cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

አሞን ዘሩፋኤል

በዚህ መንፈሳዊ ቻናል ጠቃሚ የሆኑ የቤተክርስቲያን ትምህርቶች መዝሙሮች መንፈሳዊ ግጥሞች የቅዱሳንን ምስሎች እና የተለያዪ የአገልጋዮችን ፎቶዎች አንለቃለን ተከታተሉን

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
179
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Repost from N/a
<<እንጾማለን!!>> አስ 4፥16 ከነገ ጀምሮ ኦርቶዶክሳዊ የሆነ ሁሉ ሊናገረው ይሚገባ ቃል፣ ሊተገብረው የሚገባ መንፈሳዊ ተግባር ይህ ነው። <<ለእኔም ጹሙ ሦስት ቀን ሌሊቱንና ቀኑን አትብሉም፥ አትጠጡም እኔና ደንገጥሮቼ ደግሞ እንዲሁ እንጾማለን።>> ይህን ያለችው አስቴር ናት።ይህን እንድትል ያስገደዳት መከራ ነው።በወገኖቿ ላይ ሞት አንዣቦ ነበር። ሞቱን ወደሕይወት ለመለወጥ ከሚያስፈልጉ ነገሮች ዋነኛው ጾም ነው። ስለዚህ ነው <<እንጾማለን !>> ያለችው እኛስ? ከመከራ ከሞት ነፃ ነን ? እኛም ከመከራ፣ከሞት ያድናልና። <<እንጾማለን>> እኛም ከነገ ጀምሮ እንጾማለን ምክንያቱም ዛሬ በዓለ መንፈስ ቅዱስን አክብረናል ።በዓለ ፋሲካን ፈጽመናል። ነገ ጾመ ሐዋርያት ይጀምራል።ስንበላ ቆይተናል።አሁን <<እንጾማለን!>> በቃ ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርም። በእግዚአብሔር ቃልና በጾምም ነው እንጂ።ስለዚህ እንጾማለን። ጌታችን እንዲህ አስተምሮናልና። <<በዚያን ጊዜ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው፦ እኛና ፈሪሳውያን፥ ብዙ ጊዜ የምንጦመው፥ ደቀ መዛሙርትህ ግን የማይጦሙት ስለ ምንድር ነው? አሉት። ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፥ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ።>> ማቴ ፱÷፲፬ ሙሽራው ክርስቶስ ነው የሚወሰድበት ጊዜው ዕርገት ነው ጌታችን አርጓል ሚዜዎች የሚጾሙበት ጊዜደርሷል። በአሮጌ አቆማዳ የተመሰለ የሐዋርያት ሰውነታቸው በመንፈስ ቅዱስ መውረድ ታድሷል።አሮጌው አቆማዳ ከአሬጌው ወይን ጋር አልፏል።አሁን አዲሱ የወይን ጠጅ በመንፈስ ቅዱስ በታደሰው አዲስ አቁማዳ የሐዋርያት ሰውነት ተጨምሯል። <<ያን ጊዜ ይጾማሉ።>> ይጾማሉ የተባለው ጾመ ሐዋርያት ነው። የሥራቸው መጀመሪያ ጾም ነው። ስለዚህም እኛም ኦርቶዶክሳውያን ክርስቶስን መስለን ሐዋርያትን ተከትለን <<እንጾማለን!>> ሀገራችን ከመከራ ሕዝባችን ከሞት እንዲተርፍ በረከተ ሥጋን በረከተ ነፍስን ለማግኘት <<እንጾማለን>> የቅዱሳን ሐዋርያት ጾም የእኛም የልጆቻቸው ጾም ነው። ስለዚህ ኦርቶዶክሳዊ ሁሉ ከነገ ሰኔ ፮-፲-፳፻፲፬ ዓም ጀምሮ እስከ ሀምሌ ፭-፲-፳፻፲፬ ድረስ <<እንጾማለን!!!>> እንበላለን ማለት ሳያሳፍር እንጾማለን ማለት ሊያሳፍር አይገባም!!። ስለዚህ ሁላችን እንጾማለን !! ጾሙን ፈጽመን የቅዱሳን ሐዋርያትን በረከት እንድናገኝ አምላካችን ይፍቀድልን !! መልካም ጾመ ሐዋርያት መጋቤ ሐዲስ ምስጢረ ሥላሴ ማናዬ ሰኔ ፭-፲-፳፻፲፬ ዓ/ም
نمایش همه...
​​ፆመ ሐዋርያት አንዳንዶች የሰኔ ፆም የቄስ ፆም ነው በሚል ከመፆም ወደኋላ ሲሉ ይታያሉ ነገር ግን ቅድስት ቤተክርስቲያን በአዋጅ ከምትፆማቸው ሰባት አፅዋማት አንዱ እንደመሆኑ መጠን እያንዳንዱ ክርስቲያን ቢፆመው እጅግ በርካታ በረከቶችን ያገኝበታል ከነዚህም ጥቂቶችን እነሆ 1.በረከተ ሐዋርያት ይገኝበታል ይህን ፆም መጀመርያ ፆመው እንድንፆመው ሰርዐት የሰሩልን ሐዋርያት ናቸዉ ስለዚህም ፆሙ መታሰቢያነቱ የሐዋርያት ነው የጻድቅ መታሰቢያ ደግሞ ለበረከት ነው ። ምሳ.10፥7 እኛም የሰኔን ፆም ብንፆም የሐዋርያቱን በረከት እናገኛለን ሐዋ.13፥1-3 ሐዋ.14፥23 2. በስራችንና በአገልግሎታችን በረከት እናገኛለን ሐዋርያት ይህን ፆም የፆሙት አገልግሎታቸው እንዲከናወንላቸው እንዲባረክላቸው ነው ነብዩ ነህምያም እየሩሳሌምን የመስራት ተግባሩ እንዲባረክለት በፆመው ፆም ስራው ሁሉ ተባርኮለታል። ነህም.1፥4። እኛም የሰኔን ፆም ብንፆም በዕለት ተዕለት ተግባራችን በረከት እናገኛለን። 3. ዝናብ ምህረትን ጠለ በረከትን እናገኛለን የሰኔ ፆም በአገራችን የክረምቱ መግቢያ ላይ የሚፆም ፆም ነው ይህም መጪው የክረምቱ ወራት የተስተካከለ የምህረት ዝናም እንዲኖረው ያደርጋል በነብዩ ኢዩኤል ዘመን ዝናብ ጠፍቶ ዛፎቹ ሳይቀር በደረቁ ጊዜ በፆም በፀሎት ወደ እግዚአብሔር በተማፀኑ ሰዓት ዝናመ በረከትን አግኝተዋል። ኢዩ.1፥13-14 4. በረከተ ምርትን እናገኛለን የሰኔ ፆም በሃገራችን ገበሬው ዘር መዝራት በሚጀምርበት ጊዜ የሚፆም ፆም ነው ሰለዚህም በዚህ ሰዓት የሚፆመው ፆም ዘርን እንዲባረክ በረከት እንዲበዛ ያደርጋል ይህም አገር ወገን ከረሃብ ከችግር ነፃ እንዲወጣ ያደርጋል በነብዩ ኢዩኤል እንደተገለጸው በፆም የዕህል የመጠጥ በረከት ይገኛል ። ኢዩ.2፥12-14 5. የነፋስ በረከትን እናገኛለን ፆም በመንፈስ የደከመች የዛለች ነፍስን ያበረታል የነፍስን ቁስል ይፈውሳል ስጋዊ ኃይልን ያደክማል የሥጋን ፈቃድ ለነፍስ ያስገዛል መዝ.108፥24 ፤ ገላ.5፥24 የዓለምን ሃሳብ ያስወግዳል ከእግዚአብሔር ያስታርቃል ማቴ. 17፥21 ሚስጥር ይገልጣል ዘስ.34፥27-28 ፤ ዳን. 10፥1-3 "በአምላካችን ፊት እራሳችንን እናዋርድ ዘንድ ከርሱም የቀናውን መንገድ ለእኛና ለልጆቻችን ለንብረታችንም ሁሉ እንለምን ዘንድ ...... ፆምን አውጃለሁ " መጽሐፈ ዕዝራ.8፥21 ከመዋዕለ ፆሙ ረድኤት በረከት ያሳትፈን ! ፆሙን የኃጢአት መደምሰሻ የዲያብሎስ ድል መንሻ የመንግሥተ ሰማያት መውረሻ ያድርግልን አሜንንንን !!! ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ! 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur
نمایش همه...

​​#የቀጠለ ሐዋርያት የጾሙት ጾም የኢየሱስ ክርሰቶስን ፈለግ መከተላቸውን የሚያሳይነው፡፡ መምህራቸውና አምላካቸው ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ ወንዝ በዮሐንስ እጅ ከተጠመቀ በኋላ ሌላ ሥራ ሳይጀምር ወደ ገዳመ ቆርንቶስ ገብቶ እንደጾመ ሁሉ እነርሱም በመንፈስ ቅዱስ ከተጠመቁ በኋላ አገልግሎታቸውን ከመጀመራቸውና ወደየሀገረ ስብከቶቻቸው ከመበተናቸው በፊት እግዚአብሔር መንገዳቸውን የተቃና ሥራቸውንም የተሳካ ያደርግላቸው ዘንድ ጾመዋል፡፡ ይህን ጾም ሐዋርያት ጾመው በረከት ያገኙበት ከመሆኑ ባሻገር ጌታችን ጾሞ ጹሙ እንዳላቸው እነርሱም ደግሞ ተከታይዎቻቸውን ያንኑ መልዕክት የደገሙበት ነው፡፡ በክርስቶስ ደም መሰረት ላይ እና በሐዋርያት ትምህርትና ትውፊት ላይ የተመሰረተችው ቤተ ክርስቲያናችንም ይህንን ጾም በዐዋጅ እንድንጾመው ሥርዓት ሠርታልናለች፡፡ ጾሙ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ የጾሙት እንደመሆኑ መጠን ከጌታ ትንሣኤ ከሃምሳኛው ቀን በኋላ ማለትም ከጰራቅሊጦስ ዕሁድ ማግስት ሰኞ ጀምሮ በቅዱስ ጳውሎስና በቅዱስ ጴጥርስ በዓለ እረፍት መታሰቢያ በሆነው ሐምሌ አምስት ቀን ፍጻሜውን ያገኛል፡፡ የቀናቱ ብዛትም በዐቢይ ጾም መባቻ ሁኔታ የሚወሰን ይሆናል፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን ጾሙን የበረከት፣ የንስሐ ፣ ደዌን ማራቂያ፣ ዲያቢሎስን ድል መንሻ ያድርግልን!!! ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን! ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ! 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur
نمایش همه...

​​ጾመ ሐዋርያት/የሰኔ ጾም ጾመ ሐዋርያት ሐዋርያት በጽራሐ ጽዮን መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ወደ አገልግሎት ከመግባታቸውና ወደ ሀገረ ስብከታቸው ከመበተናቸው በፊት የጾሙት ጾም ነው፡፡ የጾሙበትም ምክንያት በማርቆስ ፪፥፳ እና በማቴወስ ፱፥፲፬ ላይ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን መሰረት በማድረግ ነው፡፡ ይኸውም የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው እኛና ፈሪሳዊያን ብዙ ጊዜ የምንጾመው ደቀመዛሙርትህ ግን የማይጾሙት ስለ ምንድን ነው? አሉት፡፡ ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፡-ሚዜወች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን ? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል ያን ጊዜ ይጾማሉ፡፡››ብሎ እንደመለሰላቸው፡፡ በዚህ ምሳሌያዊ አነጋገር ሙሽራ የተባለው ካባ በመደረብ ፈንታ ዕርቃኑን ሆኖ በአክሊል ፈንታ የእሾህ አክሊል ደፍቶ በሚዜወቹ ፈንታ በጠላት ተከቦ በመዝሙርና በደስታ ፈንታ በልቅሶና በዋይታ ታጂቦ በክብር ዙፋን መቀመጥ ፈንታ በመስቀል ተሰቅሎ በጭንካር ተወጥሮ በቀራንይዎ አደባባይ ስለ እኛ የተሞሸረው/የተሰቀለው/ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ሚዜዎቹ የተባሉት ደግሞ ምንም እንኳን በሰርጉ እለት ከአንዱ በቀር (ከወንጌላዊ ዮሐንስ/ ከጎኑ ባይገኙም ኋላ መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው በሕይወትም በሞትም ሙሽራውን/ኢየሱስ ክርስቶስን/ የመሰሉ ሐዋርያት ናቸው፡፡ ይወሰዳል መባሉም እርገቱን ለመናገር ሲሆን ከዚያ በኋላ ይጾማሉ መባላቸው ደግሞ መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ለማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ኢየሱስ ሲያርግ መንፈስ ቅዱስ ይመጣልና፡፡ በዚህ ላይ ልብ ልንል የሚገባን ጉዳይ ጾም በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበረ በሐዲስ ኪዳንም የቀጠለ ሥርዓት መሆኑን ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን የነበረ ስለመሆኑ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት እና አይሁድ ብዙ ጊዜ ይጾሙ እንደነበረ ተጽፏል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት"እናንተና አይሀድ የጾማችሁት ባለማወቅ ወይም በስህተት ስለሆነ ደቀ መዛሙርቴ አይጾሙም" አላለም፡፡ ነገር ግን ለጊዜው ከእኔ ጋር ናቸው ደስ ሊላቸው ይገባል፡፡ ከሄድኩ በኋላ ግን ይጾማሉ ብሏል፡፡ ይኸውም ጾም ከአዳም ጀምሮ እስከ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እና ደቀ መዛሙርቱ ከዚያም በክርስቶስ ታድሶና ተቀድሶ ለደቀ መዛሙርቱ የተሰጠ ከዚያም ለእኛ ለተከታይዮቻቸው የተላለፈ ሥርዓት መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ ለጊዜው ሐዋርያት ሊጾሙበት ያልቻሉበት ምክንት ሊቃውንት ሲያብራሩ ፡-አንደኛ ጾም ሐዘን ነውና ሐዘኑም ኃላፊነትን ከመሸከም ጋር ተያያዥነት ያለው ነውና፡፡ ምክናያቱም መጾም አላማው ንስሐ እንደመሆኑ እንደ ቅዱስ ዳዊት ለግል ኃጢያት አሊያም እንደነነዌ ሰዎች ስለሀገር ጥፋት የሚያለቅሱበት የሚያዝኑበት ሁኔታ አለው፡፡ ክርስቶስ ደግሞ በስጋው ወራት ከአምላክነቱና ከሁሉ አባትነቱ ባሻገር ለሐዋርይት እንደ ሥጋ አባትም ወንድምም በመሆን የእነርሱን ኃላፊነት ተሸክሞላቸዋልና እርሱ በአካለ ሥጋ በአጠገባቸው እስካለ ድረስ ማዘን አልተገባቸውም፡፡ በሁለተኛነት ደግሞ ጾም ኃላፊነት ነው፡፡ኃላፊነቱን ለመሸከም ደግሞ ኃይል የሚሆናቸው መንፈስ ቅዱስ ያስፈልጋቸው ነበርና መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ እንዲጾሙ ጊዜ ሰጣቸው፡፡ ሦስተኛው ምክነያት አይሁድ ይጾሙት የነበረው በብሉይ ኪዳን ስርዓት ውስጥ ሆነው ነበር፡፡ ሐዋርያት ደግሞ የሐዲስ ኪዳን ልጆች ስለሆኑ መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው አሊያም አዲሱ ሰው በተባለው በክርስቶስ ደም ተጽናንተውና ሥጋውንና ደሙን ተቀብለው አዲሱን ሰው ለብሰው በአዲስ መንፈስና ኃይል በአዲስ ስርዓት መጾም ስለነበረባቸው በጊዜው አልጾሙም ነበር፡፡/ማቴ ፱፥፲፮-፲፯/ ይቀጥላል ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ! 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur
نمایش همه...

👉 በዓለ ኀምሳ - በዓለ ጰራቅሊጦስ 🎤 በቀሲስ ዶ/ር ዘበነ ለማ #ሼር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
ለሁሉም ሼር ያድርጉ 🔺
/በዓለ ኀምሳ/ #ሼር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
ሼር ያድርጉ 🔺
Repost from N/a
፨፨፨ለመናፍቃን የማያዳግም መልስ፨፨፨ የመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃ 1: ሥለ ሥላሴ የእግዚአብሔር አንድነትና ሶስትነት:- ✞ዘፍ 1:26 ዘፍ 3:22 ✞ዘፍ 11:18 ዘፍ 18:1-2 ✞ኢሳ 48:26 ማቴ 3:16-17 ✞ማቴ 28:19 ሉቃ 1:35 ✞ዮሐ 7:28-29 ዮሐ 14:25-26 ✞የሐ.ስራ 3:14 1ኛ ቆሮ 12:4-7 ✞2ኛ ቆሮ 13:14 ኤፌ 4:4-7 2: የእመቤታችን ቅድስናዋ ፣ ክብሯ ፣ ድንግልናዋንና አማላጅነቷ:- ✞መዝ 9:11 መዝ 13:10 ✞መዝ 44:9 መዝ 86:5 ✞መዝ 131:13 መዝ 44:2 ✞መኃ 4:12 ኢሳ 7:14 ✞ኢሳ 49:23 ኢሳ 60:14 ✞ማቴ 1:23 ሉቃ 1:28 ✞ሉቃ 1:42 ዮሐ 2:1-11 ✞ዮሐ 19:16 ሮሜ 11:26-27 ✞2ኛ ቆሮ 11:2 ራዕ 12:16 3: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፈራጅ እንጅ አማላጅ አይደለም፡- ✞ዘፍ 3:22 1ኛ ሳሙ 16:1 ✞ኢሳ 9:6 ዳን 7:14 ✞ሆሴ 13:4 ዘካ 9:9-10 ✞ሚክ 5:2 ሉቃ 1:32-33 ✞ዮሐ 10:30 ሉቃ 2:12 ✞ዮሐ 14:7 ሮሜ 9:5 ✞ቆላ 2:9-10 ቲቶ 2:11-13 ✞ዕብ 1:3-4 ዕብ 1:10-11 ✞1ኛ ጴጥ 3:23 1ኛ ዮሐ 2:23 ✞ራእ 3:22 ራእ 22:12-13 4: ስለታቦት እና ፅላት ✞ዘፃ 24:12 ዘፃ 25:10 ✞ዘፃ 25:21 ዘፃ 26:34 ✞ዘፃ 31:18 ዘፃ 32:15 ✞ዘፃ 34:1 ዘፃ 34:28 ✞ዘፃ 37:1 ዘፃ 40:20 ✞መኃ 7:89 ኢያ 3:3 ኢያ 7:6 2ኛ ቆሮ 6:16 5: ሥለ ፆም የመጽሐፍ ቅዱስ ማሥረጃ:- ✞ዘፃ 34:28 ዘፃ 9:9 ✞ሳሙ 20:26 1ሳሙ 7:6 ✞1ሳሙ 31:13 2ኛ ሳሙ 1:12 ✞2ኛ ሳሙ12:16 ዕዝ 8:21 ✞ዕዝ 68:10 ዕዝ 108:24 ✞ኢሳ 48:3 ኤር 36:9 ✞ዳን 9:3 ዳን 20:2-3 ✞ኢዩኤ 2:14 ኢዩኤ 2:12 ✞ዩና 3:5 ማቴ 4:2 ✞ማቴ 6:16:18 ማቴ 9:14-15 ✞ማቴ 17:21 ማር 2:18 ✞ማር 9:29 ሉቃ 2:37 ✞ሉቃ 18:12 የሐ.ስራ 13:3 ✞የሐ.ስራ 14:23 2ኛ ቆሮ 11:17 6: መስቀል በመጽሐፍ ቅዲስ:- ✞ማቴ 10:38 ማቴ 16:20 ✞ማር 8:34 የሐ.ስራ 5:30 ✞1ኛ ቆሮ 1:18 ገላ 3:13 ✞ገላ 6:13 ፊል 2:8 ✞ፊል 3:18 7: ጥምቀትን በተመለከተ:- ✞ሕዝ 36:25 ማቴ 3:5-6 ✞ማቴ 26:19-20 ማር 1:4-5 ✞ማር 16:16 ሉቃ 3:21 ✞ዮሐ 3:5 ዮሐ 3:22 ✞ኤፌ 4:5 ገላ 3:26-27 ✞የሐዋ 19:4 የሐዋ 18:8 ✞የሐዋ 13:24 የሐዋ 10:47 ✞የሐዋ 9:18 1ኛ ቆሮ 1:16 ✞1ኛ ቆሮ 10 :2 1ኛ ቆሮ 12:13 8:ስዕለትን በተመለከተ:- ✞ዘኁ 28:20 ዘኁ 21:2 ✞ዘፃ 23:21 መሳ 11:30 ✞መዝ 49:14 መዝ 75:11 ✞1ኛ ሳሙ 1:11 መክ 5:4-5 ✞ዮና 2:10 ናሆ 1:15 ✞የሐዋ 18:18 9: ፃድቃን ሠማዕታት ያማልዳሉ:- ✞ዘፍ 18:17-18 ዘፍ 18:23:24 ✞ዘፍ 20:7 ዘፍ 33:3 ✞ዘፍ 42:6 1ኛ ሳሙ 28 :14 ✞2ኛ ሳሙ 1:2 2ኛ ነገ 1:13 ✞2ኛ ነገ 2:15 2ኛ ነገ 4:9 ✞2ኛ ነገ 4:32-35 መዝ 88:34 ✞ማቴ 18:18 ዮሐ 20:23 ✞የሐዋ 10:25 የሐዋ 16 :29 ✞1ቆሮ 6:1-2 ፊሊ 4:6 ✞1ኛጢሞ 5:17 ያዕ 5:14 ✞ራዕ 14:13 10: መላዕክት ዘወትር በእግዚአብሔር ፊት ይቆማሉ:- ✞መዝ 148:2 ኢሳ 6:3 ✞ማቴ 4:12 ማቴ 18:10 ✞ማቴ 25:31 ማር 8:38 ✞ራእ 1:11 ሉቃ 1:19 11: መላዕክት ፀሎታችን ወደ እግዚአብሔር ያደርሳሉ:- ✞ጦቢ 12:15 ሉቃ 15:10 ✞የሐዋ 10:4 እዩብ 25:3 ✞ኤር 33:22 ዳን 7:10 ✞ሄኖ 10:1 ራዕ 5:11 12:ለመላዕክት የአክብሮት ስግደት ይገባል:- ✞ዘፍ 19:1 ማኅ 22:31 ✞ኢያ 5:14 ዳን 8:16-17 13:መላዕክት አብሣሪያን ናቸው:- ✞ዘፍ 16:11 ሉቃ 1:13 ✞ሉቃ 1:19 ሉቃ 1:30-31 ✞ሉቃ 2:10-11 14:መላዕክት በአደጋ ጊዜ ፈጥነው ይደረሣሉ:- ✞ዘፍ 22:11-12 መዝ 90:11-12 ✞ዳን 6:22 ዳን 10:13 ✞ማቴ 2:13 የሐዋ 5:19-20 ✞የሐዋ 12:7 15: ፀበል መርጨት ያስፈልጋል:- ✞ዘኁ 19:20 በተጨማሪም ሁላችንም እያንዳንዱን የመፅሐፍ ቅዱስ ክፍል ደጋግመን እናንብበው እግዚአብሔር አምላክ ማስተዋልና ጥበቡን ይስጠን አሜን፡፡
نمایش همه...
#እንደበደሌ አልከፈልከኝም እንደበደሌ አልከፈልከኝ  ፍቅር ነህና እያለፍከኝ  ምን እከፍላለሁ ላንተ የሚሆን ታውቀው የለም ወይ ችሎታዬን #አዝ ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል  ታረገዋለህ የኔን በደል  እንደምትወደኝ አዉቃለሁ እኔ  ባስመርርህም እድሜ ዘመኔ  #አዝ ከሰው ሁሉ ጋር ብትፈራረድ  የትኛዉ ይሆን ፀድቆ የሚሔድ  ያለምን ሃጢያት ደምህ ሸፈነው  የተፈወስኩት እኔም በእርሱ ነው #አዝ ዘመኔ እንደ ሳር መሆኑን አስብ  እድሜዬ ታጥሯል በጊዜ ገደብ  መልካም ሰርቼ እንዲያልፍ ወራቴ  በጎውን አብዛ በሰውነቴ #አዝ የልጅነቴን አታስብብኝ  መጨረሻዬን አሳምርልኝ  በሩን አትዝጋው ያዳራሹን  ዘይቴን ልሙላ የመቅረዙን  ሊቀ-መዘምራን ዲያቆን ቴድሮስ ዮሴፍ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
#ሰው_ሆይ_አስተውል መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይለናል። ❤️ በሚሞት ስጋችሁ ሐጢያት አይንገስ ብልቶቻችሁን የፅድቅ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር አቅርቡ (ሮሜ 6፥12-14) ❤️ ከሴት ጋር አለመገናኘት መልካም ነው ካልተቻለ ዝሙትን ለመከላከል በአንድ ይፅና ከዚህ ውጭ ጉዞ ወደ እሳት ነው (1ኛ ቆሮ 7፥1) ❤️ ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱ ያፈርሰዋል ቤተ መቅደሱም እናንተው ናችሁ (1ኛ ቆሮ 3፥17) ስንቶቻችን ነን የእግዚአብሔር ቤተ መቅደሶች እንደሆንን የምናውቀው? ❤️ ሴቶች በሚገባ ልብስ ከእረፍትና ራሳቸውን ከመግዛት ጋር ሰውነታቸውን ይሸፍኑ (1 ኛ ጢሞ 2፥9) ❤️ የወንድ ልብስ የለበሰች ሴት በአምላክ ዘንድ…የተጠላች ናት (ዘዳ 22፥5; ዘፀ 39፥28) ❤️ ፀጉሯን ሳትሸፍን የምትፀልይ ሴት እራሷን ያዋረደች ናት (1ኛ ቆሮ 11፥5) ❤️ የወይን ጠጅ ከሚጠጣ ጋር አትቀመጥ (ምሳ 23፥20) ❤️ ዘፈን የሰነፎች ዜማ ነው (መክ 7፥5) ❤️ በዛም አጋንንት ይዘፍናሉ (ኢሳ 13፥21) ስንቶቻችን ነን የእግዚአብሔርን ቃላት እየጠበቅን ያለነው? ሠምተን ለመለወጥ ያብቃን የተግባር ሰው ያድርገን። ወስብሐሃት ለእግዚአብሔር!! #ሼር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
#ኢትዮጵያንና_ህዝቦቿን ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን /2/ ድንበር የሚጠብቁትን /2/ ጠብቅ እግዚአብሔር ሠራዊቷን /4/ የደም መሬት አትሁን ደም አይፍሰስባት ካንተ የመነጨ ሰላም ይስፈንባት አሽናፊ እንድትሆን ለስምህ ተገዝታ አይንህን ሳትመልስ እያት ጠዋት ማታ #አዝ ሰንሰለት ሲፀና ለመከራ ፈርቶ ኢትዮጲያዊ መልኩን አይቀይርም ከቶ ድንቁን ብርሃን ያያል ወቶ ከጨለማ በመንገዱ ሁሉ አዳኝ ቀኝ ቀድማ #አዝ እጅግ የፈተናት ተነቅሎላት መርዙ ከእግሮቿ በታች ጠላቶች ይገዙ ደጅ ስትጠና እጆቿን ዘርግታ ጠብቅ ሠራዊቿን ዱሩ እንዳይፈታ #አዝ ከራሳቸው ይልቅ ኢትዮጵያን ወደዱ ደም ከፍለው ሊያቆዮት በዱር ተሰደዱ በሃሩር በውርጩ የሆኗትን አጥር በማይፋቅ ቀለም ፃፋቸው ለክብር ሊቀ-መዘምራን ዲያቆን ቴድሮስ ዮሴፍ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...