Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
رفتن به کانال در Telegram
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service
نمایش بیشتر3 587
مشترکین
-424 ساعت
+107 روز
+4230 روز
آرشیو پست ها
የማዘጋጃ ቤት የቅየሳ ቴክኒሻን ባለሙያ ተግባርና ኃላፊነቶች ምን ምን ናቸው?
የማዘጋጃ ቤት ቅየሳ ቴክኒሻን (ቅየሳ ባለሙያ) በከተማ ፕላንና ልማት ውስጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወተው ሲሆን፣ ዋና ተግባሩ መሬትን መለካት፣ ድንበር መለየት እና የመሬት ካርታ ማዘጋጀት ነው።
ዋና ዋና ተግባራትና ሃላፊነት
1. የመሬት ቅየሳ እና መለካት
የቦታ ድንበር መለየት፦ የአንድን መሬት፣ ቤት ወይም ንብረት ትክክለኛ ድንበር በማውጣት ማሳየት።
መለኪያ ማካሄድ፦ ዘመናዊ የቅየሳ መሳሪያዎችን (ለምሳሌ ቶታል ስቴሽን፣ ጂፒኤስ፣ ድሮን) በመጠቀም የመሬቱን ስፋት፣ ርዝመት እና ቅርፅ መለካት።
የከተማ ካርታ ማዘመን፦ አዳዲስ ህንጻዎች፣ መንገዶች እና የመሬት ክፍፍሎች እንዲታዩ የከተማውን ካርታ በየጊዜው ማዘመን።
2. የፈቃድ አሰጣጥ ሂደት ውስጥ መሳተፍ
የህንጻ ፈቃድ ፍተሻ፦ አንድ ሰው ቤት ለመገንባት ፈቃድ ሲያመለክት፣ ያቀረበው ፕላን ከሚፈቀደው የመሬት ድንበር እና የከተማ ፕላን ጋር የሚስማማ መሆኑን ማረጋገጥ።
የድንበር ማረጋገጫ፦ ንብረት ሲሸጥ ወይም ሲወረስ፣ የመሬቱ ድንበር ትክክለኛ መሆኑን በቦታው በመቅየስ ማረጋገጥ።
3. የሕገ-ወጥ ግንባታ ክትትል
ቁጥጥር፦ በከተማው ውስጥ ያለ ፈቃድ ወይም ከፈቃድ ውጭ የሚደረግ ግንባታ መኖሩን መከታተል።
ማስቆም እና ሪፖርት ማድረግ፦ ሕገ-ወጥ ግንባታ ሲገኝ ለማስቆም እና ለሕግ ባለስልጣን ሪፖርት ማድረግ።
4. የዳሰሳ ጥናት እና ሪፖርት ማቅረብ
ሪፖርት ማዘጋጀት፦ ባካሄደው ቅየሳ መሰረት ቴክኒካል ሪፖርት፣ ካርታ እና ንድፍ በማዘጋጀት ለበላይ አካል ማቅረብ።
መረጃ አያያዝ፦ የተለያዩ የመሬት መረጃዎችን (ዲጂታል እና አናሎግ) በማከማቸት፣ በማደራጀት እና ማስተዳደር።
5. ከህብረተሰቡ ጋር መገናኘት
ምክር መስጠት፦ ለአገልግሎት ፈላጊ ዜጎች የመሬት ድንበር፣ የፈቃድ አሰጣጥ ሂደት እና የከተማ ፕላን ደንቦችን በተመለከተ ማስረዳትና መምከር።
አለመግባባት መፍታት፦ በጎረቤቶች መካከል የድንበር ክርክር ሲፈጠር በቦታው በመቅየስ እውነታውን በማስረዳት አለመግባባቱን ለመፍታት መርዳት።
6. የመሳሪያ እንክብካቤ
የመሳሪያ አያያዝ፦ ውድ የሆኑ የቅየሳ መሳሪያዎችን (ቶታል ስቴሽን፣ ቴዎዶላይት፣ ወዘተ) በአግባቡ መጠቀም፣ መንከባከብ እና ማስተካከል።
- ማዘጋጃ ቤት ውስጥ የቅየሳ ቴክኒሻን ሆኖ መስራት ማለት የከተማውን ስርአት እና ውበት ለማስጠበቅ፣ የዜጎችን የባለቤትነት መብት ለማረጋገጥ እና ለዘላቂ ልማት መሰረት የሆነ መረጃ በማቅረብ ረገድ ቀጥተኛ አስተዋጽኦ ማበርከት ነው።
@consite🏗
ለጨረታ ማስከበሪያ ከመድን የሚቀርቡ ዋስትናዎች (Conditional Bond) ከዚህ በኋላ ተቀባይነት አይኖራቸውም። ስራ ተቋራጮች ለውል ማስከበሪያ ከመድን የሚያቀርቡት ዋስትና Unconditional መሆን ይጠበቅበታል።
- በነባሩ የፌደራል ግዥ መመሪያ በግንባታ ስራ ለተሰማሩ የሃገር ውስጥ ስራ ተቋራጮች በሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ የመድን ዋስትና (Conditional Insurance Bonds) ለጨረታ ማስከበሪያ ተቀባይነት የነበረው ቢሆንም አዲሱ መመሪያ ይህንን አማራጭ አላካተተም።
- ለውል ማስከበሪያ ደግሞ ከአገር ውስጥ የግንባታ ዘርፍ ሥራ ተቋራጮች ወይም መድሐኒት እና የሕክምና መሣሪያዎች አምራች ድርጅቶች ለሚፈጸም ግዥ ከታወቀ የመድን ድርጅት የሚቀርብ በሁኔታ ላይ ተመሠረተ የመድን ዋስትና ቢያቀርቡ ተቀባይነት የነበረው ቢሆንም በአዲሱ የግዥ መመሪያ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ መሆን እንዳለበት ተመላክቷል።
N.B. የሃገር ውስጥ መድን ድርጅቶች በብሄራዊ ባንክ በኩል በተሰጣቸው መመሪያ መሰረት በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ዋስትና (Unconditional) መስጠት የማይችሉ ከመሆኑ አንጻር ይህ እንዴት ተፈጻሚ ሊሆን እንደሚችል ሊታሰብበት የሚገባ ጉዳይ ነው።
- የአገር ውስጥ ስራ ተቋራጮች እንዲሁም የመድሀኒት እና ሕክምና መሳሪያ አምራች ኢንዱስትሪዎች በሁኔታ ላይ የተመሰረተ (conditional) የቅድሚያ ክፍያ ዋስትና (Advance Payment Guarantee) ከታወቀ የመድን ድርጅት ሊያቀርቡ እንደሚችሉ የሚገልፀው አንቀፅ ባለበት ፀንቷል።
@consite🏗
+2
ለመረጃ | ብሄራዊ ባንክ ውል ማስከበሪያ ና ቅድመ ክፍያ ዋስትናን በተመለከተ ከዚህ ቀደም ለኢንሹራንስ ኩባንያዎች ያስተላለፈው መመሪያ
📢 Join: @procinsightet
📬 Contact: @Procinsight_bot
👵 Discussion: @procinsightet2
👉 INTERCON Construction Chemicals
● Concrete Admixtures
● Bonding Agents
● Waterproofings
● Wall Putty, Prime Coat
● Concrete Repair Mortar
● Floor hardener, Epoxy
● Grout, Self-level mortar
● Quartz paint, Contextra
● Tile Adhesive & Tile Joint Fillers
● Geotextiles and other construction chemicals and materials
☎️ Tel: 0961955555
🔹 Address 1: Signal road, around
Dinberwa Hospital
🔹 Addres 2: Wellosefer, Infront of
Dani Plaza
👉 የደረሰኝ ሕትመት ጠይቀው ያልተረከቡ ግብር ከፋዮች በ5 የሥራ ቀናት ውስጥ ሪፖርት አንዲያደርጉ ጥሪ ቀረበ
https://t.me/ethioconradio
▪️ማሳሰብያ
🫵ለደረጃ አንድ ኮንትራክተር አባላት በሙሉ!
ጉዳዩ፡- የአገር ውስጥ ተቋራጮች የተወዳዳሪነት ደረጃ ለማውጣት የተዘጋጀ መጠይቅን (Contractor Rating Questionnaire) ይመለከታል፤
የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን ኢኒሼቲቭ (CITI 2025-2050) የኢትዮጵያን የኮንስትራክሽን ዘርፍ ለሚቀጥሉት 25 ዓመታት ለማዘመን በነሐሴ 2017 ዓ.ም (August 2025) ይፋ ተደርጓል። ይህ ኢኒሼቲቭ በርካታ ጉዳዮችን የሚዳስስ ሆኖ በዋነኝነት የዘርፉን የስራ ቅልጥፍና ማሻሻል እና የተዋናዮቹን ተወዳዳሪነት መዳሰስንና ማሻሻልን ያካትታል፡፡ ዘርፉ ካለበት ችግር ተላቆ ኢኮኖሚውን በተሟላ መልኩ እንዲደግፍና በሂደት ቢያንስ ወደ 20 የሚጠጉ ኩባንያዎች ከአገር ውጪ ጭምር ተሳታፊና ውጤታማ እንዲሆኑ ማስቻልን ያለመ ነው፡፡
ስለሆነም ማህበራችን ይህን ኢኒሼቲቭ ለመተግበር በዘርፉ የሚገኙ ተዋንያንን እንቅስቃሴ በአገር አቀፍ ደረጃ እንዲያጠና እና እንዲያስተባብር ከተዋቀረው እስቲሪንግ ኮሚቴ በአባልነት ተመርጦ ወደ ስራ ገብቷል፡፡
ስለዚህ ይህንን በኢንዱስትሪው አይነተኛ ለውጥ ሊያመጣ የሚችል ተግባር ለመጀመር መረጃዎችን አሰባስቦ በመተንተን የኢትየጵያ ኮንስትራክሽን ዘርፍ ተዋናዮች ደረጃ (2025 Ethiopian construction Sector Competitiveness Level) ይፋ ማድረግ ስለታሰበ የአገር ውስጥ ስራ ተቋራጮች የተወዳዳሪነት መጠይቅ (Contractor Rating Questionnaire) ተዘጋጅቶ በማህበራችን በኩል መረጃው እንዲሰበሰብ በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር መመሪያ ተላልፏል፡፡
በመሆኑም መጠይቁን ወስዳቹህ ሞልታችሁ ያልመለሳችሁ ደረጃ 1 አባላት በአንድ ሳምንት ውስጥ ሞልታችሁ በተቀመጠው ኢሜይል እንድትልኩልን እያልን መጠይቁ ያልደረሳቹህ ደረጃ 1 አባላት ከዚህ ደብዳቤ በታች የተቀመጠውን ሶፍት ኮፒ መጠይቅ በመሙላት፣ በድርጅታችሁ ባለቤት ወይም ከፍተኛ የስራ ኃላፊ ተፈርሞ እና ማህተም ተደርጎበት በአንድ ሳምንት ውስጥ ለከ/መ/ል/ሚኒስቴር የመሰረተ ልማት ዘርፍ ከፍተኛ አማካሪ ዶ/ር በቀለ ንጉሴ በ WhatsApp ስልክ ቁጥር +251 903 10 64 50 እና በኢሜል አድራሻ infrastrucure@mui.gov.et እንዲመልሱ በአክብሮት እየጠየቅን፣ የሚሰጡት ምላሽ የወደፊት የብቃት ማረጋገጫ ደረጃዎ (Certificate of Competence Rating) ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ እንደሚኖረው ልብ ብለው መጠይቁን በጥንቃቄ እና በትክክል እንዲሞሉ አበክረን እናሳስባለን። ለዚህ ሀገራዊ ጥረት ለሚያደርጉት ፈጣን ትብብር ከልብ እናመሰግናለን።
ከሠላምታ ጋር፣
አባሪ፡ 18 ገጽ የኮንትራክተር ደረጃ ምዘና መጠይቅ
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
