Assaye Derbie
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Assaye Derbie 的分析概览
频道 Assaye Derbie (@asayede) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 337 名订阅者,在 博客 类别中位列第 2 647,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 350 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 337 名订阅者。
根据 25 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -108,过去 24 小时变化为 -4,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 38.62%。内容发布后 24 小时内通常能获得 12.61% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 538 次浏览,首日通常累积 1 808 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 26 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 博客 类别中的关键影响点。
14 337
订阅者
-424 小时
-317 天
-10830 天
帖子存档
14 337
"የኦሮሞ ደም ከእኔ ጅስም የሚቀዳ ነው" በሚል መፈክር ዙፋን አስረክባ ከፈን በተቀበለችው የጎንደር ከተማ "ደማችን በእጃችሁ አለ" የሚል ቁጣ እየተሰማ ነው‼️
ብራቮ ጎንደር ዩኒቨርስቲ!
እምቢኝ‼️
14 337
የጠመንጃ አያያዛቸውን እና አስተያየታቸውን ስትመለከት ከስራቸው ያለው ዝሆን እንጂ በእነሱ አምሳያ የተፈጠረ ሕፃን አይመስልህም‼️
የምር እላችኋለሁ ይሄንን ፎቶ ስመለከት ከሕፃኑ ልጅ በላይ ያሳዘኑኝ እነሱ ናቸው።
14 337
ይሄንን እጅ እዩት ፥ ይሄንን ጣት እዩት
አሻራው ላይ አለ ፥ ሰባት መቶ ሕይወት።
ዛሬ በሥልጣኑ
ከአስከሬን መሀከል ፥ ማዘንን ቢነፍግም
ባይገነዝ እንኳን
በካቴና ታስሮ ፥ መታየቱ አይቀርም።
14 337
በሕይወት የቆየሁኝ
እኩዮቼ ከሚገደሉበት አካባቢ ስላልተገኘሁ ነው‼️
ፍትሕ በወተት ፈንታ ጥይት በሚጋብዙ
ጀግና አባቶች ለተገደሉ እኩዮቼ!
14 337
የአገሪቷን ጫካዎች ሁሉ...
የሕፃናት መታረጃ ቄራ ያደረገ መንግሥት
ስለ አረንጓዴ ልማት ጉዳት እንጂ ስለ ጠቀሜታው የሚያወራበት ሞራል የለውም‼️
#በቃን!
14 337
ያን የመሰለ ሥምህን እና ተጽዕኖ ፈጣሪነትህን ወርውረህ የጨፍጫፊ መንግሥት አማካሪ እስከሆንክ ድረስ "ጨፍጭፋቸው ብዬ አልመከርኩም" ማለት አትችልም‼️
ስለዚህ...
የወገኖቻችን ደም በእጅህ አለ‼️
14 337
ለብአዴን እንኩቶዎች ‼️
አሳዬ ደርቤ
የአማራ ባንክ ሥራ በጀመረበት ቀን በኦሮሚያ ክልል ከተጨፈጨፉ አማራዎች መሀከል እስካሁን የ614 አማራዎች አስከሬን ተቀብሯል፡፡ እናንተ ግን በኦሮሚያ ክልል ከተነጠፈው አስከሬን ይልቅ በአማራ ክልል ውስጥ የሚገለጽ ኀዘን የአገርን ሕልውና ያጠፋ ይመስል የሚሠራውን የማያውቅ ማቶ ተከትላችሁ መንዘላዘሉን ቀጥላችኋል፡፡
እውን ግን እናንተ ከአማራ አብራክ ወጥታችሁ፣ በአማራ ባሕል ያደጋችሁ አማራዎች ናችሁ? በፍጹም‼️ በሕይወቱ ፈንታ አሟሟቱ ያምር ዘንድ ከሚጸልየው ሕዝብ አብራክ የወጣችሁ ብትሆኑ ኖሮማ ኀዘኑን በማድበስበስ ፈንታ ፍትሕን አረጋግጣችሁ ደሙን ታብሱ ነበር፡፡ ‹‹ቀብሬን አሳምረው›› እያለ እድር ሲመሠርት የኖረው ሕዝብ በራቢስ እንደተለከፈ ውሻ በጅምላ መቃብር ውስጥ ሲገባ ድምጻችሁን አጥፍታችሁ አትመለከቱም ነበር፡፡
እውን ግን እናንተ የአማራን ሕዝብ የምትወክሉ አመራሮች ናችሁ?
በፍጹም‼️
አመራር ብትሆኑ ኖሮማ ኃላፊነታቸውን ወደ ጎን ትተው ግድያውን ያስፈጸሙ ባለሥልጣናት ቀብረር ብለው በኩራት ሲራመዱ እንደ ወንጀለኛ አንገት ደፍታችሁ ከኋላ ከኋላ አትከተሉም ነበር፡፡
እኔ እምለው ግን... ሞራላችሁን፣ ማንነታችሁን፣ ኅሊናችሁን፣ ጥላችሁ በፈርስ የተሞላ ጨጓራሁን እያሻሻችሁ ሕዝባችሁን ለማዋረድና በጅምላ ለማረድ አቅደው ከሚንቀሳቀሱ አረመኔዎች ጎን የምትርመጠመጡት ምኑ እንዳይቀር ፈርታችሁ ነው?
‹‹ሥልጣናችን እንዳይቀርብን›› እንዳትሉ መናገርን፣ ማዘንን፣ ማሰብን፣ ሰዋዊ ሥሜትን፣ የሚነጥቅ ሥልጣን ባርነት እንጂ ሹመት አይባልም፡፡ እኒህን ሁሉ ሰዋዊ ባሕርያት ያጣ ሰው የመቃብር ሳጥን ውስጥ የተጋደመ አስከሬን እንጂ ከአገር ወንበር ላይ የተሾመ ባለሥልጣን አይባልም፡፡
ባንድ ወቅት የቀድሞ ጌታችሁ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጆ አፈናውን ማጧጧፍ ሲያስብ ከኦሮሚያ ክልል የወጡ የሕዝብ ተወካዮች አዋጁን ሲቃወሙ እናንተ ግን እጃችሁን ወደላይ ከዘረጋችሁ በኋላ አንገታችሁን ወደ ኋላ አዙራችሁ በግርምትና በፍርሀት ስሜት ስትመለከቷቸው ነበር፡፡ ትናንትናም በዚያው ምክር ቤት ውስጥ ‹‹የሰባት መቶ አማራ ሞት ለአጀንዳ አይበቃም›› ሲባል መቃወሙ ቀርቶባችሁ ዳፍንት እንደያዘው በግ ዐይናችሁን አንሸዋራችሁ በዶክተር ደሳለኝ ድፍረት ስትገረሙ ነበር፡፡ አፈር ብሉ አቦ!
የአማራ ሕዝብ ከሌሎች ባያስበልጡት እንኳን እኩል የሚያደርጉት ሁሉም ጸጋዎች አሉት፡፡ እራሱን አስከብሮ ለመኖር የሚያስችል እውቀትም ሆነ ሐብት፣ የሕዝብ ብዛትም ሆነ የዳበረ እሴት አለው፡፡
ሆኖም ግን የሌሎች ክልል ወገኖቹ የሚወክሏቸውንና የሚታገሉላቸውን ልጆች ወልደው መንግሥት ሲያደርጉ ‹‹የሚከፋፍሉህንና የሚሸጡህን ወልደህ ተዋረድ›› ተብሎ የተረገመው የአማራ ሕዝብ ግን በመንግስት ወንበር ላይ እንደ እናንተ ያለ ጠላት በመሾሙ የተነሳ የማንም መቀለጃ ሆነ፡፡
ትናንት ክልሉ ሲወረር ከበላይ አካል ባገኛችሁት ፍቃድ ‹‹ተነስ›› ስትሉት ጨርቄን ማቄን ሳይል የተነሳውን ፋኖ ከተጠቀማችሁበት በኋላ ሕጋዊ ሆኖ የሚቀጥልበትን መንገድ በማመቻቸት ፈንታ ከዚያው አካል በመጣ መመሪያ መሠረት ‹‹ሕገ-ወጥ›› ተብሎ በአስር ሺህ የሚቆጠር ፋኖ በዘራፊ እጃችሁ ታፈነ፡፡
በቅርቡ ደግሞ በሕይወት መኖር የከለከላቸውን ሰባት መቶ አማራዎች ወደ መቃብር ያወረደው ኃይል ‹‹ለሞቱ ሰዎች ሲደረግ የነበረው የለቅሶ ባሕል ችግኝ በመትከል ተቀይሯል›› የሚል አዋጅ በማውረዱ የተነሳ ይሄንኑ ተግባራዊ ለማድረግ እየተንደፋደፋችሁ ነው፡፡
ሆኖም ግን ልታዋርዱት የምትሞክሩት ክቡር ሕዝብ ይሄን ውዳቂ አስተሳሰባችሁን የሚሸከምበት ጫንቃ ስለሌለው የኀዘን ቀን አውጃችሁ፣ ባንድራ ዝቅ አድርጋችሁ ተቃውሞውን እና ኀዘኑን በሰላማዊ መንገድ እንዲገልጽ ማድረግ ይኖርባችኋል፡፡ ያንን ማድረግ ካልቻላችሁ ግን በቀጣይ ቀናት ያለእናንተ ይሁንታ ወደ አደባባይ ወጥቶ ኀዘኑን ብቻ ሳይሆን ቁጣውንም ጭምር የሚገልጽ ይሆናል፡፡
14 337
በባሕር ዳር ከተማ የጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሰራተኞች በማንነታቸው ለተጨፈጨፉት ድምፅ እያሰሙ ነው! በሁሉም ቦታዎች ተጠናክሮ ይቀጥል።
14 337
በትሕነግ የሥልጣን ዘመን ብአዴኖች ሁለት ጊዜ አልቅሰዋል። መለስ ዜናዊ ሲሞት እና ዶክተር ቴዎድሮስ ለዓለም የጤና ድርጅት ሲመረጥ፤
በኦነግ ጊዜ ደግሞ የእነ ዳግማዊት ብልጽግና አምርሮ ሲያለቅስ የታየው አንድ ጊዜ ሲሆን... እርሱም ሰላም ያሳጣን መሪ የሰላም ኖቬል የተሸለመ ቀን ነበር።
እንኩቶዎች‼️
14 337
የአራት ዓመቱ ሲቃ ፤ በአራት ደቂቃ ሙዚቃ
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
‹‹ብልጭልጭ ቢሆን ዳሱ
ማን ሊታደም ከድግሱ›› በሚል አዝማች የብልጽግናን እቃቃ አናንቆታል።
‹‹ዘር ያወረው ድንበር- ማላውን የረሳ
ሳር ያለመልማል ዛሬም - በእልፍ አእላፍ ሬሳ›› በሚል ስንኝ ከሚነጠፈው ሳር ሥር የጅምላ መቃብር መኖሩን መስክሯል፡፡
‹‹ተናገር አፌ ደፍረህ -ሳትናወጥ ቀርቶ
ዝም አይሆንም ሜዳ ፥ ተራራ ሞት መጥቶ›› በማለት አፋቸውን ለጉመው የተቀመጡ ሰዎችን መከሯል፡፡
‹‹ትንሽ ጋብ እንዳለ - የጭብጨባ ጩኸት
እረጭ ሲል ውሸት - ይናገራል እውነት›› በሚል ስንኝ ከቀልማዳ አንደበት ውስጥ የሰው እውነተኛ ማንነት ይፋ እንደሚወጣ ይናገራል፡፡ (ይሄም በሌላ መልኩ ሲገለጽ ልክ እንደ ባለፈው የፓርላማ ንግግር ማለት ነው)
‹‹ቂምን ሻረውና- ወይ ፍቅርን አንግሰው
ሁለት ሆኖ አያውቅም- አንድ ነው አንድ ሰው፡፡›› በሚል ግጥም እንደ እስስት መልኩን የሚለዋውጠውን አካል ከፍቅርና ከጥላቻ መሀከል ይመርጥ ዘንድ መክሮታል፡፡
‹‹እያመመው መጣ››
እያመመው መጣ!
እያመመው መጣ!›› በሚል አዝማችም ብልጽግና ያመጣብንን ሕመም በሚገርም ዜማ ዘፍኖታል፡፡
ጃንሆይ በልባችን ውስጥ ሺህ ዓመት ንገሥ!
14 337
Share አድርገው!!
በወለጋ አካባቢ የሚኖሩ ወገኖቻችን መንግሥት እስከፈቀደላቸው ቀን ድረስ ኖረው ተጨፈጨፉ፡፡ በሰዓታት ጥቃትም ከሰባት መቶ በላይ ንጹሐን ተቀጠፉ፡፡
ይሄው አካል በሰጠን ነጻነት ልክ የምንንቀሳቀሰው ብሎም በተፈቀደልን መጠን ልክ ኀዘናችንን የምንገልጸው እኔ እና አንተ ደግሞ ወገኖቼን አስጨፍጭፈኻል ተብሎ ሊወገዝ የሚገባው አካል ጥቃቱን እንዲያወግዝልን እና የኀዘን ቀን እንዲያውጅልን በመለማመጥ ላይ እንገኛለን!
የለም የለም ወንድማለም!
በቁጥር ሲሰላ ከአንድ ቀበሌ ነዋሪ የሚበልጥ ሕዝብ የተጨፈጨፈበትና የዓለም ሚዲያዎች ‹‹የሰው ልጅ እንደ ዶሮ መቀላቱን ገልጸው ያወገዙት ጥቃት የደረሰበት አካል ወደ አደባባይ ወጥቶ ሰላማዊ በሆነ መልኩ ኀዘኑንም ሆነ ተቃውሞውን መግለጽ መብቱ ብቻ ሳይሆን ግዴታውም ጭምር ነው፡፡
ስለዚህ የሱፍ ኢብራሒም እንዳለው የታወጀብንን የዘር ማጥፋት ለማስቆም ጠንካራ ትግል የሚጠይቅ ቢሆንም ይሄን ትግል ግን ሰላማዊ በተቃውሞ ሰልፍ መጀመር ይኖርብናል፡፡
እንዲህ አይነት ሐሳብ ሲመጣ የተቃውሞ ሰልፍ ትርጉም አልባ መሆኑን የሚነግሩን ኃይሎች ዋነኛ ዓላማ የታወጀብን ማለቂያ የለሽ እልቂት በፌስቡክ ፖስት ተወስኖ እንዲቀር ማድረግ ነውና እነሱን ሳትሰማ ለሟች ወገኖቻችን ኀዘናችንን፣ ለገዳዮቹ ደግሞ ቁጣችንን የምንገልጽበት የአደባባይ መድረክ መፍጠር ግድ ይለናል፡፡
ሼር እና ፖስት በማድረግ ለሌሎች አጋሩት፡፡
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
