ሰዋስው ☘☘☘☘
رفتن به کانال در Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
نمایش بیشتر1 161
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
1 161
❤ "ስለ በኣታ ለማርያም"። ሁላችንንም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች የበኩላችንን አስተዋጽኦ እናድርግ።
❤ ውድ የቴሌግራም ቤተሰቦቼ እንደምን ሰነበታችሁ በከንባታ ጠንባሮ አላባ ሀገረ ስብከት ለሚገኘው ለደብረ መንክራት ጎፈሬ በኣታ ለማርያም የፊታችን ታኅሣሥ 3 2015 ዓ.ም ለሚከበረው ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ዓመታዊ ክብረ በዓል ማክበርያ የሚሆን ቤተ ክርስቲያኑ ምንም አይነት ገቢ ስሌለው አካባቢውም በሌሎች የእምነት ጅርጅቶች የተከበበ ስለሆነ ሁላችንም ምዕመናን ከታች በደብዳቤ ላይ የተጠቀሱት ነገሮች በመርዳት የበኩላችን አስተዋጾ እናድርግ።
❤ የደብሩየደብሩ ኣካውንት
Gofare D/mankrat beata mariam B/kirstian
የደብረ መንክራት በዓታ ማርያም ቤተ ክርስቲያን
1000366975164 ንግድ ባንክ ነው።
❤ ያስገባችሁበትን ወረቀት ፎቶ በማንሳት inbox ላይ በመላክ ይተባበሩን።
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ "ሰላም ለከ መርቆሬዎስ ዘሮም። መስተጽዕነ ፈረስ ጸሊም። አመ አንደዱ ታሕቴከ ውሉደ መርገም። እምቅሡፍ አባልከ እንተ ውኅዘ ደም። አርአያ ዝናም ብዙኅ አጥፍኦ ለፍሕም"። ትርጉም፦ በጥቊር ፈረስ ላይ የተቀመጥኽ የሮም ሰው ለኾንኸው ለመርቆሬዎስ ሰላም ይገባኻል፤ የመርገም ልጆች ከሥርኽ እሳትን ባነደዱ ጊዜ ከተገረፈው ሰውነትኽ በብዙ ዝናብ አምሳል የፈሰሰው ደም ፍሙን አጠፋው።
ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የኅዳ ር25።
+ + +
❤ "ሰላም ለመርቆሬዎስ ሰማዕት ንጹሕ ድንግል ፈጻሜ ቃለ ወንጌል"። ትርጉም፦ የወንጌል ቃል የፈጸመ ለኾነ ለንጹሕ ድንግል ሰማዕት መርቆሬዎስ ሰላምታ ይገባል። አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።
+ + +
❤ "ጸለዩ ባስልዮስ ወጎርጎሬዎስ ኀበ ሥዕሉ ለቅዱስ መርቆሬዎስ፤ ደነነ ሥዕል ከመ ኦሆ ዘይብል፤ ሰምዖሙ ጸሎቶሙ፤ ወቀተለ ፀሮሙ"። ትርጉም፦ ባስልዮስና ጎርጎርዮስ በቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕል ፊት ጸለዩ ስዕሉም ጸሎታቸው ሰምቶ እሺ እንደማለት ዘንበል አለ ጠላታቸውን ገደለላቸው (አጠፋላቸው)። የሊቁ የቅዱስ ያሬድ ዚቅ የኅዳ ር 25።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ ከዚህም በኋላ አባቱና እናቱ በሞቱ ጊዜ ንጉሡ ቅዱስ መርቆሬዎስን ወስዶ በአባቱ ፈንታ በመርዶሳውያን አገር ላይ ሾመው ቅዱስ መርቆሬዎስም መኰንንነትን በተሾመ ጊዜ ያ ገጸ ከልቡ ከርሱ ጋር ነበር ወደ ጦርነትም አብሮት የሚወጣ ሆነ። ለመዋጋትም በሚሻ ጊዜ የቀድሞ የአራዊት የሆነ ተፈጥሮውን እግዚአብሔር ይመልስለት ነበር ማንም ሊቋቋመው የሚችል የለም። ለቅዱስ መርቆሬዎስም ታላቅ የድል አድራጊነት ኃይል ተሰጠው ዜናውም በሁሉ ቦታ ተሰማ ከቤተ መንግሥት ሰዎችም ከፍ ከፍ አለ።
❤ እንዲህም ሆነ ያን ጊዜ በዚያን ወራት በሮሜ አገር ጣዖትን የሚያመልክ ዳኬዎስ የሚባል ንጉሥ አለ። ጠላቶቹም የበርበር ሰዎች ተነሡበት እርሱም ከእርሳቸው ጋር ሊዋጋ ሠራዊቱን ሰብስቦ ወጣ እነርሱ ግን እንደ ባሕር አሸዋ ብዙ ነበሩ ብዛታቸውንም በአየ ጊዜ ደንግጦ እጅግ ፈራ ቅዱስ መርቆሬዎስም "እግዚአብሔር ያጠፋቸው ዘንድ በእጃችንም አሳልፎ ሊሰጣቸው አለውና አትፍራ" አለው።
❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ መርቆሬዎስ የእግዚአብሔርን መልአክ በውጊያው ውስጥ አየው የተሳለ ሰይፍም በእጁ ውስጥ አለ ያቺንም ሰይፍ ሰጠውና እንዲህ አለው "ጠላቶችህን ድል በአደረግህ ጊዜ ፈጣሪህ እግዚአብሔር አስበው"። ጠላቶቹንም ድል አድርጎ በሰላም ተመለሰ መልአኩም ዳግመኛ ተገልጦለት "ለምን ፈጣሪህን የእግዚአብሔርን ስም መጥራት ረሳህ" አለው።ጦርነቱም ከተፈጸመ በኋላ ንጉሥ ዳኬዎስ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረግ በዓልን ሊያደርግ ወደደ ቅዱስ መርቆሬዎስም ለበዓል ማክበር አብሮት አልወጣም ወደ ቤቱ ሔደ እንጂ ሰዎችም ቅዱስ መርቆሬዎስ እንዳልመጣና ዕጣንን በማሳረግም እንዳልተባባረ አስረዱት።
❤ ከዚያንም ጊዜ ንጉሥ መልክተኞችን ልኮ ቅዱስ መርቆሬዎስን ወደርሱ አስመጣው በመዘግየቱም አድንቅ "ለአማልክት ዕጣን ለማድረግ ከእኔ ጋር ያልወጣህ የእኔን ፍቅር እንዴት ተውህ" አለው። በዚያንም ጊዜ ትጥቁንና ልብሱን ወረወረለትና ንጉሡን እንዲህ አለው "እኔ ክብር ይግባውና ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስን አልክደውም ለረከሱ ጣዖታትም አልሰግድም"። ንጉሥ ዳኬዎስም ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ እርጥብ በሆኑ የሽመል በትሮች እንዲደበድቡት አዘዘ። ሁለተኛም ከላም ቆዳ በተሠራ ጅራፍ ይገርፋት ዘንድ አዘዘ ንጉሡ እንዳዘዘ ይህን ሁሉ አደረጉበት።
❤ በዚያንም ጊዜ የአገር ሰዎች ስለ ቅዱስ መርቆሬዎስ እንዳይነሡበት ፈርቶ የቀጰዶቅያና የእስያ ክፍል ወደ ሆነች ወደ ቂሣርያ በብረት ማሠርያ አሥሮ ላከው። በዚያም እንዲአሠቃዩት አዘዘ ከአሠቃዩትም በኋላ ንጉሥ ዳኬዎስ እንዳዘዘው ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና ተጋድሎውን ፈጽሞ በመግሥተ ሰማያት የሕይወት አክሊልን ተቀበለ። የማይጠፋ ሰማያዊ አክሊልንም ተቀዳጅቶ ወደ ዘላለም ሕይወት ከገባ በኋላ በዓለሙ ሁሉ አብያተ ክርስቲያናት ታነፁለት እግዚአብሔርም ታላላቅ የሆኑ ድንቆች ተአምራትን በውስጣቸው ገለጠ።
❤ ከተአምራቱም አንዲቱ ዑልያኖስ በነገሠ ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ካደ በዚያንም ወራት ቅዱስ ባስልዮስ የቂሣርያ ሊቀ ጳጳሳት ነበረ ተአምራቱ በተጻፈበት መጽሐፍ እንደተጻፈ ምእመናን በጽኑዕ ሥቃይ ዑልያኖስ ባሠቃየ ጊዜ መክሮ አስተምሮ ከስሕተቱ ይመልሰው ዘንድ ቅዱስ ባስልዮስ ወደርሱ መጣ።
❤ ዑልያኖስም ቅዱስ ባስልዮስን በአየው ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችንን ሰደበ ቅዱስ ባስልዮስንም አሠረው በዚያ በእስር ቤትም የቅዱስ መርቆሬዎስን ሥዕል አይቶ በፊቱ ቅዱስ ባስልዮስ ጸለየ ሥዕሉም ከቦታው ታጣ። ያን ጊዜ ወደ ዑልያኖሰሰ ሒዷልና በጦርም ወግቶ ገደለውና ወዲያውኑ ወደቦታው ተመለሰ ከጦሩም አንደበት ደም ይንጠፈጠፍ ነበር። ቅዱስ ባስልዮስም ከሀዲ ዑልያኖስን እንደገደለው አውቆ እንዲህ ብሎ ተናገረ "የክርስቶስ ምስክር ሆይ የእውነት ፀር የሆነ ዑልያኖስን ገደልከውን?" ያን ጊዜ አዎን እንደሚል ሥዕሉ ራሱን ዘንበለሰ አደረገ ቅዱስ ባስልዮስም ደስ ብሎት እግዚአብሔር አመሰገነ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ መርቆሬዎስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ ገድለ መርቆሬዎስና የኅዳር 25 ስንክሳር።
+ + +
❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ልሳነ ከለባቲከ ላዕለ ጸላእቱ። አስተርአየ ፍናዊከ እግዚኦ። ፍናዊሁ ለአምላክነ ለንጉሥ ዘውስተ መቅደስ"። መዝ 67፥23-24 ወይም መዝ 88፥14-15። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥17-32 ወይም ማቴ 20፥20-24።
+ + +
❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ቅረብ ኀቤሁ ወያበርህ ለክሙ። ወኢይትኀፈር ገጽክሙ። ዝንቱ ነዳይ ጸርሐ ወእግዚአብሔር ስምዖ"። መዝ 33፥5-6 የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 12፥25-ፍ.ም፣ ያዕ 3፥4-13 እና የሐዋ ሥራ 21፥27-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 8፥22-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ እግዚእነ ነው። መልካም የሰማዕቱ የቅዱስ መርቆሬዎስ የዕረፍት በዓልና፣ ዕለተ ሰንበትና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ኅዳር ፳፭ (25) ቀን።
❤ እንኳን ለታላቁ ሰማዕት ለቅዱስ መርቆሬዎስ (ፒሉፓዴር) በንጉሥ ዳኬዎስ እጅ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ መታሰቢያ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከእስላሞች ወገን ከነበረ ቅዱስ መርቆሬዎስ ተአምር አድርጎ ከመለሰው ከቅዱስ ዮሐንስ፣ ከአቃርዎስና ከሮማኖስ ከመታሰቢያቸወ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ የዕለቱ አንገርጋሪ ግእዝ ዜማ፦ "ፈጸመ ስምዓ ቅዱስ መርቆሬዎስ፤ በመዋዕሊሁ ለዳኬዎስ ንጉሥ፤ ወኮነ መድኃኒተ ለኲሉ ዘነፍስ፤ ወተፈሥሑ፤ ባስልዮስ ወጎርጎሬዎስ"። ትርጉም፦ ቅዱስ መርቆሬዎስ በንጉሥ ዳኬዎስ በዘመኑ ምስክርነቱን ፈጸመ፤ በዚህም ለነፍሳት ሁሉ መድኃኒት ሆናቸው፤ ባስልዮስና ጎርጎርዮስ ተደሰቱ። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ።
+ + +
❤ የዚህ ሳምንት መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፭ አምላክ ፍጹም በህላዌሁ ዘሀሎ እምቅድመ ይትፈጠር ዓለም ዘበመንግሥቱ ይኴንን ዓለም ሰማየ ገብረ ለስብሐቲሁ ዓለም ፈጠረ ወምድረ ሣረረ ወገሠፀ ባሕረ ወገሠፃሙ ለኵሉ ፍጥረት እለ ውስተ ደይን ያዕርፉ ባቲ አብ ቀደሳ ለሰንበት ቅረቡ ኀቤሁ ለአምላከ ጽድቅ ማኅደር ለንጹሐን ከመ ትንሥኡ አክሊለ ስብሐት ዘአስተዳለወ ለእለ ያፈቅርዎ ፀንዑ በጸጋ በስን ወበሃይማኖት ወረሱ አክሊለ ስምዕ በእምነቶሙ እለ እምዓለም አሥመርዎ ለእግዚኦሙ መምህረ ቅዱሳን አክላለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት"። ትርጉም፦ ቅድመ ዓለም በመንግሥቱ የነበረ፣ በአናናሩ ፍጹም አምላክ የሆነ ዓለምን ይገዛል፣ ለክብሩ ሰማይን አደረገ፣ ሰማይንና ምድርን ፈጠረ፣ ባሕርን ገሠፀ ፍጥረትን ሁሉ ገሠፃቸው በመከራ ውስጥ ያሉ ያርፉበት ዘንድ አብ ሰንበትን ቀደሳት ለሚወዱት ያዘጋጀውን በንጹሐን ማደሪያ ያከብር አክሊልን ትቀዳጁ ዘንድ ወደ እውነት አምላክ ቅረቡ በዓለም ላሉ የቅዱሳን መምህራቸው፣ የሰማዕታት አክሊላቸው፣ የካህናት ክብራቸው የሆነው ጌታቸውን ደስ ያሰኙት ዘንድ በሃይማኖት፣ በጸጋና በልጅነት ጽኑ፣ በእምነታቸውም የምስክርነትን አክሊል ወረሱ። ሊቅ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ።
+ + +
❤ ቅዱስ መርቆሬዎስ፦ መርቆሬዎስ ማለት የአብ ወዳጅ ማለት ነው። በሁለተኛ ትርጓሜ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው። ይህም ቅዱስ አስሊጥ ከምትባል አገር ነው እርሷም የአባቱና የአያቱ አገር ናት እርሱ ግን ተወልዶ ያደገው በሮሜ ከተማ ነው።
❤ የአባቱና የአያቱ ሥራቸው አውሬ ማደን ነበር በአንዲት ዕለትም እንደልማዳቸው ለማደን ወጡ ከገጸ ከለባት ወገንም ሁለት ወንዶች ተገናኙአቸውና የቅዱስ መርቆሬዎስን አያት ስዲሮስ በሉት። ሁለተኛም አባቱን አሮስን ሊበሉት ፈለጉ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክም ከለከላቸው "ከእርሱ የሚወጣ መልካም ፍሬ ስለ አለ አትንኩት" አላቸው።
❤ ከዚህም በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ዙሪያቸውን በእሳት ከበባቸው በተቸገሩ ጊዜም ወደ ቅዱስ መርቆሬዎስ አባት አሮስ መጥተው ሰገዱለት በዚያንም ጊዜ እግዚአብሔር ፍጥረታቸውን ወደገራምነት ለወጠውና እንደ በጎች የዋሆች ሆኑ አብረውትም ወደ መንደር ገቡ።
❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ መርቆሬዎስ በተወለደ ጊዜ ስሙን ፒሉፓዴር ብለው ጠሩት የውሻ መልክ ያላቸው በእነርሱ ዘንድ ብዙ ዘመናት የሚኖሩ ሆኑ ከዚህም በኋላ ክርስቲያኖች ሆኑ የቅዱስ መርቆሬዎስ ወላጆች አስቀድሞ አረማውያን ነበሩና የክርስትና ጥምቀትንም ጸጋ በተቀበሩ ጊዜ የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት ኖኅ ብለው ሰየሙት እናቱንም ታቦት አሏት ፒሉፓዴርንም መርቆሬዎስ ብለው ሰየሙት። የውሻ መልክ ያላቸው ግን የእግዚአብሔር መልአክ በተገለጸላቸው ጊዜ እንደ ነገራቸው ለቅዱስ መርቆሬዎስ አባት የሚታዘዙና የሚያገለግሉ ሆኑ።
❤ ንጉሡም የኖኅንና የውሻ መልክ ያላቸውን ዜና በሰማ ጊዜ ወደርሱ አስቀረባቸው በዚያንም ጊዜ እግዚአብሔር በንጉሡ ፊት የቀድሞ ፍጥረታቸውን መልሶላቸው የንጉሡ ያቀረባቸውን ሁሉንም አራዊት አጠፏቸው። ንጉሡም ይህን በአየ ጊዜ እጅግ ፈራ የአራዊትንም ተፈጥሮአቸውን ያርቅ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እንዲማልድ የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት ለመነው። እርሱም በለመነ ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን ተፈጥሮአቸውን መልሶላቸው ገራሞች ሆኑ።
❤ ከዚህም በኋላ የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት ንጉሡ ወስዶ ገዥና የሠራዊት አለቃ አድርጎ ሾመው የውሻ አርያ ያላቸውም ይታዘዙለት ነበር ከእርሳቸውም የተነሣ ሁሉም ይፈሩ ነበር። ከዚህም በኋላ የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት የሾመውን ንጉሥ ይወጋ ዘንድ ከሀዲ ንጉሥ ተነሣ ንጉሡም ከጦር አባት ወደ ጦርነት ላከው። ከሀዲው ንጉሥ ግን እነዚያን የውሻ አርያ ያላቸውን አባብለውና ሸንግለው ወደርሱ የመጧቸው ዘንድ ወታደሮችን ላከ በአመጧቸውም ጊዜ ሃይማኖታቸውን ይለውጡ ዘንድ አብዝቶ ሸነገላቸው ባልሰሙትም ጊዜ ሊአሠቃያቸው ጀመረ አንዱ አምልጦ ሸሽቶ ወደ ጌታው ሔደ ሁለተኛውም በሰማዕትነት ሞተ።
❤ ከጦር ሜዳ የቅዱስ መርቆሬዎስ አባት በመለሰ ጊዜ ሚስቱንና ልጁን ፈለጋቸው ግን አላገኛቸውም ንጉሡ የሱ ወገኖች ድል እንደሆኑ በሰማ ጊዜ የቅዱስ መርቆሬዎስ አባት መኰንኑ የሞተ መስሎት ነበርና የቅዱስ መርቆሬዎስን እናት ወስዶ ሊአገባት ፈለገ ከንጉሥ ወታደሮችም አንዱ ንጉሡ ያሰበውን በጽሞና ነገራት። እርሷም ይህንኑ ወታደር ከአገር ውስጥ በሥውር ያወጣት ዘንድ ለመነችውና ከልጇ ከብፁዕ መርቆሬዎስ ጋር ወጥታ ወደ ሌላ አገር ሔደች። ንጉሡም ከእርሱ የሆነውን የመኰንኑም የመርቆሬዎስን አባት ሚስቱን ለማግባት ማሰቡን እንዳይነግሩት አዘዘ የውሻ መልክኮች ያላቸው ከእርሱ ጋር እንዳሉ የተቆጣም እንደሆነ እንደሚአመጣቸውና አገሮችን ያጠፋሉ ብሎ ይጠራጠራልና ስለዚህ እጅግ ይፈራዋል።
❤ ከዚህም በኋላ ደግሞ በንጉሡ ላይ ጦርነት ተነሣ የቅዱስ መርቆሬዎስም አባት ወደ ጦርነት ወጣ በእግዚአብሔርም ፈቃድ ይዘው ማረኩት ወደ ሮሜውም ንጉሥ አቀረቡት ንጉሡም ክርስቲያን ነበርና የተማረከው መኰንን ክርስቲያን መሆኑን በአወቀ ጊዜ አልገደለውም በክብር አኖረው እንጂ እጅግም ወደደውና ከጥቂት ቀኖች በኋላ በመርዶሳውያን አገሮች ሁሉ ላይ ገዥ አድርጎ ሾመው።
❤ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፈቃድ ሚስቱና ልጁ መርቆሬዎስ ወዳሉበት አገር ደረሰ ሚስቱም በቤተ ክርስቲያን ደጃፍ በአየችው ጊዜ ባሏ እንደሆነ አወቀችው እርሱ ግን አላወቃትም በአንዲትም ዕለት እርሱና ጭፍሮቹ ከእንግዳ ማረፊያ ቤት በወጡ ጊዜ ልጅዋን መርቆሬዎስን ወስዳ ያማሩ ልብሶችን አልብሳ ሒዶ ከመኰንኑ ፈረስ ላይ እንዲቀመጥ አዘዘችው እርሱም አባቱ ነው በተቀመጠም ጊዜም ጭፍሮች ይዘው ወደ መኰንኑ ፊት አቀረቡት መኰንኑም ልጁ እንደሆነ አላወቀምና በእርሱ ላይ ተቆጣ።
❤ የመርቆሬዎስ እናት መጥታ "ጌታዬ ሆይ እኛ መጻተኞች ነን አንተም መጻተኛ እንደሆንክ በአወቅሁ ጊዜ ልጅህ ሁኖ ልጄ ከአንተ ጋር እንዲሆን አሰብኩ" አለችው። እርሱም ጠየቃት እንዴት እንደተሰደደችም መረመራት እርሷም ሚስቱ እንደሆች ነገረችው በዚያንም ጊዜ አወቃት ልጁን መርቆሬዎስንም አወቀው አጅግም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔር አመሰገኑት ያንንም የእንግዳ ማረፊያ ቤት ቤተ ክርስቲያን አደረጉት እግዚአብሔርም እያመሰገኑ በአንድነት ኖሩ።
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ማቴ. 13:36-43፡ "ወእምዝ ኀዲጎ አሕዛብ ቦአ" - "በዚያን፡ጊዜ፡ሕዝቡን፡ትቶ፡ወደ፡ቤት፡ገባ። ደቀ፡መዛሙርቱም፡ወደ፡ርሱ፡ቀርበው፦የዕርሻውን፡እንክርዳድ፡ምሳሌ፡ተርጕምልን፡አሉት። እርሱም፡መልሶ፡እንዲህ፡አላቸው፦መልካምን፡ዘር፡የዘራው፡የሰው፡ልጅ፡ነው፤ዕርሻውም፡ዓለም፡ነው፤ መልካሙም፡ዘር፡የመንግሥት፡ልጆች፡ናቸው፤ እንክርዳዱም፡የክፉው፡ልጆች፡ናቸው፥የዘራውም፡ጠላት፡ዲያብሎስ፡ነው፤መከሩም፡የዓለም፡መጨረሻ፡ነው፥ዐጫጆችም፡መላእክት፡ናቸው። እንግዲህ፡እንክርዳድ፡ተለቅሞ፡በእሳት፡እንደሚቃጠል፥በዓለም፡መጨረሻ፡እንዲሁ፡ይሆናል። የሰው፡ልጅ፡መላእክቱን፡ይልካል፥ከመንግሥቱም፡እንቅፋትን፡ሁሉ፡ዐመፃንም፡የሚያደርጉትን፡ይለቅማሉ፥ ወደ፡እቶነ፡እሳትም፡ይጥሏቸዋል፤በዚያ፡ልቅሶና፡ጥርስ፡ማፋጨት፡ይሆናል። በዚያን፡ጊዜ፡ጻድቃን፡በአባታቸው፡መንግሥት፡እንደ፡ፀሐይ፡ይበራሉ። የሚሰማ፡ጆሮ፡ያለው፡ይስማ።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
1 161
24/3/2015 ዓ.ም (፳፬/፫/፳፻፲፭ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ባርክዎ ለእግዚአብሔር ኩልክሙ መላእክቲሁ
ጽኑዓን ወኀያላን እለ ትገብሩ ቃሎ
ወእለ ትሰምዑ ቃለ ነገሩ፡፡ መዝ 102፥20
🕯 ትርጉም
ቃሉን የምታደርጉ ብርቱዎችና ኀይለኞች
የቃሉንም ድምጽ የምትሰሙ መላእክት ሁሉ እግዚአብሔርን ባርኩ፡፡
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ዮሐ. 4:10-27 "ወአውሥአ ኢየሱስ ወይቤላ" - "ኢየሱስ፡መልሶ፦የእግዚአብሔርን፡ስጦታና፦ውሃ፡አጠጪኝ፡የሚልሽ፡ማን፡መሆኑንስ፡ብታውቂ፥አንቺ፡ትለምኚው፡ነበርሽ፡የሕይወትም፡ውሃ፡ይሰጥሽ፡ነበር፡አላት። ሴቲቱ፦ጌታ፡ሆይ፥መቅጃ፡የለህም፡ጕድጓዱም፡ጥልቅ፡ነው፤እንግዲህ፡የሕይወት፡ውሃ፡ከወዴት፡ታገኛለህ? በእውኑ፡አንተ፡ይህን፡ጕድጓድ፡ከሰጠን፡ከአባታችን፡ከያዕቆብ፡ትበልጣለኽን? ራሱም፡ልጆቹም፡ከብቶቹም፡ከዚህ፡ጠጥተዋል፡አለችው። ኢየሱስም፡መልሶ፦ከዚህ፡ውሃ፡የሚጠጣ፡ዅሉ፡እንደ፡ገና፡ይጠማል፤ እኔ፡ከምሰጠው፡ውሃ፡የሚጠጣ፡ዅሉ፡ግን፡ለዘለዓለም፡አይጠማም፥እኔ፡የምሰጠው፡ውሃ፡በእርሱ፡ውስጥ፡ለዘለዓለም፡ሕይወት፡የሚፈልቅ፡የውሃ፡ምንጭ፡ይኾናል፡እንጂ፡አላት። ሴቲቱ፦ጌታ፡ሆይ፥እንዳልጠማ፡ውሃም፡ልቀዳ፡ወደዚህ፡እንዳልመጣ፡ይህን፡ውሃ፡ስጠኝ፡አለችው። ኢየሱስም፦ሂጂና፡ባልሽን፡ጠርተሽ፡ወደዚህ፡ነዪ፡አላት። ሴቲቱ፡መልሳ፦ባል፡የለኝም፡አለችው። ኢየሱስ፦ባል፡የለኝም፡በማለትሽ፡መልካም፡ተናገርሽ፤ አምስት፡ባሎች፡ነበሩሽና፥አሁን፡ከአንቺ፡ጋራ፡ያለው፡ባልሽ፡አይደለም፤በዚህስ፡እውነት፡ተናገርሽ፡አላት። ሴቲቱ፦ጌታ፡ሆይ፥አንተ፡ነቢይ፡እንደ፡ሆንህ፡አያለሁ። አባቶቻችን፡በዚህ፡ተራራ፡ሰገዱ፤እናንተም፦ሰው፡ሊሰግድበት፡የሚገባው፡ስፍራ፡በኢየሩሳሌም፡ነው፡ትላላችሁ፡አለችው። ኢየሱስም፡እንዲህ፡አላት፦አንቺ፡ሴት፥እመኚኝ፥በዚህ፡ተራራ፡ወይም፡በኢየሩሳሌም፡ለአብ፡የማትሰግዱበት፡ጊዜ፡ይመጣል። እናንተስ፡ለማታውቁት፡ትሰግዳላችሁ፤እኛ፡መዳን፡ከአይሁድ፡ነውና፥ለምናውቀው፡እንሰግዳለን። ነገር፡ግን፥በእውነት፡የሚሰግዱ፡ለአብ፡በመንፈስና፡በእውነት፡የሚሰግዱበት፡ጊዜ፡ይመጣል፡አሁንም፡
ሆኗል፤አብ፡ሊሰግዱለት፡እንደ፡እነዚህ፡ያሉትን፡ይሻልና፤ እግዚአብሔር፡መንፈስ፡ነው፥ የሚሰግዱለትም፡በመንፈስና፡በእውነት፡ሊሰግዱለት፡ያስፈልጋቸዋል። ሴቲቱ፦ክርስቶስ፡የሚባል፡መሲሕ፡እንዲመጣ፡ዐውቃለኹ፤ርሱ፡ሲመጣ፡ዅሉን፡ይነግረናል፡አለችው። ኢየሱስ፦የምናገርሽ፡እኔ፡እርሱ፡ነኝ፡አላት። በዚያም፡ጊዜ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡መጡና፡ከሴት፡ጋራ፡በመነጋገሩ፡ተደነቁ፤ነገር፡ግን፦ ምን፡ትፈልጊያለሽ? ወይም፦ስለ፡ምን፡ትናገራታለህ? ያለ፡ማንም፡አልነበረም።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
1 161
24/3/2015 ዓ.ም (፳፬/፫/፳፻፲፭ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ወአስተዮሙ ከመ ዘእምቀላይ ብዙኅ።
ወአውኀዘ ማየ ከመ ዘእምአፍላግ።
ወአውፅአ ማየ እምዕብን፡፡ መዝ. 77÷15
🕯 ትርጉም
ከጥልቅ ምንጭ እንደሚገኝ ያህል በብዙ አጠጣቸው።
ውኃን ከጭንጫ አፈለቀ።
ውኃንም እንደ ወንዞች አፈሰሰ።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯1 161
😭 ዜና ዕረፍት።
😭 ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ዘሀገረ ኤርትራ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ!።
😭 የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አምስተኛ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ ቀዳማዊ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።
😭 ቅዱስነታቸው ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት 23/03/15 ዓ.ም በዘጠና ስድስት ዓመታቸው ማረፋቸው ተገልጿል። ምንጭ፦ ተዋሕዶ ሚድያ።
❤ የብፁዕነታቸው በረከት ይድርብን!!!
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ "ሰላም ለ፳ወ፬ቱ ካህናት ሰማያውያን እለ ዐውደ መንበሩ ለአብ። ወሰላም ለማዕጠንት ዘውስተ እደዊሆሙ ወሰላም ለአክሊላት ዘዲበ አርዕስቲሆሙ፤ ወሰላም ለአስማቲሆሙ፤ አካኤል፣ ፋኑኤል፣ ጋኑኤል፣ ታድኤል፣ እፍድኤል፣ ዘራኤል፣ ኤልኤል፣ ተዳኤል፣ ዮካኤል፣ ገርድኤል፣ ልፍድኤል፣ መርዋኤል፣ ኑራኤል፣ ክስልቱኤል፣ ኡራኤል፣ ባቱኤል፣ ሩአኤል፣ ሰላትኤል፣ ጣውርኤል፣ እምኑኤል፣ ፔላልኤል፣ ታልዲኤል፣ ፐስልዱኤል፣ አሌቲኤል"። ትርጉም፦ በአብ መንበር ዙሪያ ላሉ ለሃያ አራቱ ሰማያውያን ካህናት ሰላምታ ይገባል፤ በእጆቻቸው ውስጥ ላለ ማዕጠንትም ሰላምታ ይገባል፤ በራሶቻቸው ላይ ላሉ አክሊላትም ሰላምታ ይገባል፤ አካኤል፣ ፋኑኤል፣ ጋኑኤል፣ ታድኤል፣ እፍድኤል፣ ዘራኤል፣ ኤልኤል፣ ተዳኤል፣ ዮካኤል፣ ገርድኤል፣ ልፍድኤል፣ መርዋኤል፣ ኑራኤል፣ ክስልቱኤል፣ ኡራኤል፣ ባቱኤል፣ ሩአኤል፣ ሰላትኤል፣ ጣውርኤል፣ እምኑኤል፣ ፔላልኤል፣ ታልዲኤል፣ ፐስልዱኤል፣ አሌቲኤል ለተባሉ ስሞቻቸውም ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ እግዚአብሔር ድንቆች ተአምራትን የማድረግ ሀብት ሰጠው ሰይጣን እስከ ቀናበት ድረስ ወደ አገረ ገዢውም ሆዶ ይህ መነኵሴ ዮሴፍ ብዙ ገንዘብ እንዳለው አስመስሎ ነገር ሰራበት መኰንኑም በሰንሰለት ማሰርያዎች አሰረው በማግስቱም ማሰርያዎቹ ከላዩ ወደ ምድር ወድቀው ተገኙ መኰንኑም አይቶ ደነገጠ ለቅድስናውም ተገዥ ሆነ።
❤ ብዙ ከተጋጋደረ በኋላ እግዚአብሔር ከአገለገለ በኋላ በዚች ዕለት በሰላም አረፈ። በክብርም ቀበሩት ከመቃብሩም ቁጥር የሌላቸው ብዙ ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ዮሴፍ ጸሎት ይማረን በከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 24 ስንክሳር።
+ + +
❤ "ሰላም ለክሙ ካህናተ ሕጉ ወትእዛዙ። ለእግዚአብሔር ቃል ዘጶደሬ ሥጋ ዐራዙ። እምነቅዓ አፉክሙ ሐሤት ዘኢይነጽፍ ውኂዙ። ኪያየ ኅዙነ ወትኩዘ ልብ ናዝዙ። በወክንፍክሙ ብርሃናዊ ዐውድየ ሐውዙ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የኅዳር 24።
+ + +
❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ወአስተዮሙ ከመ ዘእምቀላይ ብዙኅ። ወአውኃዘ ማየ ከመ ዘእምአፍላግ። ወአውጽአ ማየ እምዕብን"። መዝ77፥15-16። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ4፥10-27።
+ + +
❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ባርክዎ ለእግዚአብሔር ኵልክሙ መላእክቲሁ። ጽኑዓን ወኃያላን እለ ትገብሩ ቃሎ። ወእለ ትሰምዑ ቃለ ነገሩ"። መዝ 102፥20። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 5፥17-ፍ.ም፣ ያዕ 5፥17-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 22፥18-21 ወይም 12፥6-12። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 13፥37-43። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ወይም የቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ቅዳሴ ነው። መልካም የሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ፣ የአቡነ ተክለሃይማኖት በዓል፤ የአቡነ ዜና ማርቆስ የልደት በዓል የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤
❤ ኅዳር ፳፬ (24) ቀን።
❤ እንኳን በእግዚአብሔ ዙፋን ዙርያ ለሚቆሙ የቅድስት ሥላሴ ዙፍን ለሚያጥኑ ለሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ (ለሱራፊል) ለበዓላቸው መታሰቢያ፣ ለናግራን አገር ቄስ ለከበረ ለቅዱስ አዝቂር፤ እርሱ ጋር አብረው ሰማዕትነት ለተቀበሉ አርባ ስምንት ሰዎች ለዕረፍታቸው በዓል፣ ለፃን አገር ለሆነ ለአባ ዮሴፍ ለዕረፍታቸው በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን በስንክሳሩ ከሚታሰቡ፦ ከቅዱሳን ጋይዮስ፣ ከቃርዮስ፣ ከጽኑዕ መስተጋድልም ከሆነና መልካም ስም አጠራር ዜና ካለው ከአባ ዲዮስቆሮስም ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ የዕለቱ አንገሪጋሪ ግእዝ ዜማ፦ ሃሌ ሉያ "ሰአሉ ለነ ካህናት ውሉደ ብርሃን ከመ ንጹኃን በጸሎትክሙ ጸልዩ ለነ ካህናት አግብርተ እግዚአብሔር እስመ ለክሙ ይቤለክሙ አማልክት አንትሙ ወደቂቀ ልዑል ኲልክሙ"፡፡ ትርጉም፦ የብርሃን ልጆች ካህናት ለምኑልን የእዚአብሔር ባለሟሎች ካህናት ጸልዩልን በጸሎታችሁ እንድን ዘንድ እናንተ አማልክት ናችሁ ሁላችሁም፣ የልዑልም ልጆች አላችሁ፡፡ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ
+ + +
❤ የዕለቱ እግ ነግ ዓራራይ ዜማ፦ "ለካህናቲከ እግዚኦ ለካህናቲከ እለ አስመሩከ ትቤሎሙ ባኡ ጽርሐ መቅደስከ ኀበ የሐድር ኃይለ ስብሐቲከ"፡፡ ትርጉም፦ ካህናቶችህ አቤቱ ካህናቶችህ ደስ ስላሰኙህ ግቡ አልካቸው ምስጋናህ ካለበት (ከምትመሰገንበት) በማደሪያህ ቤት። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ።
+ + +
❤ ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ (ለሱራፊል)፦ እሊህም ሥጋ የሌላቸው ረቂቃን የእውነት ካህናት የሆኑ ከቅዱሳን ሁሉ በላይ የሆኑና ከሰማይ ሠራዊት ሁሉ ከፍ ከፍ ያሉ ናቸው እነርሱም ለእግዚአብሔር ቀራቢዎች በመሆን ለሰው ወገን የሚማልዱ ከእጃቸው ውስጥ ካለ ማዕጠንት ጋር እንደ ዕጣን የቅዱሳንን ጸሎት የሚያቀርቡ ናቸው ያለእነርሱም አቅራቢነት ጽድቅና ምጽዋት ወደ እግዚአብሔር አይቀርብም።
❤ ወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ እንዲህ ብሎ እንደ ተናገረ። "በዙፋኑ ዙርያ ሃያ አራት መንበሮች አሉ በእነዚያ መንበሮችም ሃያ አራት አለቆች ተቀምጠዋል ነጭ ልብስ ለብሰዋል በራሳቸውም ላይ የወርቅ አክሊል አለ። ሁለተኛም እንዲህ አለ "ሌላም መልአክ መጥቶ በመሠዊያው ፊት ቁሞ የወርቅ ጽንሐሕ ይዟል በመንበሩ ፊት ባለ በወርቁ መሠዊያ ላይሞ የቅዱሳንን ሁሉ ጸሎት ያሳርግ ዘንድ ብዙ ዕጣንን ሰጡት። የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳኑ ጸሎት ጋር በዚያ መልአክ እጅ ወደ እግዚአብሔር ፊት ዐረገ"።
❤ "የነበረ የሚኖር የአማልክት አምላክ እግዚአብሔር ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ነው" እያሉ በመዓልትና በሌሊት ዕረፍት የላቸውም። እሊህም እንስሶቹ ለዘላለሙ ሕያው ለሚሆን በዙፋን ላይ ለተቀመጠ ለሱ እንዲህ እያሉ ክብር ምስጋና አቀረቡ።
❤ እሊህ ሃያ አራቱ አለቆች አክሊላቸውን በዙፋኑ ፊት አውርደው ለዘላለሙ ሕያው ለሚሆን በዙፋን ላይ ለተቀመጠ ለእርሱ ሰገዱለት። አክሊላቸውንም ወደ ዙፋኑ ፊት ወስደው "አቤቱ ፈጣሪያችን ኃይልና ምስጋና ክብር ላንተ ይገባል ይሉታል አንተ ሁሉን ፈጥረሃል የተፈጠረውም ሁሉ በአንተ ፈቃድ ይኖራልና"።
❤ እነርሱ በእግዚአብሔር ዘንድ በባለሟልነት እጅግ የቀረቡ መሆናቸውንና ስለሁላችን የአዳም ልጆች ስለሚለምኑና ስለሚማልዱ ከብሉይና ከሐዲስ የከበሩ መጻሕፍት ምስክር ኑነዋል ስለዚህም የበዓላቸውን መታሰቢያ እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አዘዙ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ በአማላጅነታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ ቄስ ቅዱስ አዝቂር፦ ይህም ንጉሥ አዝቂርን ወደ ወህኒ አስገብተው እንዲዘጉበት ጠባቂዎቹንም ከሰው ወገን ማንም እንዳይገባ ብሎ አዘዘ። ቅዱስ አዝቂርም በጸለየ ጊዜ የወህኒ ቤቱ ደጃፍ ተከፈተና ሃምሳ ሰዎች ወደርሱ ገቡ እርሱም በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቃቸው።
❤ ንጉሥ ሰራብሄልም በሰማ ጊዜ በወህኒ ቤት አውጥተው ወደሌላ አገር እንዲወስዱት አዘዘ በጉዞም ላይ ስሙ ኪርያቅ ከሚባል ሰው ጋር ተገናኘ ቀስሲስ አዝቂርም ኪርያቅን "ኪርያቅ ሆይ ላንተ የምሥራች ይገባል ለሰማዕትነት ይወስድሃልና" አለው። የንጉሥ ሎሌዎችም ሰምተው አሥረው ከእርሱ ጋር ወሰደቱ። ዳግመኛም ሁለት ሰዎች ተገናኙትና "ስለ ክርስቶስ አጥምቀን" አሉት ያን ጊዜም ቅዱስ አዝቂር ጸለየና ከበረሃ ቦታ ውኃ አፍልቆ ከኪርያቅ ጋር አጠመቃቸው።
❤ ከዚህም በኋላ ወደበረሀ ውስጥ በደረሱ ጊዜ ለእርሳቸውም ለእንስሶቻቸውም የሚጠጡት ውኃ አጥተው ወደ እግዚአብሔር እንዲለምንላቸው ቅዱስ አዝቂርን ለመኑት በጸለየም ጊዜ ደመና መጣ በመሐል እጅ በመመታፈን መጠን በገብታ ላይ ዘነበ ሰባት መቶ ያህል ሰዎች ከእንስሶቻቸው ጋር ጠጥተው ረኩ።
❤ ወደ ንጉሡም በአቀረቡት ጊዜ "ወደ አገራችን ያመጣኸው ይህ አዲስ ትምህርት ምንድነው?" አለው ቅዱስ አዝቂርም "ነቢያት በኦሪት ከሰበኩት በቀር ሌላ አዲስ ትምህርት አላመጣሁም" አለ ንጉሡም ይህን ሰምቶ በክርስቲያን ሃይማኖት ላይ ተዘባበተ። ከአይሁድ መምህራንም አንዱ ተነሥቶ እንዲህ አለ "ጌታዬ ሆይ ወደ አገሩ እንዲወስዱትና በዕንጨት ላይ ሰቅለው በሕይወት ሳለ በእሳት እንዲአቃጥሉት እዘዝ" አለው ንጉሡም እንደ አይሁዳዊው ቃል አዘዘ።
❤ ወደ ናግራን አገርም በአደረሱት ጊዜ በዕንጨት ላይ ሰቅለው ከበታቹ እሳትን አነደዱ ቅዱስ አዝቂርም ወደጌታችን ጸለየ በዚያንም ጊዜ ከማሠሪያው ተፈትቶ ከእሳት ውስጥ በደኅና ወጣ አይሁድም በደንጊያ እንውገረው ተባብለው በወገሩት ጊዜ ደንጊያዎች ተመልሰው ከአይሁድ የሚበዙትን ገደሉ። ከተረፉትም ሰይፍን አንሥተው የቅዱስ አዝቂርን ራስ ቆረጡ ምስክርነቱንም ፈጽሞ የሰማዕትነት አክሊል ተቀዳጀ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ በቅዱስ አባት አዝቂር ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ አባ ዮሴፍ፦ ለዚህም ቅዱስ ወላጆቹ በሃይማኖት የበለጸጉ ናቸው ነገር ግን ያለርሱ ልጅ አልነበራቸውም የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት መጽሐፍት ማንበብን እያስተማሩ መልካም አስተዳደግን አሳደጉት መልኩም እንደ ያዕቆብ ልጅ ዮሴፍ ያማረ ነበር በአደገም ጊዜ ሞትን የዚህ ዓለም ኀላፊት ማሰብ በልቡ አሰበ ወደ አንድ ገዳም ሆዶ መነኰሰ በጾም በጸሎት በመስገድ ተጋድሎ የተተከለ ሆኖ ጸና በአቱንም ዘግቶ በዕለ እሁድ ከቊርባን ጊዜ በቀ አይወጣም ነበር።
❤ ዜናውም በተሰማ ጊዜ ከእርሱ በረከቱን ይቀበሉ ዘንድ በአገር ዙርያ ያሉ ሰዎች የሚመጡ ሆኑ አባትና እናቱም የልጃቸውን ወሬ በሰሙ ጊዜ እርሱን ያገናኛቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እየለመኑ ነበር ወሬው በሰሙ ጊዜ ስልጃቸው መገኘት እንዲጸልይላቸው ወደ እርሱ ሄዱ እርሱ ልጃቸው እንደሆነ አላወቁምና ሰው ገላል ባለ ጊዜ ልጃቸው መሆኑን እራሱ ገለጸላቸውና ለማንም እንዳይናገሩ አዘዛቸው።
