ሰዋስው ☘☘☘☘
رفتن به کانال در Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
نمایش بیشتر1 161
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ኅዳር ፳፰ (28) ቀን።
❤ እንኳን ለአገረ ኒቅዮስ ኤጲስቆጶስ ለቅዱስ ሰረባሞን ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን።
+ + +
❤ የአገረ ኒቅዮስ ኤጲስቆጶስ ቅዱስ ሰረባሞን፦ ይህም ቅዱስ በኢየሩሳሌም አገር ከሌዊ ነገድ ለሆነ ለእስጢፋኖስ ከዘመዶቹ ውስጥ ነው። የአባቱም ስም አብርሃም ነው እርሱ የሌዊ ልጅ የዮሴፍ ልጅ ለስምዖን ወንድም ለእስጢፋኖስ እናት ወንድሟ የሆነ ነው። በተወለደም ጊዜ በአባቱ ስም ስምዖን ብለው ጠሩት አባቱም ሲሞት ክርስቲያን ይሆን ዘንድ ወደደ። ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ ተገልጸለትና ወደ ኤጲስቆጶስ አባ ዮሐንስ እንዲሔድ አዘዘወው እንዳዘዘውም ሔደ። እርሱም የመድኃኒታችንን የክርስቶስን ሰው የመሆኑን ምስጢር ገለጠለት ግን ዘመዶቹ የሆኑ አይሁድን ስለፈራ በኢየሩሳሌም አገር የክርስትና ጥምቀት ሊአጠምቀው አልደፈረም።
❤ ኤጲስቆጶሱም ስለርሱ ምን እንደሚያደርግ ሲያስብ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተገልጣለት ወደ እስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ቴዎናስ እንዲልከው አዘዘችው። ሰረባሞንም እየተጓዘ ሳለ እንሆ የእግዚአብሔር መልአክ ቀድም ብሎ በሰው አምሳል ወደ ቴዎናስ ቀርቦ ስለ ቅዱስ ሰረባሞን አስረዳው ሰረባሞንም በደረሰ ጊዜ የእግዚአብሔርን ሕግ አስተምሮ የከበረች የክርስትና ጥምቀትን አጠመቀው።
❤ ከዚህም በኋላ ከእስክንድርያ ከተማ ውጭ በሆነች በአባ ሳዊሮስ ገዳም ውስጥ መነኰሰ አባ ቴዎናስም በዐረፈ ጊዜ በእርሱ ፈንታ አባ ጰጥሮስ ተሾመ። ያን ጊዜም መልክተኞችን ልኮ ይህን አባ ሰረባሞንን ወደርሱ አስመጥቶ በሊቀ ጵጵስናው ሥራ እንዲራዳው አደረገ። ከዚህም በኋላ ኒቅዮስ ለሚባል አገር ኤጲስቆጶስነት ሾመው። ብዙዎች አብያተ ክርስቲያናትም በእርሱ ደስ አላቸው እግዚአብሔርም በእጆቹ ድንቆች ተአምራትን አደረገ በአገሩ አቅራቢያ ሰዎች የሚያመልኳቸው የጣዖት ቤቶች ነበሩ ያጠፋቸውም ዘንድ እግዚአብሔርን ለመነው በዚያንም ጊዜ ምድር አፏን ከፍታ ወጠቻቸውና በቦታው ላይ ባሕር ሁኖ ሸፈናቸው። እግዚአብሔርም በአገረ ስብከቱ ጣዖታትን ደመሰሰ ዳግመኛም አብን ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ አካል የሚያደርግ የሰባልዮስን ስድብ አስወገደ።
❤ ዲዮቅልጥያኖስም ክዶ ጣዖታትን በአመለከ ጊዜ ቅዱስ ሰረባሞን የአማልክትነሰ አምልኮ እንደሚሽር ነገሩት እርሱም ሰምቶ ተቆጣ ወደርሱም እንዲአመጡት አዘዘ ሲወስዱትም ከንጉሥ መልክተኞች ጋር እስክንድርያ ከተማ ደረሰ ሊቀ ጳጳሳት ጴጥሮስም ወደርሱ መጣ ከእርሱም ጋር ቡዙ ካህናት ነበሩ ሰላምታም ሰጡት ፊቱም እንደ እግዚአብሔር መልአክ ፊት ብሩህ ሁኖ አዩት። ወደ ንጉሡም በደረሰ ጊዜ በተለያዩ በብዙ ዓይነት ሥቃይ አሰቃየው ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ያለ ጥፋት በጤንነት አስነሣው። ይህንም ድንቅ ሥራ አይተው ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብዙዎች አመኑ።
❤ ሕዝቡ ሁሉ በእርሱ ምክንያት በጌታችን እንዳያምኑ ንጉሥ ፈርቶ የእንዴናው ገዥ አርያኖስ ወዳለበት ወደ ላይኛው ግብጽ ሰደደው በዚያ እንዲአሠቃየውና ራሱንም በሰይፍ እንዲቆርጥ በዚያንም ወቅት መኰንኑ አርያኖስ የኒቅዮስ ከተማ ወደብ አቅራቢያ በመርከብ ውስጥ ነበር። መርከቢቱም ቆመች ከቦታዋም ሊአንቀሳቅሱዋት አልተቻላቸውም ቅዱስ ሰረባሞንንም አውጥተው ለአገሩ ደቡብ ወደ ሆነ ቦታ ወስደው በዚያ ራሱን በሰይፍ ቆረጡት ምዕመናንም መጥተው ሥጋውን ወስደው በክብር ገንዙትና በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አኖሩት ከሥጋውም ድንቆች ተአምራት ሆኑ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት በቅዱስ ሰረባሞን ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 28 ስንክሳር።
+ + +
❤ "ሰላም ለከ ለቀዳሜ ሰማዕተ ዘመዱ። ወፈጻሜ ስምዕ ሱታፌ ክበዱ። ሰረባሞን ለዕሌከ አመ ዓላውያን ሰደዱ። ሶበ ርእዩ ሥዕለ ፈጣሪ ለስነ ገጹከ በዓውዱ። ታሕተ እገሪከ አናብስት ሰገዱ"።
+ + +
❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ "ፍታሕ ፍትሕየ ወባልሐኒ። ወበእንተ ቃልከ አሕይወኒ። ርኁቅ ሕይወት እምኃጥአን። መዝ118፥154-155። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ13፥10-18።
+ + +
❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "በርህ ሠረቀ ለጻድቃን። ወርቱዓነ ልብ ትፍሥሕት። ይትፌሥሑ ጻድቃን በእግዚአብሔር"። መዝ 96፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት 3፥5-15፣ 2ኛ ቆሮ 4፥1-7 ወይም ያዕ 2፥21-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 3፥12-17 የሚነበበው ወንጌል ማር 12፥25-28። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የአባታችን የአቡነ ሊቃኖስ የዕረፍትና በዓል የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜና ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ኅዳር ፳፰ (28) ቀን።
❤ እንኳን ከዘጠኙ ቅዱሳን ለአንዱ ለሆኑት በጸሎት ጊዜ የእጆቻቸው ጣቶች እንደ መብራት ያበራ ለነበሩት በአክሱም ከተማ አካባቢ የሚገኘውን ደብረ ቊንጽል ገዳም ለመሰረቱት ለአባ ሊቃኖስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን።
+ + +
❤ "ሰላም ለአባ ሊቃኖስ ዘኮነ ማኅደሮ ለመንፈስ ቅዱስ"። ትርጉም፦ ለመንፈስ ቅዱስ ማደሪያው ለኾነ ለአባ ሊቃኖስ ሰላምታ ይገባል። ሊቀ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።
+ + +
❤ አባ ሊቃኖስ፦ ቊጥራቸው ከዘጠኙ ቅዱሳን ሲኾን የመጡት ከቊስጥንጥንያ (ሮም) አገር ሲኾን በአክሱም ከተማ አካባቢ ደብረ ቊናጽል የሚል ገዳምን ገድመዋል፤ በዓለ ዕረፍታቸውም ኅዳር28 ቀን ነው፤ በጸሎት እጃቸውን በዘረጉ ጊዜ ዐሥሩ ጣቶቻቸው እንደ መብራት ይበራ እንደነበር ዜና ገድላቸው ያስረዳል። ምንጭ፦ ተአምኆ ቅዱሳን ንባቡና ትርጓሜው።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት
https://t.me/Eotcw
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሉቃ. 10:1-12 "ወእምዝ አርአየ እግዚእነ ካልአነ" - "ከዚህም፡በኋላ፡ጌታ፡ሌላዎቹን፡ሰብዓ፡ሾመ፥ሁለት፡ሁለትም፡አድርጎ፡እርሱ፡ሊሄድበት፡ወዳለው፡ከተማና፡ስፍራ፡ሁሉ፡በፊቱ፡ላካቸው። አላቸውም፦መከሩስ፡ብዙ፡ነው፥ሠራተኛዎች፡ግን፡ጥቂቶች፡ናቸው፤እንግዴህ፡የመከሩን፡ጌታ፡ለመከሩ፡ሠራተኛዎች፡እንዲልክ፡ለምኑት። ሂዱ፤እንሆ፥እንደ፡በጎች፡በተኵላዎች፡መካከል፡እልካችኋለሁ። ኰረጆም፡ከረጢትም፡ጫማም፡አትያዙ፤በመንገድም፡ለማንም፡እጅ፡አትንሡ።
ወደምትገቡበት፡ቤት፡ሁሉ፡አስቀድማችሁ፦ሰላም፡ለዚህ፡ቤት፡ይሁን፡በሉ። በዚያም፡የሰላም፡ልጅ፡ቢኖር፥ሰላማችሁ፡ያድርበታል፤አለዚያም፡ይመለስላችኋል። በዚያም፡ቤት፡ከእነርሱ፡ዘንድ፡ካለው፡እየበላችሁና፡እየጠጣችሁ፡ተቀመጡ፤ለሠራተኛ፡ደመ፡ወዙ፡ይገባዋልና።ከቤት፡ወደ፡ቤት፡አትተላለፉ። ወደምትገቡባትም፡ከተማ፡ሁሉ፡ቢቀበሏችሁ፥ያቀረቡላችሁን፡ብሉ፤በእርሷም፡ያሉትን፡ድውዮችን፡ፈውሱና፦የእግዚአብሔር፡መንግሥት፡ወደ፡እናንተ፡ቀረበች፡በሏቸው። ነገር፡ግን፥ወደምትገቡባት፡ከተማ፡ሁሉ፡ባይቀበሏችሁ፥ወደ፡አደባባይዋ፡ወጥታችሁ። ከከተማችኹ፡የተጣበቀብንን፡ትቢያ፡እንኳን፡እናራግፍላችኋለን፤የእግዚአብሔር፡መንግሥት፡ግን፡ወደ፡እናንተ፡እንደ፡ቀረበች፡ይህን፡ዕወቁ፡በሉ። እላችኋለሁ፥በዚያን፡ቀን፡ከዚያች፡ከተማ፡ይልቅ፡ለሰዶም፡ይቀልላታል።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
1 161
27/3/2015 ዓ.ም (፳፯/፫/፳፻፲፭ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ጸኒሐ ጸናሕክዎ ለእግዚአብሔር።
ሰምዐኒ ወተመይጠኒ።
ወሰምዐኒ ቃለ ስእለትየ፡፡ መዝ 39:1
ትርጉም
ቆይቼ እግዚአብሔርን ደጅ ጠናሁት፤
እርሱም ዘንበል አለልኝ።
ጩኸቴንም ሰማኝ፡፡
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ማቴ. 27:57-ፍ፡ም፡ "ወጸርሐ ካዕበ ኢየሱስ በዐቢይ ቃል" - "ኢየሱስም፡ሁለተኛ፡በታላቅ፡ድምፅ፡ጮኾ፡ነፍሱን፡ተወ። እነሆም፥የቤተ፡መቅደስ፡መጋረጃ፡ከላይ፡እስከ፡ታች፡ከሁለት፡ተቀደደ፥ምድርም፡ተናወጠች፥አለቶችም፡ተሰነጠቁ፤ መቃብሮችም፡ተከፈቱ፥ተኝተው፡ከነበሩትም፡ከቅዱሳን፡ብዙ፡ሥጋዎች፡ተነሡ፤ ከትንሣኤውም፡በኋላ፡ከመቃብሮች፡ወጥተው፡ወደ፡ቅድስት፡ከተማ፡ገቡና፡ለብዙዎች፡ታዩ። የመቶ፡አለቃም፡ከእርሱም፡ጋራ፡ኢየሱስን፡የሚጠብቁ፡መናወጡንና፡የሆነውን፡ነገር፡አይተው፦ይህ፡በእውነት፡የእግዚአብሔር፡ልጅ፡ነበረ፡ብለው፡እጅግ፡ፈሩ። ኢየሱስን፡እያገለገሉ፡ከገሊላ፡የተከተሉት፡ብዙ፡ሴቶች፡በሩቅ፡ሆነው፡ሲመለከቱ፡በዚያ፡ነበሩ፤ ከእነርሱም፡መግደላዊት፡ማርያምና፡የያዕቆብና፡የዮሳ፡እናት፡ማርያም፡የዘብዴዎስም፡የልጆቹ፡እናት፡ነበሩ። በመሸም፡ጊዜ፡ዮሴፍ፡የተባለው፡ባለጠጋ፡ሰው፡ከአርማትያስ፡መጣ፥እርሱም፡ደግሞ፡የኢየሱስ፡ደቀ፡መዝሙር፡ነበረ።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
1 161
27/3/2015 ዓ.ም (፳፯/፫/፳፻፲፭ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ለምንት አንገለጉ አሕዛብ።
ወሕዝብኒ ነበቡ ከንቶ።
ወተንሥኡ ነገሥተ ምድር፡፡ መዝ 2፥1
ትርጉም
አሕዛብ ለምን ያጉረመርማሉ።
ወገኖችስ ለምን ከንቱን ይናገራሉ?
የምድር ነገሥታት ተነሡ፡፡
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ "ሰላም ለያዕቆብ አዕጹቂሁ ዘሠምረ ወፈረየ አስካለ፤ ኵለንታሁ ዘተመትረ ወተዐገሠ ሞተ መሪረ"። ትርጉም፦ ቅርንጫፎቹ የተወደደ ለኾነ፤ ፍሬን ያፈራ፤ ኹለንተናው የተቈረጠ መሪር ሞትን የታገሠ ለኾነ ለያዕቆብ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።
+ + +
❤ "ሰላም ለያዕቆብ ዕጉሠ መከራ በሕቁ። ለእግዚአብሔር ሰማዕተ ጽድቁ። አርብዓ ወክልኤ እስከ ይከውን ኊልቁ። አባሎ በመጥባሕት አመ ሐራ ንጉሥ ሠጠቁ። መንፈቀ ሥጋሁ ጸለየ መዊቶ መንፈቁ"። ትርጉም፦ በእጅጉ (ባያሌው) መከራን የታገሠ ለእግዚአብሔር የእውነት ምስክሩ ለያዕቆብ ሰላምታ ይገባል፤ ቊጥሩ አርባ ኹለቱ እስኪኾን ድረስ የንጉሥ ጭፍሮች ሰውነቱን በሰይፍ በቈረጡ ጊዜ እኩሌታ አካሉ ሞቶ እኩሌታ አካሉ ጸለየ። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የኅዳር 27።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ ከጥቂት ቀኖች በኋላም ከሚስቱ ጋር አውጥተው ደማቸው እንደ ውኃ እስቲፈሰሰ በአለንጋዎች እንዲገረፋአቸው አዘዘ ያለ ርኅራኄም ገረፋአቸው ሚስቱም በዚህ ሥቃይ ምስክርነቷን ፈጸመች። ዳግመኛም ለጣዖታት መስገድን እሺ ይለው ዘንድ ቅዱስ ጢሞቴዎስን ማባበል ጀመረ እምቢ ባለውም ጊዜ የነዳጅ ድፍድፍ ሥጋውን ቀብተው ከእሳት ማንደጃ ውስጥ እንዲጨምሩት አዘዘ በጨመሩትም ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ ከዚህ ቃጠሎ አዳነው።
❤ ከዚህም በኋላ ሁለተኛ ወደወህኒ ቤት መለሱት ተአምራትንም የሚያደርግ ሆነ በአንዲት ዕለትም በዚያ ሲጸልይ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደርሱ መጥቶ ቃል ኪዳንን ገባለት ሰላምታንም ሰጠው። በማግሥቱም ከእሥር ቤት አውጥተው ወደ በንሑር ከተማ ወስደው ቅድስት ራሱን ቆረጡ ያን ጊዜ ንውጽውጽታ ሆነ አየርም መላእክትን ተመላች አማንያን ሰዎችም መጥተው ሥጋውን ወስደው በመልካም አገናነዝ ገንዘው ቀበሩት። የመከራውም ዘመን በአለፈ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ሠሩለት ሰኔ ሃያ ሰባት ቀንም አከበርዋት ሥጋውንም በውስጥዋ አኖሩ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕቱ በቅዱስ ጢሞቴዎስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር27 ስንክሳር።
+ + +
❤ "ሰላም እብል ለልሳንከ ዘተውህበ። መዓርዒረ ቃል ወመአድመ ንባበ። ኀቤከ ይብጻሕ ዘተዝካርየ ክታበ። ፈኑ ሊተ ፊልሞና እስመ ራሰይኩከ አበ። ሀገረ ልድያ ቀዳሚ ዘፈኖከ ርግብ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የኅዳር 27።
+ + +
❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ለምንት አንገለጉ አሕዛብ። ወሕዝብኒ ነበቡ ከንቶ። ወተንሥኡ ነገሥተ ምድር። መዝ 2፥3-4 ወይም ። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 27፥57-ፍ.ም።
+ + +
❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ጸኒሐ ጸናሕክዎ ለእግዚአብሔር። ሰምዓኒ ወተመይጠኒ። ወሰምዓኒ ቃለ ስእለትየ"። መዝ 39፥1-2 ወይም መዝ 73፥12-13። የሚነበቡት መልዕክታት ፊሊ 1፥1-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 5፥9-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 11፥25-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 10፥1-12። የቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ወይም የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የአቡነ ተክለ ሐዋርያት የዕረፍት በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ኅዳር ፳፯ (27) ቀን።
❤ እንኳን ከሰባ ሁለቱ አርድእት ለአንዱ ለቅዱስ ፊልሞና ለመታሰቢያው በዓል፣ ለፋርስ ንጉሥ ለሳፎር ልጅ ለንጉሥ ሰክራድ ከጭፍሮች ውስጥ ለሆነ ሕዋሳቱን የተቆራረጠ ለቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና በንሑር ከሚባል አገር ለሆነ ለቅዱስ ጢሞቴዎስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከመድኃኒታችን ከመድኃኔዓለም ከስቅለቱ መታሰቢያ፣ ከገርማው ከአባ ገብረ ዮሐንስ፣ ከደብረ ቊንጽል ከአባ ሊቃኖስ ከመታሰቢያቸውና ዘርቦች ከምትባል አገር ከደብረ ጒይ ከሰማዕት ቀሌምንጦስ ከመታሰቢያው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ በዚችም ዕለት ከሰባ ሁለቱ አርድእት የአንዱ የፊልሞና መታሰቢያው ነው። የቅዱስ ፊልሞና በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ ያዕቆብ ዘግሙድ፦ ይህ ለሳፎር ልጅ ለንጉሥ ሰክራድ ከጭፍሮቸሐ ውስጥ የሆነ ነው። ንጉሥ ሰክራድ እጅግ ይወደው ነበር ስለ መንግሥቱ ሥራ ሁሉ ከእርሱ ጋር ይማክር ነበርና ስለዚህም የቅዱስ ያዕቆብን ልቡና አዘንብሎ ፀሐይንና እሳትን እንዲአመልክ አደረገው። በሃይማኖቱም ከንጉሡ ጋር እንደተስማማ የተቀደሱ እናቱ ሚስቱንና እኅቱ በሰሙ ጊዜ እንዲህ ብለው ጽፈው ወደርሱ ላኩ "የቀናች የጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት ትተህ የፍጡራንን ጠባይ ለምን ተከተልክ እሊህም ፀሐይ ጨረቃ ከዋክብት እሳት ናቸው ዕወቅ ከዛሬ ጀምሮ በንጉሥ ሃይማኖት ከኖርክ እኛ ከአንተ የተለየን ነን"። የመልክታቸውንም ጽሑፍ በአነበበ ጊዜ መሪር ልቅሶን አለቀሰ "በዚህም የጥፋት ምክር ጸንቼ ብኖር ከቤተሰቦቼና ከወገኖቹ የተለየሁ መሆኔ ነው። ደግሞስ በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ፊት እንዴት እቆማለሁ" አለ።
❤ ከዚህም በኋላ የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍቶች ማንበብ ጀምረ የንጉሡን አግልግሎትም ተወ ለንጉሡም "ወዳጅህ ያዕቆብ እነሆ አገልግሎትህን አማልክቶችህም ማምለክ ተወ" ብለው ነገሩት። ንጉሡም ልኮ ወደርሱ አስቀርቦ "አገልግሎትህን ለምን ተወክ?" አለው ቅዱስ ያዕቆብም እንዲህ አለ "ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ ወንጌል በሰው ፊት ያመነብኝን ሁሉ እኔም በሰማያዊ አባቴ ፊት አምነዋለሁ በሰው ፊት የካደኝንም በአባቴ ፊትና በመላእክት ፊት እክደዋለሁ ብሏልና ስለዚህ አገልግሎትህን ፍቅርህን አማልክቶችህንም ማምለክ ትቼ ሰማይና ምድርን ፀሐይን ጨረቃን ከዋክብትን የሚታየውንና የማይታየውን ለፈጠረ ለሕያው እግዚአብሔር ልጅ ለጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ የምሰግድ ሆንኩ"።
❤ ንጉሡም ይህን በሰማ ጊዜ ደሙ እንደ ውኃ በዝቶ እስቲፈስ ታላቅ ግርፋትን እንዲገርፉት አዘዘ እርሱ ግን ከበጎ ምክሩ አልተመለሰም ዳግመኛም ሕዋሳቱነሰ በየዕለቱ እንዲቆርጡ አዘዘ የእጆቹንና የእግሮቹን ጣቶች ሃያውን ቆረጡ ክንዶቹንና እግሮቹን እስከ ጭኖቹ ድረስ ወደ አርባ ሁለት ቊራጭ በየጥቂቱ ቆረጡት። በሚቆርጡትም ጊዜ ሁሉ "ጌታዬና ንጉሤ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ዕንጨት ቅርንጫፍ ሰውነቴን በይቅርታህ ገናናነት ተቀበል የወይን አታክልት ያለው በሦስት ዓጽቅ ሲቆርጡለት ዓጽቆቹ በዝተው ይበቅላሉ ይሰፋሉ በሚያዝያ ወር አብቦ ያፈራልና" እያለ የሚዘምርና የሚያመሰግን ሆነ። ደረቱና አካሉ እንደ ግንድ ድብልብል ሁኖ በቀረ ጊዜ ነፍሱን ለመስጠት እንደ ደረሰ አውቆ በዚያን ጊዜ በዓለም ውስጥ ያሉትን ሰዎች ሁሉንም ይመራቸው ዘንድ እግዚአብሔርን ለመነው እንዲህም አለ "ለእኔ ግን ወደ አንተ የማነሣው አካል አልቀረኝም ሕዋሳቶቼ ተቆርጠው በፊቴ የወደቁ ስለሆነ አሁንም ነፍሴን ተቀበላት" አለ።
❤ በዚያንም ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾ አረጋጋው አጸናውም ያን ጊዜ ነፍሱ ደስ አላት ነፍሱንም ከመስጠቱ በፊት ወታደሩ በፍጥነት መጥቶ የከበረች ራሱን በሰይፍ ቆረጠ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ ሥጋውንም ምእመናን ሰዎች ወስደው በመልካም አገናነዝ ገነዙትና በንጹሕ ቦታ አኖሩት። እናቱ ሚስቱና እኅቱ በሰማዕትነት እንደ ሞተ በሰሙ ጊዜ አጅግ ደስ አላቸው ወደ ቅዱስ ያዕቆብም ሥጋ መጥተው ተሳለሙት አለቀሱለትም የከበሩ ልብሶችንም በላዩ አኖሩ ጣፋጮች የሆኑ ሽቱዎችንም ረጩበት።
❤ በደጋጎች ነገሥታት በአኖሬዎስና በአርቃዴዎስ በሌሎችም ዘመን አብያተ ክርስቲያን ታነፁ ገዳማትና አድባራትም ተሠሩ የሰማዕታትንም ሥጋ በውስጣቸው አኖሩ ታላላቆቸሰ ድንቆች ተአምራትም ከእሳቸው የሚታዩ ሆኑ። የፋርስ ንጉሥም ሰምቶ በቦታው ሁሉ የሰማዕታትን ሥጋ ያቃጥሉ ዘንድ አዘዘ በሚገዛውም አገር ውስጥ ምንም ምን እንዳይተው አማንያን ሰዎችም መጥተው የቅዱስ ያዕቆብን ሥጋ ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት በዚያም ወደ አገረ ሮሀ ከአገረ ሮሀም የከበረ ኤጲስቆጶስ ጴጥሮስ ወደ ግብጽ አገር ወደ ብሕንሳ ከተማ ወሰደው። በዚያም ጥቂት ጊዜ ኖረ ከርሱ ጋርም መነኰሳት ነበሩ ከቀኑ እኵሎታም ሲጸልዩ ቅዱስ ያዕቆብ ሥጋ ከብዙ የፋርስ ሰማዕታት ሥጋ ጋር በአለበት ሰማዕታት አብረዋቸው ዘመሩ ባረኳቸውም ቅዱስ ያዕቆብም "እግዚአብሔር እንዳዘዘ ሥጋዬ በዚህ ይኑር" አለ ከዚያም በኋላ ተሠወሩ።
❤ ከዚህም በኋላ የከበረ ኤጲስቆጶስ ጴጥሮስ ወደ አገሩ ሊመለስ በወደደ ጊዜ ሥጋዬ በዚህ ቦታ ይኑር ያለውን የቅዱስ ያዕቆብን ቃል ተላለፎ የቅዱስ ያዕቆብን ሥጋ ወሰደ በዚያንም ጊዜ አስቀድሞ ወደ አመለከተው ቦታ ከእጆቻቸው መካከል ተመለሰ ከሥጋውም ታላላቅ የሆኑ ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ሰማዕት በቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ ቅዱስ ጢሞቴዎስ፦ ይህም ቅዱስ ከታናሽነቱ ጀምሮ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሁል ጊዜ በጾም በጸሎት ተጠምዶ የሚኖር ነው ስሟ ሞራ የሚባል ሚስት አለችው እርሷም የአጎቱ ልጅ ናት በሥራዋ ሁሉ ደስ የምታሰኘው መልካም ሴት ናት። እንደዚህም በፍቅርና በስምምነት ሲኖሩ ከከሀዲ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ የጣዖታት ቤቶች ይከፈቱ ዘንድ አብያተ ክርስቲያናት እንዲዘጉ ትእዛዝ ወጣ። ቅዱስ ጢሞቴዎስም ይህን ሰምቶ እጅግ ደስ አለው። እርሱ ስለ ክርስቶስ ፍቅር ደሙን ያፈስ ዘንድ ይህን ዘመን ይጠብቀው ነበርና ለሚስቱም ሊሠራው ያሰበውን ነገራት እርሷም "የእግዚአብር ፈቃድ ይሁን" አለች።
❤ ከዚህም በኋላ መንገዱን ያቀናለት ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ ጌታችንም በዚያች ሌሊት በሕልሙ ተገልጾለት "ወዳጄ ጢሞቴዎስ ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን እንሆ ከጻድቃኖቼ ቊጥር ውስጥ ቆጥሬሃለሁ አሁንም ተነሣ ሚስትህንም ይዘህ ወደ ብህንሳ ከተማ ሒዳችሁ ጣዖታትን በሚያመልኩ ሁሉ ሕዝብ ፊት በስሜ ታመኑ" አለው። በነቃ ጊዜም ለሚስቱ ነገራት እርሷም ይህንኑ የሚመስል ሕልሟን ነገረችው።
❤ ከዚህም በኋላ ተነሥተው በአንድነት ሔዱ ወደ መኰንኑ ወደ ቊልቊልያኖስም ደረሱ መሰንቆና እንዚራ እያስመታ ለጣዖታቱ በዓልን ሲያከብር አገኙት ያንጊዜ ወታደሮቹ ይዘው በመኰንኑ ፊት አቆሙት ሚስቱም ተከተለችው መኰንኑም ለጣዖት መስገድን እያግባባ በርኅራኄ ቃል ተናገረው ቅዱስ ግን እርሱንና የረከሰች ሃይማኖቱን ሰደበ ስለዚህም መኰንኑ ተቆጥቶ ከሚስቱ ጋር ወደ ወህኒ ቤት እንዲአስገቡት አዘዘ።
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ኅዳር ፳፯ (27) ቀን።
❤ እንኳን ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ስለ ጌታችን ሥጋና ደም ክብር ሲሉ ቅዱስ ቊርባን የተቀበለ ሰው ያስታወከው የጠጡ ለታላቁ አባት ለአቡነ ተክለ ሐዋርያት ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን።
+ + +
❤ አቡነ ተክለ ሐዋርያት፦ አባታቸው የእናርዕት አገረ ገዥ የነበሩት እድርያስ ሲሆኑ እናታቸው ደግሞ እሌኒ ይባላሉ። የትውልድ አገራቸው ሸዋ ሲሆን በዚሁ የምትገኘውን ታላቋን ደብረ ጽሙናን ገዳም የመሠረቱ ሲሆን በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን የነበሩ ታላቅ አባት ናቸው። ገና በእናታቸው ማኅፀን ሳሉ አጋንንትን እያቃጠሉ ያጠፏቸው ነበር። የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት ተምረው ከጨረሱ በኋላ ገና በድቁና እያገለገሉ ሳለ 40 ቀን በማክፈል ይጾሙና ይጸልዩ ነበር። አባታችን የመነኰሱትና ብዙ ተጋድሏቸውን ፈጽመው ወደ ሰማይ ተነጥቀው ሥላሴን እስከማየት የደረሱት በደብረ ሊባኖስ ነው። ያመነኰሷቸውም ሁሉን በስውር ያለውን የሚያውቁት አቡነ ዮሐንስ ከማ ናቸው። አባታችን ማታ ማታ ከባሕር ውስጥ ገብተው ሲጸልዩ እያደሩ በቀን 30 ፍሬ አተር ብቻ እየተመገቡ ይጾሙ ነበር።
❤ በአባ አትናቴዎስ መቃብር ላይ ሄደው አጥብቀው የጸለዩ ፯ አክሊል የወረደላቸው ጌታ ተገልጾ ከጊዮርጊስና ከዮሐንስ መጥምቁ ጋር ነው ክፍልህ ያላቸው ጻድቅ ናቸው። በዚህም ሙታን የተነሱላችሁ ብዙ ተዓምር ያደረጉ ብርሃን የወረደላቸው ታላቅ ጻድቅ ናቸው። ሲጸልዩ ነፍሴ ፫ (ሦስት) ነገርን ትፈልጋለች ይሉ ነበር።
➻ 1 ከዚህ ዓለም ሀሜት መራቅን ፤
➻ 2 ክፉ ነገር ከማየት መራቅን ፤
➻ 3 ከንቱ ነገር ከመስማት መራቅን እያሉ ይማጸኑ ነበር።
❤ እንዲህ እያሉ በሚጸልዩበትም ወቅት መልአኩ መጣና ወደ በረሃ ምንም ሰው ወዳሌለበት ሂድ አላቸው። እንዳላቸው ወደ ምድረ ሐጋይ በዝዋይ አድርገው አልፈው ከባሕር ውስጥ በሚገኝ ዋሻ ገቡ። ከዚያ ገብተው ይጸልዩ ጀመር። በዚያም ብርሃን ወርዶላቸው ነፍሴ ሰውነቴን ተጸየፈች እያሉ ይጸልዩ ጀመር። በዚያን ጊዜ ጌታ ተገልጾላቸው ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል።
❤ አባታችን አቡነ ተክለሐዋርያት ከሌሎች ፃድቃን ለየት የሚያደርጋቸዉ፦ አንድ ዓመት የታመመ ህመምተኛ ሥጋወደሙ ወስዶ (ተቀብሎ ) ከህመሙ የተነሳ አስመለሰዉ ዲያቆኑ ያስመለሰዉን በእቃ ተቀበለዉ ። ደምና መግል የተቀላቀለበት ነበር አባታችን አቡነ ተክለሐዋርያት ሰለ ስጋወ ደሙ ክብር በዕለተ ዓርብ ሃሞትና ሆምጣጤዉን እንደ አጠጡት የወልድን የመስቀሉን መከራ አስበዉ ፈጣሪአቸዉን ከመዉደዳቸዉ የተነሳ ያንን ያስመለሰውን ግጥም አደርገዉ ጠጡት በዘያን ጊዜ ጌታችን ወደሳቸዉ መጥቶ ወዳጄ ተክለሐዋርያት ሆይ በሰው ፊት እንዳከበርከኝ በሰማያዊ መላአክትና በምድራውያን ፃድቃን ሰማእታት ፊት አከብርሃለሁ ብሎ ጣቱን አንስቶ በጣቱ ፊታቸዉን በባረከዉ ጊዜ ፊታቸዉ እንደ ፀሐይ አበራ በፊቱም ላይ ያለዉ የፀሐይ ብርሃን በምድር ላይ ሁሉ ታየ ።
🐓አንድ ዶሮ በሰንበት ቀን ከባለቤቱ አምልጦ መጥቶ አስጥለኝ ብሎ ለመናቸዉ አሳቸዉ የዶሮውን ባለቤት ሰንበት ነው አትረደዉ ቢሉት አልሰማ ሰላላቸዉ ያላቸዉን ሸማ (ልብስ ) ሰጥተዉ ዶሮውን ከመታረድ አድነውታል በስዕሉ ላይ አንደሚታየዉ።
❤ በመጨረሻም አባታችን አቡነ ተክለ ሐዋርያት ሕዳር ፳፯ ቀን በክብር አርፈዋል። መላዕክትም ፭ ሆነው ወርደው ቀብረዋቸዋል። መጀመሪያ በደብረ ብርሃን ተቀብረው ከ፲፫ ዓመት በኋላ በምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት ስር በምትገኘው ወደ ደብረ ፅሙና አፅማቸው መጥቷል። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳንና የደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር ዕፀ ጳጦስ ሰንበት ትምህርት ቤት።
+ + +
❤ "ሰላም እብል ለተክለ ሐዋርያት በተአምኆ። ወለተአምሪከ እሴብሖ። ለምሳሐ ሰንበት ሶበ ፈቀደ ይጥብሖ። ተማሕፀንኩ በጸሎትከ እንዘ ይብል ከሊሖ። በልሳነ ሰብእ ነበበ ነቃዊ ዶርሖ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የኅዳር 27።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት
https://t.me/Eotcw
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሉቃ. 21፥12-21 "ወእምቅድመ ዝንቱ ኵሉ ይእኅዙክሙ" - "ከዚህም ሁሉ በፊት እጃቸውን በላያችሁ ይጭናሉ ያሳድዱአችሁማል፤ ስለ ስሜም ወደ ምኵራብና ወደ ወኅኒ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ ወደ ነገሥታትና ወደ ገዥዎችም ይወስዱአችኋል፤ ይህም ለምስክርነት ይሆንላችኋል። ስለዚህ እንዴት እንድትመልሱ አስቀድማችሁ እንዳታስቡ በልባችሁ አኑሩት፤ ወደረኞቻችሁ ሁሉ ሊቃወሙና ሊከራከሩ የማይችሉትን አፍና ጥበብ እሰጣችኋለሁና። ወላጆችም እንኳ ወንድሞችም ዘመዶችም ወዳጆችም አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ ከእናንተም አንዳንዱን ይገድላሉ፤ በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ። ከራሳችሁም አንዲት ጠጉር እንኳ አትጠፋም፤ በመታገሣችሁም ነፍሳችሁን ታገኛላችሁ። ኢየሩሳሌም ግን በጭፍራ ተከባ ስታዩ በዚያን ጊዜ ጥፋትዋ እንደ ቀረበ እወቁ። የዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራራዎች ይሽሹ፥ በመካከልዋም ያሉ ከእርስዋ ፈቀቅ ይበሉ፥ በገጠር ያሉም ወደ እርስዋ አይግቡ።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
