fa
Feedback
Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗

رفتن به کانال در Telegram

Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service

نمایش بیشتر
3 590
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
+4830 روز
آرشیو پست ها
ውል ስንፈርም ማስተዋል የሚገባን ወሳኝ ጉዳዮች🏗
ዉል በተወያይ ወገኖች መካከል ህጋዊ ዉጤት እንዲኖረዉ አስቀድሞ የዉል አመሰራረቱ ህጋዊ መስፈርቱን ማሟላት አለበት፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን ስለ ዉል አመሰራረት በሚደነግገዉ ክፍል አንቀፅ 1678 ላይ በግልፅ እንደተቀመጠዉ የሚፀና ዉል ነዉ ለማለት መሟላት ያለባቸዉን አራት (4) ሁኔታዎች አስቀምጧል፡፡ እነሱም፡ 1ኛ. ዉል የሚፈፀመዉ ለመዋዋል ችሎታ ባላቸዉ ሰዎች መካከል መሆኑን፡፡ ይህም ማለት በህግ ፊት የሚፀና ዉል ለማድረግ ተዋዋዮች በህግ ችሎታ ያላቸዉ መሆን አለባቸዉ፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን ላይ ስለ ችሎታ በሚደነግገዉ ክፍል አንቀፅ 192 ላይ በመርህ ደረጃ ማንኛዉም ሰዉ በህግ ችሎታ እንደሌለዉ ካልተገለፀ በቀር ማንኛዉንም ህጋዊ ድረጊት ለማድረግ ችሎታ እንዳለዉ እንደሚቆጠር ተደንግጓል፡፡ በዚሁ ህግ አንቀፅ 193 ላይ እንደተደነገገዉ እድሜዉ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሰ/ሰች ወይም አይምሮዉ ህመም ያለበት ሰዉ ወይም በፍርድ ቤት የተከለከለ ሰዉ ችሎታ እንደሌለዉ ይቆጠራል፡፡ ከላይ እንደተገለፀዉ ዉል ህጋዊ ተግባር ነዉ ስለሆነም እድሜዉ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሰ/ሰች ወይም አይምሮዉ ህመም ያለበት ወይም በፍርድ ቤት የተከለከለ ሰዉ ዉል መዋዋል አይችልም፡፡ 2ኛ. ዉል የሚፈፀመዉ በተወያያቹ ነፃ ፍቃድ ብቻ መሆኑ፡፡ ይህም ማለት ተወያይ ወገኖች ዉል ዉስጥ የሚገቡት ያለማንም ጫና አድራጊነት በራሳቸዉ  ፍቃድ መሆን አለበት ማለት ነዉ፡፡ አንድ የዉል ግዴታ የተቋቋመ  መሆኑ የሚረጋገጠዉ የተዋዋዮቹ ፈቃድ በህግ አግባብ መገለፁ ሲታወቅ ነዉ፡፡ ተዋዋዮቹ በመሀከላቸዉ በህግ ፊት የሚፀና ግዴታ ለማቋቋምና ይህም ግዴታ በሚያስከትለዉ ዉጤት ለመገዛት ስምምነት ያላቸዉ መሆኑ ይፋ ሲያደርጉ ፈቃዳቸዉን ገለፁ እንላለን፡፡ በፍትሐብሔር ህጉ አንቀፅ 1679 ላይ ይህን አባባላችን በሚያጠናክር መልኩ “ዉል ተዋዋዮች በገቡባቸዉ ግዴታዎችና እነዚህም አስገዳጅ እንዲሆኑ የተስሚ መብትን በሚገልፀዉ የፈቃድ መስጠት ላይ የተመሰረተ ነዉ” በማለት ተደንግጓል፡፡ 3ኛ. ተወያይ ወገኖች የሚዋዋሉበት (ዉል ዉስጥ የሚገቡበት) ጉዳይ በእርግጠኝነት የሚቻል እና ህጋዊና ሞራላዊ ጉዳይ ላይ መሆኑ፡፡ የዉሉ ፍሬ ነገር በሰዉ ልጅ አቅም መፈጸም የሚችል እና ህጋዊና ሞራላዊ የሆነ መሆን አለበት፡፡ በሰዉ ልጅ አቅም መፈፀም የሚቻል ተግባር ማለት የሰዉ ልጅ በተፈጥሮዉ ማከናዉን የሚችለዉ ማለት ነዉ፡፡ ለአብነት የዉሉ ፍሬ ነገር እንደ እርግብ መብረር ቢሆን በሰዉ ልጅ ተፈጥሮ የማይቻል ተግባር ነዉ፡፡ ሌለዉ የዉሉ ፍሬ ነገር በህግ ያልተከለከለ ወይም ህገ-ወጥ እና በህብረተሰቡ ባህልና ወግ ተቀባይነት ያለዉ ነገር ላይ (በሌላ አባባል ከህብረተሰቡ ሞራል ጋር ያልተቃረነ ያልሆነ) መሆን አለበት፡፡ ለአብነት ፍሬ ነገሩ ሰዉ ለመግደል ቢሆን በህግ የተከለከለ ነዉ፡፡ 4ኛ. የዉል አቀራረጹ ወይም አፃፃፉ በህግ (ፎርም) ተለይተዉ የተቀመጡ ወይም ተዋዋይ ወገኖች ተለይቶ እንዲቀመጡ ከተስማሙበት የዉል ጉዳይ በቀር የተለየ የዉል ፎርም የማያስፈልግ መሆኑ፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን አንቀፅ 1678(3) ላይ እንደተደነገገዉ በግልፅ በህግ ይህን የዉል ፎርም ተከተሉ ተብሎ ካልተደነገገ በቀር ተዋዋይ ወገኖች ዉላቸዉን በፈለጉት አይነት ማድረግ ይችላሉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በዚሁ ህግ አንቀፅ 1719(1) ላይ ተዋዋይ ወገኖች የመዋዋል ነፃነት እንዳላቸዉ ሁሉ የሚዋዋሉበትን ዉል አቀራረፅ የመወሰን ነፃነትም እንዳለቸዉ በግልፅ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በመሆኑም በተለየ ሁኔታ በህግ ዉሉ በዚህ መልክ ይቀመጥ ካልተባለ በስተቀር ተዋዋዮቹ ወገኖች ዉላቸዉን በፈለጉት ፎርም ማድረግ ይችላሉ፡፡ @consite🏗

👉 የ6ኛው ዙር የ40/60  ንግድ ቤቶች የጨረታ አሸናፊዎች ዝርዝር

👉 local Abisinya ,east ,Adama, Habesha Available 👉8-24 available 👉fair price ☎️0976809090 Goin http://t.me/Honeststeel Adr
+1
👉 local Abisinya ,east ,Adama, Habesha    Available 👉8-24 available 👉fair price ☎️0976809090 Goin http://t.me/Honeststeel Adress jemo and anfo 105

💥AY የአርማታ ብረት (ፌሮ) አቅራቢ የዛሬ 21/10/2017 ዋጋ ዝርዝር ✅8 - 775 ✅10 - 1240 ✅12 - 1680 ✅14 - 2220 ✅16 - 2740 ✅20 - 4950 🙌 የጥራት ደረጃቸው
+9
💥AY የአርማታ ብረት (ፌሮ) አቅራቢ የዛሬ 21/10/2017 ዋጋ ዝርዝር ✅8 -   775 ✅10 - 1240 ✅12 - 1680 ✅14 - 2220 ✅16 - 2740 ✅20 - 4950 🙌 የጥራት ደረጃቸው ከፍ ያለ ግሬድ 7️⃣5️⃣ የሀገር ውስጥ ብረቶችን ከኛ ያገኛሉ 📍 አድራሻ - ተክለሀይማኖት      ስልክ 📲 0953420000                    0953430000 🗺️ ለአዲስ አበባ ደንበኞቻችን ከ 50 ኩንታል በላይ ሲገዙ ነፃ የመጫኛ መኪና እናመቻቻለን 🌐 https://t.me/+-TGIf3jPLFEyMzc0 የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ የየእለቱን ዋጋ ይመልከቱ

Procurement of Water Drilling /የጥልቅ ዉሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ግዥ/ The time zone is: East Africa Time (GMT+3:00) Package Information Invitation Date Jun 12, 2025 Procurement Reference No BHU-NCB-W-0089-2017-BID-Open Procurement Category Works Market Type National Procurement Method Open Procurement Classification Code Title 20110000 የጥልቅ ጉድጓድ ቁፋሮ እና ኦፕሬሽን/አሰራር መሳሪያዎች Procuring Entity Bule Hora University Site Visit Schedule Not Applicable Bid Submission Deadline Jul 4, 2025, 7:34:17 AM Bid Opening Schedule Jul 4, 2025, 8:04:17 AM መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነዉ፡፡  የጨረታዉ አሸናፊ ዕቃዎቹን በራሱ ትራንስፖርት በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ንብረት ክፍል ድረስ ገቢ ወይም ኢንስታሌሽን አድርጎ ክፍያዉን ይቀበላል፡፡  ጨረታዉ በመንግስት የግዥ መመሪያ፤ ህግ እና ደንብ መሰረት የሚመራ ይሆናል፡፡ ማሳሰቢያ፡- ጨረታዉ ላይ መሳተፍ የሚፈልግ ማንኛዉም ተጫራች የኢትዮጵያ ዲጅታል መታወቂያ ካርድ ሊኖረዉ ይገባል፡፡ ማንኛዉም ተጫራች ጨረታዉ ከመከፈቱ በፊት የጨረታ ማስከበራዉን በአካል ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የግዥ አስተዳደር ዳይሮክቶሬት ቢሮ ቁጥር 124 ድረስ ማምጣት አለበት፡፡ ለተጨመሪ ማብራሪያ፡ ስልክ ቁጥር ፡- 0464430174 /0911728310 Apply online on EGP

Contact if you need easily apply on EGP for each tender document preparation such as methodology and work program @BidandTenderBot

PROCUREMENT OF FENCE,GUARD HOUSE & ROOF MAINTENANCE The time zone is: East Africa Time (GMT+3:00) Package Information Invitation Date Jun 23, 2025 Procurement Reference No MInT-NCB-W-0075-2017-BID-Open Procurement Category Works Market Type National Procurement Method Open Clarification Request Deadline Jul 3, 2025, 5:00:00 PM Pre-Bid Conference Schedule Not Applicable Site Visit Schedule Not Applicable Bid Submission Deadline Jul 14, 2025, 10:00:00 AM Bid Opening Schedule Jul 14, 2025, 10:30:00 AM Notice Terms and Conditions The Ministry of Innovation and Technology has the right to reject the BID fully or partially Application online on EGP

Construction of a training biogas plant at ( foundation block work) Package Information Invitation Date May 26, 2025 Procurement Reference No JU-NCB-W-0087-2017-BID-Open Procurement Category Works Market Type National Procurement Method Open Lot Information Object of Procurement Lot-58 Construction ofa training biogas plant at ( foundation block work) Description Not Available Lot Number 1 Clarification Request Deadline Jun 5, 2025, 5:00:00 PM Pre-Bid Conference Schedule Not Applicable Site Visit Schedule Not Applicable Bid Submission Deadline Jun 30, 2025, 10:00:00 AM Bid Opening Schedule Jun 30, 2025, 10:30:00 AM Average Annual Turnover The peak annual construction turnover calculated as total certified payments received for contracts in progress or completed within the last 2 (two) years must exceed 72,000,000ETB (Seventy two million Ethiopian birr) Application on EGP

ደሞዝ አልከፈልከኝም በሚል ምክንያት አሰሪውን የገደለ ወንጀለኛ በ21አመት ፅኑ እስራት ተቀጣ፡፡ ተከሳሹ ጌቱ መስፍን ይባላል፤ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው ነሀሴ 27 ቀን 2014 ዓ/ም ከረፋዱ 4 ሰ
+1
ደሞዝ አልከፈልከኝም በሚል ምክንያት አሰሪውን የገደለ ወንጀለኛ በ21አመት ፅኑ እስራት ተቀጣ፡፡ ተከሳሹ ጌቱ መስፍን ይባላል፤ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው ነሀሴ 27 ቀን 2014 ዓ/ም ከረፋዱ 4 ሰዓት ከ30 ሲሆን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ለገሃር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ኖህ ሪል ስቴት ከሚያሰራው ህንፃ 16ኛ ጅምር ፎቅ ላይ ነው። ሟች ሀጂብ ያሲን የተባለው ግለሰብ ከኖህ ሪል እስቴት ኮንትራት በመውሰድ ከስሩ በርካታ ሰራተኞችን ቀጥሮ የሚያሰራ ግለሰብ ነው። ነሀሴ 27 ቀን 2014 ዓ/ም የዘወትር ስራውን ለማሰራት ሰራተኞችን ወደ የስራቸው ያሰማራል። ተከሳሽም ሟች የነበረበት ቦታ ጭር ማለቱን እና ማንም አለመኖሩን እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመውሰድ ደሞዜን ከለከልከኝ በሚል ምክንያት በተፈጠረ አለመግባባት ሟች ሀጂብ ያሲንን ስራ እየሰራ ባለበት 16ኛ ፎቅ ላይ በፌሮ ብረት ግንባሩን በመምታት እና አንገቱን በሽቦ ገመድ በማነቅና በማሰር ህይወቱ እንዲያልፍ በማድረግ ሟችን ከህንፃው ተሸክሞ በማውረድ የህንፃው መሰረት ስር የሚገኝ የተጠራቀመ ውሃ ውስጥ አስከሬኑን በመጣል ከአካባቢው ይሰወራል። የወንጀሉ መፈፀም ሪፖርት የደረሰው ፖሊስ ወንጀል ፈፃሚውን ለመያዝ በተደረገ ጥረት ተከሳሽ ጌቱ መስፍን ወንጀሉን ከፈፀመ በኋላ ምንም እንዳልተፈፀመ በኔጌሌ ቦረና ከተማ በአንድ ተቋም ውስጥ ተቀጥሮ በመስራት ላይ እንዳለ በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል። በተከሳሽ ጌቱ መስፍን ላይ ለሚመለከተው የፍትህ አካል በመላክ ክስ እንደተመሰረተበት የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ ተከሳሽ ጌቱ ጥፋተኛ ሆኖ በማግኘቱ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት በ21 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ እንደተወሰነበት ገልጿል። አዲስ አበባ ፖሊስ

A variety of modern window designs and styles, including sliding, tilt-and-turn, casement, and pivoting windows. These versat
+2
A variety of modern window designs and styles, including sliding, tilt-and-turn, casement, and pivoting windows. These versatile options offer different functionalities, aesthetics, and ventilation possibilities for any space .. ከቱርክ በምናስመጣቸው UPVC ማቴሪያሎች በተለያዩ ዲዛይኖች እንደፍላጎትዎ በሮች፣ መስኮቶች እና ፓርቲሽኖች የፈለጉት ብዛት በሰዓቱ አምርተን ገጥመን እናስረክንዎታለን! አድራሻ 📍ጋዜቦ አደባባይ ከሙልሙል አጠገብ 📞+251930099146/45

👉 INTERCON Construction Chemicals ● Concrete Admixtures ● Bonding Agents ● Waterproofings ● Wall Putty, Prime Coat ● Concret
👉 INTERCON Construction Chemicals  ● Concrete Admixtures ● Bonding Agents ● Waterproofings ● Wall Putty, Prime Coat ● Concrete Repair Mortar ● Floor hardener, Epoxy ● Grout, Self-level mortar ● Quartz paint, Contextra ● Tile Adhesive & Tile Joint Fillers  ● Geotextiles and other construction chemicals and materials Tel: 0961955555 Address: Signal, around signal mall

👉ለጨረታ ማስከበሪያ ከመድን የሚቀርቡ ዋስትናዎች (Conditional Bond) ከዚህ በኋላ ተቀባይነት አይኖራቸውም። 💫ስራ ተቋራጮች ለውል ማስከበሪያ ከመድን የሚያቀርቡት ዋስትና Unconditional  መሆን ይጠበቅበታል። 📌 በነባሩ የፌደራል ግዥ መመሪያ በግንባታ ስራ ለተሰማሩ የሃገር ውስጥ ስራ ተቋራጮች በሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ የመድን ዋስትና (Conditional Insurance Bonds) ለጨረታ ማስከበሪያ ተቀባይነት የነበረው ቢሆንም አዲሱ መመሪያ ይህንን አማራጭ አላካተተም። 📌 ለውል ማስከበሪያ ደግሞ  ከአገር ውስጥ የግንባታ ዘርፍ ሥራ ተቋራጮች ወይም መድሐኒት እና የሕክምና መሣሪያዎች አምራች ድርጅቶች ለሚፈጸም ግዥ ከታወቀ የመድን ድርጅት የሚቀርብ በሁኔታ ላይ ተመሠረተ የመድን ዋስትና ቢያቀርቡ ተቀባይነት የነበረው ቢሆንም በአዲሱ የግዥ መመሪያ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ መሆን እንዳለበት ተመላክቷል። N.B. የሃገር ውስጥ መድን ድርጅቶች በብሄራዊ ባንክ በኩል በተሰጣቸው መመሪያ መሰረት በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ዋስትና (Unconditional) መስጠት የማይችሉ ከመሆኑ አንጻር ይህ እንዴት ተፈጻሚ ሊሆን እንደሚችል ሊታሰብበት የሚገባ ጉዳይ ነው። 📌 የአገር ውስጥ ስራ ተቋራጮች እንዲሁም የመድሀኒት እና ሕክምና መሳሪያ አምራች ኢንዱስትሪዎች በሁኔታ ላይ የተመሰረተ (conditional) የቅድሚያ ክፍያ ዋስትና ከታወቀ የመድን ድርጅት ሊያቀርቡ እንደሚችሉ የሚገልፀው አንቀፅ ባለበት ፀንቷል።

BATCODA-Technical Specification.pdf3.07 KB

🔵 ተቋራጮችና የተቋራጭ አማካሪዎች ምዘና እና ደረጃ ይወጣላቸዋል ተባለ ከተያዘዉ ዓመት ጀምሮ ዉጤታማና ተወዳዳሪ  የሆኑ ተቋራጮችና አማካሪዎች እንዲሁም የመንግስት ፕሮጀክቶች ባለቤቶችን ለመለየት እንዲቻል ምዘናና ደረጃ ይወጣላቸዋል ተብሏል፡፡ ‹‹የሃገር ዉስጥ የግንባታ ኢንደስትሪ ዘርፍ ተፎካካሪነት እና ምዘና ›› በተሰኘ መንገድ ነዉ ተመዝነዉ ደረጃ እንደሚሰጣቸዉ የተገለጸዉ፡፡ 🔷 የከተማና መሰረተ ልማት ሚንስቴር ሚንስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ፤የኮንስትራክሺን ዘርፍ የአፈጻጸም ደረጃ ለማሻሻልና የዘርፉን ጤናማነት እንዲሁም  ብቃት ያለዉ ተወዳዳሪ የኮንስትራክሺን ኢንደስትሪ እንዲሆን እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ 🔷 የኮንስትራክሺን ኢንደስትሪ ምክርቤትን  ጨምሮ የሚመለከታቸዉ የዘርፉ ተዋናዮች በግልም ሆነ ባማህበር ያሉ ባለድርሻ አካላት የበኩላቸዉን አስተዋጾ እንዲያበረክቱ ሚኒስትሯ ጠይቀዋል፡፡ 🔷 ዘርፉ ግዙፍ ካፒታል የሚፈልግ፤በሃገርም ሆነ በዉጭ የሚመረቱ ግብዓቶችን የሚጠቀም፤ከፍተኛ የሆነ የሰለጠነ የሰዉ ሃይል የሚያስፈልገዉ፤ቴክኖሎጂዎችን የሚጠቀም  እንደመሆኑ መጠን ከፍተኛ ትኩረትን ይፈልጋልም ሲሉም ሚኒስትሯ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ 🔷 በዚህም በተቋራጮች እና በተቋራጭ አማካሪዎች  ምዘናና ደረጃ እንደሚወጣ እንዲሁም ዉጤቱ ልህዝብ ይገለጻል ያሉት ሚኒስትሯ በሂደቱ ዉጤታማ የሆኑ ባለሙያዎች  እዉቅና እና በጨረታ ወቅት የተለየ እድል የሚያገኙበት ሁኔታ ይመቻችላቸዋል ሲሉም ተናግረዋል፡፡ 🔷 በሚቀጥሉት ጥቂት አመታትም ቢያንስ ወደ 20 ለሚጠጉ ዉጤታማ  የግንባታ ተቋራጮችና አማካሪዎች በየዓመቱ የሚደረገዉን ግምገማና የደረጃ ሊየታን መሰረት በማድረግ  በዉጭ ገበያ ላይ ሃገርን ወክለዉ ተወዳዳሪ ሆነዉ እንዲሰሩ ድጋፍ ይደረግላቸዋል ብለዋል፡፡ 🔷 በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪዉ አጠቃላይ በፕሮጀክቶች አካሄድ ላይ  ያለዉን ዉስብስብ ችግር የሚለይ መፍትሄ የሚሰጥ ማእቀፍ ፤‹‹ኢዝ ኦፍ ዱይንግ ቢዝነስ ኢን ኮንስትራክሺን ሴክተር›› ተግባራዊ ይደረጋልም ብለዋል፡፡ 🔷 አሁን ባለዉ አካሄድ ዘርፉ በአሳሳቢ ደረጃላይ ይገኛል ያሉት ሚኒስትሯ ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ፤ዘርፉን ለማሻሻል ይደረጉ የነበሩ ጥረቶች በተበታተነ መንገድ በመሆኑ፤የዘርፉ ተዋናዮች ለዘርፉ እድገት የበኩላቸዉን አበርክቶ እንዳያደርጉ ችግር ሆኖ መቆቱን አንስተዋል፡፡ 🔷 ሆኖም ዘርፉን ለማሳደግ አሁን ለሚደረገዉ ጥረት ዉጤታማነት እነዚህ ስራዎች በፖሊሲ እና ህጋዊ ማእቀፍ ኖሯቸዉ አፈጻተማቸዉ ወጥ እንዲሆን ቀድሞ የነበረዉ አሰራር በአዲስ ተቀይሮ በስራ ላይ እንደሚዉልም አንስተዋል፡፡ በተጨማሪም ከዚህ በፊት ያልነበረ ኮንስትራክሺን ኢንዱስትሪ አዋጂ በስራ ላይ ከሚገኘዉ የህንጻ አዋጅ ጋር ተቀናጂቶ፤ ኢንደስትሪዉንና የዘርፉን ስራዎች ዘመኑን በዋጀ መልኩ በማካተት በአጭር ጊዜ ዉስጥ በስራ ላይ ይዉላል ሲሉም ተናግረዋል፡፡ (107.8)

👉የቤት ገበያችን ወቅታዊ የቁጥሮች ወሬ ( ከትልቅ ፎቅ የረዘመ ) 📜የሪል እስቴት ኢንቨስትመንትና ግብይት በጥናት በሚመሰረቱ ገላጭ የቁጥር ቀመር ውጤቶች ላይ ተመስርቶ የሚደረግ ነው። ነገር ግን በሀገራችን በየወቅቱ በዘርፉ ያሉትን መረጃዎች አሰናድቶ ገላጭ ቁጥሮችን የሚያሳውቅ ተቋም ስለሌለን ብዙዎች ከኢንቨስትመንትና ግብይት ማሳያ ቁጥሮች ይልቅ ዲዛይንና የቢዝነስ ስትራቴጂ በመኮራረጅ ወይም ተመሳሳይ ባለሙያዎችን በመጋራት ተመሳሳይ ዲዛይንና ግንባታ የግብይት አካሄድንም በመከተል ተመሳሳይ ስህተት እየሰሩ ተመሳሳይ ኪሳራና የመሸጥ ችግር ሲደርስባቸው ቤት ፈላጊዎችም በአቅማቸው ሊገዙት የሚችል የቤት የአማራጭ እጦት እንዲገጥማቸው ሆኗል። የእኛ ቁጥር የሌለን በመሆኑ ሰሞኑን the ethiopian reporter የወጣው ጽሁፍ ሀገራችን በቤት ውድነት መለኪያ መስፈርት (Housing affordability index)  47.1 በማምጣት ከዓለማችን ለዜጎቿ ቤትን በውድ ዋጋ በማቅረብ ሶስተኛ ደረጃን ማግኘቷ ተገልጾ ጉድ እየተባለ ነው። The reoprter በመረጃ ምንጭነት የጠቀሰው የኑሮ ዘይቤ ጉዳዮችን በቋሚነት የሚተነትነው NUMBEO በከተሞች ደረጃ ባወጣው የ2025 ግማሽ ዓመት ወቅታዊ ሪፖርት ላይ መዲናችን አዲስ አበባን የቤት ዋጋን ለአመታዊ የቤተሰብ ገቢ (price to income ratio ) ስሌት 55.8 በማምጣት ከዓለም ላይ ለዜጎቿ ውድ ቤት በማቅረብ ቀዳሚዋ ያደርጋታል። የቁጥሩን ተአማኒነት ለማረጋገጥ ትልሳቢ ያደረጋቸውን መነሻዎች ተመልክቼ ከወቅታዊ የሀገራችን ገበያ አንጻር ለማመሳከር ሞክሬ የሚከተለውን አስተያየት አክዬበት ሌሎች ገላጭ ቁጥሮችንም ለማብራራት ሞክሬያለሁ እነሆ:- የ NUMBEO  ታሳቢዎች ፩) ወርሃዊ የኪራይ ዋጋ በ USD 1) ባለ አንድ መኝታ አፖርትመንት በከተማ መሃል 721.195  2) ባለ አንድ መኝታ በከተማ ዳርቻ 477.50 3) ባለ 3 መኝታ በከተማ መሃል 1831.50 4) ባለ 3 መኝታ በከተማ ዳርቻ 971.50 ፪) የአፓርትመንት ቤቶች መግዣ ዋጋ በካሬሜትር በ USD 1) በከተማ መሃል .... 2545.70 2) በከተማ ዳርቻ .... 1826.75 ፫) ወርሃዊ ደመወዝና የቤት ብድር ወለድ 1) የተጣራ መካከለኛ የወር ገቢ ...196.00 USD 2) የቤት ብድር ወለድ (%)  .... 17.67USD የNUMBEO መረጃዎችን ስንፈትሻቸው የቤቶች ዋጋ ተብሎ ለከተማችን ዳርቻ የተወሰደው የተጋነነ ሆኖ እናገኘዋለን።በወቅታዊ ገበያ በከተማ ዳርቻ ያሉ አፓርትመንት ቤቶች አማካኝ ዋጋ ከ 1000USD በላይ አይዘልቅም። ለማነጻጸሪያነት በአፍሪካ ደረጃ የሪል እስቴት ኢንቨስትመንት መረጃዎችን የሚተነትነው www.theafricanvestor.com ከሳምንት በፊት ባሰራጨው መረጃ መሰረት የአዲስ አበባ የአፓርትመንት ቤቶች ወቅታዊ አማካይ ዋጋ ከ 1500- 1680USD/Sqm እንደሆነ ይገልጽልናል። ወቅታዊ ሁኔታዎችን ስናገናዝብ የ theafricanvestor የዋጋ ግምት የተሻለ ገላጭ ሆኖ እናገኘዋለን። በNUMBEO ታሳቢዎች የተሰሉ የዘርፉ አመላካች ቁጥሮችና ገለጻዎቻቸው **** ፩) የዋጋ ና ገቢ ንጽጽር ( Price to Income ratio) 55.77 ( ከተማችንን ከዓለም ለዜጎቿ በውድ በማቅረብ በአንደኝነት ያስቀምጣታል) ። የ theafricanvestor መረጃዎች የNEMBEO የዋጋ ለገቢ ስሌት ላይ ብንጠቀም ስሌቱ 42.85 ይሆናል። በዚህም በተሻሻለ ስሌትም ቢሆን ሀገራችን አንደኝነቷን አስጠብቃ ለዜጎቿ ቤት መግዛት እጅግ አዳጋች (Extremely unaffordable )የሆነባት ያደርጋታል። ይህ ቁጥር ጤናማ ሆኖ ዜጎች ቤት እንዲኖራቸው የሚሆነው የproce to income ratio ከ 5 ያነሰ እንዲሆን ይጠበቃል። ለዚህም የቤት ዋጋ እንዲቀንስ የሚያደርጉና የዜጎችን ገቢ የሚያሳድጉ  ተግባራት ሊሰሩ ይገባል። ፪)  Mortgage as percentage income ( የቤት ብድርን ከገቢ ጋር ንጽጽር) በNEMBEO ታሳቢዎች መሰረት ይህ ምጣኔ 1015.73% ሲሆን ይህ ቁጥር መካከለኛ ገቢ አላቸው የሚባሉ ዜጎች በሃያ ዓመታት የሚከፈል ብድር ቢያገኙ ሊከፍሉ እንደማይችሉ የሚያሳይ ያለውን የቤት ዋጋ ውድነትና የብድር ወለድ ውድነት ነው።ይህ ቁጥር ከ 28-35 እንዳይበልጥ ይመከራል። ፫) Loan affordability index ( የዜጎች የመበደር አቅም መለኪያ).... 0.1 ይህ መካከለኛ ገቢ ያላቸው ዜጎችን ለብድር ብቁ መሆን ለማሳየት የሚሰራ ስሌት ሲሆን አማካይ የወር ደመወዝን ከአማካይ የቤት ዋጋ ጋር በማካፈል በመቶኛ የሚገለጽ ቁጥር ሲሆን ቁጥሩ ከፍ ሲል የመበደር አቅም ከፍ ማለቱን ያሳያል። በዚህ ስሌት መሰረት የእኛ ቤት ለግዛት የመበደር አቅም እጅግ የማይቻል ( Severe Housing Crisis )  መሆኑን የሚያሳይ ሲሆን በገበያ ውስጥ ካሉት ቤቶች ውስጥ 10% የሚሆኑት ብቻ ገዢ ሊያገኙ እንደሚችሉ የሚያስረዳም ነው። ፬) Price to Rent Ratio ( በግዢና በኪራይ መካከል ያለ ንጽጽር) በከተማ መሃል ...13.03 በከተማ ዳርቻ .... 16.56 ይህ ቤት መግዣና አመታዊ የኪራይ ዋጋን በማካፈል የሚገኝ ቁጥር ሲሆን የከተማ መሃሉ ከመግዛት ይልቅ መከራየት የተሻለ እንደሆነ ሲያሳይ በከተማ ዳርቻ  ከመከራየት መግዛት የተሻለ እንደሆነ ያሳያል። ፭) Gross Rental Income ( ጠቅላላ ዓመታዊ የኪራይ ገቢን ከቤት መግዣ ዋጋ ጋር የሚደረግ ንጽጽር) በከተማ መሃል ....7.67% በከተማ ዳርቻ .... 6.04% ይህ ስሌት ገዝተው ለማከራየት ለሚያስቡ የሚጠቅም ሲሆን ቁጥሩ ከ 6% ከበለጠ ለቤት ገዝቶ አከራዮች ጥሩ እንደሆነ ይገልጻል። በዚህም መሰረት ቤት ገዝቶ ለማከራየት በከተማ መሃል ያለው ወቅታዊ ገበያ ከከተማ ዳርቻ የተሻለ እንደሆነ ያሳያል። ስናጠቃልለው ወቅታዊው የቤት ኢንቨስትመንትና ገበያ ነገር እንዲህ ሊባል ይችላል ፩) ለቤት ገዢዎች :- በጣም ለጥቂቶች ካልሆነ የማይቻል መሆኑን ያሳያል። ፪) አልሚዎች:- የቤት ገዢዎችን አቅም ያገናዘቡ ቤቶችን በጥናት ላይ ተመስርተው መገንባት እንዳለባቸውና በተመሳሳይ ሁኔታ ከቀጠሉ አይተውትም ሰምተውትም የማያውቁት የቁም ኪሳራ ሊደርስባቸው እንደሚችል አስበው ባሉበት ደረጃ ቆም ብለው መከለስ ያለባቸው ከልሰው ለገበያው የሚመጥኑ ቤቶች መገንባት እንዳለባቸው ያሳስባል። ፫) መንግስት :- በቀመር ውጤት የተገለጹት ቁጥሮች እንዲሻሻሉ የሚያደርጉ የመሬት አቅርቦትን በቅናሽ ( በነጻ) በማቅረብ፣ ከቀረጥ ነጻ መብቶችን በመፍቀድ፣ ከቤት ግብይት ጋር የተያያዙ ቀረጦችን በመተው፣ ለቤት አልሚዎችም ለቤት ገዢዎችም የሚሆን ብድር እጅግ አነስተኛ በሆነ ብድር እንዲቀርብ በማድረግ፣ የዜጎች ገቢን ሊያሳድጉ የሚችሉ የኢንቨስትመንትና የስራ ዕድሎችን በማስፋት ... ፬) ቤት ገዝተው ማከራየት ለሚያስቡ :- የከተማ መሃል ቤቶች የተሻለ ( 7.67%) ገቢ ሊያስገኙላቸው ስለሚችሉ ከተማ መሃል ላይ ትኩረት ቢያደርጉ ይመከራሉ። ኢ/ር ደሳለኝ ከበደ የሪል ስቴት ቢዝነስ አማካሪ @etconp

موقعیت جغرافیایی

🧱New Point Bricks factory 🧱新点砖厂*✨ 🧱Our Bricks:- Tough,Don't decay, warp or twist, resistance to water & harsh soils, don't
+9
🧱New Point Bricks factory 🧱新点砖厂*✨ 🧱Our Bricks:- Tough,Don't decay, warp or twist, resistance to water & harsh soils, don't fade....🧱🧱👉🧱🧱🧱 ጥራት ያላቸውን እና ለተለያዩ ለግንባታ አገልግሎት የሚውሉ የቀይ ሸክላ (ጡቦችን) እናመርታለን። 🧱 ለሙሉ የቤት ግንባታ፣ 🧱ለባንክ ቤት ካዝና፣ 🧱 ለግቢ አጥር ማጠሪያ፣ 🧱 ለመንገድ ዳር ጠርዞች፣ 🧱  ለሆቴሎች፣ሬስቶራንት፣እና ካፌዎች ማሳመሪያ ፣ 🧱 ለx-ray ክፍሎች፣ 🧱 ለፍሳሽ ማንዋሎች፣ 🧱 ለኪችን ሲንክ ማስቀመጫ ፣ 🧱 ለሻወር ገንዳ ማሰቀመጫ፣ 🧱 የPBC ፍሳሽ ማስወገጃ ለመሸፈን፣ 🧱 ለአበባ መትከያ 🧱 ለብረት ማቅለጫ ፈርኒስ፣ 🧱 ለፒዛ ኦቭን፣ 🧱 ለምድጃ፣ 🧱 ለቆሻሻ ማቃጠያ......🧱🧱. Join Telegram channel https://t.me/+d8A-rQlF5p5lZThk for more information contact 🧱📲👉0912854327&0902378888 thank you 谢谢

በአለማችን ላይ ዌብሳይት በደንብ ከሚጠቀሙ ሀምሳ ሀገራት መሀከል የኢትዮጵያ ስም የለም!🏗 - ሌላው የሚገርመው በአለማችን ላይ 2 መቶ ሚሊዮን የሚሆኑ አክቲቭ ዌብሳይቶች አሉ ። እና ይህን ያህል ቁ
በአለማችን ላይ ዌብሳይት በደንብ ከሚጠቀሙ ሀምሳ ሀገራት መሀከል የኢትዮጵያ ስም የለም!🏗
- ሌላው የሚገርመው በአለማችን ላይ 2 መቶ ሚሊዮን የሚሆኑ አክቲቭ ዌብሳይቶች አሉ ። እና ይህን ያህል ቁጥር ካለው የአለማችን ዌብሳይቶች ውስጥ በኢትዮጵያ ያለው የተመዘገበ ዌብሳይት ቁጥር ግን ከ18 እስከ 25 ሺህ ብቻ እንደሆነ ይገመታል ። - እንግዲህ በአለም አቀፍ ደረጃ በየአንድ ሰአቱ 4 ሺህ አዳዲስ ዌብሳይቶች በሚከፈቱበት ወቅት ላይ. . የኛ ሀገር የድረገፅ ተጠቃሚዎች ሰላሳ ሺህ እንኳን አለመሙላቱ ያስገርማል ። - ቢያንስ ቢዝነስ የሚሰሩ ሰወች እንኳን ስለ ድረገፅ ያላቸው ግንዛቤ የሚያስገምት ነው ። 1964 ላይ ናይክ ሲመሰረት ባሉት ሱቆቹና አከፋፋዮቹ አማካኝነት ገበያው አሪፍ ነው የተባለ በቀን አራት ጫማዎች ይሸጥ ነበር። ባብዛኛው ግን ናይክ ይሸጥ የነበረው ሶስት ጫማ ነው ። ከአመታት በኋላ ዛሬ ላይ ደሞ በባለፈው አመት ብቻ የናይክ ሽያጭ በቀን ሁለት ሚሊየን ጫማ ደርሷል ። ከዚህ ውስጥ ደግሞ ግማሽ ፐርሰንት የሚሆነው ሽያጭ የተከናወነው በኦንላይን በተደረገ ግብይት ነው ። ናይክ ወደዚህ የኦንላይን ግብይት ባይገባ አንድ ሚሊየን ሰወች ቤታቸው ቁጭ ብለው ላይገዙት ይችሉ ነበር እንደማለት ነው ። ዌብሳይት እቃ ለሚሸጡ ብቻ አይደለም ለአገልግሎት ሰጭዎች እንዲሁም ላብዛኛው ድርጅቶችና ተቋማት የሚጠቅም ነገር ነው። ይህን ይህን ስናይ የዌብሳይት ጥቅም ገና ብዙ አልገባንም ማለት ይቻላል! - ዛሬ ላይ ቢዝነስ ካርድ መስጠት ባህላዊ ዘዴ እየሆነ መጥቷል። ቢዝነስ ካርድ አለህ ? አይባልም። ዌብሳይትህን ንገረኝ ነው የሚባለው። አገልግሎት ሰጭም ሆነ የተለያዩ ምርቶችን ሻጭና አምራች ሆኖ ዌብሳይት ከሌለው አግባብ አይደለም። Via~ዋሲሁን ተስፋዬ @consite🏗