن به کانال در Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

نمایش بیشتر
1 161
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ሉቃ. 2:1-8 "ወኮነ በውእቱ መዋዕል" - "በዚያም፡ወራት፡ዓለሙ፡ሁሉ፡እንዲጻፍ፡ከአውግስጦስ፡ቄሳር፡ትእዛዝ፡ወጣች። ቄሬኔዎስ፡በሶርያ፡አገር፡ገዢ፡በነበረ፡ጊዜ፡ይህ፡የመጀመሪያ፡ጽሕፈት፡ሆነ። ሁሉም፡እያንዳንዱ፡ይጻፍ፡ዘንድ፡ወደ፡ከተማው፡ሄደ። ዮሴፍም፡ደግሞ፡ከዳዊት፡ቤትና፡ወገን፡ስለ፡ነበረ፡ከገሊላ፡ከናዝሬት፡ከተማ፡ተነሥቶ፡ቤተ፡ልሔም፡ወደምትባል፡ወደዳዊት፡ከተማ፡ወደ፡ይሁዳ፥ፀንሳ፡ከነበረች፡ከዕጮኛው፡ከማርያም፡ጋራ፡ይጻፍ፡ዘንድ፡ወጣ። በዚያም፡ሳሉ፡የመውለጃዋ፡ወራት፡ደረሰ፥የበኵር፡ልጇንም፡ወለደች፥በመጠቅለያም፡ጠቀለለችው፤በእንግዳዎችም፡ማደሪያ፡ስፍራ፡ስላልነበራቸው፡በግርግም፡አስተኛችው። በዚያም፡ምድር፡መንጋቸውን፡በሌሊት፡ሲጠብቁ፡በሜዳ፡ያደሩ፡እረኛዎች፡ነበሩ።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

1.28 KB

29/3/2015 ዓ.ም (፳፱/፫/፳፻፲፭ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ምስሌከ ቀዳማዊ በዕለተ ኃይል። በብርሃኖሙ ለቅዱሳን። ወለድኩከ እምከርሥ እምቅድመ ኮከበ ጽባሕ፡፡ መዝ. 109፥3 🕯 ትርጉም ከአንተ ጋር ቀድሞ በኃይልህ ቀን። በቅዱሳን ብርሃን። ከአጥቢያ ኮከብ አስቀድሞ ከሆድ ወለድሁህ። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯

photo content
+1

❤ ከዚህም በኋላ መኰንኑ ቀውስጦስ ወደ ንጉሥ ሔዶ በዚያው በዘገየ ጊዜ ወንድሙ የመኰንኑን የቀውስጦስን ሚስት ሊአገባት አሰበ እርሷም በአወቀች ጊዜ አባታቸው እስቲመለስ ወደ አቴና ሔዳ ጥበብን ታስተምራቸወሰ ዘንድ ቀሌምንጦስንና ታናሽ ወንድሙን ይዛ በመርከብ ተሳፈረች። በዚያንም ጊዜ ብርቱ ነፋስ በመንፈሱ ማዕበል ተነሥቶ መርከቡ ተሰበረ ቀሌምንጦስም በመርከቡ ስባሪ ተንጠለጠለ የባሕሩም ሞገድ ወደ እስክንድርያ አገር አደረሰውና በዚያ ጥቂት ቀኖች ኖረ። በዚያንም ወቅት የከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ጴጥሮስ ቃል ጠራውና ወደ እስክንድርያ አገር እንዲሔድ አዘዘው በሔደም ጊዜ በውስጥዋ የወንጌልን ቃል ሰበከ ከዚህ ከቅዱስ ቀሌምንጦስ በቀር ከአገር ሰው አንድ እንኳን ያመነ የለም እርሱ የቅዱስ ሐዋርያ ጴጥሮስን ትምህርት በሰማ ጊዜ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ የክርስቶስን ጥምቀትን ተጠመቀ። ❤ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስም የጌታችንን የመለኮቱን ምሥጢር ለሚያመልኩትም የሚሰጣቸውን ብልጽግናውንና ክብሩን በስሙም ኃይል ድንቅ ተአምራትም እንደሚደረግ ገለጠለት። ከዚችም ዕለት ጀምሮ ቀሌምንጦስ ቅዱስ ጴጥሮስን ተከተለው ደቀ መዝመሩም ሆነ እርሱም የሐዋርያትን ገድላቸውን ከዐላውያን ነገሥታትና መኳንንት የደረሰባቸውን ሥቃይ ሁሉ ጻፈ። ከዚህም በኋላ በብዙ አገሮች ውስጥ አስተማረ ሐዋርያትም በጉባኤ ተነጋግረው የሠሩአቸውን የሥርዓት መጻሕፍትን ለርሱ ሰጡት። ❤ ከዚህም በኋላ በሮሜ አገር ሊቀ ጵጵስና ተሾመ በትምህርቱም ከሰዎቿ ብዙዎችን እግዚአብሔርን ወደማወቅ መለሳቸው። ስለርሱም ከሀዲ ንጉሥ ጠራብሎስ ሰምቶ ጭፍራ ልኮ ወደርሱ አስመጥቶ "ክርስቶስን ክደህ ለአማልክት ስገድ" አለው ትእዛዙንም ባልሰማ ጊዜ በዚያ ያሠቃዩት ዘንድ ወደ አንዲት አገር ሰደደው እርሱ በላዩ እንዳይነሡበት ከአገር ሰዎችና ከዘመዶቹ የተነሣ ፈርቷልና መኰንኑንም ጽኑዕ ሥቃይን እንዲአሠቃየው አዘዘው። ❤ የዚያችም አገር መኰንን በመርከቦች ውስጥ የሚኖር እግሮች ያሉት ከባድ ብረት በአንገቱ ውስጥ አንጠልጥሎ ከባሕር ውስጥ አሠጠመው ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ ወንጌልን እንደ ሰበኩ ሐዋርያትም በመንግሥተ ሰማያት የምስክርነት አክሊል ተቀበለ። ❤ እንዲህም ሆነ አንዲት ዓመትም ስትፈጸም ባሕሩ ተገልጦ እንደተኛ ሁኖ የቅዱስ ቀሌምንጦስ ሥጋ በጥልቁ ባሕር ውስጥ ታየ። እርሱም ሕይወት ያለው ይመስል ነበር ሰዎችም ገብተው ከእርሱ ተባረኩ የከበረ የደንጊያ ሣጥንም አምጥተው ሥጋውን በውስጡ አድርገው አንሥተው ከባሕር ውስጥ ሊአወጡት ፈለጉ ግን ከቦታው ሊአንቀሳቅሱት አልቻሉም ከባሕር ውስጥ መውጣትን እንዳልፈለገ አወቁ በዚያም ትተውት ወደ ቤቶቻቸው ሔዱ። ከዚህም በኋላ በመታሰቢያው ቀን በየዓመቱ ያቺ ባሕር ከቅዱስ ቀሌምንጦስ ሥጋ ላይ የምትገለጥ ሆነች ምእመናንም ሁሉ ገብተው ከእርሱ ይባረካሉ መታሰቢያውንም በማድረግ በዓሉን ያከብራሉ ከዚያም በኋላ ወጥተው ወደቤታቸው ይገባሉ። ❤ ከአስደናቂዎች ተአምራቶቹም ከተጻፋት ያዩ ይህን ተናገሩ በአንዲት ዓመት ከሥጋው ሊባረኩ በገቡ ጊዜ የቅዱስ ቀሌምንጦስ ሥጋው ካለበት ሣጥን ዘንድ ሲወጡ ታናሽ ሕፃን እንደረሱ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚወዱት ቅዱሳኑ ክብራቸውን ከርሱ የተቀበሉትንም ጸጋ ይገልጥ ዘንድ ወዷልና። ወላጆቹም ከወጡ በኋላ ሕፃኑን ፈለጉት ግን አላገኙትም ባሕሩም በላዩ ተከድኖ ነበር ሙቶ በባሕር ውስጥ ያሉ አራዊት የበሉት መስሏቸው አለቀሱለት እንደ ሥርዓቱም በማዕጠንትና በቊርባን ቅዳሴ መታሰቢያውን አደረጉ። ❤ በዳግመኛውም ዓመት ያቺ ባሕር ተገለጣ እንደ ልማዳቸው ገቡ ሕፃኑንም በሕይወት ሁኖ በቅዱስ ቀሌምንጦስ የሥጋ ሣጥን ዘንድ ቁሞ አገኙት "በዚህ ባሕር ውስጥ አኗኗርህ እንዴት ነበር ምን ትበላ ነበር የባሕር አራዊትስ እንዴት አልበሉህም" ብለው ጠየቁት። እርሱም ቅዱስ ቀሌምንጦስ ያበላኝ ነበር እግዚአብሔርም በባሕር ካሉ አራዊት ይጠብቀኝ ነበር" ብሎ መለሰ ሰምተውም እጅግ አደነቁ በቅዱሳኑና ስለ ከበረ ስሙ ደማቸውን በአፈሰሱ ሰማዕታት የሚመሰገን ምስጉን እግዚአብሔርን አመሰገኑት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያው ቅዱስ ቀሌምንጦስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 29 ስንክሳር። + + + ❤ "ሰላም ለከ ቀሌምንጦስ አቡነ። አበ መንፈስነ። ከመ ናጽንዕ ዘልፈ ዘትምህርትከ አሚነ። ጽሒፎሙ ሐዋርያት ኃደጉ ለነ። ምስለ ቀሌምንጦስ እንዘ ይብሉ መልእክተ ፈኖነ። ሊቁ አርከ ሥሉስ አርኬ የኅዳር 29። + + + ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ምስሌከ ቀዳማዊ በዕለተ ኃይል። ወብርሃኖሙ ለቅዱሳን። ወለድኩከ እምከርሥ እምቅድመ ኮከበ ጽባሕ"። መዝ 109፥3። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 2፥1-8። + + + ❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ኪያየ ይጸንሑ ኃጥአን ይቀትሉኒ። እስከ ስምዐከ ለበውኩ። ለኲሉ ግብር ርኢኩ ማኅለቅቶ"። መዝ 118፥95-96። የሚነበቡት መልዕክታት ፊል 3፥1-15፣ 1ኛ ጴጥ 5፥5-13 እና የሐዋ ሥራ 27፥39-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 10፥1-22። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ቀሌምንጦስ፣ የተፍጻሜተ ሰማዕት የአባ ጴጥሮስ፣ አቡነ ፄዋለ ጽጽቅ የዕረፍታቸው በዓል፣ የአቡነ ዮሐንስ ዘጠገሮ የልደት በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ። ሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት https://t.me/Eotcw

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ኅዳር ፳፱ (29) ቀን። ❤ እንኳን ከሰባ ሁለት አርድእት አንዱ ለአንዱ ለሆነው ለሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ደቀ መዝሙር ለቅዱስ ቀሌምንጦስ ለዕረፍት በዓል፣ ለእስክንድር ዐሥራ ሰባተኛ ሊቀ ጳጳሳት ለተፍጻሜተ ሰማዕት ለቅዱስ ጴጥሮስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደአሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከጌታችን ልደት ወራዊ መታሰቢያ (በዓለ ወልድ) በዓልና በከሀዲው ንጉሥ በዲዮቅልጥያኖስ ዘመን በሰማዕትነት ከዐረፉ ከአርባ ሰባት አእላፋት ከመታሰቢያቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ ተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስ፦ የዚህ አባት ወላጅ አባቱ በእስክድርያ አገር ሊቀ ካህናት ስሙ ቴዎድሮስነው እናቱም ስም ሶፍያ እነርሱም እግዚአብሔርን የሚፈሩ ጻድቃን ነበሩ፡፡ ነገር ግን ልጅ ስላልነበራቸው እጅግ ያዝኑ ነበር፡፡ ሶፍያም በአምስተኛኛው ቀን የቅዱሳን ሐዋርያትን የቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስን በዓል ለማክበር ወደ ቤተ ክርስቲያን ስትሄድ ሌሎቹ ሰዎች ከልጃቸው ጋር ለበዓሉ ሲሄዱ አይታ አዘነች፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ሄዳ እግዚአብሔርን ልጅ እንዲሰጣት በቅዱሳን ሐዋርያቱ ስም ለመነችው፡፡ በዚያችም ሌሊት የከበሩ ሁለቱ ሐዋርያት ተገለጡላትና "የከበረ ልጅ ትወልጃለሽ ስሙንም ጴጥሮስ በይው" አሏት፡፡ እርሷም ከወለደች በኋላ ስሙን ጴጥሮስ አለችው፡፡ ❤ ሰባት ዓመትም በሆነው ጊዜ የሃይማኖትን ምሥጢር ይማር ዘንድ ወስዳ ለሊቀ ጳጳሳቱ ለአባ ቴዎናስ ሰጠችው፡፡ ሊቀ ጳጳሳቱም በሥርዓት አሳደጉትና ከእርሳቸው ጋር የሚያገለግል ሆነ፡፡ እርሳቸውም ከማረፋቸው በፊት ጴጥሮስ በእሳቸው ቦታ እንዲሾም ተናገሩ፡፡ ካረፉም በኋላ ተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስ ተሾመና በታላቅ ተጋድሎ እየኖረ አገልግሎቱን በሚገባ አከናወነ፡፡ በእርሱም ዘመን የአንጾኪያዋ ታላቅ ሰማዕት ቅድስት ሣራ ልጆቿን ልታስጠምቅ ወደ እርሱ መጣች፡፡ እርሷም የከሀዲው የዲዮቅልጥያኖስ ባለሟል የሆነ የአንዱ መኳንንት ሚስት ነበረች፡፡ በሏ ንጉሡን በመፍራት ሃይማኖቱን ሲክድ እርሷ ግን በእምነቷ ጸናች፡፡ሁለት ልጆችንም ስትወልድ የክርስትና ጥምቀትን ልታስጠምቃቸው አልቻለችም፡፡ ምክንያቱም በአንጾከያ አብያተ ክርስቲያናት በሙሉ ወድመው ነበር፡፡ ወደ እስክንድርያም ሄዳ በአቡነ ጴጥሮስ እጅ ልታስጠምቃቸው አሽከሮቿን ይዛ ተነሣችና በመርከብ ተሳፈረች፡፡ በመሀልም ኃይለኛ ማዕበል ተነሥቶ መርከቢቱ ልትሰምጥ ሆነ፡፡ ቅድስት ሣራም ልጆቿ ሳይጠመቁ እንዳይሞቱ በማለት ጸሎት ካደረገች በኋላ የቀኙን ጡቷን በምላጭ ቀዳ በደሟ የልጆቿን ግንባር በመስቀል ምልክት አደረገችባቸው፡፡ በጀርባቸውና በደረታቸውም ላይ እንዲሁ አድርጋ በባሕሩ ውስጥ አጠመቀቻቸው፡፡ በዚህም ጊዜ ታላቅ ፀጥታ ሆነና ማዕበሉ ጠፋ፡፡ ❤ እስክንድርያም ደርሳ ከአባ ጴጥሮስ ዘንድ ልጆቿን ልታስጠምቅ አቀረበቻቸው፡፡ ተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስም ብዙ ልጆችን እያጠመቀ በተራ ደግሞ የቅድስት ሣራን ልጆች ሊያጠምቅ ሲል ውኃው እየረጋበት እምቢ አለው፡፡ እስከ ሦስት ጊዜም እንዲሁ ሆነ፡፡ ምን እንደሆነ ቅድስት ሣራን ሲጠይቃት ያደረገችውን ነገረችው፡፡ ይህንንም ሲሰማ እጅግ በመደነቅ "አንዲት ቤተ ክርስቲያን እንዲህ ትላለች እንዲህም ትሠራለች" ብሎ ጌታችንን አመሰገነው፡፡ እርሷም ፈርታ ይቅር በሉኝ ብላ እግሩ ላይ ስትወድቅ እርሱም "አይዞሽ አትፍሪ፣ ሃይማኖትሽ ፍጹም ነው፣ አንቺ ባጠመቅሻቸው ጊዜ በመለኮታዊ እጆቹ ያጠመቃቸው ባለቤቱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" አላት፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ሥጋ ወደሙን ከነልጆቿ አቀብሏትና ወደ አንጾኪያ ተመለሰች፡፡ ❤ ሌላው በቅዱስ ጴጥሮስ ዘመን የተፈጸመው ነገር የአርዮስ መነሳት ነው፡፡ ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና ጌታችንን "ወልድ ፍጡር ነው" ብሎ የተነሣውንና ሰይጣን በልቡ ያደረውን አርዮስን ከስህተቱ ይመለስ ዘንድ ቅዱስ ጴጥሮስ ብዙ መከረው፡፡ ነገር ግን አርዮስ እምቢ ቢለው እረግሞ አውግዞታል፡፡ የንጉሡን አማልክት እንዳያመልኩ በሁሉ ቦታ ቅዱስ ጴጥሮስ እያስተማረ መሆኑን ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ሰማ፡፡ ወታደሮቹንም ልኮ አስሮ አስመጣው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ሕዝቡ ስለ እርሱ ሊሞት የተዘጋጀ መሆኑን በተመለከተ ጊዜ ነፍሱን አሳልፎ ሊሰጥ ወደደ፡፡ ሕዝቡንም በቀናች ሃይማኖት እንዲጸኑ ካስተማራቸው በኋላ አጽናንቶ አሰናበታቸው፡፡ አርዮስም ቅዱስ ጴጥሮስ በንጉሡ ትእዛዝ እንደሚሞት ካወቀ በኋላ ከውግዘቱ እንዲፈታው አኪላስንና እለ እስክንድሮስን አማላጅ አድርጎ ላካቸው፡፡ እነርሱም አርዮስን ከውግዘቱ እንዲፈታው ሄደው ቅዱስ ጴጥሮስ ለመኑት ነገር ግን እርሱ ከውግዘቱ ላይ ሌላ ውግዘት ጨመረበት፡፡ ❤ ጌታችንም ልብሱ የተቀደደ ልጅ ሆኖ ተገልጦለት "አርዮስ ልብሴን ቀደደብኝ" ብሎኛል ብሎ ለእነ አኪላስ አስረዳቸው፡፡ ይህም ከባሕርይ አባቴ ለየኝ ማለቱ ነው፡፡ ሁለተኛም "ከአርዮስ ተጠበቁ፣ በክህነት ሥራም አትሳተፉ እርሱ ለክብር ባለቤት ለክርስቶስ ጠላቱ ነውና" አላቸው፡፡ ይህንንም ከነገራቸው በኋላ ሕዝቡ ሳያየው ሊገድለው ካለው ንጉሥ ከዲዮቅልጥያኖስ ጋር ስለሞቱ በስውር ተማከረ፡፡ ይኸውም ሕዝቡ ሳይሰማ እንዴት ይገድሉት ዘንድ ነው፡፡ ንጉሡም አስቀድሞ በእስር ቤት አቆይቶ ልዩ ልዩ በሆኑ ጽኑ ማሠቃያዎች አሠቃይቶት ነበር፡፡ አሁንም ቅዱስ ጴጥሮስ በእስር ቤት ሳለ መስኮቱን ሲያንኳኳላቸው ወታደሮቹ ሰው ሳያይና ሳይሰማ በስውር መጥተው አንገቱን እንዲቆርጡት ተማከረ፡፡ ጌታችንንም በጸሎቱ "የደሜ መፍሰስ ለጣዖታት አምልኮ መጨረሻ ይሁን ከሁሉ ዓለምም ይጥፋ…" ብሎ ለመነው፡፡ ወዲያውም ከሰማይ "አሜን ይሁን ይደረግ" የሚል ድምፅ መጣለት፡፡ ይህንንም ድምፅ በእስር ቤቱ አቅራቢያ የነበረች አንዲት ድንግል ብላቴና ሰምታ ለሕዝቡ ተናግራለች፡፡ ❤ አባ ጴጥሮስም ጸሎቱን ከጨረሰ በኋላ የሚሰይፉትን ወታደሮች ጠርቶ "የታዘዛችሁትን ፈጽሙ" አላቸውና መጥተው ሰየፉት፡፡ በማግስቱም ሕዝቡ ቅዱስ ጴጥሮስ በሰማዕትነት ማረፉን በሰሙ ጊዜ ወደ እስር ቤቱ መጥተው ሥጋውን አንሥተው ወደ ቤተ ክርስቲያን አግብተው በወንበሩ ላይ አስቀመጡት፡፡ ይህም ቅዱስ ጴጥሮስን በሕይወት እያለ ከዚህ በፊት በወንበሩ ላይ ሲቀመጥ ማንም አይቶት አያውቅም ነበርና ነው፡፡ አንድ ቀን "በወንበርህ ላይ የማትቀመጥ ለምድነው?" ብለው ጠይቀውት ነበር፡፡ እርሱም "እኔ እግዚአብሔር በወንበሩ ላይ ተቀምጦ አያለሁና ስለዚህ በዚህ ወንበር ላይ መቀመጥን እፈራለሁ" ብሏቸዋል፡፡ ❤ ግንዘቱንም አከናውነው ከተመረጡ ሊቃነ ጳጳሳት ከሥጋቸው ጋር ሥጋውን አኖሩ እርሱም በወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ወንበር በሹመት የኖረው ዐሥራ አራት ዓመት ነው የተሾመውም ዲዮቅልጥያኖስ በነገሠ በሃያ ስድስት ዓመት ነው ከሥጋውም ብዙ ድንቅ ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ አባት በአባ ጴጥሮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ ቅዱስ ቀሌምንጦስ፦ ይህም ቅዱስ ከመንግሥት ልጆች ወገን የሆነ ለሮሜ ንጉሥ የጭፍራ አለቃ ለሆነ ለቀውስጦስ ልጁ ነው ደጎች የሆኑ አባትና እናቱም ቅዱስ ጴጥሮስ የወንጌል ትምህርት በሰበከ ጊዜ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ገንዘባቸውንም ሁሉ ለድኆችና ለችግረኞች ምጽዋት አድርገው ሰጡ።

photo content
+4

❤ አባታችን ከሰማይ መስቀል የወረደላቸው ሲሆን ዛሬም በገዳማቸው የሔደ ሰው በወረደው በእጃቸው መስቀል እየተዳበሰ ቆመው በጸለዩበት ባሕር በጠበላቸው ይጠመቃል፡፡ በተጨማሪም ይይዙት በነበረውም መቋሚያቸው በመዳበስ በረከትን ማግኘት ይቻላል፡፡ ቆመው ከጸለዩበት ባሕር ውስጥ ደረቅ አሸዋ ይወጣል፡፡ አባ ዮሐንስ 500 ዓመት ከኖሩ በኋላ ዕረፍተ ዘመናቸው ሲደርስ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ከ15 ነቢያት፣ ከ12 ሐዋርያት፣ ሄሮድስ ያስፈጃቸው ከመቶ አርባ አራት ሺ ሕፃናት፣ ከአብርሃም ከይስሐቅ፣ ከዕቆብ ጋር ሁሉንም ነገደ መላእክትን፣ ጻድቃን ሰማዕታትን ሁሉ አስከትሎ መጥቶ ታላቅ ቃልኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ "ስምህን የጠራ ገዳምህን የረገጠ፣ መባ የሰጠ፣ ቤተ ክርስትያንህን የሠራ ያሠራ የረዳ፣ ገድልህን የሰማ ያሰማ ያስተረጎመ፣ መታሰቢያን ያደረገ እስከ 10 ትውልድ እምርልሀለው፤ ንስሀ ሳይገባ አይሞትም፣ ልጅ መውለድ ባይችል እኔ ልጅ እሰጠዋለሁ፤ ገድልህን በቤትህ ያስቀመጠ እርኩስ መንፈስ፣ ክፉ አጋንንት ቸነፈር ወባ መልአከ ጽልመት አይነካውም፡፡ በገዳምህ መነኵሴ ቢቀበር በሰማይ ክንፍ አበቅልለታለሁ፤ አይሁድም አረማዊም ያላመነ ያልተጠመቀ በገዳምህ መጥቶ ቢያርፍ ይቅር እልልሃለሁ፣ እንደ መቃብሬ ጉልጎታ እንደተቀበረ አድርጌ እቆጥርልሃለሁ…" የሚል ቃል ኪዳን ከሰጣቸው በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ ❤ ቅዱስ አባታችንም በ 500 ዓመታቸው ሐምሌ 29 ቀን ዐርፈው በጎንድ ተክለ ሃይማኖት ተቀብረዋል፡፡ በሰሜን ጎንደር የሚገኘውን ይህንን ገዳም ጻድቁ ራሳቸው ናቸው የመሠረቱት፡፡ ነገር ግን የገዳሙን ስያሜ በአባታቸው በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ስም አድርገውታል፡፡ አቡነ ዮሐንስ ካረፉ በኋላ በእርግማናቸው መሠረት በመንዝና በይፋት ብርዱ ድርቁ ስለበዛባቸው አንድ ብቁ ባሕታዊ ከበዓታቸው ወጥተው "በሐሜታችሁ ምክንያት እጨ ዮሐንስ ስለረገማችሁ ነው የእርሱን ዐፅም ካላመጣችሁ ብርዱ ውርጩ ድርቁም አይጠፋላችሁም" አሏቸው፡፡ ሕዝቡም አባታችን በጉንድ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከተቀበሩ ከ 134 ዓመት በኋላ በቅዱሳን እየተመሩ ሄደው በሌሊት ግማሽ ዐፅማቸውን አምጥተው በሀገራቸው አምጥተው ስላስቀመጡ ብርዱና ውርጩ በመንዝ እየቀነሰላቸው መጥቷል፡፡ ❤ ዛሬም በሀገሩ ብርዱና ውርጭ ሲበዛ የጻድቁን ታቦት ሲያወጡ ውርጩ ይጠፋል፡፡ ጠገሮ በሚባለው ገዳማቸው ውስጥ የሚገኘው ጠበላቸው እጅግ አስደናቂ ነው፡፡ ግማሽ ዐፅማቸውን ከጉንደ ተክለሃይማኖት አምጥተው አርባ ሐራ መድኃኔዓለም አጠገብ በላይ በፍሩክታ ኪዳነምሕረት መጋቢት 18 ፍልሰተ ዐፅማቸው ተከናወነ፡፡ ምድሪቷም ተባረከች፣ የዘሩትንም አበቀለች፣ ውርጩም ብርዱም ቀነሰ፣ ዝናብ አልዘንብ ሲል ወይም ሰብል የሚጨርስ አንበጣ ሲመጣ ታቦታቸው ወጥቶ ምህላ ይያዛል ወድያውም መቅሰፍት ይርቃል፣ ዝናብም ይዘንባል፡፡ ጻድቁ ደመናን፣ ጨረቃንና ፀሐይን በእጃቸው እየያዙ ይጸልዩ ነበር፡፡ በጠገሮ፣ በአዘሎ፣ በፍርኩታና በሌሎቹም ታላላቅ ቦታቦዎች ላይ በእያንዳንዱ ገዳም ሃምሳ ሃምሳ ዓመት በጸሎት ኖረው በአጠቃላይ በ500 ዓመታቸው ነው ያረፉት፡፡ ዐፅማቸው መንዝ ከአርባ ሐራ መድኃኔዓለም አጠገብ ፍርኩታ ኪዳነ ምሕረት ገዳም ውስጥ ይገኛል፡፡ ከአባታች ከእጨጌ አቡነ ዮሐንስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸውም ይማረን። ምንጭ፦ ገድለ እጨጌ (እጨ) አቡነ ዮሐንስ ዘጠገሮና መዝገበ ቅዱሳን መጽሐፍ። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ኅዳር ፳፱ (29) ቀን። ❤ እንኳን ለኢትዮጵያኑ ጻድቃን በጸሎታቸው የተከዜን ባሕር ለሁለት ለከፈሉ ለአቡነ ገብረ መስቀል ዘለጋሶ ለመታሰቢያቸው በዓል፣ የአየር አጋንንት ከእናቱ ጋራ ተገናግቶ የተወለደው መጥቆራ ተብሎ ይጠራ የነበረው አቡነ ተክለሃይማኖትና አቡነ ዜና ማርቆስም በጸሎታቸው ወደ እግዚአብሔር ለምነው በመስቀሉ ኃይል ድል ካደረጉት በኋላ ወደ ሰው አርአያነት እንዲለወጥ አድገውት ሥሙን ለውጠው አመንኵሰው ለታላቅ የቅድስና ደረጃ ለአበቁቱ ለአቡነ ፄዋለ ጽጽቅ ለዕረፍት በዓል፣ ለታላቁ አባት በፀሐይ ላይ 50 ዓመት፣ በጨረቃ ላይ 50 ዓመት፣ በደመና ላይ 50 እንዲሁም ዓለምን በክንፋቸው በመዞር በደመና ላይ 50 ለኖሩ ከሰው ተወልደው ከመላእክት ለተደመሩ ጻድቅ ለእጨጌ (እጨ) ለአቡነ ዮሐንስ ዘጠገሮ ለልደታቸው በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሰን። + + + ❤ አቡነ ገብረ መስቀል ዘለጋሶ፦ ትውልድ አገራቸው ትግራይ አድዋ ሲሆን የአቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ሃሌ ሉያ ልጅ ናቸው። አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ሃሌ ሉያ ያሳደጓቸው የቆብ አባታቸው ሲሆኑ ያመነኰሷቸው ግን አቡነ እንጦንዮስ ዘደብረ ተንኮክ ናቸው። አቡነ ገብረ መስቀል ዘለጋሶ በጸሎታቸው የተከዜን ባሕር በሁለት የከፈሉ ታላቅ አባት ናቸው። በምናኔ ሕይወት 80 ዓመት ሲቆዩ የሴት ፊት ሳያዩና ዓለምን ሳያውቁ ነው የኖሩት። በትግራይ ሽሬ ዘለጋሶ የተባለውን ትልቅ ገዳም ቆርቁረው በዚያው ዐርፈው ተቀብረዋል። ከአቡነ ገብረ መስቀል ዘለጋሶ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳንና ቅዱሳን በዓላት። + + + ❤ አቡነ ፄዋለ ጽድቅ፡- ይኸውም ቅዱስ አባት ቀድሞ መጥቆራ ተብሎ ይጠራ የነበረ አጋንንት የነበረ ነው፡፡ አባቱም "ፈረጎ" የተባለ የአየር አጋንንት ሲሆን እናቱን ደፍሮ ተገናኛትና መጥቆራ ተወለደ፡፡ እርሱም እጅግ ኃይለኛ ነበርና እነ አቡነ ተክለሃይማኖትንና አቡነ ዜና ማርቆስን ሳይቀር በእጅጉ ይፈትናቸውና ይበረታባቸው ነበር፡፡ አቡነ ተክለሃይማኖትና አቡነ ዜና ማርቆስም በጸሎታቸው ወደ እግዚአብሔር ለምነው በመስቀሉ ኃይል ድል ካደረጉት በኋላ ወደ ሰው አርአያነት እንዲለወጥ አድገውት አመንኵሰው ለታላቅ የቅድስና ደረጃ አብቅተውታል፡፡ ስሙንም "አቡነ ፄዋለ ጽድቅ" አሉት፡፡ እርሱም በጾም በጸሎት ተወስኖ በእጅጉ በታላቅ ተጋድሎ ኖሮ ከብቃት ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ በሞት ሊያርፍ ሲል ጌታችን ተገልጦለት ታላቅ ቃልኪዳን ገብቶለታል፡፡ በሀገራችን በስሙ ቤተ ክርስቲያን ተሠርቶለት ጽላት ተቀርጾለት ይገኛል፡፡ ከአቡነ ፄዋለ ጽድቅ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከቱን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን። ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት። + + + ❤ እጨጌ (እጨ) አቡነ ዮሐንስ ዘጠገሮ፦ ጻድቁ አባታችን የተወለዱት በኢየሩሳሌም አውራጃ ልዩ ስሙ ሳሬራ በሚባል ቦታ ነው፡፡ የካቲት 28 ቀን ተፀንሰው ህዳር 28 ቀን ተወለዱ፡፡ ነገር ግን በዓለ የልደታቸው በዓል የሚከበረው ከወራዊ በዓላቸው ጋራ ኅዳር 29 ቀን ነው። አባታቸው ድላሶር እናታቸው እምነ ጽዮን ይባላሉ፡፡ ሲወለዱ በወላጆቻቸው ቤት ውስጥ ብርሃን ወርዷል፡፡ ወላጆቻቸውም እግዚአብሔርን የሚፈሩ ደጋግ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ አባታችን ገና በተወለዱ በ5 ዓመታቸው ወላጆቻቸው ወደ እግዚአብሔር ቤት ይዘዋቸው የእመቤታችንን ሥዕል ተመልክተው በደስታ ተመልተው ሳቁ፡፡ አምላክን የወለደች የብርሃን እናቱ እመቤታችንም ከምሥሉ ወጥታ "በምን አውቀኸኝ ነው?" ብላ አቅፋ ሳመችውና "ከእንግዲ ወዲህ የልጄ አገልጋይ ትሆናለህ ኑሮህም እንደ መላእክት ይሆናል በአንተ ምክንያት ብዙ ሰዎች ይድናሉ በምድር ላይም 500 ዓመት ትኖራለህ…" ብላ ባርካው ተሰወረች፡፡ ❤ ከዚያችም ቀን ጀምሮ አባ ዮሐንስ ለክርስቶስ ተላልፎ ተሰጠ፡፡ 50 ዓመትም በበረሃ ሲጋደል ኖሮ ከ50 ዓመት በኋላ በደመና ተጭኖ በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል መሪነት ወደ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ መጡ፡፡ ጻድቁ አባታችን በአቡነ ተክለሃይማኖት ዘመን መጨረሻ የመጡ ሲሆን ምንኵስና ከደብረ ሊባኖስ ገዳም ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ተቀብለው በዚያው በድብረ ሊባኖስ ገዳም ለ50 ዓመት በጾምና በጸሎት በተጋድሎ ኖዋል፡፡ ከዚኽም በኋላ አባ ዮሐንስ ወደ ተዘጋጀላቸው ምድር በቅዱስ ገብርኤል አሳሳቢነት ወደ ጠገሮ መጡ፡፡ ይኽም ጠገሮ ያለው ገዳማቸው በሰሜን ሸዋ በመንዝና ይፋት ክልል መዘዞ በሚባል ቦታ ሲደርሱ በእግር አንድ ሰዓት ከተጓዙ በኃላ ይገኛል፡፡ ❤ ሕዝቡ በተለምዶ እጨ ዮሐንስ እያለ ይጠራቸዋል እንጂ ስማቸው እጨጌ ዮሐንስ ነው፡፡ አቡነ እጨጌ ዮሐንስ መስቀል ከሰማይ የወረደላቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ መስቀሉም ሁልጊዜ ተአምር ይሠራል፡፡ በልደታቸው ቀን ኅዳር 29 ቀን መስቀሉ ከመቅደሱ ወጥቶ በካህናቱ ታጅቦ ወደ ጸበሉ ሲወርድ ከየት እንደመጣ ሳይታሰብ ደመና መጥቶ ከመስቀሉ ላይ ብቻ እረቦና እንደ ጃንጥላ ተዘርግቶ አብሮ ወደ ጸበሉ ይወርዳል፡፡ እዛው ቆይቶ መስቀሉ ሲመለስም አብሮ አጅቦ ይመለስና መስቀሉ ቤተ መቅደስ ውስጥ ሲገባ ደመናው ወዴት እንደተበተነ ሳይታወቅ ይጠፋል፡፡ ይህ በዘመናችንም ጭምር እየታየ ያለ ታላቅ ተአምር ነው፡፡ ❤ አባታችን በታላቀ ተጋድሎ ሣሉ ሰይጣን የሀገሩን ሰዎች በጠላትነት እንዲነሡባቸው አደረገ፡፡ ሰዎቹም አባታችንን እንዴት እንደሚያጠፏቸው ይማከሩ ጀመር፡፡ ሊገድሏቸው ፈልገው ቅድስናቸው በሁሉ ዘንድ የታወቀ ነውና ፈሩ፡፡ ከዚህም በኋላ "ለምን ከመንደራችን ከወንድ ያረገዘች ሴት ፈልገን እሳቸው አስረገዟት ብለን በሐሰት እንከሳቸው?" ብለው ተማከሩ፡፡ ብዙ ወርቅና ብርም ለአንዲት ሴት ሰጥተው በሐሰት ከእርሱ አርግዣለሁ ብላ እንድትመሰክር አደረጓት፡፡ አባታችንም በሕዝብ ፊት በሐሰት ተከሰሱ፡፡ ጻድቁም "አንቺ ሴት ከእኔ ነው ያረገሽው?" አሏት እርሷም "አዎ ከአንተ ነው ልትክድ ነው እንዴ?" አለቻቸው፡፡ አባታችንም በዚህ አዝነው "በአንቺና በእኔ መካከል እግዚአብሔር ይፍረድ" ሲሉ ያች ሴት ወዲያው ለሁለት ተሰንጥቃ ሞተች፡፡ የአገሩ ሰዎችም እጅግ ፈሩ፡፡ አባታችንም ምድሪቱን እረገሟት፡፡ "የተዘራው ዘር አይብቀልብሽ፣ የተተከለው አይፅደቅ፣ ብርድና ውርጭ ይፈራረቅብሽ" ብለው እረግመዋት በደመና ተጭነው ወደ ሰሜን ጎንደር እስቴ ጉንደ ተክለተሃማኖት ሔዱ፡፡ ❤ አቡነ ዮሐንስ በመላው ኢትዮጵያ ወንጌልን እየተዘዋወሩ ያስተማሩ ሲሆን ከቅድስናቸው የተነሣ በፀሐይ ላይ 50 ዓመት፣ በጨረቃ ላይ 50 ዓመት፣ በደመና ላይ 50 እንዲሁም ዓለምን በክንፋቸው በመዞር በደመና ላይ 50 የኖሩ ከሰው ተወልደው ከመላእክት የተደመሩ ታላቅ ጻድቅ ናቸው፡፡ በይፋት ጠግሮ በዓለወልድ፣ በአፋር አዘሎ፣ በመንዝ ፍርኩታ ኪዳነምሕረት፣ በደብረ ሊባኖስ፣ በጎንድ ተክለ ሃይማኖት በሌሎችም ቦታዎች በመዘዋወር በታላቅ ተጋድሎ ኖረዋል፡፡

#እጅግ_አሳዛኝ_ዜና! እባካችሁ በእመብርሃን #ሸርርርርር...አድርጉት...❗ የዲያቆን ቢኒያም ፍሬው ስቃይ በዚህ ይብቃ❗❗❗ የምታቁት ሰዎች ታቁታላችሁ፤ የማታቁት ግን ለዲያቆን ቢኒያም ማለት ስለክርስቶስ አምላክነት ነጥብ በነጥብ እያብራራ አህዛብን መልስ የሚያሳጣ የዘመኑ እንቁ ሀዋርያ ነው። በዚህ ትልቅ እውቀቱም ብዙ ጊዜ ስለክርስቶስ አምላክነት ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ሙስሊሞች በተለያዩ ሲዲዎች ሲጠይቁትና ትችት ሲያቀርቡበት እሱ ግን ስለክርስቶስ አምላክነት ነጥብ በነጥብ፤ ግልጽ በግልፅ እያብራራ መልስ ከማሳጣቱም በላይ የቁራንን ምንነትና የመሀመድን አስተምህሮ በማያሻማ ማስረጃ እየተነተነ ያቀርብላቸው ነበር። በዚህ ተግባሩ ግራ የተጋቡትና አንገታቸውን የደፉት ሙስሊሞችና ኡስታዞቻቸው (በተለይ #ሳዲቅ የተባለው ኡስታዝ) በመኪና አደጋና በተለያዩ የጥቃት መንገዶች የመግደል ሙከራ ቢያደርጉበትም፤ በእግዚአብሔር ድንቅ ጥበቃ ጥቃቱ አልተሳካላቸውም። አሁን ግን በሙስሊሞች የግድያ ርብርብ ምክንያት ዲያቆን ቢኒያም ቤቱን ለቆ ከአገልግሎት ርቆ በጫካ ከቤተሰቦቹ ጋር እየተንገላታ እንዳለና ቤተሰቦቹም አብረውት በስቃይ ውስጥ እንደሆኑ ተናግሯል። የሚያሳዝነው ነገር ይህንን ጉዳይ እንኳንስ ሲኖዶሱ መንግስትም እንደሚያውቀው በማስረዳት፤ በምዕመናን ደረጃ ግን ከጥቂቶች በስተቀር አብዛኛዎቹ ምዕመናን ያለበትን ሁኔታ እንደማያውቁት ያስረዳል። †††ይህንን ጉዳይ እያወቃችሁ ቃል ያልተነፈሳችሁ አገልጋዮችና አባቶች ግን እግዚአብሔር ቢያውቀውም አዝነንባችኋል፤ እሱም ይፈርዳል❗😭 ይህንን መረጃ የምታነቡ ወገኖች፤ በእግዚአብሔር ስም ለመምህራችን #ሼር በማድረግ ድምፅ እንሁንለት፡ ያለበትን ሁኔታ የህግ አካላት እንዲያውቁትና የሀይማኖት አባቶችም እንዲነቁ እናድርግ ! አለበለዛ መናገር እየቻልን ዝም በማለታችን በክርስቶስ ክርስቲያን የሆነ ወንድማችን ድምጽ ካልሆንለት በሰማይ ቤት ይፋረደናል...በየጉሩፖች በእየአካውንቶች #ሼር_ሼር አድርጉት በአዛኝቷ😭

photo content

photo content
+2

😭 ዜና ዕረፍት የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዳዊት ዐረፉ። 😭 ብፁዕነታቸው አቡነ ዳዊት በኮፕቲክ ቤተክርስቲያን የማንሱራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው ሲያገለግሉ የነበረ ሲሆን ባደረባቸው ሕመም ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ተለይተዋል። 😭 ብፁዕነታቸው በግብጽ ሻብራ ግዛት በፈረንጆቹ በጃንዋሪ 25 1957 የተወለዱ ሲሆን በ1978 ከፋይን የሥነ ጥበብ ኮሌጅ ተመርቀው በኋላም ወደ ባራሙሲ የእመቤታችን ገዳም ገብተው በምንኩስና ተወስነው ከቆዩ በኋላ በ2002 ዓ.ም በቅዱስነታቸው አቡነ ሺኖዳ ሣልሳይ ኤጲስቆጶስነት ተሹመው እስከ ሕልፈተ ሕይወታቸው ድረስ የማንሱራ ጳጳስ ሆነው ሲያገለግሉ እንደነበር ተነግሯል። 😭 ብፁዕነታቸው በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ጠዋት ከዚህ በሞተ ሥጋ መለየታቸው ተዘግቧል። ❤ የብፁዕነታቸው በረከት በሁላችንም ላይ ይደርብን። https://t.me/Eotcw