fa
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

رفتن به کانال در Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

نمایش بیشتر
1 161
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በዕለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ማቴ. 5፥38-ፍ፡ም፡ "ሰማዕክሙ ከመ ትብህለ ቤዛ ዐይን" -"ዐይን፡ስለ፡ዐይን፡ጥርስም፡ስለ፡ጥርስ፡እንደ፡ተባለ፡ሰምታችኋል። እኔ፡ግን፡እላችኋለሁ፥ክፉውን፡አትቃወሙ፤ዳሩ፡ግን፡ቀኝ፡ጕንጭህን፡በጥፊ፡ለሚመታህ፡ሁሉ፡ሁለተኛውን፡ደግሞ፡አዙርለት፤ እንዲከስህም፡እጀ፡ጠባብህንም፡እንዲወስድ፡ለሚወድ፡መጐናጸፊያህን፡ደግሞ፡ተውለት፤ ማንም፡ሰው፡አንድ፡ምዕራፍ፡ትሄድ፡ዘንድ፡ቢያስገድድህ፡ሁለተኛውን፡ከእርሱ፡ጋራ፡ሂድ። ለሚለምንህ፡ስጥ፥ከአንተም፡ይበደር፡ዘንድ፡ከሚወደ፟ው፡ፈቀቅ፡አትበል። ባልንጀራህን፡ውደድ፡ጠላትህንም፡ጥላ፡እንደ፡ተባለ፡ሰምታችኋል። እኔ፡ግን፡እላችኋለሁ፥በሰማያት፡ላለ፡አባታችሁ፡ልጆች፡ትሆኑ፡ዘንድ፡ጠላቶቻችሁን፡ውደዱ፥የሚረግሟችሁንም፡መርቁ፥ለሚጠሏችሁም፡መልካም፡አድርጉ፥ስለሚያሳድዷችሁም፡ጸልዩ፤እርሱ፡ በክፉዎችና፡በበጎዎች፡ላይ፡ፀሓይን፡ያወጣልና፥በጻድቃንና፡በኀጢአተኛዎችም፡ላይ፡ዝናቡን፡ያዘንባልና። የሚወዷ፟ችሁን፡ብትወዱ፡ምን፡ዋጋ፡አላችሁ? ቀራጮችስ፡ያንኑ፡ያደርጉ፡የለምን? ወንድሞቻችሁንም፡ብቻ፡እጅ፡ብትነሡ፡ምን፡ብልጫ፡ታደርጋላችሁ? አሕዛብስ፡ያንኑ፡ያደርጉ፡ የለምን? እንግዲህ፡የሰማዩ፡አባታችሁ፡ፍጹም፡እንደ፡ሆነ፡እናንተ፡ፍጹማን፡ሁኑ።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

1.42 KB

5/4/2013 ዓ.ም (፭/፬/፳፻፲፫ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ወይእዜኒ መኑ ተስፋየ አኮኑ እግዚአብሔር። ወትዕግሥትየኒ እምኀቤከ ውእቱ። እምኵሉ ኃጢአትየ አድኀንከኒ፡፡ መዝ. 38፥7 🕯 ትርጉም አሁንስ ተስፋዬ ማን ነው? እግዚአብሔር አይደለምን? ትዕግሥቴም ከአንተ ዘንድ ነው። ከኃጢአቴ ሁሉ አድነኝ፡፡ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯

+2
ዘስብከት መኃትው፡ዋዜማ-ሰላም @EOTCW

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ሰላም ለከ መርዓዊ ሥርግው። በደመ ስምዕ ቀይሕ ወልብሰ አሚን ጽዕድው። ፊቅጦር ሰማዕት ዘደወለ ሻው። አጥዕሞ ለማኅሌትየ ውስተ ዕዝን ኵሉ ዕደው። ከመ ምረተ ማይ ነቢይ ቀሰመ በፄው። ትርጉም፦ በቀይ የምስክርነት ደምና በነጭ የእምነት ልብስ ያጌጥኸ ሙሽራ ሆይ ሰላምታ ላንተ ይገባል፤ በሻው አውራጃ ምስክር የኾንኽ ፊቅጦር የውሃውን ምረት ነቢይ ኤልሳዕ በጨው እንጣፈጠው በወንዶች ዦሮ ኹሉ ምስጋናዬን አጣፍጠው። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ 5። https://t.me/Eotcw

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ሰላም ለአውጋንያ ዘተመሰለት ሕጽወ። በእንተ ክርስቶስ ታዝኅን መነኰሳተ አኃወ። ወጽድቀ አቡሃ ፊልጶስ እዜኑ መትልወ። እመንግሥተ ምድር ኃላፊ ለመንግሥተ ሰማይ አድለወ። እስከ በትሪያርከ ኮነ ዘይጌሥጽ አበወ"። ትርጉም፦ ወንድሞች መነኰሳትን ታረጋጋ ዘንድ ስለ ክርስቶስ በጀንደረባ የተመሰለች ለኾነች ለአውጋንያ ሰላምታ ይገባል፤ የአባቷ የፊልጶስን ጽድቅ አስከትዬ እናገራለኍ፤ ከኃላፊው የምድር መንግሥት ይልቅ ለመንግሥተ ሰማያት አደልቷልና፤ አባቶችን የሚገሥጽ በትርያርክ እስኪኾን ድረስ። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ 5። https://t.me/Eotcw

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ታኅሣሥ ፭ (5)። ❤ እንኳን ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ለእግዚአብሔር ሕግ ለሚቀና ገድለኛ ለሆነ ለንጹሕ ድንግል ለቅዱስ አባት ለአባ ገብረ ናዝራዊ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። + + + ❤ አባ ገብረ ናዝራዊ፦ የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ በወገን የከበሩ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ናቸው አባቱም የቤተ ክርስቲያንን ሕጓንና ሥርዓቷን የሚጠብቅ ካህን ነው እናቱም ፈጣሪዋን የምትወድ ደግ ሴት ናት። ይህም ቅዱስ በተወለደ ጊዜ በዕውቀት እግዚአብሔርን በመፍራት በመማር አደገ ከዚህም በኋላ ዲቁናን በተሾመ ጊዜ የብሉይና የሐዲስ መጻሕፍትን የሚያነብ ሆነ በኦሪትም ውስጥ "የሰንበትን ቀን የሻረና ሥራ የሠራባት በሞት ይቀጣ" የሚል አገኘ። ከወንጌልም ውስጥ እንዲህ የሚል አገኘ "ከእነዚህ ትእዛዛት ታንሳለች ብሎ የሚያስተምር አንዲቱን የሻረ ለሰውም እንዲህ ብሎ የሚያስተምር በመንግሥተ ሰማይ የተለየ ይሆናል የሚያደርግና የሚያስተም ግን እርሱ በመንግሥተ ሰማይ ታላቅ ይሆናል" ዳግመኛም መድኃኒታችን "አባትና እናቱን ያልተው ሰውነቱንም ለመከራ አሳልፎ ያልጣላት ሊአገለግለኝ ደቀ መዝሙሬም ሊሆነኝ አይችልም" ያለውን አስተዋለ። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ አቡነ ጎርጎርዮስ ሔደ እርሱም ጽጋጃ በሚባል ገዳም የአቡነ አኖሬዎስ ልጅ ነው በዚያም መንኵሶ በጾም፣ በጸሎትና በስግደት እየተጋ ኖረ። ከዚህም በኋላ ቅስና ተሾመ ከዚያም ወደ ትግራይ አገር ሔዶ ከአባ ያዕቆብ ጋር ተገናኝቶ በቅዱሳት መጻሕፍት ቃሎች ተነጋገሩ። ከዚህም በኋላ ሀሳብን ገለጠለት አባ ያዕቆብም "እንዴት ይቻላል" አለው አባ ገብረ ናዝራዊም "እግዚአብሔር ይረዳኛል" አለ። ከአባ ያዕቆብም ጒልት ተቀብሎ እርስበርሳቸው በእግዚአብሔር ፈቃድ ተለያዩ። ❤ ከዚህም በኋላ ተስፋፍቶ ገዳምን ሠራ ብዙ ሰዎችም ወደርሱ ተሰብስበው መነኰሳትን ሆኑ ስለሰንበታትና በዓላትም አከባበር እንደሚገባ ሥርዓትን ሠራ። ለመነኰሳትም ከመድኃኒታችን ከልደቱና ከጥምቀቱ በዓል ከሰንበታትና ከበዓለ ሃምሳ በቀር በየሰሞኑ ሁሉ እስከ ማታ ያለ ማቋረጥ መጾም እንደሚገባቸው ሥርዓትን ሠራ። ዳግመኛም የሌላውን ገንዘብ እንዳይነኩ እንዳይረግሙ በሕያው እግዚአብሔርም ስም እንዳይምሉም ለልጆቹ ይህን ሁሉ ያስተምራቸው ነበር። ለእርሱ ግን ለሚጸልየው ጸሎት ልክ የለውም ነቢይ ዳዊት "እግዚአብሔርን ሁል ጊዜ አመሰግነዋለሁ። ምስጋናውም ዘወትር በአፌ ውስጥ አለ" ያለውን አስቦ ዳግመኛም "ትእዛዝህን በማሰብ እጫወታለሁ ሕግህን እሻለሁ ትእዛዞችህንም አስተምራለሁ ቃልህም አልረሳም" ያለውን አስቦ። ❤ ዳግመኛም ከሰባውና ደም ካለው ጣዕም ካላቸውም መብሎች ሁሉ ይከለከላል የጌታውን መከራ ለነፍሱ ያሳስባታልና ዕንባው ያለ ማቋረጥ ይፈስ ነበር ያለ ማቋረጥም ይሰግዳል ያመሰግናልም እንግዳና መጻተኛውን ይቀበላል "በጽዮን ዘር በኢየሩሳሌም ቤቶች ያለሐት ብፁዕ ነው" ያለውን የነቢይ ቃል አስቦ ድኆችንና ችግረኞችን ይጎበኛቸዋል። ለዚህም አባት ትሩፋቱ ብዙ ነው ደጋግ ተአምራትንም በማድረግ በሰው ልቡናም ተሠውሮ ያለውን በማወቅ ብዙ የተለያዩ ሀብቶች ተሰጥተውታል ለልጆቹም የቀናች ሃይማኖትን አስተማራቸው በእርሷም እንዲጸኑ አዘዛቸው ከዚህም በኋላ በሸመገለ ጊዜ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በዚች ቀን ታኅሣሥ5 ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት በአባ ገብረ ናዝራዊ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 5 ስንክሳር። https://t.me/Eotcw

❤ ከዚህም በኋላ ሰይጣን በአንዲት ሴት ልብ ክፉ አሳብ አሳደረባት ከአዳነቻት በኋላ ወንድ መስላታለችና "ገዳምህንና ምንኵስናህን ትተህ ለእኔ ባል ሁነኝ ብዙ ገንዘብ አለኝና" አለቻት። አባ አውጋንዮስ የተባለችው ቅድስቷም "እናቴ ሆይ ከእኔ ዘንድ ሒጂ ሰይጣን በከንቱ አድክሞሻል" አለቻት በአሳፈረቻትም ጊዜ ወደ እስክንድርያ ገዥ ሒዳ እንዲህ አለችው "እኔ ወደ ዕገሌ ቦታ በሔድኩ ጊዜ ሊደፍረኝ ሽቶ ወጣት መነኵሴ በሌሊት ወደእኔ መጣ ወደ አገልጋዮቼም ስጮህ ከእኔ ዘንድ ወጥቶ ሸሸ"። መኰንኑም በሰማ ጊዜ ይኸውም የቅድስት አውጋንያ አባቷ የሆነ መነኰሳቱን ሁሉ አሥረው ያመጧቸው ዘንድ አዘዘ በአደረሷቸውም ጊዜ እንዲአሠቃያቸው ለሌላ መኰንን አሳልፎ ሰጣቸው ከሥቃይም ጽናት የተነሣ ከእርሳቸው የሞቱ አሉ። ❤ የመነኰሳቱንም መጐሳቈል በአየች ጊዜ መኰንን አባቷን እንዲህ አለችው "ጌታዬ ሆይ ምሥጢሬን ዕውነቱን እነግርህ ዘንድ የምፈልገውንም እንዳትከለክለኝ ማልልኝ" አለችው። በማለላትም ጊዜ ወደ ሥውር ቦታ ወስዳ ምስጢርዋን ሁሉ ገለጠችለትና ልጁ አውጋንያ እርሷ እንደሆነች አስረዳችው። መኰንኑም አይቶ "በእውነት አንቺ ልጄ አውጋንያ ነሽ እኔም በአምላክሽ አመንኩ" አላት። በዚያንም ጊዜ መነኰሳቱን ይፈቷቸው ዘንድ በመሠቃየት የሞቱትንም ይቀብሩአቸው ዘንድ አዘዘ ወዲውኑ ከቤተሰቦቹ ሁሉ ጋር ተጠምቆ ሁሉም ክርስቲያን ሆኑ። ❤ የእስክንድርያ ሰዎችም የሃይማኖቱን ጽናት በአዩ ጊዜ በወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ሾሙት ክብር ይግባውና የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት እያስተማረ ብዙ ዓመታትን ኖረ። ከዚህም በኋላ በእርሱ ላይ ሌላ ከሀዲ መኰንን ተነሥቶ ይህን ሊቀ ጳጳሳት ፊልጶስን በሥውር ይገድሉት ዘንድ ጭፍሮቹን ላከ በቤተ ክርስቲያንም ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ገደሉት የሰማዕትነት አክሊል አገኘ። ❤ የሮሜ ሊቀ ጳጳሳትም የቅድስት አውጋንያን ዜና በሰማ ጊዜ ወደርሱ ወስዶ እርሱ በሠራው ገዳም ላይ እመ ምኔት አድርጎ ሾማት የመነኰሳይያቱም ብዛት ሦስት ሺህ ሦስት መቶ ነው እነዚያንም ከእርሷ ጋር የኖሩ ሁለት ጃንደረቦች በሁለት አገሮች ላይ ኤጲስቆጶስትነት ሾማቸው። ከዚህም በኋላ ሌላ ከሀዲ መኰንን በተሾመ ጊዜ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ነፍሷን ለሞት አሳልፋ እስከ ሰጠች ድረስ ቅድስት አውጋንያን ይዞ በጽኑ ሥቃይ አሠቃያት የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለች። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት አውጋንያ በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ "ሰላም ለፊቅጦር ፍቁረ አምላኩ"። ትርጉም፦ የአምላኩ ወዳጅ ለኾነ ለፊቅጦር ሰላምታ ይገባል። አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። + + + ❤ ቅዱስ ፊቅጦር፦ የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም መርመር የእናቱ ስም ማርታ ይባላል እነርሱም ያለ ፍርሀት እግዚአብሔርን የሚያመልኩት እውነተኞች ጻድቃን ናቸው ነገር ግን ልጅ አልነበራቸውምና ክብር ይግባውና ጌታችንን እየለመኑ ኖሩ ለድኆችም ምጽዋትን ይሰጡ ነበር። እግዚአብሔርም ልመናቸውን ተቀብለ ይቺ የተባረከች ማርታም ይህን ሊቅ ፊቅጦርን ፀንሳ ግንቦት ዘጠኝ ቀን ወለደችው እግዚአብሔርን በመፍራትም ሠርተው ቀጥተው አሳደጉት። ❤ ሃያ ዓመትም ሲሆነው አባቱ ወደ ንጉሥ አቀረበውና ንጉሡም በአባቱ ፈንታ ምስፍና ሾመው አባቱ በዕድሜው ሸምግሎ ነበርና። ከጥቂት ወራትም በኋላ ጣዖታትን የማያመልኩ ክርስቲያኖችን ሁሉ ይገድል ዘንድ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ምልክትን ወደ እንጽና አገር መኰንን ደረሰ። መኰንኑም ክርስቲያኖችን እየፈለገ ወደ ሻው ከተማ ደረሰ ያን ጊዜ ክብር ይግባውና ክርስቶስን እንደሚአመልከው ክፉዎች ሰዎች ይህን ቅዱስ ፊቅጦርን ወነጀሉት ያን ጊዜም እንዲአመጡት አዘዘና በአመጡት ጊዜ ለጣዖታት እንዲሠዋ አስገደደው እምቢ በአለውም ጊዜ በወህኒ ቤት እንደመአሥሩት አዘዘ። ❤ በዚያም እያለ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ወደ ሰማይ አወጣው የወህኒ ቤት ጠባቂዎችም በአጡት ጊዜ ተሸበሩ። ከሰባት ቀኖችም በኋላ አግኝተውት ወደ መኰንኑ ወሰዱት መኰንኑ ግን ራራለትና ወደ ንጉሡ ሰደደው ንጉሡም እግዚአብሔርን ከማምለክ ይመልሰው ዘንድ በማባበል ብዙ ሽነገለው። መመለስም በተሳነው ጊዜ አውጣኪያኖስ ወደሚባል መኰንን ሰደደው። እንዲህም ብሎ አዘዘው "እንሆ ፊቅጦርን ወደአንተ ልኬዋለሁ ያንተን ምክር ከሰማ ለአማልክት ይሠዋ ካልሰማህ ግን ግደለው እንጂ አትራራለት"። አለው። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ መኰንኑ ሊወስዱት እጆቹንና እግሮቹን አሠሩ በአፉም የብረት ልጓም አግብተው በመርከብ አሳፈሩት የእግዚአብሔርም መልአክ ወርዶ ከማሠሪያው ፈትቶ ወደ መኰንኑ አደረሰው ቅዱስ ፊቅጦርም መኰንኑንና ከሀዲውን ንጉሥ ሊረግም ጀመረ መኰንኑም ተቆጣ ጽኑዕ ሥቃይንም አሠቃይቶ በወህኒ ቤት አሠረው። በዚያም ሳለ ክብር ይግባውና መድኃኒታችን በብርሃን ሠረገላ ላይ ሁኖ ተገለጠለትና ቃል ኪዳን ሰጠው ከዚያችም ቀን ጀምሮ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ ብዙ በሽተኞችን የሚፈውስ ሆነ። ❤ መኰንኑም ይህን ሰምቶ ተቆጣ ወደርሱ አስመጣውና ይመለሰው ዘንድ ደግሞ ሸነገለው ቅዱስ ፊቅጦር ግን የረከሱ አማልክቶቹን ረገመ በዚያንም ጊዜ በፈረስ ጅራት ላይ አሥረው የአንድ ቀን መንገድ ያህል እንዲጐትቱት ከዚያም ከውሽባ ቤት እሳት ማንደጃ ውስጥ እንዲጨመሰሩት አዘዘ እንዲህም መልካም ተጋድሎውን ፈጸመ። ሥጋውን ግን ከዚያ ውሽባ ቤት አላወጡትም በመሰላል ወርደው በአማሩ ልብሶች ገንዘው በሽቱዎች አጣፈጡት እንጂ በላዩ ቤተ ክርስቲያንን ሠሩ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ፊቅጦር በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ5 ስንክሳር። + + + ❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "ተንሥኡ ላዕሌየ ሰማዕት ዐመፃ። ወዘኢየአምር ነበቡ ላዕሌየ። ፈደዩኒ እኪተ ህየንተ ሠናይት"። መዝ 34፥11-12። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 10፥11-ፍ.ም ወይም ገላ 3፥21-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 5፥9-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 16፥14-16። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥35-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም በዓል ነቢዩ ናሆም የዕረፍት በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት https://t.me/Eotcw

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ታኅሣሥ ፭ (5) ቀን። ❤ እንኳን ዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ ለሆነው ለኬልቅዩ ልጅ ለታላቁ ነቢይ ለቅዱስ ናሆም ለዕረፍት በዓል፣ ከሮም አገር ለሆነች ለቅድስት አውጋንያ ሰማዕትነት ለተቀበለችበት ለዕረፍቷ በዓልና አስዩጥ አውራጃ ሻው ከሚባል ከተማ ለሆነ ለቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት፣ ቅዱሳን ከፊንጦስ፣ ከሐናንያ፣ ከባርክዮስ፣ ከዮሐንስ፣ ከተጋዳይዋ ከቅድስት አውጋንያ አባት ከፊልጶስና ከሰማዕት ቅዱስ ኤላውትሮስ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ ነቢዩ ቅዱስ ናሆም፦ ከስምዖን ነገድ የሆነ ይህ ጻድቅ ነቢይ ከነቢዩ ሙሴ በትንቢት ዐሥራ ሰባተኛ ነው። በካህኑ ዮዳሄ በነገሥታቱ በኢዮአስ፣ በአስሜስያስ፣ በልጁ በኦዝያን ዘመን ትንቢት ተናገረ ስለ ክህደታቸውና ጣዖታትን ስለ ማምለካቸውም የእስራኤልን ልጆች ገሠጻቸው። እግዚአብሔርም ምንም መሐሪና ይቅር ባይ ምሕረቱም የበዛ ቢሆን ካልተመለሱ ጠላቶቹን ይበቀላቸው ዘንድ እንደ አለው ለሚቃወሙትም የፍርድ ቀን እንደሚጠብቃቸው በትንቢት ገለጠ። ❤ ዳግመኛም ስለ ከበረ የወንጌል ትምህርትና ስለ ሐዋርያት እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ "የምሥራች የሚናገሩ ሰዎች እግራቸው እንሆ በተራራ ላይ ቁሟል ሰላምንም ይናገራሉ"። ስለነነዌም ውኃና እሳት ያጠፋአት ዘንድ እንዳላቸው ትንቢት ተናገረ እንደ ቃሉ ሆነ ከዕውነት መንገድ ተመልሰው በበደሉ ሰዎች ላይ እግዚአብሔር በውስጡ ታላቅ ንውጽውጽታ አድርጎ እሳትም አውርዶ እኩሌታዋን አቃጥሏልና። በንስሐ ጸንተው ወደ እግዚአብሔር የተመለሱትን ግን ከክፉ ነገር ከቶ ምንም ምን አልደረሰባቸውም። የትንቢቱንም ወራት ሲፈጸም እግዚአብሔርም አገልግሎ በዚች ቀን ታኅሣሥ5 በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ነቢይ በቅዱስ ናሆም ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ "ሰላም ለአውጋንያ ቅድስት፤ ፍኖተ ስምዕ ዘሮጸት ከመ ወራዙት"። ትርጉም፦ እንደ ጐልማሳ ወደ ምስክርነት ጐዳና የሮጠች ለኾነች ለቅድስት አውጋንያ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። + + + ❤ ቅድስት አውጋንያ፦ የዚችም ቅድስት የአባቷ ስም ፊልጶስ ነው እርሱም የእስክንድርያ አገር ገዥ ነበር ጣዖትንም ያመልካል ስሙ መምድያኖስ የሚባል የሮም ንጉሥም ለጣዖት የሚሰግድ ነው ይቺም ቅድስት አውጋንያ በእስክድርያ ከተማ ተወለደች እናቷም ክርስቲያን ስለሆነች በሥውር የክርስቲያን ሃይማኖትን አስተማረቻት። ❤ በአደገችም ጊዜ ታላላቆች መኳንንት አጯት አባቷም ይህን በነገራት ጊዜ "አባቴ ሆይ መጀመሪያ ወደ እስክንድርያ ገዳም እንድገባና እንድጎበኝ ተራሮችን በማየት ዐይኖቼ አይተው ደስ ይለኝ ዘንድ ፍቀድልኝ" አለችው አባቷም ሰምቶ ሁለት ጃንደረቦችን ጨምሮ የወደደችውን ታደርግ ዘንድ ፈቀደላት። በወጣችም ጊዜ የመነኰሳትን ገዳማት ሁሉ ዞረች ስሙ ቴዎድሮስ የሚባል ጻድቅ ደግ ኤጲስቆጶስ ወደሚኖርባትም ቤተ ክርስቲያን ደረሰች ቀረብ ብላም በልቧ ያለውን ሁሉ ነገረችው ካጃንደረቦቿም ጋር ተጠምቃ በዚያ መነኰሰች በወንድ አምሳልም ሁና ስሟን አባ አውጋንዮስ አሰኘች እርሷ ሴት እንደሆነች ማንም አላወቀም። ወደ አባቷም ባልተመለሰች ጊዜ በቦታው ሁሉ ፈለጋት ሲአጣትም በርሷ አምሳል ጣዖት ሠርቶ ማታና ጧት እየሰገደላት ኖረ። ❤ አንድ ዓመትም ከኖረች በኋላ የዚያ ቦታ አበ ምኔት አረፈ መነኰሳቱም መረጧትና አበ ምኔት አድርገው ሾሟት እግዚአብሔርም አጋንንትን ታስወጣ ዘንድ የዕውራንን ዐይኖች ትገልጥ ዘንድ ደዌውን ሁሉ ታድን ዘንድ ሀብተ ፈውስን ሰጣት።

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ሉቃ 9:46-56 "ወሐለዩ በበይናቲሆሙ እንዘ ይብሉ" - "ከነርሱም፡ማን፡እንዲበልጥ፡ክርክር፡ተነሣባቸው። ኢየሱስም፡የልባቸውን፡ዐሳብ፡ዐውቆ፡ሕፃንን፡ያዘ፤በአጠገቡም፡አቁሞ፦ ማንም፡ይህን፡ሕፃን፡በስሜ፡የሚቀበል፡እኔን፡ይቀበላል፤ የሚቀበለኝም፡ሁሉ፡የላከኝን፡ይቀበላል፤ከሁላችሁ፡የሚያንስ፡እርሱ፡ታላቅ፡ነውና፥አላቸው። ዮሐንስም፡መልሶ፦አቤቱ፥አንድ፡ሰው፡በስምህ፡አጋንንትን፡ሲያወጣ፡አየነው፥ከእኛ፡ጋራም፡ስለማይከተል፡ከለከልነው፡አለው። ኢየሱስ፡ግን፦ የማይቃወማችሁ፡ከእናንተ፡ጋራ፡ነውና፥ አትከልክሉት፡አለው። የሚወጣበትም፡ወራት፡በቀረበ፡ጊዜ፡ወደ፡ኢየሩሳሌም፡ለመሄድ፡ፊቱን፡አቀና፥ በፊቱም፡መልክተኛዎችን፡ሰደደ።ሄደውም፡ሊያሰናዱለት፡ወደ፡አንድ፡ወደሳምራውያን፡መንደር፡ገቡ፤ ፊቱም፡ወደ፡ኢየሩሳሌም፡እንደሚሄድ፡ስለ፡ነበር፥አልተቀበሉትም። ደቀ፡መዛሙርቱም፡ያዕቆብና፡ዮሐንስ፡አይተው፦ጌታ፡ሆይ፥ኤልያስ፡ደግሞ፡እንዳደረገ፡እሳት፡ከሰማይ፡ወርዶ፡ያጥፋቸው፡እንል፡ዘንድ፡ትወዳለህን፧አሉት። እርሱ፡ግን፡ዘወር፡ብሎ፡ገሠጻቸውና፦ምን፡ዐይነት፡መንፈስ፡እንደ፡ሆነላችሁ፡አታውቁም፤ የሰው፡ልጅ፡የሰውን፡ነፍስ፡ሊያድን፡እንጂ፡ሊያጠፋ፡አልመጣም፡አለ።ወደ፡ሌላ፡መንደርም፡ሄዱ።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

04/4/2015 ዓ.ም (፬/፬/፳፻፲፭ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ወነደ እሳት ውስተ ተዐይኒሆሙ። ወአውዐዮሙ ነበልባል ለኃጥአን። ወገብሩ ላሕመ በኮሬብ። መዝ. 105÷15 🕯 ትርጉም በማኅበራቸውም እሳት ነደደች። ነበልባልም ኃጥኣንን አቃጠላቸው። በኰሬብም ጥጃን ሠሩ። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ዮሐ. 1:38-46፡"ወተመይጦ እግዚእ ኢየሱስ" - "ኢየሱስም፡ዘወር፡ብሎ፡ሲከተሉትም፡አይቶ፦ምን፡ትፈልጋላችሁ? አላቸው። እነርሱም፦ረቢ፥ወዴት፡ትኖራለህ? አሉት፤ትርጓሜው፡መምህር፡ሆይ፡ማለት፡ነው። መጥታችሁ፡እዩ፡አላቸው። መጥተው፡የሚኖርበትን፡አዩ፥በዚያም፡ቀን፡በርሱ፡ዘንድ፡ዋሉ፤ዐሥር፡ሰዓት፡ያህል፡ነበረ። ከዮሐንስ፡ዘንድ፡ሰምተው፡ከተከተሉት፡ከሁለቱ፡አንዱ፡የስምዖን፡ጴጥሮስ፡ወንድም፡እንድርያስ፡ነበረ። እርሱ፡አስቀድሞ፡የራሱን፡ወንድም፡ስምዖንን፡አገኘውና፦ መሲሕን፡አግኝተናል፡አለው፤ትርጓሜውም፡ ክርስቶስ፡ማለት፡ነው። ወደ፡ኢየሱስም፡አመጣው። ኢየሱስም፡ተመልክቶ፦አንተ፡የዮና፡ልጅ፡ስምዖን፡ነህ፤አንተ፡ኬፋ፡ትባላለህ፡አለው፤ትርጓሜው፡ጴጥሮስ፡ማለት፡ነው። በነገው፡ኢየሱስ፡ወደ፡ገሊላ፡ሊወጣ፡ወደደ፥ፊልጶስንም፡አገኘና፦ተከተለኝ፡አለው። ፊልጶስም፡ከእንድርያስና፡ከጴጥሮስ፡ከተማ፡ከቤተ፡ሳይዳ፡ነበረ። ፊልጶስ፡ናትናኤልን፡አግኝቶ፦ሙሴ፡በሕግ፡ነቢያትም፡ስለ፡ርሱ፡የጻፉትን፡የዮሴፍን፡ልጅ፡የናዝሬቱን፡ኢየሱስን፡አግኝተነዋል፡አለው።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

1.23 KB

4/4/2015 ዓ.ም (፬/፬/፳፻፲፭ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ውስተ ኲሉ ምድር ወፅአ ነገገሮሙ። ወእስከ አፅናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ። ወውስተ ፀሐይ ሤመ ጽላሎቶ፡፡ መዝ. 18፥4 🕯 ትርጉም ድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ። ቃላቸውም እስከዓለም ዳርቻ ወጣ። በእነርሱም ውስጥ የፀሐይን ድንኳን አደረገ። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯