ሰዋስው ☘☘☘☘
رفتن به کانال در Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
نمایش بیشتر1 161
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
1 161
26/3/2015 ዓ.ም (፳፮/፫/፳፻፲፭ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
እስመ ተዘከረነ ዘይትኀሠሥ ደሞሙ።
ወኢረሥዐ ዐውያቶሙ ለነድያን።
ተሣሃለኒ እግዚኦ ወርኢ ዘከመ የሐሙኒ ጸላዕትየ፡፡ መዝ 9፥12
🕯 ትርጉም
ደማቸውን የሚመራመር እርሱ ዐስቧልና። የድሃዎችንም ጩኸት አልረሳምና።
አቤቱ ዕዘንልኝ ጠላቶቼም የሚያመጡብኝን መከራ እይ።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ማር. 13:11-14፡ "ወሶቤሃ ያበጽሑኩሙ ኢትቅድሙ" - "ሲጐትቱአችሁና አሳልፈው ሲሰጡአችሁም ምን እንድትናገሩ አስቀድማችሁ አትጨነቁ፥ ዳሩ ግን በዚያች ሰዓት የሚሰጣችሁን ተናገሩ፤ የሚነግረው መንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ እናንተ አይደላችሁምና። ወንድምም ወንድሙን አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፥ ልጆችም በወላጆቻቸው ላይ ይነሣሉ። ይገድሉአቸውማል፤ ነገር ግን በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋት ርኵሰት በማይገባው ስፍራ ቆሞ ብታዩ፥ አንባቢው ያስተውል፥ በዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራሮች ይሽሹ።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
1 161
26/3/2015 ዓ.ም (፳፮/፫/፳፻፲፭ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
አድኅነኒ እግዚኦ እምፀርዕየ።
ወአንግፈኒ እምእለ ቆሙ ላዕሌየ።
ወባልሐኒ እምገበርተ አመፃ፡፡ መዝ. 58፥1
🕯 ትርጉም
አምላኬ ሆይ ከጠላቶቼ አድነኝ፤
በላዬም ከቆሙት አስጥለኝ።
ከግፍ፡አድራጊዎች ታደገኝ።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯1 161
እንኳን ለሰማዕቱ ቅዱስ መርቆርዮስ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
የቀጣዮቹን በዓላት
1.የታህሳስ 12 የጻዲቁ አባታችን አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ በዓል ስርአተ ዋዜማና ማህሌት
2 የታህሳስ 13 በዓለ ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት ስርአተ ማህሌት
3.የታህሳስ 19 በዓለ ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት ስርአተ ዋዜማ ናማህሌት
4. የታህሳስ 24 በዓለ ተክለኃይማኖት ጻድቅ ስርአተ ዋዜማ ናማህሌት
5.የታህሳስ 28 በዓለ አማኑኤል
6.የታህሳስ 29 በዓለ ልደት ስርአተ ዋዜማ ናማህሌት
7.የየሳምንት መዝሙሮች
ቀደም ብሎ ወደናንተ ይላካል! ይጠብቁን @EOTCW
@EOTCW
https://t.me/Eotcw
# Join & share #
1 161
❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ "ሰላም ለአባ ሰላማ ውስተ ምድርነ ዘተፈነወ ለብሔረ አግአዚ ጽድቀ ዘዜነወ ትእዛዛተ ሕይወት ዘመጠወ።" ትርጉም፦ የሕይወት ትዕዛዛትን የሰጠ ነጻ አውጪ ለኾነች አገር ኢትዮጵያ ጽድቅን ያስተማረ፤ ወደ ምድራችን (ወደ አገራችን) የተላከ ለኾነ ለአባ ሰላማ ሰላምታ ይገባል። አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ "ሰላም ለዘበናግራን ሰማዕታት ሰላም ለአቡሆሙ ኂሩት። ሰላም ለቀሳውስት ወለዲያቆናት ወለመነኰሳት ወለመበለታት። ሰላም ለአእሩግ ወለሕፃናት ሰላም ለእድ ወለአንስት። ሰላም ለኵሎሙ እለ በናግራን ሰማዕታት እለ ቦኡ ሀገረ እንተ ትመስል ኢየሩሳሬም እንተ በሰማያት፤ ወደቂቃ ይመስሉ ከዋክብተ ብሩሃነ፤ አድባሪሃ ቅዱሳን ወከዋክብቲሃ ይጸንሑ እስከ አርያም፤ ለቀበላሁ ለወልደ ማርያም"። ትርጉም፦ በናግራን ሰማዕታት ለኾኑ፤ ለአባታቸውም ኂሩት ሰላምታ ይገባል። ለቀሳውስትና ለዲያቆናት ለመነኰሳትና ለድኾች ሴቶች ሰላምታ ይገባል፤ ለሽማግሎችና ለሕፃናት ሰላምታ ይገባል፤ ለወንዶችና ለሴቶች ሰላምታ ይገባል። በሰማያት ያለች ኢየሩሳሌምን ወደ ምትመስል አገር የገቡ በናግራን ላሉ ሰማዕታት ኹሉ ሰላምታ ይገባል፤ ልጆቿም ብሩሃን ከዋክብትን ይመስላሉ፤ ተራሮቿም የተቀደሱ ናቸው፤ ከዋክብቷም የማርያምን ልጅ ክርስቶስን ለመቀበል እስከ ሰማይ ድረስ ደጅ ይጠናሉ። አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።
+ + +
❤ "ሰላም እብል ስነክሙ መአድመ። ከዋክብተ ናግራን ሰማዕት ዘአብራህክሙ ዓለመ። ዓራቄ ኩኑነ ወመስተሳልመ። በቅድመ አምላክ ፈታሒ አመ ኃጢአትነ ቆመ። በእንተ ስሙ ዘከአውክሙ አርእይዎ ደመ። ትርጉም፦ ዓለምን ያበራችኍ የናግራን ከዋክብት ሰማዕት ሆይ ላማረ ደም ግባታችኍ ሰላም እላለኊ፤ ኃጢአታችን በፈራጅ አምላክ ፊት በቆመ ጊዜ አስታራቂና አስማሚ ኹኑን! በስሙ ያፈሰሳችኹትን ደም አሳዩት!። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የኅዳር 26።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ የክርስቲያን ወገኖችም ይህን አይተው እኩሌቶቹ ወደ እሳት እኩሌቶቹም ወደ ሰይፍ ተቀዳደሙ የአይሁድ ጉባኤ ዕጹብ ዕጹብ ብለው እስኪያደንቁ ድረስ ከዚህም በኋላ እሳቱ በሰማይ ውስጥ መልቶ አርባ ቀን አርባ ሌሊት ታየ። የአይሁድ ንጉሥ ፊንሐስም ወደአገሩ በሔደ ጊዜ ወደ ነገሥታቱ ሁሉ በኃይሉ እየተመካ ላከባቸው የሮሜ ንጉሥ ዮስጢኖስም ሰምቶ ወደ እስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አባ ጢሞቴዎስ ላከ በአገረ ናግራን ለሚኖሩ የክርስቲያን ወገኖች ደማቸውን ይበቀል ዘንድ ለኢትዮጵያ ንጉሥ ለካሌብ መልእክት እንዲልክ ነው።
❤ የኢትዮጵያ ንጉሥ ካሌብም መልእክት በደረሰው ጊዜ ፈጥኖ ተነሣ በዋሻ ከሚኖር ከአባ ጰንጠሌዎን በረከትን ተቀብሎ ከብዙ ሠራዊት ጋር በመርከቦች ተጭኖ ሔደ በደረሰም ጊዜ የሳባን ንጉሥ የፊንሐስን አገር አጠፋ ሰውም ሆነ እንስሳም ሆነ ሸሽቶ የሚያመልጥ እንኳ ምንም ምን ሳይቀር አጠፋቸው የናግራንን ከተማ ሕንፃዋን አደሰ የሰማዕታትንም መታሰቢያ አቆመ። ከዚህም በኋላ ወደ ሮሜ ንጉሥ ዮስጢኖስ ወደ እስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጢሞቴዎስ የምሥራች ላከ እነርሱም ሰምተው እጅግ ደስ አላቸው እግዚአብሔርንም አመሰገኑት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ በናግራን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 26 ስንክሳር።
+ + +
❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "አድኅነኒ እግዚኦ እምፀርየ። ወአንግፈኒ እምእለ ቆሙ ላዕሌየ። ወባልሐኒ እምገበርተ ዐመፃ"። መዝ 58፥1-2። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 21፥12-21
+ + +
❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "እስመ ተዘከረ ዘይትኃሠሥ ደሞሙ። ወኢረስዐ አውያቶሙ ለነዳያን። ተሣሃለኒ እግዚኦ ወርኢ ዘከመ የሐመኒ ጸላእትየ"። መዝ 9፥12-13 ወይም መዝ 115፥15-16። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 6፥1-12 ፣ 1ኛ ጴጥ 5፥7-9 እና የሐዋ ሥራ 20፥28-31። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 21፥12-21። የሚቀደሰው የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ነው። መልካም የአቡነ ሀብተ ማርያም፣ የአቡነ ኢየሱስ ሞዐ የዕረፍት በዓል፤ የአቡነ ሰላማ የልደት በዓል፣ የናግራ ሰማዕታት መታሰቢያ በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ኅዳር ፳፮ (26) ቀን።
❤ እንኳን ለአገረ ናግራን ሰማዕታትና ለአባታቸው ለቅዱስ ኂሩት ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው መታሰቢያቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቅዱስ ቢላርያኖስ ከሚስቱ ኪልቅያና ከእኅቱ ታቱስብያ በሰማዕትነት ከዐረፉ፣ ከደሴተ ሰንሲላ ኤጲስቆጶስ ከአባ ጎርጎርዮስ፣ ከጌልዮስ፣ ከምክዋስና ከማርልዮስ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ የዕለቱ እስመ ለዓለም ምሕረቱ፦ "ኦ ዓባይ ሀገር ሀገረ ናግራን ከዋክብትኪ ብሩሃን ወዕፀውኪ ፍሱሐን ወካህናትኪኒ ነባብያን ወዲያቆናትኪኒ ላእካን ወሕዝብኪኒ መሐይምናን እለ ተጠምቁ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን"። ትርጉም፦ ከፍ ያለች የናግራን ከተማ ሆይ ከዋክብቶችሽ ብሩሃን ናቸው ካህናቶችሽ የተማሩ ናቸው ዲያቆናቶሽም ተላላኪዎች ናቸው ሕዝቦችሽም አምነው በቅድስት ቤተ ክርስቲያን የተጠመቁ ናቸው። ሊቅ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ።
+ + +
❤ የአገረ ናግራን ሰማዕታት አባታቸውም ቅዱስ ኂሩት፦ ይህም ዮስጢኖስ ለቊስጥንጥንያ በነገሠ በአምስተኛው ዓመት ለኢየሩሳሌም አባ ዮሐንስ ለእስክንድርያ አባ ጢሞቴዎስ ለቊስንጥንጥንያም አባ ጢሞቴዎስ ለአንጾኪያ አባ አውፍራስዮስ ሊቃነ ጳጳሳት ሁነው ሳለ በኢትዮጵያም ጻድቁ ካሌብ ነግሦ ሳለ በዚያን ወራት ለአይሁድ ስሙ ፊንሐስ የሚባል አይሁዳዊ ነገሠ።
❤ በመጀመርያ ግን ሳባ የተባለች አገር በኢትዮጵያ ነገሥታት እጅ ውስጥ ነበረች የሮም ነገሥታት አስባስያኖስና ጥጦስ ከኢየሩሳሌም አይሁድን በአሳደዷቸው ጊዜ ይቺን ሳባን አይሁድ ወረሷት። በውስጧም በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምኑ ብዙዎች ክርስቲያኖች በሚኖሩባት ታላቅ ከተማ አለች ይህም የተረገመ አይሁዳዊ ፊንሐስ ሊአጠፋት በመጣ ጊዜ የዚችን የከበረች አገር በመስቀል ምልክት በዙሪያዋ ያለ ቅጽርዋን በበሮቿና በግንብ አጥርዋ ላይ ያሉ ብዙ አርበኞች ሠራዊትን አይቶ በምንም ምክንያት ሊገባባት ስለአልተቻለው ተቆጣ። እግዚአብሔር አጽንቷታልና ነገር ግን በውጭ ያገኛቸውን ገበሬዎች ገደለ ታናናሾችንም ማርኮ ለባሮቹ ሰጣቸው።
❤ ይህም ዲያብሎስን የሚመስለው አይሁዳዊ የኦሪትና የነቢያት ፈጣሪ በሆነ በእግዚአብሔር ስም እየማለ በተንኰል መልእክትን ላከ እንዲህም አላቸው "እኔ ከእናንተ ጋር ጠብ አልሻም ከአገር ሰው አንዱን እንኳ ማጥፋት አልፈልግም ነገር ግን የከተማዋን አሠራርዋን አደባባዮቿን ገበያዎቿን ማየት እሻለሁ" ለአገር ሰዎችም የተናገረው እውነት መስላቸው። የካዕቢ ልጅ አባት ኂሩት "ይህን አይሁዳዊ አትመኑት ሐሰተኛ ነውና ደጁንም አትክፈቱለት" አላቸው አባት ኂሩትንም አልሰሙትም ደጁንም ከፈቱለትና ሰዎች ገንዘባቸውን እንዲዘርፋአቸው አዘዘ። ሁለተኛም ነባልባሉ ወደ አየር እስቲደርስ እሳትን አንድደው የአገሪቱን ኤጲስቆጶስ አባ ጳውሎስን እንዲአመጡት አዘዘ እርሱ እንደ ሞተም በነገሩት ጊዜ ዐፅሙን ከመቃብር አውጥቶ አቃጠለው።
❤ ከዚህም በኋላ ቀሳውስትን ዲያቆናትን መነኰሳትን፣ አንባቢዎችንና መዘምራኑን በቀንና በሌሊት መጻሕፍትን በማንበብ የሚተጉትን ሰበሰበ እነርሱንም ከእሳት ውስጥ ጨመራቸው ቊጥራቸው አራት ሺህ ሃያ ሰባት ነፍስ ሆነ ክርስቲያኖችን በዚህ ሊአስፈራራቸው አስቧልና። ዳግመኛም የብረት ዛንጅር በቅዱስ አባት ኂሩት አንገት ውስጥ እንዲአስገቡ እጆቹንና እግሮቹንም እንዲአሥሩት አዘዘ ታላላቆችንና የአገሩን መኳንንትንም እንዲአሥሩአቸው ክርስቶስን የማይክደው ሁሉ እንዲህ ተሠቃይቶ በክፋ አሟሟት ይሞታል የሚል ዐዋጅ ነጋሪ እየጮኸ በከተማው ውስጥ እንዲአዞቸው አዘዘ።
❤ ቅዱሳን ክርስቲያን ወገኖች በሰሙ ጊዜ እንዲህ እያሉ ጮኹ "እኛ ያመንበትንና በስሙ የተጠመቅንበትን ክብር ይግባውና ክርስቶስን አንክደውም ይህ ርጉም አይሁዳዊም ሰምቶ ወንዶችና ሴቶችን ወጣቶችንና ሕፃናትን ሽማግሎችን ሁሉንም እንዲገድሉ አዘዘና ገደሉአቸው ቊራቸውም አራት ሺህ ሁለት መቶ ኃምሳ ሁለት ነፍስ ሆነ።
❤ ከዚህም በኋላ የቅዱስ ኂሩትን ሚስት ቅድስት ድማህን ከሁለት ሴቶች ልጆቿ ጋር ያዟት እነርሱም በቤታቸው መስኮት ከሚገባው በቀር ፀሐይ ያልነካቸው ናቸው ደርሰውም በአይሁዳዊ ንጉሥ ፊት በቆሙ ጊዜ እርሱም ሃይማኖታቸውን ያስክዳቸው ዘንድ በብዙ ተንኮል ሊሸነግራቸው ጀመረ እምቢ ባሉትም ጊዜ የራሳቸውን መሸፈኛ እንዲገልጧቸው አዘዘ የአገር ሴቶችም እስከ ሚያለቅሱ ድረስ ከልጆቿም የምታንስ አንዲቱ ዕድሜዋ ዐሥራ ሁለት ዓመት የሆነ ከንጉሡ ፊት ላይ ምራቋን ተፋችበት። ወታደሩም አይቶ ሰይፋን መዝዞ አንገቷን ቆረጠ የእኅቷንም አንገት ቆረጠ። ድማህ የልጆቿን ደም እንዲአጠጧት አዘዘ እርሷም ቀምሳ "የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አመሰግንሃለሁ እንደቊርባን መሥዋዕት የሆነውን የልጆቼን ደም እኔ ባሪያህ እንድቀምስ አድርገሃልና" አለች። በዚያንም ጊዜ ርሷንም በሰይፍ አንገቷን እንዲቆርጡ ዳግመኛ አዘዘ ተጋድሎአቸውንም ፈጸሙ።
❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ኂሩትን ከአሥር ቤት እንዲአመጡት ንጉሥ አዘዘ ከርሱም ጋር አንድ ሺህ አርባ እሥረኞች ሰዎች አሉ ሃይማኖቱንም ይተው ዘንድ አስገደደው። ቅዱስ ኂሩትም ንጉሡን እንዲህ አለው "ክብር ይግባውና ጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን እያመለክሁት ስኖር ሰባ ስምንት ዓመት ሆነኝ እስከ አራት ትውልድ ለማየትም ደርሼአለሁ ዛሬም ስለ ከበረ ስሙ ምስክር ሁኜ ስሞት እጅግ ደስ ይለኛል። እኔኮ አስቀድሜ መሐላህን እንዳያምኑ ለወገኖቼ ነግሬአቸው ነበር አንተ ሐሰተኛ ነህና ነገር ግን ይህ ሁሉ በእግዚአብሔር ፈቃድ ነው የሆነው ለዚህም ተጋድሎ ላደረሰኝ ለእርሱ ምስጋና ይሁን" ንጉሡም ይህን ሰምቶ ተቆጣ ወደ ወንዝም ወስደው በዚያ አንገቱን እንዲቆርጡት አዘዘ።
❤ ቅዱስ አባት ኂሩትም በሰማ ጊዜ ደሰሰ አለው የሮምንና የኢትዮጵያን መንግሥት ያጸና ዘንድ የተረገመ አይሁዳዊውን መንግሥት ያጠፋ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ ሕዝቡንም ባረካቸው። ከእርሳቸው ጋር በሰላምታ ተሰናበታቸው ከዚህም በኋላ የቅዱሳኑን ራሶቻቸውን ቆረጧቸው በዚያም የአምስት ዓመት ልጅ ያላት አንዲት ክርስቲያን ሴት ነበረች ከቅዱሳን ደም ወስዳ ተቀባች ልጅዋንም ቀባችው ወታደሮችም አይተው ከእሳት ጨመርዋት ልጅዋን ግን አይሁድ ወደእነርሱ ወስደው ወደ ንጉሥን አቀረቡት ንጉሡም "እኔን ትወዳለህ? ወይስ ክርስቶስ የሚሉትን?" አለው ሕፃኑም "እኔስ የእጁ ሥራ ነኝና ክርስቶስን እወደዋለሁ ይልቅስ ልቀቀኝ ወደ እናቴ ልሒድ" አለው በከለከለውም ጊዜ እግሩን ነከሰው አምልጦም ሩጦ ከእሳቱ ውስጥ ገባ። ሁለተኛም የዐሥር ወር ሕፃን እንደተሸከመች አንዲትን ሴት አመጧት እርሷም "ልጄ ሆይ ላዝንልህ አልቻልኩም" አለችው ያ ሕፃንም "እናቴ ሆይ በፍጥነት ወደ ዘላለም ሕይወት እንሒድ ይቺን እሳት ከዛሬ በቀር አናያትምና" አላት በዚያንም ጊዜ ከልጅዋ ጋር ወደ እሳት ውስጥ ተወረወረች።
1 161
ሞዐ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ ፍሬምናጦስም ወደ እስክንድሪያ ለመሄድ አስቦ ሳለ እንደተኛ እመቤታችን ድንግል ማርያም ተገልጣለት "ዲቁናና ቅስናን መቀበል ይገባሃል፣ ለጵጵስና ተዘጋጅ፣ እግዚአብሔር ይህችን ከፍ ያለችውን ማዕረግ ሰጥተሃልና የልጄ ወዳጅ ሆይ በጸሎትህና በልመናህ በስብከትህም የኢትዮጵያ ሰዎች ሁሉ ይድናሉ፣ በእጅህ ጥምቀትንና ሥጋ ወደሙን ይቀበላሉ" አለችው፡፡ ጌታችንም እንዲሁ ተገልጦለት "ወደ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አትናቴዎስ ሄደህ ከፍ ያችውን ማዕረግ ተቀብለህ የኢትዮጵያን ሰዎች አጥምቅልኝ፣ ነቢዩ ዳዊት ስለ እነርሱ "ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች" ብሎ ተናግሯልና" አለው፡፡ ከዚህም በኋላ አቡነ ሰላማ ቅዱሳኑን ነገሥታት አብርሃንና አጽብሓን አግኝቶ ከእነርሱም ጋር ተማክሮ ወደ እስክንድሪያ ሄዶ በቅዱስ አትናቴዎስ እጅ በአገራችን ላይ የመጀመሪያው ሊቀ ጳጳስ ሆኖ ታኅሳስ 18 ቀን ተሾመ፡፡ ስሙንም ሰላማ ከሣቴ ብርሃን አለው፡፡ ሰላማ ማለት እግዚአብሔርንና ሰውን የሚያስታርቅ ማለት ነው፡፡ ከሣቴ ብርሃን ማለትም ሃይማኖትን ገልጦ የሚያስተምር ማለት ነው፡፡ ቅዱስ አትናቴዎስም ከሾመው በኋላ ታቦትና በጣም ብዙ ንዋያተ ቅድሳትንና መገልገያ ዕቃዎችን ሰጥቶ መርቆ በሰላም ወደ ኢትዮጵያ ላከው...፡፡ አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ፦ አገራቸው ጎንደር ክፍለ ሀገር ስማዳ ወረዳ ሲና ዳኅና በሚባል ቦታ ነሐሴ 26 ቀን ተፀንሰው ግንቦት 26 ቀን 1210 ዓ.ም ከአባታቸው ከቅዱስ ዘክርስቶስና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ክብራ ተወለዱ፡፡ የተወለዱትም በቅዱስ ነአኲቶ ለአብ ዘመነ መንግሥት ነው፡፡
❤ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት የቆብ አባት ሲሆኑ ታላቁን ሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስን ገዳም የቆረቆሩ ደገኛ አባት ናቸው፡፡ ዕድሜያቸው 30 ዓመት እስከሚደርስ ድረስ ከቤተሰቦቻቸው ትምህርተ ሃይማኖትንና ግብረ ገብን ሲማሩ ከቆዩ በኋላ በ1240 ዓ.ም ይህንን ዓለም በመተው ወደ ደብረ ዳሞ ገዳም ገቡ፡፡ በደብረ ዳሞ ገዳም መነኰሳቱን እየረዱ፣ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እያጠኑ፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን እየገለበጡ ለሰባት ዓመታት ከቆዩ በኋላ የደብረ ዳሞ 3ኛ አበ ምኔት ከሆኑት ከአባ ዮሐኒ እጅ ምንኩስናን በ1247 ዓ.ም ተቀበሉ፡፡
❤ አንድ ቀን ሌሊት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ወደርሳቸው መጥቶ "የስምህ መክበርያ ወደሆነው ሐይቅ ወደ ተባለው ሥፍራ ሂድ" አላቸው፡፡ አባታችንም "ቦታውን እንዴት ዐውቀዋለሁ?" በማለት መልአኩን ቢጠይቁት "ተነሥ! ጉዞህን ጀምር ቦታውን እኔ አሳይሃለሁ" አላቸው፡፡ አባ ኢየሱስ ሞዐ በመልአኩ እንደታዘዙት ከበዓታቸው ተነሥተው ተከተሉት፡፡ የብዙ ወራት መንገድ የሆነውን ጐዳናም በስድስት ሰዓት አደረሳቸው፡፡ በዚያን ወቅት ከሐይቅ ገዳም በስተ ሰሜን ወደነበረው የቅዱሳን ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ደረሱ፡፡ ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ከመግባታቸው በፊት ለ6 ወራት ያህል በቅዱሳን በጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን አገልግለዋል፡፡ ያገለግሉበት በነበረው ቤተ ክርስቲያን ቀን ቀን ሕዝቡን ሲያስተምሩ በመዋል ሲመሽ ወደ ሐይቁ በመግባት ሲጸልዩ ያድሩ ነበር፡፡ በሐይቅ እስጢፋኖስና በዙርያው ለነበሩ አበው ማታ ማታ አንድ ብርሃን ወደ ሐይቁ ሲገባ ጠዋት ጠዋትም ሲወጣ ይታያቸው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን በገዳሙ አባቶች ልመናና በልዑል እግዚአብሔር ትዕዛዝ ወደ ሐይቅ ገዳም ገብተው አበምኔት ሆኑ፡፡
❤ ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ከደሴ 30 ኪሎ ሜትር ርቆ የሚገኝ ሲሆን የመሠረቱት ካልዕ ሰላማ የተባሉ ግብፃዊ ጻድቅ ናቸው፡፡ ሐይቅን አባ ሰላማ ካልዕና ዐፄ ድል ነአድ በ862 ዓ.ም ነው የቆረቆሩት። ገዳሙን ካቀኑት በኋላ "የማንን ታቦት እናስገባ?" ብለው ሲያስቡ ቶራ የምትባል እንስሳ ጭነት ተጭና ከመካከላቸው ተገኘች፤ ጭነቱን አውርደው ቢያዩት በሐር ጨርቅ የተጠቀለለ የቅዱስ እስጢፋኖስንና የቅዱስ ጊዮርጊስን ሁለት ታቦት አገኙ፡፡ በላዩም ላይ "ይህንን ታቦት በኢየሩሳሌም የሚኖሩ የተሰወሩ ቅዱሳን ከእግዚአብሔር ታዘው የላኩት ነው" የሚል ጽሑፍ አገኙ፡፡ ይህ ከሆነ ከ400 ዘመን በኋላ ነው አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ወደዚህ ቦታ የመጡት፡፡ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ለ52 ዓመት ቀን ቀን መንፈሳዊ ሥራቸውን እየሠሩ ሌሊት ሌሊት ሐይቁ ውስጥ ቆመው ሲጸልዩ ያድራሉ፡፡
❤ አባ ኢየሱስ ሞዐ በሐይቅ እስጢፋኖስ በአበ ምኔትነት በቆዩባቸው 45 ዓመታት ከየገዳማቱ ቅዱሳን መጻሕፍትን በመገልበጥና በማሰባሰብ የመጀመርያው ዘመናዊ የቤተ ክርስቲያን ቤተ መጻሕፍት በሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም እንዲቋቋም አድርገዋል፡፡ በዚሁ ገዳም ውስጥ የመጀመርያውን የቤተ ክርስቲያን ቋሚ ትምህርት ቤት በማቋቋም 800 መነኮሳትን በትምህርተ ሃይማኖት አሠልጥነው በንቡረ ዕድነት ማዕረግ ሾመው በመላ ሀገራችን እንዲሠማሩ አድርገዋቸዋል፡፡ ከእነዚህም ተማሪዎቻቸው መካከል አቡነ ተክለ ሃይማኖት (ደብረ ሊባኖስ)፣ አቡነ ኂሩተ አምላክ (ጣና ሐይቅ ዳጋ እስጢፋኖስ)፣ አቡነ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ (ቦረና)፣ አባ በጸሎተ ሚካኤል (ቦረና)፣ አቡነ ገብረ እንድርያስ (ቦረና)፣ አቡነ ሕዝቅያስ (ቦረና)፣ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ (ዳውንት)፣ አቡነ አሮን (መቄት)፣ አቡነ ተክለ ኢየሱስ ሞዐ (ሐይቅ)፣ አቡነ አላኒቆስ (ትግራይ)፣ አቡነ በግዑ (ሐይቅ)፣ አቡነ ሠረቀ ብርሃን (ሐይቅ)፣ አቡነ ብስጣውሮስ (ሐይቅ)፣ አቡነ ዮሴፍ (ላስታ) ዋና ዋናዎቹና በጣም ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ ጻደቁን ንጉሥ ዐፄ ይኩኖ አምላክንም በትምህርተ ሃይማኖት አንጸውና ኮትኩተው ያሳደጉት ጻድቁ አባታችን ናቸው፡፡
❤ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ መጥተው በሐይቁ ዳር ቆመው ሳለ ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ በእግሩ በውኃው ላይ እየሄደ እያሳያቸው ተከትለውት እንዲሄዱ ነገራቸው። አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ሐይቁን በእግራቸው ጠቅጥቀው ተራምደው ተሻግረው አቡነ ኢየሱስ ሞዐን አገኟቸው፡፡ እርሳቸውም አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ እርሳቸው እየመጡ እንደሆነ በመንፈስ ዐውቀው ነበርና ሲያገኟቸው በጣም ተደስተው ከተቀበሏቸው በኋላ አመነኵሰዋቸዋል፡፡ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ እጅግ በጣም ብዙ መነኰሳትን አፍርተዋል፡፡ የመጀመሪያው መነኩሴ አባ እንጦንስ ነው፡፡ እንጦንስ መቃርስን፣ መቃርስ ጳኵሚስን፣ ጳጉሚስ ቴዎድሮስን፣ አቡነ አረጋዊንና 8ቱን ቅዱሳን አመነኰሱ፡፡ አቡነ አረጋዊም ወደ ኢትዮጵያ በ460 ዓ.ም መጥተው ክርስቶስ ቤዛን፣ አባ ክርስቶስ ቤዛም መስቀለ ሞዐን፣ መስቀለ ሞዐም አባ ዮሐኒን፣ አባ ዮሐኒም አባ ኢየሱስ ሞዐን፣ አባ ኢየሱም ሞዐም አቡነ ተክለ ሃይማኖትን አመነኰሱ፡፡ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ምን ያህል ቀደምትና ባለ ታሪክ አባት እንደሆኑ ከዚህ መረዳት ይቻላል፡፡
❤ በዮዲት ጉዲት እጅጉን ተጐድታ የነበረችው አገራችን ዳግም የወንጌሉ ብርሃን እንዲበራባት ሊቃውንት፣ እንዳይታጡባት፣ ቅዱሳት መጻሕፍት እንዳይቆነጻጸሉ፣ መነኰሳት አባቶች ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ወርደው ገዳማትን እንዲያስፋፉ ያደረጉት አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለአገራችን ትልቅ ባለውለታ ናቸው፡፡ በተለይም በሐይቅ እስጢፋኖስ ያፈሯቸውን 800 ሊቃውንት በመላዋ ኢትዮጵያ በመሰማራታቸው ዛሬ የምናያቸውን አብዛኛዎቹን ገዳማትና ቅዱሳት መጻሕፍት አቆይተውልናል፡፡ አባታችን ለ45 ዓመታት ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳምን በአበ ምኔትነት እያስተዳደሩ ከቆዩ በኋላ ኅዳር 26 ቀን 1292 ዓ.ም በዕለተ እሑድ ዐርፈዋል፡፡ ከአባታችከኢየሱስ
1 161
❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ኅዳር ፳፮ (26) ቀን።
❤ እንኳን ለኢትዮጵያውያኑ ጻድቃን ታላቁን ገዳም ሐይቅ እስጢፍኖስ ለመሰረቱት ለአቡነ ኢየሱስ ሞዐና ለታላቁ አባት ለአቡነ ሀብተ ማርያም ለዕረፍታቸው በዓል፣ ለኢትዮጵያ የመጀመርያው ሊቀ ጳጳስ ለነበሩት ለአቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ለልደት በዓል በሰላም አደረሰን።
+ + +
❤ ስለ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም ዕረፍት፦ ... ከዚህም በኋላ ዕለተ ሞቱ በደረሰ ጊዜ ለሞቱ ምክንያት የሚሆን ቸነፈር ያዘው፤ መድኃኔዓለም አምላካችን በዐቢይ ምስጋና ወደ እርሱ መጥቶ "ሰላም ለአንተ ይሁን ወዳጄ ሀብተ ማርያም ሆይ ዛሬ ግን ወደ አንተ የመጣሁት ከድካም ወደ ዕረፍት እወስድህ ዘንድ ነው ሰባት የጽድቅ የክብር አክሊሎችን አዘጋጅቼለሃለሁ አንደኛው ስለ ንጹሕ ድንግልናህ፣ ሁለተኛው ዓለምንና በውስጡ ያለውን ንቀህ በመኖርህ፣ ሦስተኛው ስለ ፍጹም ምንኵስናህ፣ አራተኛው ዘወትር አራቱ ወንጌላትን በማንበብህ በመጸለይህ ስለ እኔ ምክንያት፣ አምስተኛው በረኃብህ፣ ስድስተኛው በጾም ስለ ተጋደልክ፣ ሰባተኛው በልብህ ቂምና ጥላቻን ትዕቢትን ትምክህትን ባለማሳደርህና በልብህ ውስጥ ባለማስቀመጥህ፣ ስለ ንጹሕ ተልዕኮ ክነትህ ስለ ምዑዝ ዕጣንህና ስለ ንጹሕ መሥዋዕትህ ነው፤ እኒህ ሰባት አክሊላትም እያንዳንዳቸው ባለ ዐሥራ አምስት ኅብርና ጌጥ ያላቸው ናቸው። አህጉረ ገነትም በውስጧ አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያለው ትገባበት ዘንድ አንተና እንዳንተ ላሉ ወዳጆችህ የሚገቡበት ቤት እሰጥሃለሁ በምሰጥህም ቤት መታሰቢያህን ያደረገ በጸሎቶህ የተማፀነ ይገባል የወርቅ ጫማን፤ የእሳት መስቀልን የብርሃን ልብስን ድብቅ መናን እሰጥሃለሁ" አለው።
❤ መድኃኔዓለምም ይህንን ቃል ኪዳን ሲሰጠው ዘጠና ዘጠኙ ነገደ መላእክት በየሥርዓታቸው መጥተው ቆሙ፣ "ወዳጃችን አባ ሀብተ ማርያም ሆይ ሰላም ለአንተ ይሁን ዛሬስ በዝማሬና በማኅሌት ከፀሐይና ከጨረቃ ከከዋክብትም ሰባት እጅ ወደ ምታበራ ወደ ሰማያዊት ሀገር እንወስድህ ዘንድ ደስ ይበልህ" አሉት፤ ቅዱስ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም "ለእግዚአብሔር በሰማያት ምስጋና ይሁን በምድርም የሰውን ልጅ ለወደደውና ላፈቀረው" ብሎ አመሰገነ። ይህንንም ባለ ጊዜ አምላክ በሦስትነቱ ተገልጾ ታየው፤ "ከዮሐንስ መጥምቅ ጎን ለጎን ቀጥላ ያለችውንና ከፀሐይ እልፍ እጅ የበለጠ የምታበራውን አገር እንድሰጥህ እንሆ በማይሻር ቃሌ ማልኩልህ" አለው፣
❤ "እውነት እውነት እልሃለሁ መታሰቢያህም ያደረገ ስምህንም የጠራ ለቤተ ክርስቲያንህም ዕጣን የሰጠ ወይም ዘቢብ የሰጠ ወይን መብራት የሰጠ ከአንተ ጋር ይኖራል አራቱ ወንጌልንም ታነብ ስለ ነበር ለእያንዳንዷም የወንጌል ቃል ፍሬህን አንድ ሺህ አንድ ሺህ አደረኩልህ ይህ ቃል ኪዳን ለአመኑ ልጆችህና መታሰቢያህን ለሚያደርጉ ሁሉ ማየ ጸሎቱን ለሚጠመቁ ለሚያነቡ ለሚያስነብቡ ይህን ቃለ ኪዳን ሰጥቻለሁ" አለው።
❤ ይህንንም ካለው በኋላ ጌታችን አፋን ሦስት ጊዜ ሳመው፤ ያን ጊዜም ከመድኃኔዓለም ጣዕም ፍቅር የተነሣ ነፍሱ ከሥጋው ተለየች፤ ጌታችንም ተቀብሎ አቀፋት ከእርሱም ጋር ወደ ሰማይ አሳረጋት ያን ጊዜም በቅዱሳን ሠራዊተ መላእክት ዘንድ ታላቅ እልልታና ብዙ ደስታ ሆነ በሰማያዊ መላእክት በምድራዊያን ስውራን ቅዱሳን ዘንድ ታላቅ ደስታ ሆነ በሐሳበ ዕብራውያን በናኢብሮስ ታስሪን ወርህ 22 ቀን በኢትዮጵያ ኅዳር26 ቀን በሰማዕታተ ናግራን በዓል በ6ሺ 9መቶ 99 ዓመተ ኩነኔ በኋላ 1ሺ 499 ዓ.ም በሆነ ዘመን ዕለት የአባታችን የአቡነ ሀብተ ማርያም ነፍሱ ከሥጋው ተለየች፤ ያን ጊዜም ከአባታችን ከአቡነ ሀብተ ማርያም የሕይወት መንፈሳቸው ከወጣች በኋላ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው በዝማሬ በማኅሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት አጽም ጋር በጻድቁ መቃብር ቀበሩት። ከአባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን።
ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ሀብተ ማርያም 18፥18-27።
+ + +
❤ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን፡- ቅዱስ አባታችን አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በኋላ በ245 ዓ.ም በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ኅዳር 26 ቀን ሲወለዱ ታላቅ ብርሃን ከሰማይ ወርዶ ለ7 ቀናት አብርቷል፡፡ ቅዱሳን መላእክትም ወደ ምድር ወርደው ጻደቁ በመወለዳቸው ታላቅ ደስታን አድርገዋል፡፡ አባታችን በተወለዱ ጊዜ "ለአብ ስግለት ለወልድ ስግደት ለመንፈስ ቅዱስ ስግደት ይገባል፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጡኝ ቅድመ ዓለም ለነበሩ ዛሬም ላሉ ዓለምን አሳልፈው ለሚኖሩ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል" ብለው ዳግመኛም "አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ" ብለው ፈጣሪያቸውን በአንድነት በሦስትነት አመስግነዋል፡፡ ቅዱስ አባታችን በሌላኛው ስማቸው ፍሬምናጦስ እየተባሉ ይጠራሉ፡፡ በ40 ቀናቸው ጌታ በተጠመቀበት በዮርዳኖስ ያጠመቋቸውና ስመ ክርስትና የሰጧቸው ሊቀ ጳጳስ "ይህ ሕፃን ለኢትዮጵያውን ሁሉ ብርሃን ይሆንላቸዋል" በማለት ትንቢት ተናግረዋል፡፡
❤ አቡነ ሰላማ በሊቀ ጳጳሱ በቅዱስ አትናቴዎስ በሚገባ ተምረው ካደጉ በኋላ በ257 ዓ.ም ከኢየሩሳሌም ወደ ኢትዮጵያ ስሙ ሜርጵዮስ ከሚባል ከአንድ ነጋዴ ጋር መጡ፡፡ ከእነሱም ጋር አድስዮስ የሚባል ልጅ ነበር፡፡ ወደ ሀገራችንም ሊመጡ የቻሉት እንዴት ነው? ቢሉ መጀመሪያ ለሰባት ወር በአንድ ሌላ አገር ኖረው ወደ ኢየሩሳሌም ሊመለሱ ሲሉ የበረሃ ሽፍቶች ሜርጵዮስንና ሌሎች መንገደኞችን ገደሏቸውና ሁለቱን ልጆች ማርከው ወስደው ስሙ አልአሜዳ ለሚባል ለአክሱም ንጉሥ ሰጡት፡፡ እርሱም አድስዮስን የቤተክርስቲያን የአልባሳትና የዕቃ ቤት ጠባቂ አድርጎ ሲሾመው ፍሬምናጦስን ደግሞ የቤተ ክርስቲያንና የሕግ ጠባቂ አደረገው-የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓቷንና አገልግሎቷን ጠንቅቆ ያውቅ ነበርና፡፡ እርሱም በአክሱምም በተጋድሎና በትጋት ኖረ፡፡ ቅዳሜና እሁድ የዛፍ ቅጠሎችን ከመመገብ በቀር ሌላ ምግብ አይቀምስም ነበር፡፡ በየቀኑም አምስት ሺህ ስግደትን ይሰግድ ነበር፡፡ በእርሱም የተጋድሎ ዘመን ደጋግ የሆኑ ነገሥታት አብርሃና አጽብሓ ነገሡ፡፡ እነርሱም ሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍሬምናጦስን በጣም ይወዱት ነበር፡፡
❤ አንድ ቀን ፍሬምናጦስ የአክሱሙን ኤጲስ ቆጶስ ቅዱስ ሚናስን "ግዝረትና እምነት በእናንተ ዘንድ አለ ነገር ግን ጥምቀትና ሥጋ ወደሙ መቀበል በእናንተ ዘንድ የለም" አለው፡፡ ቅዱስ ሚናስም "ግዝረትንስ አባቶቻችን ሌዋውያን አመጡ፣ በክርስቶስ ማመንን ሕንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት ጃንደረባ አመጣልን፡፡ ስለ ጥምቀትና ሥጋ ወደሙ ሐዋርያ ወደ እኛ አልተላከም ነገር ግን ያልከውን ሁሉ የሚያደርግልን የሚባርከንና የሚቀድሰን ጳጳስን ታመጣልን ዘንድ ሊቀ ጳጳሱ ወዳለበት ወደ እስክንድሪያ አገር አንተ ሂድ" አለው፡፡ ጥምቀትስ በጃንደረባው በኩል አገራችን ገብቶ ነበር ነገር ግን ገና ስላልተጠናከና ብዙ ሕዝብም አልተጠመቀም ነበርና አባታችን ፍሬምናጦስ አጠናክሮ ያልተጠመቀውን ሁሉ አጥምቆአል፡፡
