fa
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

رفتن به کانال در Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

نمایش بیشتر
1 161
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
ማማተብ እስኪ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ብለን አማትበን ሰይጣንን ከኛ እናርቀው እንደ መድኃኔአለም እናማትብ እስኪ ማማተብ ማለት አማተበ ወይም አመሳቀለ ከሚል የግዕዝ ግሰ የተወሰደ ሲሆን ትርጓሜውም ምልክት ማድሸግ ወይም መባረክ ማለት ነው። ስናማትብ ወንጌልን እየሰበክን እንደሆነ ስንቶቻችን እናውቃለን። ስናማትብ 1.በመጀመሪያ መሆን ያለበት) እጃችን ከግንባራችን ወደ ሆዳችን ስናደርግ....ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ከድግል ማርያም ማህፀን አደረ ስንል ነው።። በሁለተኛ ደረጃ መሆን የለበት) እጃችንን ከሆዳችን አንስተን ወደ ግራ ትከሻችን ከዛም ወደ ቀኝ ትከሻችን ስናደርግ....እኛን ከነበርንበት የሲኦል ኑሮ ወደ ገነትና እውነተኛው መንገድ አሸጋገረን ስንል ነው። በመጨረሻም የሚሆነው) እጃችን ከቀኝ ትከሻችን አንስተን ወደ ሆዳችን ስንመልሰው ...ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያመ ተወልዷል እያልን ነው። ልክ ሶስተኛውን ደረጃ ስንጨርስ የመስቀል ቅርጽ ሰራን ማለት ነው። ይህ ሊሆን ደግሞ ከላይ የተጠቀሱትን ሶስት ደረጃዎች መጨረስ ግድ ይለናል። እኛ የተዋሕዶ ልጆች በሙሉ ይህንን ደረጃ ጠብቀን በማማተብ ወንጌልን እንሰብካለን። በታላቁ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ በወንጌል አላፍርም ምክንያቱም ለሚያምን ሁሉ ለድህነት የሚሆን የእግዚአብሔር ሃይል ነው" ሮሜ 1÷16 ተብሎ ተፅፏልና። አንዳንድ ምእመናን ስናማትብ ካለማወቀቅ የተነሳ ይሁን ወይ በችኮላ በትክክሉ አናማትብም የማማተብ ትርጉሙ ሳይገባን ስለቀረ ነው? ግማሹ ምእመን ልክ እንደተዋጊ በሬ እጃቸውን ብቻ በግንባራቸው ላይ በማድረግ ግንባራቸው ሲያወዛውዙ ይታያሉ። ግማሹ ደግሞ ፊታቸው ላይ በእጃቸው ክብ ሰርተው ይታያሉ። ግማሹም ሲያማትቡ አይጨርሱትም ወገኖቼ ይህ በፍፁም መሆን የለበትም። ማንኛውንም የመድኃኔአለም ስዕል አድኖ እንደምናይ ተጠቋማችን ጣት ከፍ አድርገን ሌሎችን ግማሽ አጥፈን በጠቋማችን መሀል አሳልፈን ነው የምናማትበው በስነርዓቱ ወንጌልን እየሰበኩ ነው። እኛም ይህን ያወቅን ለሌሎች እናስተመምር በደንብ እናማትብ ወንጌልን እንስበክ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖታችን ለዘለአለም ፀንታ ትኑር የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት አይለየን AMEN ፫ እኔ በእግዚአብሔር ጣት አጋንንትን አስወጣለሁ ሉቃስ 11፥20

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ዮሐ. 16:1-8፡ "ዘንተ ነገርኩክሙ" - "እንዳትሰናከሉ ይህን ተናግሬያችኋለሁ። ከምኵራባቸው ያወጧችኋል፤ ከዚህ በላይ ደግሞ የሚገድላችሁ ሁሉ እግዚአብሔርን እንደሚያገለግል የሚመስልበት ጊዜ ይመጣል። ይህንም የሚያደርጉባችሁ አብንና እኔን ስላላወቁ ነው። ነገር ግን፥ ጊዜው ሲደርስ እኔ እንደ ነገርኋችሁ ታስቡ ዘንድ ይህን ተናግሬያችኋለሁ። ከእንናንተም ጋራ ስለ ነበርሁ በመጀመሪያ ይህን አልነገርኋችሁም። አሁን ግን ወደላከኝ እሄዳለሁ ከእናንተም፦ ወዴት ትሄዳለህ? ብሎ የሚጠይቀኝ የለም። ነገር ግን፥ ይህን ስለ ተናገርኋችሁ ሐዘን በልባችሁ ሞልቷል። እኔ፡ግን፡እውነት እነግራችኋለሁ፤እኔ፡እንድሄድ፡ይሻላችኋል። እኔ ባልሄድ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣምና፤ እኔ ብሄድ ግን እርሱን እልክላችኋለሁ። እርሱም፡መጥቶ፡ስለ፡ኃጢአት፡ስለ፡ጽድቅም፡ስለ፡ፍርድም፡ዓለምን፡ይወቅሳል።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

1.40 KB

30/3/2015 ዓ.ም (፴/፫/፳፻፲፭ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ክቡር ንጉሥ ፍትሐ ያፈቅር ። አንተ አጽናዕካ ለጽድቅ በኃይልከ። ፍትሐ ወጽድቀ ለያዕቆብ አንተ ገበርከ፡፡ መዝ 98:4 🕯 ትርጉም የንጉሥ ክብር ፍርድን ይወዳል። አንተ ቅንነትን አጸናህ። ለያዕቆብ ፍርድንና ጽድቅን አንተ አደረግህ። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ሉቃ. 15:11-ፍ፡ም፡ "ወይቤ አሐዱ ብእሲ ቦቱ" - "እንዲህም፡አለ፦አንድ፡ሰው፡ኹለት፡ልጆች፡ነበሩት። ከነርሱም፡ታናሹ፡አባቱን፦አባቴ፡ሆይ፥ከገንዘብህ፡የሚደርሰኝን፡ክፍል፡ስጠኝ፡አለው።ገንዘቡንም፡ አካፈላቸው። ከጥቂት፡ቀንም፡በኋላ፡ታናሹ፡ልጅ፡ገንዘቡን፡ሁሉ፡ሰብስቦ፡ወደ፡ሩቅ፡አገር፡ሄደ፥ከዚያም፡እያባከነ፡ገንዘቡን፡በተነ። ሁሉንም፡ካከሰረ፡በኋላ፡በዚያች፡አገር፡ጽኑ፡ራብ፡ሆነ፥እርሱም፡ይጨነቅ፡ጀመር። ሄዶም፡ከዚያች፡አገር፡ሰዎች፡ከአንዱ፡ጋራ፡ተዳበለ፥ርሱም፡ዕሪያ፡ሊያሰማራ፡ወደ፡ሜዳ፡ሰደደው። ዕሪያዎችም፡ከሚበሉት፡ዐሠር፡ሊጠግብ፡ይመኝ፡ነበር፥የሚሰጠውም፡አልነበረም። ወደ፡ልቡም፡ተመልሶ፡እንዲህ፡አለ፦እንጀራ፡የሚተርፋቸው፡የአባቴ፡ሞያተኛዎች፡ስንት፡ናቸው፧እኔ፡ግን፡ከዚህ፡በራብ፡እጠፋለሁ። ተነሥቼም፡ወደ፡አባቴ፡እሄዳለሁና፦አባቴ፡ሆይ፥በሰማይና፡በፊትህ፡በደልሁ፥ ወደ፡ፊትም፡ልጅህ፡ልባል፡አይገባኝም፤ከሞያተኛዎችህ፡እንደ፡አንዱ፡አድርገኝ፡እለዋለሁ። ተነሥቶም፡ወደ፡አባቱ፡መጣ። እርሱም፡ገና፡ሩቅ፡ሳለ፡አባቱ፡አየውና፡አዘነለት፥ሮጦም፡ዐንገቱን፡ዐቀፈውና፡ሳመው። ልጁም፦አባቴ፡ሆይ፥በሰማይና፡በፊትህ፡በደልሁ፥ወደ፡ፊትም፡ልጅህ፡ልባል፡አይገባኝም፡አለው። አባቱ፡ግን፡ባሪያዎቹን፡አለ፦ፈጥናችኹ፡ከዅሉ፡የተሻለ፡ልብስ፡አምጡና፡አልብሱት፥ለእጁ፡ቀለበት፡ለእግሩም፡ጫማ፡ስጡ፤ የሰባውን፡ፊሪዳ፡አምጥታችኹ፡ዕረዱት፥እንብላም፡ደስም፡ይበለን፤ ይህ፡ልጄ፡ሞቶ፡ነበርና፥ደግሞም፡ሕያው፡ሆኗል፤ ጠፍቶም፡ነበር፡ተገኝቷልም።ደስም፡ይላቸው፡ ጀመር። ታላቁ፡ልጁ፡በዕርሻ፡ነበረ፤መጥቶም፡ወደ፡ቤት፡በቀረበ፡ጊዜ፡የመሰንቆና፡የዘፈን፡ድምፅ፡ሰማ፤ ከብላቴናዎችም፡አንዱን፡ጠርቶ፦ይህ፡ምንድር፡ነው፧ብሎ፡ጠየቀ። እርሱም፦ወንድምህ፡መጥቷልና፥በደኅና፡ስላገኘው፥አባትህ፡የሰባውን፡ፊሪዳ፡ዐረደለት፡አለው። ተቈጣም፡ሊገባም፡አልወደደም፤አባቱም፡ወጥቶ፡ለመነው። እርሱ፡ግን፡መልሶ፡አባቱን፦እንሆ፥ይህን፡ያህል፡ዓመት፡እንደ፡ባሪያ፡ተገዝቼልሃለሁ፡ከትእዛዝህም፡ከቶ፡አልተላለፍሁም፤ለኔም፡ከወዳጆቼ፡ጋራ፡ደስ፡እንዲለኝ፡አንድ፡ጥቦት፡ስንኳ፡አልሰጠኸኝም፤ ነገር፡ግን፥ገንዘብህን፡ከጋለሞታዎች፡ጋራ፡በልቶ፡ይህ፡ልጅህ፡በመጣ፡ጊዜ፥የሰባውን፡ፊሪዳ፡አረድህለት፡አለው። እርሱ፡ግን፦ልጄ፡ሆይ፥አንተ፡ሁልጊዜ፡ከእኔ፡ጋራ፡ነህ፥ለኔም፡የሆነ፡ሁሉ፡የአንተ፡ነው፤ ዳሩ፡ግን፡ይህ፡ወንድምህ፡ሞቶ፡ነበረ፡ሕያው፡ስለ፡ሆነ፡ጠፍቶም፡ነበር፡ስለ፡ተገኘ፡ደስ፡እንዲለን፡ ፍሥሓም፡እንድናደርግ፡ይገባናል፡አለው። ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

1.28 KB

30/3/2015 ዓ.ም (፴/፫/፳፻፲፭ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ተሣሃለኒ እግዚኦበከመ ዕበየ ሣህለከ ። ወበከመ ብዙኀ ምሕረትከ ደምስስ ኃጥየትየ። ኅፅበኒ ወአንጽሐኒ እምኃጥያትየ። መዝ 50፥1 🕯 ትርጉም አቤቱ፥ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ። እንደ ምሕረትህም ብዛት መተላለፌን ደምስስ። ከበደሌ ፈጽሞ ዕጠበኝ። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯

photo content
+2

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ሰላም ለአሜዳ ወለሰልአዶባ ወለገብረ መስቀል ነገሥት ኄራን ወራትዓን ወለሃይምናን፤ ሕዝቦሙ በጽድቅ እለ ኰነኑ ጽድቀ ወሃይማኖተ እለ ዴገኑ፤ በትእዛዘ አምላኮሙ እለ ሖሩ፤ ለምግባረ ጽድቅ ርእሶሙ እለ አግረሩ"። ትርጉም፦ ለበጎ ምግባር ራሳቸውን ያስገዙ፤ በአምላካቸውም ትእዛዝ የኼዱ፤ ጽድቅና ሃይማኖትን የተከተሉ፤ ወገናቸውን በእውነት የገዙ፤ አማኖች ቅኖችና ደጋጎች የነበሩ ለኾኑ ነገሥታት ለገብረ መስቀልም፤ ለሰልአዶባና ለአሜዳ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት https://t.me/Eotcw

photo content
+1

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ኅዳር ፴ (30) ቀን። ❤ እንኳን ለቊስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት ለቅዱስ አባት ለአባ አካክዮስ ለዕረፍት፣ ለቅዱሳን ለቆዝሞስና ለድምያኖስም ቤተ ክርስቲያናቸው ለከበረችበት በዓል በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከሰማዕት ከአባ መርቆሬዎስ ከመታሰቢያ በዓሉ፣ ከአናንዮስ ዘዓምድና ከአባ ጴጥሮስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ የቊስጥንጥንያ አገር ሊቀ ጳጳሳት አባ አካክዮስ፦ ይህም ቅዱስ ቸር የሆነ ምሁር ነው አምላክ ያጻፋቸውንም መጻሕፍት ቃላቸውን አሳምሮ የሚተርጒም አዋቂ ነው በቊስጥንጥንያ ቤተ ክርስቲያንም ቅስና ተሹሞ ነበር በኬልቄዶንም ስብሰባ በሆነ ጊዜ ይህ አባት በጉባኤው ውስጥ በሆነው ሁሉ ደስ አላለውም ስለ እውቀቱም እንዲመጣ በፈለጉት ጊዜ እርሱ አሞኛል ብሎ ስራሱ ምክንያት ሰጠ። ❤ በእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት በቅዱስ ዲዮስቆሮስ ላይ ስለ ደረሰበት ሥቃይ በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ ሃይማኖታቸው የቀና እንደሆነ በሚያውቃቸው ባልንጀሮቹ በሆኑ በወዳጆቹ በወታደር አለቆችና በመኰንኖች ፊት የአንድነት ጉባኤያቸውን ረገመ "ከእሊህም ክፉዎች ከጉባኤያቸው አንድ ያላረገኝ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ" አለ። የቊስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት እንጣልዮስም በዐረፈ ጊዜ ሃይማኖቱ የቀና እንደ ሆነ ስለ አወቁ የአገሩ ሊቃውንትና መኳንት ይህን አባት አካክዮስን መረጡት። እርሱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሆነውን መጣላትና መለያየትን ያስወግዳል በማለት ተስፋ አድርገው በቊስጥንጥንያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት። ❤ በተሾመ ጊዜም ከብቻው እግዚአብሔር በቀር ማንም ሊአስወግደው የማይችል የጥልና የመለያየት የማይድን በሽታ አገኘ በልቡም አስቦ "መጀመሪያ ራሴን አድን ዘንድ አይሻለኝምን" አለ የቅዱሳን አባቶችን የቄርሎስና ዲዮስቆሮስን የቀናች ሃይማኖት የተማረና እርሷ የጸና መሆኑን እየታመነለት ከዚህም በማስከተል በክህነት ሥራ በመሳተፍ ይቀበለው ዘንድ ወደ እስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ወደ ሦስተኛው ጴጥሮስ መልእክት ላከ። አባ ጴጥሮስም መልክቱን በአነበበ ጊዜ ደስ ብሎት ታላቅ ክብርን አከበረው ያቺንም መልክት በጉባኤ ፊት አስነበባት ከዚህም በኋላ አባ ጴጥሮስ ለመልእክቱ መልስ ጽፎ ከሦስት ኤጲስቆጶሳት ጋር ወደ አካክዮስ ላከ እነርሱም ወደ ቊስጥንጥንያ ከአባ አካክዮስ ዘንድ በደረሱ ጊዜ የአባ ጴጥሮስን ደብዳቤ ሰጡት እርሱም ሃይማኖታቸው በቀና በወዳጆቹና በአገሩ መኳንንት ፊት አነበባት። ሁሉም ደስ አላቸው አባ አካክዮስም እሊህን ኤጲስቆጶሳት ታላቅ ክብርን አከበራቸው ወደ አንድ ገዳም ወሰዳቸው መሥዋዕትንም አዘጋጅቶ የቊርባን ቅዳሴ በመቀደስ ከእርሳቸወሰ ጋር አንድ ሆነ ከእሳቸውም ቡራኬ ተቀበለ። ❤ ዳግመኛም ከአባ አትናቴዎስ ከአባ ጢሞቴዎስ ከአባ ቄርሎስ ከአባ ዲዮስቆሮስ ከሃይማኖታቸው የሚተላለፈውን እያወገዘ ጻፈ ያቺንም የመልክት ደብዳቤ ሰጣቸውና በፍቅር በሰላም አሰናበታቸው። ወደ አባ ጴጥሮስም በደረሱ ጊዜ አባ አካክዮስ ያደረገውን ሁሉ ነገሩት የመልእክቱንም ደብዳቤ ሰጡት እርሱም ደስ አለው ስሙንም በማዕጠንትና በቊርባን ጊዜ እንዲጠሩ አዘዘ። ዜናውም በሮሜውያን ኤጲስቆጶሳት ዘንድ በተሰማ ጊዜ አባ አካክዮስን ከቊስጥንጥንያ መንበር አሳደዱት በቀናች ሃይማኖት እንደ ጸና በደሴት ውስጥ ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ አካክዮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 30 ስንክሳር። + + + ❤ "ሰላም ለአካክዮስ ለእንጣልዮስ ዋርሱ። ዘዐቢይ ስነ ሞገሱ። ማኅበረ ኬልቄዶን አብዳን አመ ሰደድዎ እምአትሮንሱ። እንበለ ይዕሉ ሃይማኖቶ ወእንበለ ጽድቆ የሐሱ። በኢየሱስ ክርስቶስ አዕረፈት ነፍሱ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የኅዳር 30። + + + ❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "ክብር ንጉሥ ፍትሐ ያፈቅር። አንተ አፅናዕካ ለጽድቅ በኃይልከ። ፍትሕ ወጽድቀ ለያዕቆብ አንተ ገበርከ"። መዝ 98፥4-5 ወይም መዝ 25፥5። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 1፥5-15፣ 1ጴጥ 2፥13-21 እና የሐዋ ሥራ 23፥10-32። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ16፥1-8 ወይም ሉቃ 19፥11-28። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የጻድቁ ንጉሥ የቅዱስ ገብረ መስቀል የዕረፍት በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ። ሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት https://t.me/Eotcw

photo content
+1

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ኅዳር ፴ (30) ቀን። ❤ እንኳን ለኢትዮጵያዊው ለጻድቁ ንጉሥ ለዐፄ ገብረ መስቀል ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። + + + ❤ ጻድቁ ንጉሥ ዐፄ ገብረ መስቀል፦ ይኸውም ንጉሥ ታላቁ ጻድቅ አቡነ አረጋዊ ከሰማይ በወረደላቸው ኅብስት ቀድሰው ያቆረቡትና መንግሥቱን የባረኩለት ነው። ዐፄ ካሌብ የናግራንን ሰማዕታት ደም ተበቅሎ በድል ከተመለሰ በኋላ ከአቡነ ጰንጠሎዎን እጅ መንኰሶ ገዳም ከገባ በኋላ ልጁ ገብረ መስቀል ነገሠ። ዐፄ ገብረ መስቀል በእውነትና በቅንነት ከነገሠ በኋላ አመራሩ ከአህጉሪቷ ጽንፍ እስከ ጽንፍ ደረሰ። በዘመኑም ሁሉ መንግሥቱን የሚቃወም አልተነሣም፤ እርሱም ቤተክርስቲያንን ከመሥራት በቀር ወደ ጦርነት የሄደበት ጊዜ የለም። ❤ መንግሥቱንም ይባረክለት ዘንድ ሠራዊቱን ይዞ ወደ አባታችን ወደ አቡነ አረጋዊ ዘንድ ደብረ ዳሞ ሄደና በፊታቸው ሰግዶ "አባቴ ሆይ! እኔን ባሪያህን፣ መንግሥቴንና ሕዝቤን ሠራዊቴንም ሁሉ ባርክ" እያለ አጥብቆ ማለዳቸው። አባታችን አረጋዊም "የአባቶችህን የዳዊትና የሰሎሞንን መንግሥት የባረከ፣ የአባትህን የካሌብንም መንግሥት የባረከ እግዚአብሔር የአንተንም መንግሥት ይባርክ... "ብለው ባረኩት። ከዚህም በኋላ ንጉሥ ዐፄ ገብረ መስቀል አቡነ አረጋዊን የት ቦታ ላይ ቤተ ክርስቲያን እንደሚሠራ ጠይቋቸው ካሳዩት በኋላ ሲሠራ ሁለት ዓመት የፈጀበት ግሩም ቤተ ክርስቲያን ሠራላቸውና 12 የወርቅና የብር መስቀሎችን ጨምሮ ብዙ ንዋያተ ቅዱሳቶችንና ሥጦታዎች ሰጣቸው። ጳጳስም አስመጥቶ አስባረካትና ከማኅበረ በኩር ያመጣውን በወርቅ በብር የተለበጠች የእመቤታችንን ታቦት በውስጧ አስገባ። ጳጳሱና ንጉሡ ዐፄ ገብረ መስቀልም አቡነ አረጋዊን "ቀድሰህ አቊርበን" ብለውት ይቀድሱ ዘንድ በገቡ ጊዜ መላእክት ሙቀት ያልተለየው ኅብስትና ወይኑን በጽዋ ለቅዳሴው የሚያስፈልገውንም ሁሉ ከሰማይ አወረዱላቸውና ቀድሰው ሲያበቁ ሁሉንም አቆረባቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ንጉሡ ዐፄ ገብረ መስቀል ከተራራው ጫፍ በሚወርዱበት ጊዜ አባታችንን "ይህን የተራራውን መውጫ መሰላል ላፍርሰው ወይስ ልተወው?" አሏቸው። አባታችንም "ለልጅ ልጅ መታሰቢያ እንዲሆን ይህን ድንቅ ሥራ እያየ በፍጥረቱ ሁሉ አንደበት እግዚአብሔር ይመሰገን ዘንድ የደረጃውን መሰላል አፍርሰው፤ ነገር ግን ስለዘንዶው ጅራት ፋንታ ገመድ አብጅ" አለው። ንጉሡም እንደታዘዘው የደረጃውን መሰላል አፈሰውና ወደ ቤተ መንግሥቱ ተመለሰ። ጻድቁ ንጉሥ ዐፄ ገብረ መስቀል ካበረከተልን ትልቅ ውለታው ውስጥ አንዱ ዛሬ በዩኔስኮ የተመዘገበውን የመስቀል በዓልን በአደባባይ እንዲከበር ያደረገ መሆኑ ነው። በዘመኑም ካህናቱ ሕዝቡ ሁሉ አደይ አበባ ይዘው ወደ አደባባይ በመውጣት በያሬዳዊ ዝማሬ የመስቀልን በዓል ያከብሩ ነበር። ❤ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ብርሃኗ የሆነ ነገር ግን እርሷ እንደሚገባው መጠን ያላከበረችው ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ በዚህ ጻድቅ ንጉሥ በዐፄ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት የነበረ ነው። አብረውም ብዙ ታሪኮችን ፈጽመዋል። የተለያዩ ገዳማትን በመዟዟር ቅዱስ ያሬድ ዜማን ሲያስተምር ንጉሡ ደግሞ የቤተ ክርስቲያንን ይዞታ ያስፋፋና ቋሚ መተዳደሪያ ይሰጡ ገዳማቱን ያጠናክሩ ነበር። አቡነ አረጋዊ ደግሞ አብረው ምንኵስናን ያስፋፉ ነበር። ሦስቱም ይህን ተግባራዊ እንዳደረጉ ለማሳያ ይሆን ዘንድ ቅዱስ ያሬድ 3 ዓመት ዝማሬ መዋሥዕት ያስተማረባትና ዛሬም ድረስ ማስመስከሪያ የሆነችውን እጅግ ጥንታዊቷን ዙር አባ ጽርሕ አርያም አቡነ አረጋዊ ገዳምን እንደምሳሌ ማየት እንችላለን። አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ያሬድ በቅዱስ ዑራኤል መሪነት በሐረግ ተስበው ዓምባው ላይ ከወጡ በኋላ ንጉሡ ዐፄ ገብረ መስቀል ደግሞ ተራራውን ባርከው ከፍለው መንገድ አበጅተውላቸው ወደ ዓምባው ወጥተው ሦስቱም በዚያ በጋራ ኖረው ብዙ መንፈሳዊ ሥራን ሠርተዋል። ❤ ጻድቁ ንጉሥ ዐፄ ገብረ መስቀል ከተሰዓቱ ቅዱሳን ጋር ሆኖ ብዙ መንፈሳዊ ሥራን ሠርቷል። ዐፄ ገብረ መስቀል በጽድቅ ሕይወት እየተመላለሱ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለአገራችን የዋሉት ውለታ እጅግ ብዙ ነው። ዕረፍታቸውም በዚች ቀን ኅዳር 30 ነው። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ። + + + ❤ "ሰላም ለከ ንጉሥ ክቡር። እንተ ትትሜካህ በኃይሉ ለእግዚአብሔር። ገብረ መስቀል መዊዒ ወመግረሬ ፀር። በመዋዕሊከ መዋዕለ ሰላም ወፍቅር። ማኅሌተ ሰማይ መዝሙር ተከስተ በምድር"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የኅዳር 30። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት https://t.me/Eotcw

photo content
+3

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ ፭ኛው የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ሥርዓተ ቀብር ለብዙ ዓመታት ባገለገሉባት ደብረ ምዕዋን አቡነ ብፁዕ አምላክ ገዳም ተፈጸመ።

photo content
+2

😭 የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ ቀዳማይ የቀብር ሥነ ሥርዓት ነገ ኅዳር ፳፱ ይፈጸማል። 😭 የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ቀዳማይ የቀብር ሥነ ሥርዓት ነገ ሐሙስ ሕዳር 29 ቀን 2015 ዓ.ም በአሥመራ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ይፈጸማል። 😭 በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ ለመታደም የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ጨምሮ ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ልዑካቸውን እየላኩ ይገኛሉ። 😭 ቅዱስነታቸው ባደረባቸው ሕመም ምክንያት በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ሕዳር 23 ቀን 2015 ዓ.ም በዘጠና ስድስት ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን በተለያዮ ሚዲያዎች መዘገቡ ይታወሳል። 😭 ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ ቀዳማዊ የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን ተከትሎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በቅዱስነታቸው ሥርዓተ ቀብር ላይ የሚገኙ ልዑካንን በዛሬው ዕለት ወደ አስመራ እንዲጓዙ ወስኗል። 😭 ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊና የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የታላቋ ብሪታኒያ እና የሩቅ ምሥራቅ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ ተመድቦው በአስመራ በሚካሄደው ሥርዓተ ቀብር ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ይወክላሉ። @sigewe https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ዮሐ. 10:1-22፡ "አማን አማን እብለክሙ" - "እውነት፡እውነት፡እላችኋለሁ፥ወደበጎች፡በረት፡በበሩ፡የማይገባ፡በሌላ፡መንገድ፡ግን፡የሚወጣ፡እርሱ፡ሌባ፡ወንበዴም፡ነው፤ በበሩ፡የሚገባ፡ግን፡የበጎች፡እረኛ፡ነው። ለእርሱ፡በረኛው፡ይከፍትለታል፤በጎቹም፡ድምፁን፡ይሰሙታል፥የራሱንም፡በጎች፡በየስማቸው፡ጠርቶ፡ይወስዳቸዋል። የራሱንም፡ሁሉ፡ካወጣቸው፡በኋላ፡በፊታቸው፡ይሄዳል፥በጎቹም፡ድምፁን፡ያውቃሉና፡ይከተሉታል፤ ከሌላው፡ግን፡ይሸሻሉ፡እንጂ፡አይከተሉትም፥የሌላዎችን፡ድምፅ፡አያውቁምና። ኢየሱስ፡ይህን፡ምሳሌ፡ነገራቸው፤እነርሱ፡ግን፡የነገራቸው፡ምን፡እንደ፡ሆነ፡አላስተዋሉም። ኢየሱስም፡ደግሞ፡አላቸው፦እውነት፡እውነት፡እላችኋለሁ፥እኔ፡የበጎች፡በር፡ነኝ። ከእኔ፡በፊት፡የመጡ፡ሁሉ፡ሌባዎችና፡ወንበዴዎች፡ናቸው፤ዳሩ፡ግን፡በጎቹ፡አልሰሟቸውም። በሩ፡እኔ፡ነኝ፤በእኔ፡የሚገባ፡ቢኖር፡ይድናል፥ይገባልም፡ይወጣልም፡መሰማሪያም፡ያገኛል። ሌባው፡ሊሰርቅና፡ሊያርድ፡ሊያጠፋም፡እንጂ፡ስለ፡ሌላ፡አይመጣም፤እኔ፡ሕይወት፡እንዲሆንላቸው፡ እንዲበዛላቸውም፡መጣሁ። መልካም፡እረኛ፡እኔ፡ነኝ።መልካም፡እረኛ፡ነፍሱን፡ስለ፡በጎቹ፡ያኖራል። እረኛ፡ያልሆነው፡በጎቹም፡የርሱ፡ያልሆኑ፡ሞያተኛ፡ግን፥ተኵላ፡ሲመጣ፡ባየ፡ጊዜ፥በጎቹን፡ትቶ፡ይሸሻል፤ተኵላም፡ይነጥቃቸዋል፡በጎቹንም፡ይበትናቸዋል። ሞያተኛ፡ስለ፡ሆነ፡ለበጎቹም፡ስለማይገደው፡ሞያተኛው፡ይሸሻል። መልካም፡እረኛ፡እኔ፡ነኝ፥አብም፡እንደሚያውቀኝ፡እኔም፡አብን፡እንደማውቀው፡የራሴን፡በጎች፡ዐውቃለሁ፡የራሴም፡በጎች፡ያውቁኛል፤ነፍሴንም፡ስለ፡በጎች፡አኖራለሁ። ከዚህም፡በረት፡ያልሆኑ፡ሌላዎች፡በጎች፡አሉኝ፤እነርሱን፡ደግሞ፡ላመጣ፡ይገ፟ባ፟ኛል፥ድምፄንም፡ይሰማሉ፥አንድም፡መንጋ፡ይሆናሉ፥እረኛውም፡አንድ። ነፍሴን፡ደግሞ፡አነሣት፡ዘንድ፡አኖራለሁና፡ስለዚህ፡አብ፡ይወደኛል። እኔ፡በፈቃዴ፡አኖራታለሁ፡እንጂ፡ከእኔ፡ማንም፡አይወስዳትም።ላኖራት፡ሥልጣን፡አለኝ፡ደግሞም፡ላነሣት፡ሥልጣን፡አለኝ፡ይህችን፡ትእዛዝ፡ከአባቴ፡ተቀበልሁ። እንግዲህ፡ከዚህ፡ቃል፡የተነሣ፡በአይሁድ፡መካከል፡እንደ፡ገና፡መለያየት፡ሆነ። ከእነርሱም፡ብዙዎች፦ጋኔን፡አለበት፡አብዷልም፤ስለ፡ምንስ፡ትሰሙታላችሁ፧አሉ። ሌላዎችም፦ይህ፡ጋኔን፡ያለበት፡ሰው፡ቃል፡አይደለም፤ጋኔን፡የዕውሮችን፡ዐይኖች፡ሊከፍት፡ይችላልን፧አሉ። በኢየሩሳሌምም፡የመቅደስ፡መታደስ፡በዓል፡ሆነ።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

1.15 KB

29/3/2015 ዓ.ም (፳፱/፫/፳፻፲፭ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ኪያየ ይጸንሑ ኃጥአን ይቀትሉኒ። እስመ ስምዐከ ለበውኩ። ለኲሉ ግብር ርኢኩ ማኅለቅቶ፡፡ መዝ 118:95 🕯 ትርጉም ኃጢአተኛዎች ያጠፉኝ ዘንድ ጠበቁኝ። ምስክርህን ግን መረመርሁ። የሥራህን ሁሉ ፍጻሜ አየኹ። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯