ሰዋስው ☘☘☘☘
رفتن به کانال در Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
نمایش بیشتر1 161
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
1 161
+ + +
❤ አባ ማቴዎስ፦ ይህም አባት ከታናሽነቱ ጀምሮ በፈሪሃ እግዚአብሔር ጸንቶ ያደነገ ነው ከገዳማት በአንዱ መንኲሶ በጾም በጸሎት የሚጋደል ሆነ በገዳሙም ውስጥ ለራሱ መኖርያ ሠራ ደቀ መዛሙርቱ አባ ሰራብዮንና አባ ኅድራ ሥራውንና ተጋድሎውን ተአምራቱን እንደተናገሩቱ መረብን በመሥራት ሽያጩ ለድኆች ይመጸውታል።
❤ እነርሱም እንዲህ ብለው ተናገሩ በአንዲት ዕለትም ከማደሪውም በውጪ ተቀምጦ ሳለ በማደሪያውም አንዱ ከሌላው ጋር እንዲነጋገር ሆኖ ቃልን ሰማን በገባንም ጊዜ ከእርሱ በቀር ያገኘነው የለም። "አባታችን ሆይ በውጪ ሳለን ከአንተ ጋር ሰው እንዲነጋገር ድምጽ ሰምተን ነበር በገባን ጊዜ ከአንተ በቀር ያገኘነው የለም" አልነው። በብዙ ትሕትና እንዲህ አለን "ልጆቼ ሆይ የምትጠብቀኝን የሞት ፃዕርና ስቃዮችን ለነፍሴ በማሳሰብ የኃጢያቴን ብዛ አስቤ ከራሴ ጋር ተነጋገሩኩ። ለድኃ ማቴዎስ ወዮለት ንጽሕናን ቅድናን በለበሱ መላእክት የጻድቃንና የሰማዕታት ጉባኤ አንድነት በአለበት በልዑል እግዚአብሔር ፊት ራቁቱን ያቆሙታልና እንዲህ አድርገው የኃጥኣንን ሥቃይ የጻድቃንን መልካም ዋጋ ለልጆቹ አስተማራቸው።
❤ ቅዱስ ማቴዎስ በሠራት ገዳም ውስጥ ጸሎትን ተጋድሎን አገልግሎትን በማድረግ ጸንቶ ኖረ ገዳሙም በአባ ጳኲሚስ ስም አከበረ እርሷም የታወቀች ሰሌን ያለባት ተራራ ነች። ርኩሳት የሆኑ ረቂቅ ሰይጣናት በቀንና በሌሊት የሚያስፈራሩት ሆኑ በየአይነቱ በተለያዩ መልክ ፊት ለፊት እያያቸው እርሱ በፊቱ ይሮጣሉ በኋላ ይከተሉታል እርሱ አይፈራቸውም እጆቹን ዘርግቱ በመስቀል ምልክት ሲያማትብ በዚያን ጊዜ በንፋስ ፊት እንዳለ ጢስ ይበተናሉ።
❤ በአንዲት ዕለትም ጥቂት እንጀራና ውኃ በመንቀል ከገዳሙ ውስጥ ይዞ በበረሃ ውስጥ ወደአለች ዋሻው እንዲሆዱና እርሱ በማግሥቱ እስኪመጣ በዚያ እንዲጠብቀው ረድኡን ሰራብዮንን አዘዘው። ሰራብዮንም ወደ ዋሻው ሲደርስ ሁሉት አራዊት በውስጡ ተኝቶ አገኘ በርቶ በሩን ዘግቶ ከዐለት ቋጥኝ ድንጋይ ወጣ። ከዚህም በኋላ አባ ዳንኤል የዳዊትን መዝሙር እያነበበ መጣ ረድኡንም አይቶ ፈገግ ብሎ ሳቀ "ሰራብዮን ሆይ እኔ ወደ አንተ እስክመጣ ለምን ወደ ዋሻው ውስጥ ለምን አልገባህም" አለው። እርሱም ረድኡ "ሁለት ታላላቅ አውሬዎች ተኝተው ስላገኘው እነርሱን ፈርቼ አልገባሁም" አለው። ንጹሕ ነፍስ ያለው የዋህ የሆነ የተመሰገነ "ልጄ እመነኝ እኔ ከእነርሱ ጋር ስኖር ዐሥራ ሁለት ዓመት ሆነኝ ያሳደግኋቸው እኔ ነኝ ይህንንም እንጀራና ውኃ እንድታመጣ ያዘዝኩህ ለእነርሱ ነው" አለው። ከዚህም በኋላ በሩን በከፈተ ጊዜ እነዚያ አውሬዎች ወደ እርሱም ወጥተው ቅዱስ አባት ማቴዎስን እግሮቹን ላሱ ባልጆሮቹም ሆነውት በታላቅ መለማመጥ ተገዙለት ያንንም ውኃ በገዳው ላይ አፈሰሰላቸው ጠጡ እንጀራውንም በሉ ከዚህም በኋላ ወደ ዱር ሔዱ።
❤ ይህም አባ ማቴዎስ የዜናው መሰማት በቦታ ሁሉ እስከመላ ድረስ ተአምራትን እያደረገ ኖረ በየአይነቱ በሆነ ደዌ የተያዙትን ያመጡለታል። እርሱም በላዩ በአደረች በእግዚአብሔር ኃይል ይፈውሳችዋል።
❤ ከተአምራቶቹንም አንዱን በአንዲት ቀንም ጋጌን ያደረበት ዲዳ ሰውን ወደ እርሱ አመጡ ቅዱን ማቴዎስን በአየው ጊዜ በታላቅ ድምጽ ጮኸ ሰውየውም ከምድር ላይ ጣለው ቅዱሱም በዘይት ላይ ጸለየ በመስቀል ምልክትም አማትቦ ቀባው በዚያንም ጊዜ ድኖ አዕምሮው ተመለሰ የሚሰማና የሚናገርም ሆነ ደስ ብሎትም ወደ ቤቱ ሆደ። ጨዋዎችም በመጡ ጊዜ ማዕድ ያቀርብላደውና በሰላም በፍቅር ያሰናብታቸዋል እነርሱም ለበረከት እያሉ ጥቂት ቁራሽ ወደ ቤታቸው ይመስዳሉ በበሽተኞችም ላይ በአደረጉ ጊዜ ወዲያውኑ ድነው እግዚአብሔር ያመሰግኑታል።
❤ ሁለተኛ ተአምር በአንዲትም ዕለት ደምግባቷም ያማረ ጋጌንም ያደረባትም ብላቴና ወደ እርሱ አመጡ እርሷ ብዙ ጊዜ ልብሷን ትቀዳለች ወደ እርሷም መቅረብ የሚችል የለም ወላጆቿም በታላቅ ኃዘን ውስጥ ይኖራሉ ቅዱስ አባ ማቴዎስም በላይዋ ጸለየና ክብር ይግባውና ኢየሱስ ክርቶስም ዘይቱን ቀብቶ አዳናት።
❤ ሦስተኛ ተአምር በአንዲት ዕለት እጅግ በከፋችና ታላቅ በሆነች ኃጢአት ላይ የወደቀች ኃጢያተኛ ሴት ወደ እርሱ አመጡ እርሷ ጸንሳ የመውለጀዋ ጊዜ የደረሰ ነው በቀንና በሌሊትም በምጥ ሕማም ትሰቃይ ነበር አባ ማቴዎስም "ልጄ ሆይ ኃጢአትሽን እመኚ በእግዚአብሔር ፊት አትዋሺ" አላት እርሷም እንዲህ አለችዉ "እኔ ከሁለት ወንድማማቾች ጋር እነርሱ ሳያውቁ ሳመነዝር ኖርኩ በጸነስኩም ጊዜ ሕጻኑን በመርዝ አውጥቼ ለውሾች ሰጠሁት" አባ ማቴዎስም በሰማ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ በዚያንም ጊዜ ለሌሎች መቀጣጫ ትሆን ዘንድ ምድር አፏን ከፍታ ዋጠቻት።
❤ የዚህም አባት ተአምራቶቹ ብዙ ናቸው ተነግሮ አያልቅም በአንዲትም ቀን በበረሀ ውስጥ ሲጓዝ ጅብ ልብሶቹን በጥርሶቿ ይዛ ሳበችውና በሠንጣቃ ገደል ውስጥ የወደቁ ልጆቿን አሳየችው በአወጣላትም ጊዜ ሰገደችለት እግሮቹንም ላሰች።
❤ ከዚህም በኋላ ዕረፍቱ ሲቀርብ በታኅሣሥ ሦስት ቀን ወደ ሠርግ እንደሚጠራው ራእይን አየ ይኸውም የቅዱሳን አባቶች የአባ እንጦንስ የአባ መቃርስ የአባ ጳኲሚስ የአባ ቴዎድሮስ የአባ ሙሴ ጸሊም የአባ ሲኖዳ የአንድነት ተድላ ደስታ ወዳለበት ነው። እነርሱም በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ከእኛ ጋር ትኖር ዘንድ ወደእኛ መምጣትህ መልካም ነው" አሉት ብዙ አትክልቶችና ዙፋኖች ወዳሉት ታላቅ አዳራሽም ደጅ አደረሱት ማቴዎስ ይገባ ዘንድ የአዳራሹን ደጆች ክፈቱ የሚልንም ቃል ሰማ ከዚህም በኋላ በታኅሣሥ ሰባት ቀን ዐረፈ ሦስት አክሊላትንም ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ማቴዎስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 7 ስንክሳር።
+ + +
❤ "ሶበ ሰአለ ኀቤኪ እንዘ ስመኪ ይሰሚ። በእንተ አውሎጊስ ማሕመሚ። አእጋረ ክርስቶስ ሎቱ እንዘ ትስዕሚ። በከመ አድኃንኪ ነፍስ ዳንኤል ቀዳሚ። አድኅኖትየ ማርያም ድግሚ። ትርጉም፦ አባ ዳንኤል አስጨናቂ ስለነበረው አውሎጊስ ስምሽን እየጠራ ወዳንቺ በለመነ ጊዜ የክርስቶስን እግር እየሳምሽለት ቀድሞ የአባ ዳንኤልን ሰውነት እንዳዳንሽ ማርያም እኔንም ደግመሽ አድኚ። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ7።
+ + +
❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "ሌሊተ ተዛዋዕኩ ምስለ ልብየ ወአንቃሕክዋ ለነፍስየ። ቦኑ ለዓለም ይገድፍ እግዚአብሔር። ወኢይደግምኑ እንከ ተሣህሎ"። መዝ 76፥6-7። የሚነበቡት መልዕክታት ኤፌ 6፥10-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 3፥10-15 እና የሐዋ ሥራ 16፥16-25። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 15፥20-24 ወይም ማር 16፥15-ፍ.ም የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ቄርሎስ ቅዳሴ ነው። መልካም የጾም ጊዜና በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ታኅሣሥ ፯ (7) ቀን።
❤ እንኳን የማኅቶተ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ያሬድ ዜማ አገልግሎት ላይ ለዋለበት ቀን መታሰቢያ በዓል፣ ለታላቁ አባት አአራዊቶች ጋር ይኖር ለነበረ ጅቦች ሳይቀር ይሰግዱለት ለነበረ ለታወቀች እስዋን ለተባለች ገዳም አበምኔት ለሆነ ለሚጋደል ለቅዱስ አባት አባ ማቴዎስ ለዕረፍት በዓልና በአባ መቃርስ ገዳም በደብረ ሲሐት ለሚኖር ለአባ ዳንኤል ለዕረፍት በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ከሚታሰቡ፦ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ እንደሚወለድ በከበሩ ነቢያት አፍ ለመሰበኩ መታሰቢያ ከሆነ፣ ከብፅዕት ዲዮጥርስ ከመታሰቢያዋ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ የቅዱስ ያሬድ ዜማ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ስለ መዋሉ፦ ዐፄ ገብረ መስቀል የቅዱስ ያሬድ ባሕረ ጥበባት ዜማን ጣዕም ሰምተው ከተረዱ በኋላ ሊቃውንትና ካህናቱን ሰብስበው "ይኽን የያሬድ ዜማ ተቀበሉትና ለቅድስት ቤተክርስትያን መገልገያ ይኹን" ባሉ ጊዜ ካህናትና ሊቃውንቱ "ምን ምልክት ዐይተን እንቀበለው? እንደሐዋርያት እጅና እግሩን ለተሳለ ቀኖት (ችንካር)፤ አፉን ለመረረ ሐሞት ሰጥቶ አላየነው?!" ብለው ሲመልሱላቸው ዐፄ ገብረ መስቀልም "እንግዲያውስ አንድ ሱባዔ እንያዝና እርሱ አምላካችን ይግለፅልን!" ብለው ሱባዔ ያዙ።
❤ ካህናት እና ሊቃውንት በታኅሣሥ ወር ከሰኞ እስከ እሑድ አንድ ሱባዔ ይዘው የአክሱም ጽዮን ማርያምን ቤተክርስቲያን እየዞሩ አራት መቶ እግዚኦታ እና አርባ አንድ በእንተማርያም እያደረሱ ምሕላውን አከናወኑ።
❤ በሰባተኛው ቀን በዕለተ እሑድ ልመናቸውን ጨርሰው ሲያሳርጉ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዐርብ እንደተሰቀለ ኾኖ ስለካህኑ ቅዱስ ያሬድ ዜማ ሰማያዊነት ሊመሰክር በጽዮን ማርያም ቤተክርስቲያን ጉልላት ላይ ተገለፀ።
❤ አባታችን ቅዱስ ያሬድም ይኽንን አስመልክቶ ፦
❤ "ዘበመስቀሉ ተቀነወ ወበነቢያት ተሰብከ መላእክት ወሊቃነ መላእክት ሰብሕዎ ኪያሁ ንሰብክ መድኅነ"። ትርጉም፦ በነቢያት ትንቢት የተነገረለትና በመስቀሉ ላይ የተቸነከረው ጌታ መላእክት እና የመላእክት አለቆች አመሰገኑት፤ እኛም እርሱ መድኃኒት እንደኾነ እንናገራለን።
❤ ቀኑም ቅዱስ ያሬድ ሰማያዊውን ዜማ ማስተማር የጀመረበት ፥ የነቢያት "ይወርዳል - ይወለዳል" ትንቢት የተፈጸመበት መኾኑን ለማጠየቅ "ስብከት" ተባለ።
+ በዚያችም ቀን ቅዱስ ያሬድ ከሰማይ የተቀበለው ዜማ ወደቤተክርስቲያን ገባ - የቤተክርስቲያን ብርሃኗ በራ!
❤ "የመላእክትን እንጀራ የሰው ልጅ በላ፥ ለኢትዮጵያ ሰዎችም ምግባቸውን ሰጠኻቸው" የተባለው የቅዱስ ዳዊት የትንቢት ቃል ተፈጸመ ምንኛ ይደንቅ!። ምንጭ፦ የቤተክርስቲያን ብርሃን ቅዱስ ያሬድ (ታደሰ ዓለማየሁ)።
+ + +
❤ "ሰላም ለአባ ዳንኤል ፍጹም መነኰስ ውርዝው በመንፈስ ዘተሐበዮ ለአውላኪስ"። ትርጉም ለአውላክሲስ (አውሎጊስን) የተዋሰው በመንፈስ የጐለመለ ለኾነ ለፍጹም መነኰስ ለአባ ዳንኤል ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በሰዓታቱ ላይ።
+ + +
❤ አባ ዳንኤል፦ ይህም አባት በአባ መቃርስ ገዳም በደብረ ሲሐት የሚኖር ነው። አባ ዳንኤልም ስሟን እንጣልዮስ አሰኝታ የነበረች ንግሥት በጥሪቃን የገነዛት ነው እርሷም ከሞቷ በኋላ እንጂ ሴት እንደሆች አልታወቀችም ነበር።
❤ በአንዲት ቀንም ወደ እስክንድርያ አገር ከረድኡ ጋር ሲጓዝ ስሙ ምህርካ የሚባል እብድ አገኘ ብዙ እብዶችም ይከተሉታል ለአገሩ ሰዎችም በእውነት ያበደ ይመስላቸው ነበር አባ ዳንኤልም እጁን ይዞ ወደ ሊቀ ጳጳሳቱ ወስዶ ትሩፋቱን ተጋድሎውን ነገረው እንዲነግራቸውም በአማሉት ጊዜ ከዝሙት ጦር ለመሸሽ ራሱን እብድ እንዳስመሰለ ነገራቸው ሰምተውም እግዚአብሔርን አመሰገኑት።
❤ በአንዲትም ዕለት ወደ አንዲት አገር ደረሰ በዚያም አውሎጊስ የሚባል ለድኆች የሚራራ እንግዳም የሚቀበል ደንጊያ በመውቀር የሚኖር ሰው አገኘ እርሱንም ተቀብሎ በደስታ አሳደረው መልካም ሥራውንም በአየ ጊዜ ድኆችን የሚረዳበት ገንዘብን ለአውሎጊስ ይሰጠው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ስለርሱ ለመነ ጌታችንም በሕፃን አምሳል ተገለጠለትና "ገንዘብ ባገኘ ጊዜ ጣባዩን እንዳይለውጥ አንተ ትዋሰዋለህን?" አለው አባ ዳንኤልም "አዎን እዋስዋለሁ" አለ።
❤ ከዚህም በኋላ አውሎጊስ በድስት የመላ ወርቅን አግኝቶ ያንን ይዞ ወደ ንጉሥ ሔዶ የጭፍራ አለቃ ሆኖ ተሾመ ጠባዩንም ለወጠ። ጠባዩንም እንደለወጠ አባ ዳንኤል ሰምቶ ልመክረውና ሊገሥጸው ሔደ የአውሎጊስ ወታደሮች ለሞት እስኪደርስ ድረስ ደበደቡት በዚያም እያዘነ ሳለ ያ ሕፃን ታየው አባ ዳንኤልንም "ለምን በሌላ ሰው ነገር ገባህ" ብሎ እንዲሰቅሉት አዘዘ። ከዚህም በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መጥታ ለሕፃኑ ሰገደች እግሮቹንም እየሳመች ስለ አባ ዳንኤል ለምና ከስቅላት አዳነችው።
❤ ከዚህም በኋላ ሌላ ንጉሥ በነገሠ ጊዜ አውሎጊስ ሊገለው ፈለገው ያን ጊዜ አውሎጊስ ሸሸ ወደ አገሩም ደርሶ ወደ ቀድሞ ሥራው ተመለሰ። በአንዲት ቀንም በሌሊት በበረሃ በጨረቃ ብርሃን ሲጓዝ በተራራ ላይ ተቀምጣ ሴት አገኘ ጠጉሯም ሥጋዋን ሁሉ ሸፍኖአል እየተጋደለች ሠላሳ ስምንት ዓመት የኖረች ናተ ምጢርዋንም ሁሉ ነግራው ከዚህ በኋላ ዐረፈች።
❤ ከዚህም በኋላ በአንዲት ቀን የሊዮን ደብዳቤ ሰውዎች አምጥው በሕዝብ ፊት አነበቧት አባ ዳንኤልም ዘሎ ቀደዳትና "የኬልቄዶን ሃይማኖት የተወገዘ ነው" አለ ወታደሮችም አይተው ደብድቡት ከገዳሙም አሳደዱት።
❤ በአንዲት ቀንም አባ ዳንኤል ከደናግል ገዳም ደርሶ ደጁን አንኳኳ አባ ዳንኤልም እንደሆነ አውቀው ከፈቱለትና በደስታ ተቀበሉ። ከእነርሱም አንዲቷ እራሷን እብድ አስመስላ በደጅ የምትተኛ አለች ስለ እርሷም እመ ምኔቷን ጠየቃት እርሷም "እብድ ናት" አለችው። እርሱም መስተጋድል ቅድስት ሴት እንጂ እብድ እንዳልሆነች ነገራት። እብድ የተባለችውም በሌሊትም ተነሥታ "የከበራችሁ እህቶቼ ስለ አሳዛንኳችሁ ይቅል በሉኝ" ብላ ጽፋ ያንን ትታ ታጣች ደናግሎም እጅግ አዘኑ ተጸጸቱም።
❤ በውስጡ ብዙ ደናግል የሚኖሩበት ገዳም ነበር መዝጊያውም የጸና ነው። ገንዘባቸውን ይበረብሩ ዘንድ ሰይጣን ወንበዴዎችን በላያቸው አስነሣ የወንበዴዎችም አለቃ በመራቀቅ በራሱ ላይ ቆብ አድርጎ በአባ ዳንኤል ለብሶ ደጃፋቸውን ሔዶ በማንኳኳት "አባ ዳንኤል ነኝ" አለ አይተውም ከፈቱለት በደስታም ተቀበሉት እግሩንም አጠቡትና ስለ በረከት የእግሮቹንም እጣቢ በየፊታቸው እረጩ ከውስጣቸው አንዲት ዕውር ነበረች ውኃው ሲነካት አይኖቿ በሩላት ደናግሉም "አንተ አባ ዳንኤል ንዑድ ክቡሩ ነህ" አሉት የሽፍቶች አለቃ አይቶ ተጸጸተም ከአባ ዳንኤል ዘንድ መንኲሶ የሚጋደል ሆነ።
❤ ዕረፍቱም በቀረበ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ነገረው ጥቂት ጊዜም ታመመ ክብር ይግባውና ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጸለየና ታኅሣሥ 7 ቀን በሰላም ዐረፈ። እግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ዳንኤል ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
1 161
ታህሳስ 6
ቅድስት አርሴማ(ቅዳሴ ቤቷ)
✝እናታችን ቅድስት አርሴማን በምን እንመስላታለን? እርሷ በአድማስ ላይ ተቀምጦ እንደሚያበራ እንቁ ናትና ክብሯ ብዙ ነው።
✝መድኃኒታችን ክርስቶስ በወንጌል እንዳለው "በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሠወር አይቻላትምና።"(ማቴ. ፭፥፲፩) የሰማዕቷ ሕይወት በፊታችን እንደ ብርሃን ተገልጦ ይታያል። ቅድስት አርሴማ እንደ ልጅ ወላጆቿን በመታዘዝ ደስ ያሰኘች ቡርክት ናት። ቅድስት አርሴማ ይህ ቀረሽ የማይሏት ውብ ናት።
ቅድስት አርሴማ ድንግል ናት። ቅድስት አርሴማ ባሕታዊት ጻድቅ ናት። ቅድስት አርሴማ ኃያል ሰማዕት ናት። ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ፦ አበው በትውፊት እንደ ነገሩን ቅዱሱ ጐርጐርዮስ የታላቋ ሰማዕት ቅድስት አርሴማ ትልቅ ወንድም ነው። በዜና ሰማዕታት ተጽፎ እንደሚገኘው በዚያ የመከራ ዘመን ቅዱስ ጐርጐርዮስ ሦስት ኃላፊነቶች ነበሩበት፦ ፩.ቅድስት አርሴማን ጨምሮ ደናግሉን ማጽናት ፪.ትምሕርተ ቤተ ክርስቲያንን በሚገባ ማጥናት ፫.የሚመጣውን መከራ ለመቀበል ራሱን ማዘጋጀት። ቅዱሱ ሦስቱንም ኃላፊነቶች በሚገባ በመወጣቱ ከራሱ አልፎ ለሌሎቹ አርአያ መሆን ቻለ። ያቺን ንጽሕት አርበኛ ቅድስት አርሴማንም አጽንቶ የደናግሉ መሪ አደረጋት።
✝መከራው ገፍቶ እስከ መጣበት ጊዜ በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ ሆነው ይጸልዩ፣ ይጾሙ፣ ገዳማዊ ሥራንም ይሠሩ ነበር። ለዚህም ነው ቅድስት አርሴማና ቅዱስ ጐርጐርዮስን ጻድቃን የምንላቸው። በኋላ ግን ማኅደረ ሰይጣን ዲዮቅልጢያኖስ በመልኳ ተማርኮ ቅድስት አርሴማን ካላገባሁ በማለቱ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ድንግሏን አርሴማን ጨምሮ ክርስቲያኖችን ይዞ ወደ አርማንያ ተሰደደ። በአርማንያም በአንድ ገዳም ውስጥ ተደብቀው በጾምና በጸሎት ለጥቂት ጊዜ ቆዩ። ነገር ግን ረሃብ ፈጃቸው። የሚላስ የሚቀመስ ነገር በአካባቢው ባለ መኖሩ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ወደ ከተማ ለመውጣት ተገደደ። በዚያም በድርጣድስ ቤተ መንግሥት ውስጥ ባርነት ተቀጠረ። በሚያገኛት ገንዘብም ወገኖቹን ይረዳ ነበር። መከራው ግን አለቀቃቸውም።
ርጉም ዲዮቅልጢያኖስ ቅዱሳኑ ወደ አርማንያ መሔዳቸውን ስለ ሰማ ይዞ እንዲልክለት ድርጣድስን ላከው። ድርጣድስ ግን ቅድስት አርሴማን ባያት ጊዜ ከውበቷ የተነሳ መታገስ ባለመቻሉ "ካላገባሁሽ" አላት። ድንግሊቱ ግን "እኔ የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ፤ አይሆንም።" አለችው። ሊያስፈራራት ሞከረ። ዓይኗ እያየ ደናግሉን ጨፈጨፋቸው። አልሳካልህ ቢለው በአደባባይ በግድ ሊያገባት ቢሞክር እጁን ጠምዝዛ በሰው ሁሉ ፊት መሬት ላይ ጣለችው። እጅግ ስላፈረ አስገረፋት፣ አሰቃያት፣ ዓይኗንም አወጣ። በመጨረሻም አንገቷን አስቆርጦ ከሰማዕታቱ ጋር ተራራ ላይ ጣላት። ከነገር ሁሉ በኋላ ድርጣድስና ባለሟሎቹ ለአደን በሔዱበት ርኩስ መንፈስ ወደ አውሬነት (እሪያነት) ቀየራቸው።
✝የንጉሡ እንስሳ (አውሬ) መሆን በአርማንያ ታላቅ ድንጋጤን ፈጠረ። የንጉሡ እኅት ስታለቅስ በራእይ "ለእመ ኢያዕረግምዎ ለጐርጐርዮስ አልብክሙ ድኂን - ጐርጐርዮስን ከተቀበረበት ካላወጣችሁት አትድኑም።" አላቸው። ወዲያውም ቆፍረው አወጡት። ቅዱሱ እንደ ወጣ ዕረፍትን አልፈለገም።
ለአሥራ አምስት ዓመታት ቀባሪ አጥቶ የተበተነውን የቅድስት አርሴማንና የሰማዕታቱን አጽም ሰብስቦ በክብር አኖረው። ድርጣድስና ባለሟሎቹንም ወደ በርሃ ሒዶ ፈወሳቸው። የሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ አጽም በአሥራ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከሌሎች ሰማዕታት አጽም ጋር ኢትዮጵያ እንደ መጣ አባቶቻችን በትውፊት ነግረውናል። ለዚህም ነው ቡርክቷ እናታችን ከሌሎች ሃገራት ለይታ ለኢትዮጵያውያን ልዩ ፍቅር ያላት።
✝በዋናው ገዳሟ (ወሎ /ኩላማሶ/ ስባ ውስጥ የሚገኝ ነው።) ጨምሮ ስሟ በተጠራበት ሁሉ ኃይልን ታደርጋለችና። ነገር ግን ወንድሞቼና እኅቶቼ በቅድስቷ እናታችን ስም የሚነግዱ ሥጋውያን ሰዎች በዝተዋልና እንጠንቀቅ። የሰማዕቷ ክብር ብዙ ነውና በሕልም ላይ ብቻ አንታመን። አባ እንጦንስ እንዳሉት "በሕልሙ የሚታመን ሰው ከንቱ ነውና።" (መዝ. ፸፭፥፭) በዚህ ዕለት ከሰማዕቷ ጋር የመንፈስ እናቷን ቅድስት አጋታን ልናስባት ይገባናል። ይህች እናት እመ ምኔት ስትሆን ቅድስት አርሴማን ታስተምራት፣ ታጸናት፣ ከጐኗም ትቆምላት ነበር።
✝ ረሃቧን፣ ጥሟን፣ ስደቷን፣ መከራዋንም ሁሉ አብራት ተሳትፋለች። በፍጻሜውም አብራት ተሰይፋለች። ይህች ዕለት ለቅድስት አርሴማና ለተከታዮቿ ሰማዕታት የፍልሰትና የቅዳሴ ቤት መታሰቢያ ናት።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ለወዳጅዎ ያጋሩ
💚 @EOTCW 💚
https://t.me/Eotcw
1 161
🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
ሥርዓተ ማኅሌት ዘታኅሣሥ ቅድስት አርሴማ "ታኅሣሥ ፮
🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ (ሥርዓተ ነግሥ)
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገአርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።
መልክአ ሥላሴ
ሰላም ለአብ ገባሬ ኩሉ ዓለም ለወልድሰላም
ወለመንፈስ ቅዱስ ሰላም ለማርያም ሰላም
ወለመላእክት ሰላም ሰላም ለነቢያት
ወለሐዋርያት ሰላም ለሰማዕታት ሰላም
ወለጻድቃን ሰላም፡፡
ዚቅ
ሃሌሉያ ለአብ ሃሌሉያ ለወልድ ሃሌሉያ
ወለመንፈስ ቅዱስ ንዜኑ ሂሩተ ዘአርሴማ
ትዕግስት በእንተ ጽድቅ ዘኮነ ሰማዕተ አፍርሃ
ኲናተ ወአስይፍተ በስሒተ ወረሰ በገድሉ ዘሰማይ
መንግስት።
ዘመንክር ጣዕሙ
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ
ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤መሠረተ ሕይወት
ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤
ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤
እግዚአብሔርይ ትባረክ ወይትአኮት ስሙ፡፡
ዚቅ
ጻድቃን ይበውዑ ውስቴታ የዋሃን የዓውዱ
መሠረታ ሰማዕት ይቀውሙ ዓውደ በዕለተ
አርሴማ ስብሐት የዓውዳ ለቅድስት
ቤተክርስቲያን።
መልክአ አርሴማ
ሰላም ለዝክረ ስምኪ በስንዱነ ኪዳን ጥብሉል
ወለስእርትኪ ሰላም ዘፅርየት ኀብሩ ፅዱል
ስርጉተ ትዕግስት አርሴማ ወዑፅፍተ ሐዲስ
ገድል ይጽሐፍ በልሳንየ ወበዘእንቲአየ ቃል መፆረ ትርጓሜ ረቂቅ ኃይልኪ ፊደል።
ዚቅ
ዕግትዋ ለአርሴማ ወሐቀፍዋ ወተናገሩ በውስተ
ማኅፈዲሃ ሃሌሉያ ሃሌሉያ ሃሌሉያ ነቢያት
አቅርንቲሃ ወሐዋርያት መኃትዊሃ ማህበረ ቅዱሳን ወሰማዕት ቅድሜሃ ወድኅሬሃ።
ወረብ
ዕግትዋለአርሴማ ወሐቀፍዋወተናገሩበውስተ
ማህፈዲሃ/፪/
ነቢያትአቅርንቲሃወሐዋርያትመኃትዊሃማህበረ
ቅዱሳንወሰማዕት/፪/
መልክአ አርሴማ/መልክአ ማርያም
ሰላም ለእራኀትኪ ሐብተ ጸጋዉሀብ፤
ወከአፃብእኪ ዘኮና መሀትወጥበብ፤
ትምክህተ ቅዱሳን አርሴማ ወዘሰማዕታት መክብብ፤ ከመ እኪድ አራዊተ ወአርእስተ ኩሉ
አቅረብ፤ ፈንዊ ሊተ ስልጣን ዘአብ።
ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሉያ ቤተክርስትያን መርሐቱ ለአልፋ
ታቦቱ አሐትዊሃ ፯ቱከዋክብቲሃ ሰማዕታት
እሙንቱ።
ወረብ
ዓይ ይእቲ ዛቲ እንተ አሠሥዋ ነቢያት ሐመረ
ብርሃን ወዖድዋ አመ አመአይኅ/፪/
ይቤሎ ለየኀ ግበር ታቦተ በዘትድኅን ባቲ
እትአመን እስመ አርአያ መስቀል ይእቲ/፪/
መልክአ አርሴማ
ሰላም ለአብራክኪ ምኩራበ ፀሎት ወሰጊድ
ዘይትስሃን ቦቱ ነሶሳ ወእግር ወእድ ቤተክርስቲያናዊት አርሴማ ኀርምተ ኑፋቄ
ወካህድ አመ እቀምስ ስቃየ እምነ እልዋን
ዐውድ አድለቅለቀት ምድር እምግርማ መብረቅ
ወነጎድጓድ ወቀስተደመናተ ተክለ አምሳለ
ለዓምድ።
ዚቅ
ክቡራትዕንቊ መሠረታ ግብተ
በረሀ ገዳ እምፀሐይ መስቀለ ክርስቶስ
መሠረታ ለቅሰድስት ቤተክርስቲያን ሃሌ ሉያ
ሃሌ ሉያ ሃሌሉያ ይጥዕመኒ ስማ
ወረብ
ኪዳንኪ ኮነ ኪዳንኪ ኮነ ኪዳንኪ ኮነ/፪/
ለኃጥአን ቤዛነ ኪዳንኪ ኮነ ለኃጥአን ቤዛነ
ኪዳንኪ ኮነ/፪/
መልክአ አርሴማ
ሰላም ለፍልሰተ ስጋኪ በቃለ ፈጣሪ ዘተቀደሰ
ወንብረተ ዝንቱ ዓለም እንተ ኢኀሰሰ አርሴማ
ብፅዕት ከመ ኢይርአይ ተፅናሰ ሴስየኒ
እመዝገብኪ አምጣነ ኢይክል ሐሪሰ ወእስእለኪ
ተሀብኒ ሐፍሰ።
ዚቅ
ኦ ብእሲቶ ዓቢይ ሐይማኖትኪ ይኩንኪ
በከመ ተአመንኪ በጽድቅ እስመ በእንተ ክርስቶስ
ወጠንኪ አጥባዕኪ ወኢናፈቂ ወገብርኪ ፈቃደ ልዑል ከመ ትባዒ ሀገረ እንተ ኬንያሃ ወሃናጺሃ ወልደ እግዚአብሔር::
ወረብ
አርሴማ ሰማዕት ስርጉት በሃይማኖት
ወበመንፈስ ቅዱስ ክልልት/፪/
ከመ ቂርቆስ ሕፃን ኢያፍርሃ ነበልባለ እሳት/፪/
ምልጣን
ብፅዕት ከርስ እንተ ፆረተኪ ወብፁዓት አጥባዕት
እለ ሕፀናኪ አርሴማ ሰማዕት ዘፍጹም
ድንግልናኪ አማን ምስራቀ ፀሃይት ዌድሰኪ።
ወረብ ዘአንገርጋሪ
ብፅዕት ከርስ እንተ ፆረተኪ ወብፁዓት አጥባዕት
እለሕፀናኪ ተክዕወ ሞገስ እምከናፍርኪ/፪/
ወበእንላዝ ደናግል አፍቀራኪ አፍቀራኪ አርሴማ
ሰማዕት/፪/
እስመ ለዓለም
አዋልደ ንግስት ለክብርከ ወትቀውም ንግስት
በየማንከ በአልባሰ ወርቅ ዑፅፍት ወኁብርት
ደናግል አፍቀረከ ወተለዋ ድህሬከ በእንተ መዓዛ
ዕፍረትከ ፤ጸ፤ እለ ጸዉዖን ንጉሥ ውስተ ጽርሑ ከመ ይባዓ ውስተ ፍሰሐሁ ፤ጸ፤ ወበእለቦአ ምስሌሁ ወበእለይቤላሁ እግዚአ እግዚኦ አርኀወነ ፤ጸ፤ ሐምስ እምኔሆን አብደት ወሐምስ ጠባባት ፤ጸ፤ ዳዊትኒ ይቤ በጽሑ መላእክት ወቦሙ መዘምራን ማዕከለ ደናግል ዘባጥያተ ከበሮ፡፡
ዓዲ(ወይም)እስመ ለዓለም
ለዛቲብእሲት......በል
ሰላም
ማህደረ ሰላምነ ቅድስት ደብተራ እሞሙ
ለሠማእት ወእኅቶሙ ለመላእክት ንዑን ስግድ
ኩልነ ኃበ ማርያም እምነ።
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዕለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ማቴ. 17፥14-24 "ወበጺሖሙ ኀበ ሕዝብ" -"ወደ፡ሕዝቡም፡ሲደርሱ፡አንድ፡ሰው፡ወደ፡ርሱ፡ቀረበና፡ተንበርክኮ፦ጌታ፡ሆይ፥ልጄን፡ማርልኝ፥በጨረቃ፡እየተነሣበት፡ክፉኛ፡ይሣቀያልና፤ ብዙ፡ጊዜ፡በእሳት፡ብዙ፡ጊዜም፡በውሃ፡ይወድቃልና። ወደ፡ደቀ፡መዛሙርትህም፡አመጣሁት፡ሊፈውሱትም፡አቃታቸው፡አለው። ኢየሱስም፡መልሶ፦የማታምን፡ጠማማ፡ትውልድ፡ሆይ፥እስከ፡መቼ፡ከእናንተ፡ጋራ፡እኖራለሁ? እስከ፡መቼስ፡እታገሣችኋለሁ? ወደዚህ፡ወደ፡እኔ፡አምጡት፡አለ። ኢየሱስም፡ገሠጸው፡ጋኔኑም፡ከእርሱ፡ወጣ፥ብላቴናውም፡ከዚያች፡ሰዓት፡ጀምሮ፡ተፈወሰ። ከዚህ፡በኋላ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ብቻቸውን፡ወደ፡ኢየሱስ፡ቀረቡና፦እኛ፡ልናወጣው፡ያልቻልን፡ስለ፡
ምን፡ነው? አሉት። ኢየሱስም፦ስለእምነታችሁ፡ማነስ፡ነው፤እውነት፡እላችኋለሁ፥የሰናፍጭ፡ቅንጣት፡የሚያኽል፡እምነት፡ቢኖራችሁ፥ይህን፡ተራራ፦ከዚህ፡ወደዚያ፡ዕለፍ፡ብትሉት፡ያልፋል፤የሚሳናችሁም፡ነገር፡የለም። ይህ፡ዐይነት፡ግን፡ከጸሎትና፡ከጦም፡በቀር፡አይወጣም፡አላቸው። በገሊላም፡ሲመላለሱ፥ኢየሱስ፦የሰው፡ልጅ፡በሰዎች፡እጅ፡ዐልፎ፡ይሰጥ፡ዘንድ፡አለው፥ይገድሉትማል፥ በሦስተኛውም፡ቀን፡ይነሣል፡አላቸው።እጅግም፡ዐዘኑ። ወደ፡ቅፍርናሖምም፡በመጡ፡ጊዜ፡ግብር፡የሚቀበሉ፡ሰዎች፡ወደ፡ጴጥሮስ፡ቀረቡና፦መምህራችሁ፡ሁለቱን፡ዲናር፡አይገብርምን? አሉት።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
1 161
06/04/2015 ዓ.ም (፮/፬/፳፻፲፭ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ወለእመኒ ፈለሱ አድባር ውስተ ልበ ባሕር።
ደምፁ ወተሐምጉ ማያቲሆሙ።
ወአድለቅለቁ አድባር እምኃይሉ፡፡ መዝ. 45፥2
🕯 ትርጉም
ተራራዎችም ወደባሕር ልብ ቢወሰዱ፥ አንፈራም።
ውሃዎቻቸው ጮኹ፤ ተናወጡም።
ተራራዎችም ከኃይሉ የተነሣ ተናወጡ።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዕለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ማቴ. 5፥39-ፍ፡ም፡ "ወአንሰ እብለክሙ" - "እኔ፡ግን፡እላችኋለሁ፥ክፉውን፡አትቃወሙ፤ዳሩ፡ግን፡ቀኝ፡ጕንጭህን፡በጥፊ፡ለሚመታህ፡ሁሉ፡ሁለተኛውን፡ደግሞ፡አዙርለት፤ እንዲከስህም፡እጀ፡ጠባብህንም፡እንዲወስድ፡ለሚወድ፡መጐናጸፊያህን፡ደግሞ፡ተውለት፤ ማንም፡ሰው፡አንድ፡ምዕራፍ፡ትሄድ፡ዘንድ፡ቢያስገድድህ፡ሁለተኛውን፡ከእርሱ፡ጋራ፡ሂድ። ለሚለምንህ፡ስጥ፥ከአንተም፡ይበደር፡ዘንድ፡ከሚወደ፟ው፡ፈቀቅ፡አትበል። ባልንጀራህን፡ውደድ፡ጠላትህንም፡ጥላ፡እንደ፡ተባለ፡ሰምታችኋል። እኔ፡ግን፡እላችኋለሁ፥በሰማያት፡ላለ፡አባታችሁ፡ልጆች፡ትሆኑ፡ዘንድ፡ጠላቶቻችሁን፡ውደዱ፥የሚረግሟችሁንም፡መርቁ፥ለሚጠሏችሁም፡መልካም፡አድርጉ፥ስለሚያሳድዷችሁም፡ጸልዩ፤እርሱ፡
በክፉዎችና፡በበጎዎች፡ላይ፡ፀሓይን፡ያወጣልና፥በጻድቃንና፡በኀጢአተኛዎችም፡ላይ፡ዝናቡን፡ያዘንባልና። የሚወዷ፟ችሁን፡ብትወዱ፡ምን፡ዋጋ፡አላችሁ? ቀራጮችስ፡ያንኑ፡ያደርጉ፡የለምን? ወንድሞቻችሁንም፡ብቻ፡እጅ፡ብትነሡ፡ምን፡ብልጫ፡ታደርጋላችሁ? አሕዛብስ፡ያንኑ፡ያደርጉ፡
የለምን? እንግዲህ፡የሰማዩ፡አባታችሁ፡ፍጹም፡እንደ፡ሆነ፡እናንተ፡ፍጹማን፡ሁኑ።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
1 161
6/4/2015 ዓ.ም (፮/፬/፳፻፲፭ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ይኄይስ ሕዳጥ ዘበጽድቅ።
እምብዙኅ ብዕለ ኃጥአን።።
እስመ ይትቀጥቀጥ ኃይሎሙ ለኃጥአን። መዝ 36፥16
🕯 ትርጉም
ለጻድቅ ያለው ጥቂት፤
ከብዙ ከኀጢአተኛዎች ሀብት ይበልጣል።
የኃጥኣን ክንድ ትሰበራለችና።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ "ሰላም ለአርሴማ ቅድስት ከመ በቀልት ዘይመስል ቆማ፤ ወዘከለላ ዘመንፈስ ግርማ ዘፈጽመት ገድላ በጻማ ወበመንግሥተ ሰማይ ዐቢይ ስማ"። ትርጉም፦ ገድሏን በሥቃይ የፈጸመች፤ የመንፈስ ግርማ የጋረዳትና ቁመቷ እንደ ዘንባባ የሚመስል ለምትኾን ለቅድስት አርሴማ ሰላምታ ይገባል፤ በመንግሥተ ሰማይም ስሟ ታላቅ ነው። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።
+ + +
❤ "ሰላም ለዘእረፉ ምስሌኪ ፳ወ፯ ሰማዕታት። ምስሌኪ ረድኤቶሙ ትረድ ላዕሌየ ዘምስለ ብዙኃ ምሕረት። ወኅበ ኀለወ ስሞሙ ምስ ስምኪ ቅድስት። አዲ ኢይቅረበ አርሴማ እማመ ብድብድ ወሞት። በኵሉ አዝማን ወበኵሉ ዓመታት"። ትርጉም፦ ከአንቺ ጋር ለአረፉ ለሃያ ሰባቱ ሰማዕታት ሰላምታ ይገባል። ከብዙ ይቅርታ ጋር እና ቅድስት ከምትሆን ስምሽም ጋር ስማቸው ወደ አለበት ቦታ ረድኤታቸው በኔ ላይ ትወርድ ዘንድ ቅድስት አርሴማ ሆይ በሁሉ ዘመንና በሁሉ ዓመታት የሞትና የሕማም በሽታ ዳግመኛ አይቅረብ። መልክአ ቅድስት አርሴማ።
https://t.me/Eotcw
1 161
ወገኖችእንድትረዳችሁ ይሁን። እኔንም ለማን እንዳትገልጠኝ እለምንሃለሁ እኔ የዚህ ዓለም ክብር መሸከም አልችልምና ነገር ግን የምልህን አድርግ አንተም ንጉሡ ይነሣልኝ የሚልህ ተራራ ትይዩ ካህናቶችና ከሕዝቡ ጋር ቁም ወንጌሎችን፣ መስቀሎችን፣ ማዕጠንቶችን፣ የሰም መብራቶችን ያዙ ንጉሡም ከነሠራዊቱ በአንዲት ዳርቻ ይቁም እኔም ማንም እንዳውቀኝ ከሕዝቡ ጋር ተደባልቄ በፊትህ እቆማለሁ አርባ አንድ ጊዜ ኪራላይሶን እያላችሁ በመጮህ ወደ እግዚአብሔር ማልዱ ይኸውም አቤቱ ክርስቶስ ማረን ራራል ይቅር በለን ማለት ነው። ከዚህም በኋላ ሕዝቡን ዝም እንዲሉ እዘዛቸው እኔም ያንጊዜ ስሰግድ አንተም ስገድ እንዲህም ሦስት ጊዜ አድርገህ በዚህ ተራራ አንጻር ማሕያዊ መስቀል ምልክት በየስግደትህ አማትብ" አለው።
❤ ሊቀ ጳጳሳቱ ይህ ሰምቶ ለወገኖቹ በማሰማት አስገነዘባቸው በዚህም ተራራ በሌላ ገጽ ከሠራዊቱ ጋር ወጥቶ እንዲቆም ለንጉሡ ነገረው ሊቀ ጳጳሳቱ እንደነገራቸው ሁሉም ወጥተው ቆሙ ከዚህ በኋላ ሊጸልዩ ጀመሩ አርባ አንድ ጊዜ አቤቱ ክርስቶስ ማረን አሉ ከዚህም በኋላ ሊቀ ጳጳሳቱ ሦስት ጊዜ ሰገደ ሲነሳም ወደዚያ ተራራ አማተበ በዚያ ጊዜ ተራራ ከቦታው ተነቅሎ በአየር ላይ ተንሳፈፈ ሊቀ ጳጳሳቱ ሕዝቡ ሲሰግዱ ያ ተራራ ወደ ቦታው ይወርዳል ከሰገዱበትም ሲነሱ ከቦታው ተነቅሎ ወደ አየር ወጥቶ ይንሳፈፍል እንዲህም ሦስት ጊዜ አደረገ ሕዝሙ ሁሉ ይህ ድንቅ ሥራ አይተው አደነቁ ምስጉን እግዚአብሔርን አመሰገኑት ሊቀ ጳጳሳቱ አባ አብርሃምንም ፈሩት ንጉሡሙ ወደ ርሱ አስቀርቦ ታላቅ ክብር አከበረው እንህም አለው "የምትሻው ለምነኝ ከእኔ ተመኝ ምን ምንም አልከለክልህም" ንጉሡም ሊቀ ጳጳሳቱ ግድ ለምነኝ በለው ጊዜ "አብያተ ክርስቲያን ልሠራ እሻለሁ ይልቁን የሰማዕቱን ቅዱስ መርቆሬዎስን ቤተ ክርስቲያን በምስር አገር ልሰራ እሻለሁ" አለው። እንደወደደውም ይሰራ ዘንድ አዘዘለት ከቤተ መንግሥቱም ብዙ ገንዘብን አቀረበለት ሊቀ ጳጳሳት አባ አብርሃምም "በምድር ላይ እግዚአብሔር እድሜህን ያርዝም መንግሥትህ ያጽና እኔ ገንዘብ አልሻም" አለው። ይህንንም በአለው ጊዜ ንጉሥ አደነቀ የዚህን ዓለም ገንዘብ መናቁን እጅግ ወደደው።
❤ ከዚህም በኋላ የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያን ሥራዋ እስኪፈጸም ሌሎችም በግቡጽ አገር የተሰሩ ብዙዎች አብያተ ክርስቲያኖች እስቲሠሩ ንጉሡ በፈረስ ተቀምጦ ከሠራቱ ጋር በመሆን ከሊቀ ጳጳሳቱ ጋር አብሮ ለሥራ ይሰለፍ ነበር የሚቃወሙ ክፉዎች ሰዎች የተሠራውንም ያፈርሱ ዘንድ የሚሹ ስለነበር ስለዚህ ንጉሥ አጽንቶ አስጠበቀ። ተጋድሎውንም በፈጸመ ጊዜ እግዚአብሔርም አገልግሎ በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ስድስት ዓመት ከስድስት ወር ከኖረ በኋላ በዚች ቀን ታኅሣሥ6 ዐረፈ። በዚህም አባት በገድሉ መጽሐፍ ያ ስለ ዕቊባቶቹ ያወገዘው ጸሐፊ በመርዝ ገደለው የሚል አለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት በአባ አብርሃም ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 6 ሰንክሳር።
+ + +
❤ "ሰላም ለከ ለአብርሃም ነጋዲ። ወሊቀ ጳጳሳት ዓዲ። ሶበ ዐጸወ ቅድሜከ በግዝፈተ ልብ አባዲ። ሰምዖ ቃለ ግዘት እምልሳንከ ነዳዲ። መድረከ ኆኅቱ ተሠጥቀ ለብእሲ ከሀዲ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ6።
+ + +
❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ይኄይስ ሕጻጥ ዘበጽድቅ። እምብዙኅ ብዕለ ኃጥአን። እስመ ይትቀጥቀጥ ኃይሎሙ ለኃጥአን"። መዝ36፥16-17። የሚነበበው ወንጌል ማቴ5፥34-ፍ.ም።
+ + +
❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ወእለመኒ ፈለሱ አድባር ውስተ ልበ ባሕር። ደምፀ ወተሐምጉ ማያቲሆሙ። ወአድለቅለቁ አድባር እምኃይሉ"። መዝ 45፥2-3። የሚነበቡት መልዕክታት ገላ 4፥12-21፣ 1ኛ ጴጥ 5፥2-9 እና የሐዋ ሥራ 5፥1-11። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 17፥14-24። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅድስት አርሴማ በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ታኅሣሥ ፮ (6) ቀን።
❤ እንኳን ለታላቁ አባት ተራራ ላፈለሰ ለእስክንድርያው ስልሳ ሁለተኛ ሊቀ ጳጳስ ለአቡነ አብርሃም ሶርያዊ ለዕረፍት በዓል፣ ከእርሱ ጋር ተራራን አብሮ ላፈለሰው ለቅዱስ ስምዖን ጫማ ሰፊ ለመታሰቢያ በዓሉ፣ ለታላቋ ሰማዕት ለቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያኗ ለከበረችበትና ለሥጋዋ ፍልሰት መታሰቢያ ዓመታዊ በዓል፣ ከእርሷ ጋር ለተገደሉ ሃያ ሰባት ደናግል ለሥጋቸው ፍልሰትና በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቀሲስ ሰማዕት ከቅዱስ እንጣልዮስ፣ ከቅዱሳን አረሚ ከነበረ ከኤልያስ፣ ከበጥልስ፣ ከሱርፍት፣ ከማርያ፣ ከሚካኤል፣ ከይልሰውል፣ ከተለሜዎስ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ በዚችም ቀን የድንግሊቱ አርሴማ ቤተ ክርስቲያኗ የከበረችበትና የሥጋዋ ፍልሰት የሆነበት ከእርሷ ጋር የተገደሉ የሃያ ሰባት ደናግልም የሥጋቸው ፍልሰት የሆነበት ነው። ይችንም ቅድስት አርሴማኔ ንጉሥ ድርጣድስ "ይህን ታላቅ ክብር ካለው ከእኛ ጋር መኖርን እምቢ ያልሽ ልብ የለሽምን" አላት እርሷም "በሰማያት ያለው ይበልጣል እጅግም ይሻላል" አለችው ወደ ጐን ወስደው ልብሷን ገፈው አንገቷን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የደናግሉንም ሁሉ አንገት እንዲቆርጡ አዘዘና ተቆረጡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት አርሴማና በደናግሉ ጸሎት ይማረን በረከታቸው ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ አባ አብርሃም ሶርያዊ፦ ይህም አባት ከምሥራቅ አገር የክርስቲያ ወገን ነው እርሱም ብዙ ገንዘብ ያለው ነጋዴ ነበር እየነገደም ብዙ ጊዜ ወደ ምስር አገር ደረሰ ከዚህም በኋላ በውስጧ የሚኖር ሆነ ከእርሱም ለድኆችና ለችግረኞች ርኅራኄ ማድረግና ብዙ ትሩፋቶች ተገለጡ። የደግነቱና የትሩፋቱ የአዋቂነቱም ዜና በተሰማ ጊዜ አባቶች ኤጲስቆጶሳት የአገር ታላላቆችና ምሁራኖች በእስክንድርያ አገር ሊቀ ጵጵስና ይሾሙት ዘንድ ተስማሙ።
❤ በዚያንም ጊዜ በእግዚአብሔር ፈቃድ ሊቀ ጵጵስና ተሾመ ከዚህም በኋላ ገንዘቡን ሁሉ ለድኆችና ለችግረኞች ሰጥቶ የሊቀ ጵጵስናውን ሥራ መሥራት ጀመረ። በሹመቱም ወራት ክፉ ልማድን ሁሉ አስወግደ ኤጲስቆጶሳቱንም ሰዎች ዕቁባቶቻቸውን እንዲተው አወገዛቸው ውግዘቱንም በሰሙ ጊዜ ሁሉም ፈርተው ክፋ ልማዳቸውን ተው ወደርሱም መጥተው ከእግሮቹ በታች ወድቀው በደላቸውን ያስተሰርይላቸው ዘንድ ለመኑት።
❤ የንጉሥ ጸሐፊ ከሆነ ከአንድ ሰው በቀር ቃሉን ያስተሐቅር ዘንድ የደፈረ ማንም የለም። ይህም ልዑል እግዚአብሔርን ስለ ማይፈራ የዚህን የቅዱስ አባት ግዝትን አላሰፈራም ይህ አባት ግን ስለ ራሱ ድኅነት ብዙ ጊዜ ለመነው ከክፋቱ ተመልሶ ከመቅሠፍት ይድንም ዘንድ ገሠጸው መከረውም ሰውዬው ግን አልሰማውም። ይህም አባት ማስተማሩንና መገሠጹን ስልችቶ አልተወውም ለሌሎች ዕንቅፋት እንዳይሆን ስለዚህ ወደዚያ ሰው ቤት ሔደ የሊቀ ጳጳሳቱንም መምጣት በሰማ ጊዜ ደጁን ዘጋ ይህ አባትም ደጁን እያንኳኳ ሁለት ሰዓት ያህል ቆመ ከዚህም በኋላ "የዚህ ሰው ደሙ በራሱ ላይ ነው እኔ ከደሙ ንጹሕ ነኝ" ብሎ የእግሩን ትቢያ አራግፎ ተመለሰ። ወዲያውኑ ከዚህ ሰው ላይ ምልክትን ጌታችን ገለጸ ከደንጊያ የተሠራ የቤቱ መድረክ ከሁለት ተከፈለ ይህ ፈጽሞ ድንቅ ነውና ከዚህ አባት ግዝት የተነሣ ጠንካራው ዐለት ተሠነጠቀ ለመለም የነበረ የሰውየው ልብ ግን ከዐለት ጠነከረ።
❤ ዳግመኛም ድንቅ ምልክትን እግዚአብሔር በዚህ ሰው ላይ አደረገ ከድኆች ሁሉ እጅግ የባሰ ድኃ ሁኖአልና ከሹመቱም በጒስቊልናው ሻሩት ከገንዘቡም አንዲት መሐልቅ እንኳ አልቀረለትም ደግሞም ሥጋውን ጭንቅ በሆነ ደዌ ቀሠፈው እጆቹና እግሮቹም ተቆራርጠው በክፉ አሟሟት ሞተ ለሁሉም መቀጣጫ ሆነ ብዙዎች ከኃጢአተኞች ውስጥ ንስሐ ገቡ።
❤ በዚህም አባት ዘመን ለምስር ንጉሥ የጭራ አለቃ የሆነ አንድ ሰው ነበር እርሱም ወደ እስልምና ሕግ የገባ አይሁዳዊ ነው ለዚህም የጭፍራ አለቃ አይሁዳዊ የሆነ ወጃጅ ነበረው ወደ ንጉሡም አብሮት እየገባ ከንጉሥ ጋር ይነጋገራል ከጭፍራው አለቃው ጋር ወዳጅ ስለሆነ በንጉሥ ባለሟልነት በአገኘ ጊዜ ንጉሡን እንዲህ አለው "ጌታዬ ንጉሥ ሆይ ሊቀ ጳጳሳትን እንድታስመጣውና በፊትህ እንድከራከረው ተመኛቻለሁ" ንጉሡም ይህን አባት ሊቀ ጳጳሳት አባ አብርሃምን አስመጣው ከእርሱም ጋር የመቅፋዕ ልጅ የእስሙናይም ኤጲስቆጶስ አባ ሳዊሮስ ነበር ይህ አይሁዳዊ ከእርሳቸው ጋር በተከራከረ ጊዜ ረትተው አሳፈሩት ንጉሡም ሊቀ ጳጳሳቱንና ከእርሱር ጋር ያሉት ታላቅ ክብርን አከበራቸው። በፍቅር በሰላምም ወደ ቤተቻው አሰናበታቸው።
❤ የጭፍራ አለቃና ወደጃጁ አይሁዳዊው አፈሩ ሊቀ ጳጳሳቱን የክርስትያን ወገኖችንም የሚወድቁበትን የሚፈልጉ ሆኑ በአንዲት ቀንም የጭፍራ አለቃ ወደ ንጉሥ ገቡቶ "ጌታዬ ንጉሥ የማስረዳህ አለ እሊህ ክርስቲያኖች ሃይማኖት የላቸውም እኮን ወንጌላቸው የሰናፍጭ ቅንጣት ታህል ሃይማኖት ካላችሁ ይህን ተራራ ከዚህ ተነቅለህ ወደዚያ ሄድ ብትሉት ይሆዳል የሚሳናችሁ የለም" ይላልና አለው። ንጉሡም ይህ በሰማ ጊዜ ለሊቀ ጳጳሳት አባ አብርሃምን ልኮ አስመጣውና "ወንጌላችሁ የሰናፍጭ ቅጣት ታህል ሃይማኖት ካላችሁ ይህን ተራራ ከዚህ ተነቅለህ ወደዚያ ሒድ ብትሉት ይሆዳል ይላል ስለዚህ ነገር ምን ትላላችሁ" አለው። ሊቀ ጳጳሳቱም "እውነት ነው የከበረ ወንጌል ይላል" አለው። ንጉሡም መልሶ እንዲህ አለው "እነሆ ይህ ሃይማኖት ያላችሁ እናንተ የብዙ ብዙ ናችሁ ከእናንተ ውስጥ ይህ ምልክት የሚገልጽ አንድ ሰው ልታመጣል እሻለሁ አለዛም ለክርስቲያን ወገኖች ሁሉ አንተ አለቃቸው ነህና ይህ ምልክት ትገልጥ ዘንድ ይገባሃል" አለው። ሊቀ ጳጳሳቱ ሰምቶ ደነገጠ እጅግም ፈራ ንጉሡንም "እስከ ሦስት ቀን ታገሰኝ" አለው። ንጉሡም ይሁንልህ አለው።
❤ ሊቀ ጳጳሳቱም ከንጉሡ ወቶ በአቅራቢያው የሚገኙት ኤጲስቆሳቱን፣ ካህናቱን፣ መነኰሳቱን ሁሉ ሰበሰባቸው በምስር አገር በመሐልቃ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በእሊህ በሦስት ቀኖች እየጾሙና እየጸለዩ የእመቤታችን ሥዕል ፊት ቆመው ወደ እግዚአብሔር ሲማልዱ ቆዩ። በሦስተኛው ቀን በሌሊት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለሊቀ ጳጳሳቱ በብሩህ ገጽ ተገልጣ እንዲህ አለችው " በፊቴ ያፈሰስከውን እንባ ተቀብያለሁ ስለ አንተ ልጄን ለምኘዋለሁና አትፍራ አሁንም የብረት አፈር በአለበት ሜዳ ወደ ገበያ በሚወስደው ጎዳና ተነስተህ ሂድ አንድ አይና የሆነ የውኃ እንስራ የተሸከመ ሰው ታገኛለህ ይህ ምልክት እርሱ ያደርግልሃልና እርሱ ያዘው የዚህ ሰው ስሙ ጫማ ሰፊ ስምዖን ይባላል እርሱም ስለምወደው ልጄ ኢየሱስ ክርስቶስ ትእዛዝ ዓይኑን አውልቆ ጥሏልና"።
❤ በዚህም ጊዜ ሊቀ ጳጳሳቱ ተነሥቶ ፈጥኖ ሔደ ያንንም ሰው አግኝቶ ያዘው "የክርስቲያን ወገኞች እዘንላቸው ራራላቸው አምላክ የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንደተ ገለጸችለትና እርሱን እንዳመለከተችሁ ነገረው" እርሱ ወደ ሊቀ ጳጳሳቱን ሰግዶ "አባቴ ሆይ እኔ ኃጥያተኛ በደለኛ ነኝና ይቅርታ አድርግልኝ ይህን የምትለኝን ላደርገው የማልችል ነኝ ነገር ግን የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጸሎት በእናንተ በከበረች ጸሎትህ የክርስቲያ
1 161
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ማቴ. 10:35-ፍ፡ም፡ "ወመጻእኩ እፍልጥ ብእሴ" - "ሰውን፡ከአባቱ፥ሴት፡ልጅንም፡ከእናቷ፥ምራትንም፡ከአማቷ፡እለያይ፡ዘንድ፡መጥቻለሁና፤ ለሰውም፡ቤተ፡ሰዎቹ፡ጠላቶች፡ይሆኑበታል። ከእኔ፡ይልቅ፡አባቱን፡ወይም፡እናቱን፡የሚወድ፡ለእኔ፡ሊሆን፡አይገ፟ባ፟ውም፤ከእኔ፡ይልቅም፡ወንድ፡ልጁን፡ወይም፡ሴት፡ልጁን፡የሚወድ፡ለእኔ፡ሊሆን፡አይገ፟ባ፟ውም፤ መስቀሉንም፡የማይዝ፡በኋላዬም፡የማይከተለኝ፡ለእኔ፡ሊሆን፡አይገ፟ባ፟ውም። ነፍሱን፡የሚያገኝ፡ያጠፋታል፥ነፍሱንም፡ስለ፡እኔ፡የሚያጠፋ፡ያገኛታል። እናንተን፡የሚቀበል፡እኔን፡ይቀበላል፥እኔንም፡የሚቀበል፡የላከኝን፡ይቀበላል። ነቢይን፡በነቢይ፡ስም፡የሚቀበል፡የነቢይን፡ዋጋ፡ይወስዳል፥ ጻድቅንም፡በጻድቅ፡ስም፡የሚቀበል፡የጻድቁን፡ዋጋ፡ይወስዳል። ማንም፡ከነዚህ፡ከታናናሾቹ፡ለአንዱ፡ቀዝቃዛ፡ጽዋ፡ውሃ፡ብቻ፡በደቀ፡መዝሙር፡ስም፡የሚያጠጣ፥እውነት፡እላችኋለሁ፥ዋጋው፡አይጠፋበትም።"
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
1 161
5/04/2013 ዓ.ም (፭/፬/፳፻፲፫ ዓ.ም)
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ተንሥኡ ላዕሌየ ሰማዕተ ዐመፃ።
ወዘኢየአምር ነበቡ ላዕሌየ።
ፈደዩኒ እኪተ ህየንተ ሠናይት፡፡ መዝ. 34፥3
🕯 ትርጉም
የሐሰት ምስክሮች በጠላት ተነሱብኝ።
በእኔ ላይም የማላውቀውን ነገር ተናገሩብኝ።
በጎ ስለአደረግሁላቸው ፈንታ ክፉ ብድራት መለሱልኝ።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
