fa
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام Assaye Derbie

کانال Assaye Derbie (@asayede) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 336 مشترک است و جایگاه 2 651 را در دسته وبلاگ‌ها و رتبه 2 347 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 336 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 26 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -104 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -8 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 35.99% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 12.61% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 158 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 808 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 30 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 27 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته وبلاگ‌ها تبدیل کرده‌اند.

14 336
مشترکین
-824 ساعت
-327 روز
-10430 روز
آرشیو پست ها
እባክህ አማራ❗️ አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ በአገርህ የብስ ላይ- ሰትሸቅል ኖረህ- ስትለፋ እንደ ዜጋ የጉምዝ ታጣቂ- በእሳት ቢያወድመውም- የላብህን ዋጋ ልጅ እና ሚስትህን- ቀብረህ ብትወጣም- ከአርሲ ወለ
እባክህ አማራ❗️ አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ በአገርህ የብስ ላይ- ሰትሸቅል ኖረህ- ስትለፋ እንደ ዜጋ የጉምዝ ታጣቂ- በእሳት ቢያወድመውም- የላብህን ዋጋ ልጅ እና ሚስትህን- ቀብረህ ብትወጣም- ከአርሲ ወለጋ እባክህ አማራ፥ የተሻለው ሄዶ፥ የባሰ እንዳይመጣ መንግሥትን አትውቀስ፥ ከአፍህ ክፉ አይውጣ፡፡ እንኳን'ስ ወለጋ- በጠራራ ጸሐይ- ካለህበት መጥቶ እንደ አጣዬ ምድር.. ጎጆህን በጅምላ- ቢያወድመው አንኩቶ እባክህ አማራ- ለአገር ስትል ታገስ- ፈጽሞ አትቆጣ ለውጡን ጠልፎ የሚያስቀር፥ የባሰ እንዳይመጣ፡፡ እኛው ለእኛው ቀርቶ፥ ብርታት የተሰማው፥ የሱዳን ታጣቂ ድንበር ሰብሮ ገብቶ- በገዛ አገርህ ላይ ፥ ቢያደርግህ ተጠቂ የተወረረ ርስት፥ በሺ ዓመቱም ቢሆን፥ መመለሱ ላይቀር እባክህ አማራ፥ የባሰ እንዳይመጣ፥ ንጉሡን አታማር፡፡ የእንትና ገበሬ- ክረምቱ ሳያልፈው፥ እንዲያርስና እንዲያርም በሚል ቅን ውሳኔ- መንግሥት ሲወጣ፥ አድርጎ ተኩስ አቁም የጦርነት ሜዳው- ከአንተ ማሳ ሆኖ- መሬትህ ቢያድርም ፆም ወሎየን ከወሎ፥ ጎንደሬን ከጎንደር፥ ቢያፈናቅሉትም ጠላትህን ውጠህ አስቀረው ስትባል፥ ክተት ሲታወጅ ክላሽ ብታጣ እንኳን.. በድንጋይ በሽመል፥ ወይም በባዶ እጅ ሆ ብለህ መነሳት፥ አርፈህ መክተት እንጂ እኔን እና አገሬን፥ ይጠብቃል ብዬ፥ ግብር የምከፍለው መንግሥት ወዴ'ት ሄደ፥ ጦሩን'ስ ምን በላው፥ ...የሚለው ወቀሳ የባሰን አምጥቶ፥ የሚያሳይ ነውና፥ ኢትዮጵያችን ፈርሳ እባክህ አማራ፥ ለዚች አገር ስትል በደልና ግፉን፥ ሁሉኑም ነገር ቻል ወዘተ ወዘተ እያለ ቀጣይ ነው፥ የካድሬዎች ተግሳጽ፥ የአማራዎች ስጋት የባሰ ባይኖርም፥ ከዚህ በላይ በደል፥ ከዚህ በላይ ቅጣት፡፡ Share

"አማራን ድል ማድረግ የሚቻለው በበዓል ቀን ነው " አሳዬ ደርቤ ------- ሰሜን ወሎን በማውደም ላይ የሚገኙት ጠላቶቻችን ‹‹የአዲሱን ዓመት በዓል የምናከብረው አማራን በመግደልና በማፈናቀል ነው›› ብለው ጥቃታቸውን አስፋፍተዋል፡፡ በተለያዩ ግንባሮች ከሞት አምልጦ በሽንፈት የተመለሰ ወራሪ ጦራቸውንም በዋግና በሰሜን ወሎ ግንባር አዝምተውታል፡፡ ስለሆነም የፌደራል መንግሥቱም ሆነ የአማራ ክልል መንግስት በትግል መሃከል የሚያከበረው በዓል ሕዝብን ዋጋ እንዳያስከፍል በእነዚህ ግንባሮች የመጣውን ጠላት የሚመክት ሠራዊት ማሰማራት ይኖርባቸዋል፡፡ ሶሻል ሚዲያ የምትጠቀሙ ወገኖችም በዓልን ከማክበር በፊት እራስን ማስከበር ይቀድማልና ጠላቶቻችን ‹‹አማራን ድል ማድረግ የሚቻለው በበዓል ቀን ነው›› በሚል አስተሳሰብ እየተንቀሳቀሱ ስለሆነ አውዳመት ባልነው ቀን ዘግናኝ ውድመት እንዳናስተናግድ ትልቅ ትኩረት ሰጥተን ልንሠራበት ይገባል፡፡ #Share

የቪዛ ማዕቀብ አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ጌታቸው ረዳም ሳማንታ ፓወር ጋር ደውሎ "በመለኮታዊ ተዓምር ከአንበሳ መንጋጋ ያመለጠ መንጋችንን ይዘን እግራችን ወደመራን አቅጣጫ እየፈረጠጥን ስለሆነ 'ተሸንፈው ወጡ' ከማለት አድኚን" አላት። እሷም በትዊተሯ አማካኝነት "ህውሓት ሆይ ከአማራና ከአፋር ክልል ባስቸኳይ ለቅቀህ ውጣ" የሚል ትዕዛዝ አስተላለፈች። ከዚህም ማሳሰቢያዋ ስር አገኘሁ ተሻገር ምን ቢል ጥሩ ነው? "የቪዛ ማዕቀብ ስለተጣለባቸው መውጣት አይችሉም" 😁 #Share

"ሊጥ እና እንጀራ ሳይቀር የምትዘርፉት ለምንድን ነው?" በማለት ጋዜጠኛው ሲጠይቅ አንዱ የትሕነግ ምርኮኛ ምን ቢል ጥሩ ነው? "ሰማህ ወንድሜ እናንተ 'እንጀራ አሥር ብር ገባብን' የሚል ጡር ትናገራላችሁ። እኛ እኮ እንጀራ ከበላን አሥር ወር አለፈን። ወደዚህ ልንዘምት የቻልነውም 'የአማራ ሕዝብ የጤፍ እንጀራ እንጂ ክላሽና ውዥግራ የለውም' ብለው ስላታለሉን ነው" 😭😂

ጀግናው የደቡብ ጎንደር አስተዳደሪ አቶ ቀለመ ወርቅ ቅድም በቴሌቪዥን ምን አለ? አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ‹‹እኔ የሚያሳስበኝ ‹‹ክልላችን ውስጥ የገባውን አሸባሪ መደምሰስ እንችላለን ወይ›› የሚለው ጉዳይ
ጀግናው የደቡብ ጎንደር አስተዳደሪ አቶ ቀለመ ወርቅ ቅድም በቴሌቪዥን ምን አለ? አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ‹‹እኔ የሚያሳስበኝ ‹‹ክልላችን ውስጥ የገባውን አሸባሪ መደምሰስ እንችላለን ወይ›› የሚለው ጉዳይ ሳይሆን ‹‹መቼ እንደመስሰዋለን›› የሚለው ነው፡፡ ምክንያቱም ከባዱ ነገር የህውሓት ወራሪ መንጋ የሚከስምበትን ቀን መገመቱ እንጂ ክስመቱ አይቀሬ መሆኑን ማወቁ አይደለም፡፡ ከዚህ አንጻር ትናንት መላው የደቡብ ጎንደር ፋኖ ከመከላከያ ሠራዊቱና ከአማራ ልዩሃይል ጋር ተቧድኖ ባደረገው ተጋድሎ በትንሽ መስዋዕትነት በሺህዎች የሚቆጠሩ የሽብር ቡድኑን አባላት ምርኮኛን ሙት ማድረግ ተችሏል፡፡ እጃችንን አጣጥፈን ብንቀመጥ ኖሮ ግን ደብረ ታቦር ተጨፍጭፋና ተዘርፋ ታድር ነበር፡፡ ከፈረጠጠው በተጨማሪ የማረክነውና የረፈረፍነው አሸባሪ ሁሉ እኛን ሲረፈርፍ የሚያድር ነበር፡፡ ስለዚህ ትግላችን ከህውሓት አሸባሪ ጋር ብቻ ሳይሆን ከጊዜ ጋር መሆን አለበት፡፡ እያንዳንዷ ሰከንድ እኛን እያዳከመች ጠላታችንን የምታጠናክር ናትና ክልላችን ውስጥ ያለው አሸባሪ ግብዓተ መሬት እስኪፈጸም ድረስ ዋነኛ ትግላችን ከህውሓት ጋር ሳይሆን ከሰዓት ጋር መሆን አለበት፡፡ በእያንዳንዷ ደቂቃ እየተዘረፍን፣ እየተገደልን፣ እየተፈናቀልን ስለሆነ እያንዳንዱ አማራ በቁርጠኝነት ተነስቶ ይሄን አሸባሪ በቀናት ውስጥ ማጽዳት ይኖርበታል፡፡ በተረጋጋ መንፈስ አርሶ አደሩ ማሣውን እና ሰብሉን የወረረውን አረም እንዲያርም፣ ነጋዴው ወደ ንግዱ እንዲሰማራ ብሎም ሁሉም በሙያው ተሰማርቶ እንዲሰራ ምድራችን ውስጥ የገባውን የወያኔ አረም ነቅለን መጣል አለብን፡፡ መቼ? ከአሁን ውጭ ጊዜ የለንም፡፡›› ወገን የሆንክ ሁሉ ሼር አድርገህ ለሌሎች አጋራው፡፡

ሽንፈትን ለሚያከፋፍሉ ደካሞች አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ የማሸነፍ ሃይል አካላዊ ብቻ ሳይሆን ስነ ልቦናዊ ነው፡፡ በመሆኑም ተሸናፊዎች የጎሊያድን ግዝፈት የፍርሐታቸው ምንጭ ሲያደርጉት፣ ዳዊቶች ግን ‹‹ይሄን ለኢላማ የሚመች ግዙፍ ሰውየማ መገንደስ አያቅተኝም›› ብለው ከግዙፍ አካል ላይ ድል ይሸምታሉ፡፡ እናም እላችኋለሁ… ስለ ጠላታችሁ ስታስቡ ድክመቱ ላይ አተኩሩ፡፡ እራሳችሁን ስትገመግሙ ደግሞ ከጉድለታችሁ በላይ ያላችሁን ጸጋ መርምሩ፡፡ ድክመቶቻችሁን ተቀብላችሁ በማስታመም ፈንታ ወደ ጥንካሬ ቀይሩ፡፡ ለምሳሌ ያህል የትሕነግ አሸባሪ ወረራ የፈጸመብን በሕዝብ ቁጥራችን ፈንታ ዝግጅት አለማድረጋችንን ታሳቢ በማድረግ ነው፡፡ እኛ ደግሞ ድል ማድረግ የምንችለው ተደራጅቶ ለመጣብን አሸባሪ በመደናገጥ ሳይሆን የሕዝባችንን ብዛት ወደ ጸጋነት በመለወጥ ነው፡፡ ያኔ ትልቅ ውቅያኖስ ትፈጥርና ከውስጥህ ሰርጎ የገባውን ሐይቅና ኩሬ ትውጠዋለህ፡፡ (የዓድዋ ድልም የተመዘገበው የጠላትን ዘመናዊ ሠራዊትና ጥይት በማካበድ ሳይሆን ለእራስ ጸጋ ዋጋ በመስጠት ነው፡፡ ) ሌላው ደግሞ…. የትኛውም ድል የብዙ አፋዊ ፕሮፖጋንዳና የትንሽ ተግባራዊ ትግል ውጤት ነው፡፡ በዚህም መሠረት ብልጦች ከጥይታቸው አስቀድመው ፕሮፖጋንዳቸውን እየተኮሱ የተጋጣሚያቸውን ስነ ልቦና ይሰልባሉ፡፡ ከርቀት ሆነው በሚነዙት የግነት ወሬ በባላንጣቸው ልብ ውስጥ ያለውን ብርታት ያሟሟሉ፡፡ ከዚያም በፕሮፖጋንዳቸው ተሸንፎ የጠበቃቸውን ሕዝብ በጦር መሣሪያቸው ይገድላሉ፡፡ ወይም ደግሞ ይማርካሉ፡፡ ስለሆነም …. ➜ከወገንህ የምትሠማውን መልካም ዜና እያራከስክ፣ ከጠላት የሚረጭልህን ፕሮፖጋንዳ አታግበስብስ፡፡ ➜የራስህን ሚዲያዎችና መሪዎች አንደበት አፍነህ፣ በTMH እና በጌታቸው ረዳ ፖስት አትልፈስፈስ፡፡ ➜መከላከያ ሠራዊታችን እና ልዩ ሃይላችን የሚቆጣጠሩትን ስፍራ እያናናቅክ፣ ባንክ ፊት ተነስተው የሚለቁልህ ፎቶ አሳድገህ ‹‹እንትና ከተማን ተቆጣጠሩት›› የሚል ወሬ አታናፍስ፡፡ ➜ከአሸባሪው ጋር በሚደረገው ጦርነት ላይ ሳትሳተፍ ይቅርና ተሳትፈህ ብትሸነፍ እንኳን ሌላ ትግልና ሌላ ድል ከፊትህ መኖሩን አስብ እንጂ መሸነፍህን አትመን፡፡ በየትኛውም ትግል ላይ ተሸናፊ የሚሆነው ለመሸነፍ ዝግጁ የሆነው አካል በመሆኑ የአሸናፊነት ስነ ልቦና ላላቸው ጥቂት ወራሪዎች ትልቅ ሕዝብ ይገብራል፡፡ በትንሽ ትግል ድል ማድረግ የሚችል ግዙፍ ሕዝብ ያንን ባለማድረጉ የተነሳ ከትንሽ ታጋዮች እጅ ወድቆ ሃያ ሰባት ዓመት ይገዛል፡፡ እናም እልኻለሁ… ከትግል ሜዳ ላይ ስትገባ የምታገኘው ሪስክ፣ ድል አድርገው ሲገቡ ከሚያጋጥምህ ሪስክ ጋር ሲወዳደር ኢምንት ነው፡፡ ምክንያቱም ከትግል ሜዳ ላይ መራር ትግል ብቻ ሳይሆን ጣፋጭ ድልም አለ፡፡ ከመሸነፍ በተጨማሪ ማሸነፍ አለ፡፡ ከአሸባሪ ሃይሉ ድል ውስጥ ግን ሞት፣ ባርነት፣ ስዴት፣ አንገት መድፋት፣ ከሚባሉ ነገሮች ውጭ ምንም አይነት አማራጭ የለም፡፡ ስለዚህ ጠላትህ አምጥቶ ከሚያስረክብህ ሪስክ ይልቅ ትግል ውስጥ ያለውን ትንሽ ሪስክ ወስደህ ለጥቂት አሸባሪዎች ከመንበርከክ እራስህንና ሕዝብህን አድን፡፡ መዝመት ካልቻልክ ደግሞ ከጌታቸው ረዳ ፕሮፖጋንዳ የምትሸምተውን ሽንፈት ለሌሎች አታከፋፍል፡፡ በባዶ እጁ መከላከያ ሠራዊትን ወግቶና ጦር መሣሪያ ቀምቶ የመጣ አሸባሪ ምድርህን ሲወርረው ቀምተህ መዋጋት ባትችል እንኳን ‹‹በባዶ እጅህ ከምትታገል፣ በባዶ እጅህ ተገደል›› እያልክ ወገንህን አትቀስቅስ፡፡ በተረፈ ድል ማድረጋችን አይቀሬ ነው፡፡ Share

አስዳሳችና አሳዛኝ እለታዊ መረጃዎች አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ከአስደሳቹ ስንጀምር፡- ➜የምዕራብ እዝ 24ኛ ቴዎድሮስ ክፍለ ጦር ከአማራ ልዩሃይልና ታጣቂ ጋር ሆኖ በማይጠብሪ ግንባር በወሰደው እርምጃ 222 አሸባሪዎችን ደምስሶ በርካታ የጦር መሳሪያዎችን ማርኳል፡፡ ባሁኑ ሰዓትም ትግሉ ቀጥሎ ሠራዊታችን ወደ ፊት በመገስገስ ላይ ይገኛል፡፡ ➜የፌደራል ፖሊስ ሰሜን ዳይሬክቶሬት ዲቪዥን ከመከላከያ ሠራዊቱና ከአማራ ልዩ ሃይል ጋር ሆኖ በቆቦ ግንባር በወሰደው እርምጃ አሸባሪው ሃይል የሸመቀባቸውን የአርሴማ ተራሮች በመቆጣጠር ለአካባቢው ታጣቂ አስረክበዋል፡፡ በዚህም ዘመቻ ላይ በርካታ አሸባሪ መደምሰስና የጦር መሣሪያ መማረክ ተችሏል፡፡ ➜የህውሓትን የሽብር ተልዕኮ ይዘው ወደ ቤኒሻንጉል ጉምዝ ያመሩ 32 አሸባሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ አሳዛኝ መረጃ፡- ➖➖➖ ➜የትሕነግ አሸባሪ በሰሜን ወሎ ሀብሩ ወረዳ የምትገኘውን የአጋምሳ ቀበሌ በከባድ መሳሪያ በመደብደብ መንደሯን ሙሉ በሙሉ ማውደሙን ከሚገልጽ የሳተላይት ምሥል ጋር ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ንጹሐን መገደላቸውን Telegraph ዘግቧል፡፡ ጥንቃቄ የሚያሻው መረጃ፡- ➖➖➖➖ ➜የኦነግ ታጣቂ ሰሜን ሸዋ ላይ ዳግም ጥቃት ለማድረግ በእንቅስቃሴ ላይ መሆኑን የሚገልጽ መረጃዎች እየወጡ ስለሆነ የሰሜን ሸዋ ፋኖ ጥብቅ አደረጃጀትና ዝግጅት ሊያደርግ ይገባዋል፡፡ የትሕነግና የኦነግ አሸባሪዎችን ጥምረት ዋነኛ ዓላማው አማራን ማውደም ነውና የትኛውንም ወረራ የሚቀለብስ ብሎም ዘላቂ ድል የሚያጎናጽፍ ስነልቦናዊ እና አካላዊ ጥንካሬ፣ ሕዝባዊ አንድነትና አደረጃጀት ገንብተን ለሕልውናችን ልንታገል ይገባናል፡፡ የአማራን ክልል የደፈረው አሸባሪ ቀያችን ድረስ ሲመጣ የሚመክት አማራ ብቻ ሳይሆን ሰሜን ወሎ ሲወረር ገስግሶ የሚደርስ የሰሜና ሸዋና የደቡብ ወሎ አማራ፣ ጎንደር ሲጠቃ ደጀን ሆኖ የሚገኝ የጎጃም አማራ ሊኖረን ይገባል፡፡ ምንም እንኳን ባሁኑ ሰዓት ስለ አደረጃጀት ማውራት ትክክል ባይሆንም መዘግየቱን የተረዳ ሕዝብ ፍጥነቱን መጨመር እንጂ ተገትሮ መጠበቅ ስሌለበት ወረራ በተፈጸመባቸው ማግሥት በቅጽበት ውስጥ ተደራጅተው ከተጠቂነት ወደ አጥቂነት እንደሚሸጋገሩ አባቶቻችን ልንሆን ይገባል፡፡ Share

አንድ የአማራ ፋኖ እየተዋጋ ሳለ ግራ እጁን ይመታና ጎንደር ሆስፒታል ይገባል። ከዚያም ዶክተሩ የቆሰለ እጁን አሽጎ ተገቢውን ሕክምና ከሰጠው በኋላ የሦስት ቀን መርፌ ሲያዝለት ፋኖው እንደሚሻቅል ገልፆ "ሁሉንም አሁን ውጋኝ" ብሎት ነበረ። ዶክተሩ ግን ችግሩን ተረድቶ "እሺ" የሚል ባለመሆኑ ወጣቱ እንዲህ እያለ ክላሹን ይዞ ወጣ። "ልዋጋ መጥቼ ስወጋ አልከርምም" 😁

‹‹ልጆቻችንን ውለዱ›› ተብለው መቀሌ ላይ የታገቱ አሸባሪዎች አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ እይውልህ ወንድማለም… የህውሓትን መሸነፍ ከእኔና ከአንተ በላይ ጌታቸው ረዳ ጠንቅቆ ይረዳል፡፡ አማራ ክልል የገባው ጦር ባሕር ዳር እና ሸገር ቀርቶ መቀሌ መመለስ እንደማይችል ሁሉም የህውሓት መሪዎች በግልጽ አውቀዋል፡፡ ስለሆነም በጌታቸው ረዳ ፖስት አንተ ትወዛገባለህ እንጂ እሱ የሚጽፈው ማንንም ለማስፈራራት ሳይሆን በአገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ የክልሉን ተወላጆች ለማረጋጋት ነው፡፡ ‹‹ሕዝባዊ›› የሚል ሥም በተሠጠው ስሜታዊ ጦርነት ዲያስፖራው ተስፋ ቆርጦ ሞታችንን እንዳያፋጥነው ጠንክረህ ተበሽከት›› የሚል ትዕዛዝ ተሰጥቶት ነው "የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም" በሚል ሒሳብ ከጦር ሜዳ ላይ የነጠፈውን ድል ከጭንቅላቱ እያፈለቀ የሚቀደደው፡፡ ከዚህ ውጭ ክልልህ ውስጥ ገብቶ እግሩ ወዳመራው ስፍራ የሚርመሰመሰው አሸባሪ እስካሁን ድረስ በሕይወት መቆየት የቻለው በእሱ ብርታት ሳይሆን ባንተ ድክመት ነው፡፡ ‹‹መንግሥት ባለበት አገር ሟች እንጂ ገዳይ መሆን አልችልም›› ብለህ ችላ ስላልከው ነው፡፡ በተረፈ ከቀየህ የገባው ሠራዊት ቀርቶ ትግራይ ክልል ያሉት የአሸባሪው መሪዎች ከመቀሌ ከተማ በሕይወት መውጣት የማይችሉበት ሁኔታ መፈጠሩን ልነግርህ እፈልጋለሁ፡፡ ‹‹አማራ እና አፋር ክልል ውስጥ አስገብታችሁ የምታንከራትቷቸው ልጆቻችን በሕይወት ሳይመለሱ ከዚህች ከተማ በሕይወት አትወጡም›› ተብለው መታገታቸውን እነግርኻለሁ፡፡ እነ ጌታቸው ረዳ ለሁለተኛ ዙር እልቂት ያዘጋጁት ሕዝባዊ ማዕበል ፊቱን ወደ አመራሮቹ አዙሮ ሊበላቸው አቆብቁቧል፡፡ ለጥቂት አመራሮች ደህንነት ሲባል ኑሮውን፣ ሰላሙን፣ ልጆቹን፣ ከተማውን መገበሩን ባለቀ ሠዓት የተረዳው ሕዝብ በጸጸትና በንዴት ማእበል እየተናጠ መሪዎቹን ቅርጫ ለማድረግ መመካከር ጀምሯል፡፡ ባንዳንድ ቦታዎች እንደውም ‹‹ዘማች›› በሚል ሥም ተጨማሪ ሟች ሕጻናት ፍለጋ የሚንቀሳቀሱ ካድሬዎች ጦር ሜዳ በላካቸው ልጆቹ ናፍቆት በሚንገበገበው ሕዝብ እየታነቁ እንደወጡ የሚቀሩበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ ስለሆነም በመላው ኢትዮጵያና ባሕር ማዶ የሚኖረውን የክልሉን ተወላጅ የማረጋጋት ተግባሩን ለጌታቸው ረዳ ያስረከቡት የአሸባሪው መሪዎች እስካሁን ድረስ በሕይወት የቆዩት ወልዲያ ዙሪያና ጎንደር አካባቢ የሚቅበዘበዝ ታጣቂያቸው ደብረ ብርሐንን አልፎ ወደ አዲስ አበባ መቃረቡን የሚያበስሩ ዜናዎችን በመለፈፍ ነው፡፡ ባዶ ሞሰብ ከያዘ ባዶ ቤት ሆኖ ልጁን የሚጠብቀውን ሕዝብ ማረጋጋት የቻሉት በርሐብ የሚንገበገብ ሆዱን በድል ዜና በማጥገብ ነው፡፡ እናም እልኻለሁ… ሁለት አማራጭ አለን… ➜አንድም ክልልላችን ውስጥ የገባውን ወራሪ ውጠን በማስቀረት መላው የትሕነግ አመራር በእራሱ ሕዝብ ተጨፍጭፎ በእራሱ ክልል እንዲቀበር ማድረግ ➜ወይም ደግሞ ከእግራችን ስር ያለው እባብ ሰኮናችንን እንዲነድፈን ፈቅደን በእኛ ሕልፈትና ውድመት ለመሞት የተዘጋጀውን የሽብር ጦርና አመራር ሕይወት መዝራት… ሆኖም ግን የእኔም ሆነ የአንተ ብቸኛ ምርጫ ከእግራችን ስር ያለውን እባብ ከእጃችን ውስጥ ባለው ዱላ ጨፍጭፈን መቅበር ነውና ደጃችንን የሚዞረውን መላዕከ ሞት ውጠን ለማስቀረት እንረባረብ። #Share

‹‹ልጆቻችንን ሳታስረክቡ የትም አትሄዱም›› ተብለው መቀሌ ላይ የታገቱ አሸባሪዎች አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ እይውልህ ወንድማለም… የህውሓትን መሸነፍ ከእኔና ከአንተ በላይ ጌታቸው ረዳ ጠንቅቆ ተረድቷል፡፡ አማራ ክልል የገባው ጦር ባሕር ዳር ቀርቶ መቀሌ መመለስ እንደማይችል ሁሉም የህውሓት መሪዎች በግልጽ አውቀዋል፡፡ ስለሆነም በጌታቸው ረዳ ፖስት አንተ ትወዛገባለህ እንጂ እሱ የሚጽፈው ማንንም ለማስፈራራት ሳይሆን በአገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ የክልሉን ተወላጆች ለማረጋጋት ነው፡፡ ‹‹ሕዝባዊ›› የሚል ሥም በተሠጠው ስሜታዊ ጦርነት ዲያስፖራው ተስፋ ቆርጦ ሞታችንን እንዳያፋጥነው ጠንክረህ ተበሽከት›› የሚል ትዕዛዝ ተሰጥቶት ነው ከጦር ሜዳ ላይ የነጠፈውን ድል ከጭንቅላቱ እያፈለቀ የሚቀደደው፡፡ ከዚህ ውጭ ክልልህ ውስጥ ገብቶ እግሩ ወዳመራው ስፍራ የሚርመሰመሰው አሸባሪ እስካሁን ድረስ በሕይወት መቆየት የቻለው በእሱ ብርታት ሳይሆን ባንተ ድክመት ነው፡፡ ‹‹መንግሥት ባለበት አገር ሟች እንጂ ገዳይ መሆን አልችልም›› ብለህ ችላ ስላልከው ነው፡፡ በተረፈ ከቀየህ የገባው ሠራዊት ቀርቶ ትግራይ ክልል ያሉት የአሸባሪው መሪዎች ከመቀሌ ከተማ በሕይወት መውጣት የማይችሉበት ሁኔታ መፈጠሩን ልነግርህ እፈልጋለሁ፡፡ ‹‹አማራ እና አፋር ክልል ውስጥ አስገብታችሁ የምታንከራትቷቸው ልጆቻችን በሕይወት ሳይመለሱ ከዚህች ከተማ በሕይወት አትወጡም›› ተብለው መታገታቸውን እነግርኻለሁ፡፡ እነ ጌታቸው ረዳ ለሁለተኛ ዙር እልቂት ያዘጋጁት ሕዝባዊ ማዕበል ፊቱን ወደ አመራሮቹ አዙሮ ሊበላቸው አቆብቁቧል፡፡ ለጥቂት አመራሮች ደህንነት ሲባል ኑሮውን፣ ሰላሙን፣ ልጆቹን፣ ከተማውን መገበሩን ባለቀ ሠዓት የተረዳው ሕዝብ በጸጸትና በንዴት ማእበል እየተናጠ መሪዎቹን ቅርጫ ለማድረግ መመካከር ጀምሯል፡፡ ባንዳንድ ቦታዎች እንደውም ‹‹ዘማች›› በሚል ሥም ተጨማሪ ሟች ሕጻናት ፍለጋ የሚንቀሳቀሱ ካድሬዎች ጦር ሜዳ በላካቸው ልጆቹ ናፍቆት በሚንገበገበው ሕዝብ እየታነቁ እንደወጡ የሚቀሩበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ ስለሆነም በመላው ኢትዮጵያና ባሕር ማዶ የሚኖረውን የክልሉን ተወላጅ የማረጋጋት ተግባሩን ለጌታቸው ረዳ ያስረከቡት የአሸባሪው መሪዎች እስካሁን ድረስ በሕይወት የቆዩት ወልዲያ ዙሪያና ጎንደር አካባቢ የሚቅበዘበዝ ታጣቂያቸው ደብረ ብርሐንን አልፎ ወደ አዲስ አበባ መቃረቡን የሚያበስሩ ዜናዎችን በመለፈፍ ነው፡፡ ባዶ ሞሰብ ከያዘ ባዶ ቤት ሆኖ ልጁን የሚጠብቀውን ሕዝብ ማረጋጋት የቻሉት በርሐብ የሚንገበገብ ሆዱን በድል ዜና በማጥገብ ነው፡፡ እናም እልኻለሁ… ሁለት አማራጭ አለህ… ➜አንድም ክልልህ ውስጥ የገባውን ወራሪ ውጠህ በማስቀረት መላው የትሕነግ አመራር በእራሱ ሕዝብ መዳፍ ተጨፍጭፎ በእራሱ ክልል እንዲቀበር ማድረግ ➜ወይም ደግሞ ከእግርህ ስር ያለው እባብ ሰኮናህን አንዲነድፍ ፈቅደህ በአንተ ሕልፈትና ውድመት ለመሞት የተዘጋጀውን ጦርና አመራር ሕይወት መዝራት… ሆኖም ግን የእኔም ሆነ የአንተ ብቸኛ ምርጫ ከእግራችን ስር ያለውን እባብ ከእጃችን ውስጥ ባለው ዱላ ጨፍጭፈን መቅበር ነውና ደጃችንን የሚዞረውን መላዕከ ሞት ውጠን በማስቀረት ሕልውናችንን ማስቀጠል ግድ ይለናል።

ጋይንት ላይ እረግፈዋል። ጌቻቸው ረዳ ንፋስ መውጫን የተቆጣጠረው ብቻውን ነው
+3
ጋይንት ላይ እረግፈዋል። ጌቻቸው ረዳ ንፋስ መውጫን የተቆጣጠረው ብቻውን ነው

የዛሬው ዜና አዲስ ቁማር ከሌለው በቀር "ሰበር" አይሆንም! አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ትልቅ ሰበር ዜና ሊሆን የሚችለው ኦነግ ሸኔ እና ትሕነግ ፍቺ ቢፈጸሙ እንጂ ‹‹ሕብረት ለመመስረት ተስማሙ›› የሚለው ጉዳይ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ኦነግ ሼኔ ከህውሓት ጋር አጋር መሆኑን ያረጋገጠው የኦሮሞ ቄሮዎች እና ፋኖዎች ባደረጉት ትግል ትሕነግ ተባርሮ ወደ መቀሌ በገባ ማግሥት ነው፡፡ በዶክተር ዐቢይና በቲም ለማ የሚመራው ለውጥ ሳይፈተን በፊት ነው አምሳ ዓመት ሙሉ ጫካ ለጫካ ሲያንከራትቱት ከኖሩት የትሕነግ አመራሮች ጋር መቀሌ ላይ ሕብረት ፈጥሮ ከእነ ትጥቁ ከበረሃ ወደ አገር ቤት ያስገባውን ሃይል መታገል የጀመረው፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ በትግል ሱስ የተለከፈው ኦነግ ሼኔ የሚያቀነቅናቸው ጥያቄዎች ሁሉ መልስ ቢያገኙ እንኳን ‹‹የእኔን ጥያቄ መመለስ ያለብኝ እኔው ነኝ›› ብሎ ትግሉን ይቀጥላል እንጂ እፎይ ብሎ አይቀመጥም፡፡ ሌላው ቀርቶ የሥልጣን ጥያቄው መልስ ቢያገኝ እንኳን ሁሉም አመራሮች ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው አራት ኪሎ መግባት ካልቻሉ ዝቅ ያለ ሥልጣን ያገኙት አመራሮች ጫካ ገብተው ቤተ-መንግሥት የገባውን ጠቅላይ ሚኒስትራቸውን ይታገሉታል እንጂ ድል አድርገናል ብለው አያስቡም፡፡ እንደውም ከጃል መሮ ይልቅ ጌታቸው ረዳ አራት ኪሎ ቢገባ ይመርጣሉ፡፡ ከዚያ ውጭ የሕዝብን ጥያቄ ማስመለስ ቀርቶ የድርጅታቸውን አንድነት ማስቀጠል ተስኗቸው ‹‹በእንትና የሚመራው›› በሚል መጠሪያ አራት ኦነግ እንደመሠረቱት ሁሉ ኦነግ ሼኔ ድል ሲያደርግ ሌለኛው ኦነግ ተነስቶ ወደ ትግል መግባቱ አይቀሬ ነው፡፡ በተረፈ በኦነግና በኦፊኮ መሃከል ካለው ስምምነት ይልቅ በኦነግና በትሕነግ መሃከል ያለው የጌታና የአሽከር ግንኙነት በፍቅር ላይ የተመሠረተና ረዥም ዓመታት ያስቆጠረ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ‹‹ሕብረት ፈጥረው አብረው ለመሥራት ተስማምተዋል›› የሚለው የዛሬው ዜናም ሌላ ድብቅ ዓላማ ከሌለው በቀር "ፍቅር እስከ መቃብር" በሚል ርዕስ ‹‹በሕብረት ለመሞት ተስማምተዋል›› ተብሎ ነው መዘገብ ያለበት፡፡ ምክንያቱም የፌደራሉ እና የኦሮሚያ ክልል መንግሥት አሸባሪው ሃይል ጠንክሮ እንዲወጣ ካልፈቀዱለት በቀር በመግለጫ ሲደመስሱትና ሲያስነሱት የኖሩትን ይሄን ሽፍታ በጦር መደምሰስ ይሳናቸዋል ብዬ አላስብም፡፡ 😁 ከሁሉም በላይ ደግሞ መንግሥት የትሕነግ አሸባሪን ሙሉ ለሙሉ ለማክሰም የሚያስችል ቁርጠኝነት ካለው ህውሓት ሲደመሰስ የኦነግና የጉምዝ ታጣቂዎችም በእራሳቸው ጊዜ አፈር የሚለብሱ ይሆናሉ፡፡ ለአሸባሪዎች ስንቅና ትጥቅ በማቅረብ የተጠመዱት የሱዳን እና ግብጽ መንግሥታትም በልዩ ጥቃት ፈንታ የልዩ ጥቅም ምንጫችን መሆናቸው አይቀሬ ነው፡፡ ድል ለኢትዮጵያ! #Share

ለወገን አክቲቪስቶች (አሳዬ ደርቤ) ➖➖➖➖ ➜የጠላት ሚዲያ ላይ ስለቀረበ ጥቅመኛና ተራ ሰው እያወራችሁ እውቅናን አትፍጠሩ፤ ➜ትግሉን እና ሕዝባችንን የሚደግፉ ፖስቶችን ሼር አድርጉ፡፡ የጠላቶቻችንን ግን ስክሪን ሾት በመቀባበል ፈንታ ሪፖርት ማድረግ ልመዱ፤ ➜የህልውና አደጋ ተጋርጦበት እርሻውን ጥሎ የዘመተውን ሕዝባዊ ጦር የሌሎች ስጋት ሆኖ እንዲታይ የሚያደርጉ ፖስቶችን አትለጥፉ፤ ➜የወገን ጦርን አደጋ ውስጥ ከሚከቱ እውነተኛ መረጃዎች ይልቅ ጠላቶቻችንን የሚያወዛግቡ ምናባዊ መረጃዎች የተሻሉ መሆናቸውን እወቁ፤ ➜የትኛውንም የድል ዜና ስትዘግቡ መከላከያ ሠራዊታችንን እና ልዩ ሃይላችንን አስቀድሙ፤ ➜ከወገን ጦር መሃከል የምታወድሱት እንጂ የምታንኳስሱት አይኑር፤ ➜ከአሸባሪው ጋር ከፍተኛ ተጋድሎ በማድረግ ላይ የሚገኘውን የአፋር ሕዝብ ድምጽም፣ አቅምም እንሁነው፤ ➜የትውተር ዘመቻ ላይ ተሳተፉ፤ #Share

የወያኔ ልጆች የአንድ ወር ቅጣት ያስወሰኑበት የቀድሞ የፌስቡክ አካውንቴ ሊከፈት 10 ቀን ቀርቶታል። እስከዚያው ይሄን ሊንክ በመጫን በአዲሱ ገፄ ሊያገኙኝ ይችላሉ። https://www.facebook.com/Asaye-Derbie-100999818947578/

የወያኔ የሽብር ጦር ሰሜን ወሎ ላይ ያደረሰው ጉዳትና መፍትሔው፦ (አሳዬ ደርቤ ➖➖➖➖ ➜አራት መቶ ሺህ ሕዝብ ተፈናቅሎ በደሴ ዙሪያ ተጠልሏል። ➜ከ3200 በላይ ተሽከርካሪዎች ከሰሜን ወሎ ተዘርፈው ወደ መቀሌ ተወስደዋል፤ ➜የራያና ቆቦን አማራ ከፊት አሰልፎ በወገናቸው የሚገደሉ የጥይት ማብረጃ አድርጓቸዋል። ➜በመርሳ ከተማ አካባቢ የብልጽግና ደጋፊዎች የሚላቸውን ሰዎች ሲገድልና ቤታቸውን ሲያቃጥል አድሯል። ➜አሸባሪው ሃይል በገባባቸው አካባቢዎች ሁሉ የተገኙ ሕንፃዎችን እና ዐይነ- ግቡ ቤቶችን በማቃጠል የአጣየን ተሞክሮ አስፋፍቶታል። ➜በከተማ ውስጥ ያገኘውን ንብረት (ሊጥ እና ማቡኪያ ሳይቀር) ወደ መቀሌ በማጓጓዝ በባዶ ቤት የተሞሉ 5 ወረዳዎችን ፈጥሯል። ➜በአሥር ሺዎች የሚገመቱ ንጹሐን ሕይወታቸውን አጥተዋል ➜ወልዲያ ከተማን በከባድ መሳሪያ በመደብደብ ላይ ይገኛል። ➜በወሎ ሕዝብ ዘንድ የመንግሥት አልባነት ስሜት ተፈጥሯል። 🔷🔷 የሚጠበቁ እርምጃዎች፦ ➖➖➖➖ ➜ከመዋጋት በተጨማሪ የተማረኩ መሳሪያዎችን በመቀማት ሥራ ላይ የተሰማራው መከላከያ የሰበሰበውን ክላሽ ለአካባቢው ሕዝብ እንዲያስታጥቅ ማድረግ፤ ➜የተናጠል ተኩስ አቁሙን በመተው መከላከያውን እና የጦር ጀቶችን ወደ ሥራ ማስገባት፤ ➜"ወልዲያን አልተቆጣጠሯትም" ከሚል መረጃ አውጥቶ "ቆቦን እና ራያን ተቆጣጥረናል" ለማለት የሚያስችል ሰፊ ዘመቻ ማድረግ፤ ➜አሸባሪው ሃይል ከተረጋጋ ቀጠና ተቀምጦ አማራ ክልልን ማውደም ስለሌለበት በምድርም ሆነ በአየር የሚኖርበትን ምቹጌ መረበሽ፤ ➜የትሕነግን ጦር በመከላከል ፈንታ እንደ መጀመሪያው ዙር ጦርነት ወደ ማጥቃት መሸጋገር፤ ➜አሸባሪው ሃይል መላውን ሕዝብ እያፈሰ ባለበት ሁኔታ በፍቃደኛ ወጣቶች መመከት ስለማይቻል በሁሉም የአማራ ክልል ወረዳዎች ላይ የዘማች ኮታ መጣል፤ ➜ከሁሉም ክልሎች የተውጣጣ ተጨማሪ ልዩ ሃይል ማሰማራት፤ ➜የጦር ሜዳውን ወደ አሸባሪው ምቹጌ በመውሰድ ንጹሐንን እያፈሰ የሚያዘምትበትን ምቹ ሁኔታ ማጥበብ፤ ➜ከትሕነግ ጋር የሚደረገውን ጦርነት ለአማራ ክልል በመተው ፈንታ የኢትዮጵያ ጉዳይ ማድረግ፤ 🔷 Share ያድርጉት

የኢትዮጵያን እዳ የተሸከመችው የወልዲያ ከተማ አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ከአሸባሪው መንጋ ጋር የሚደረገው ጦርነት እያንዳንዱን ወጣት ብርቱ ሠራዊት አድርጎታል፡፡ ከዚህ ሠራዊት መሃከልም የማረጋጋትና የማዋጋት መክሊት የተቸረው ሙሐመድ ያሲን የተባለ የጦር ጠበብት መፍለቅ ችሏል፡፡ በሌሎች ግንባሮች ግንባር ግንባሩን ሲባል የከረመው አሸባሪ ደግሞ ወልዲያ ከተማን የትኩረት ማዕከሉ አድርጓታል። አማራ ሕዝብ ላይ አለኝ የሚለውን ሒሳብ ለማወራረድ ብሎም በጥጋብ ስሜት ወደ ጦርነት ገብቶ በርሐብ የሚቆሻመድ ጦሩን ለመመገብ ከዚህ በፊት ቂም የቋጠረባትን የወልዲያ ከተማን ለመቆጣጠር ከፍተኛ ትግል በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ የጁዎች ግን ክንዳቸውን ሳይንተራሱ ከተማቸውን የሚያስቀምሱ አልሆኑም፡፡ ከሲኖትራክ እየተራገፈ ልጋጉን ለሚያዝረበርበው የተራበ ጅብ አምቦ ላይ ያጋጠመውን አይነት ትግል አቀጣጥለው ጠበቁት እንጂ ወልዲያ እንደ አጣዬ እንዲትሆን አልፈቀዱም፡፡ . በመሆኑም የቆቦን መያዝ በሰሙበት ቅጽበት ወደ ደሴ የሸሹ አንዳንድ አመራሮቻቸውን ተከትለው በመሸሽ ፈንታ የሙሐመድ ያሲንን ጽናት በመጋራት ከመከላከያ ሠራዊቱና ከአማራ ልዩሃይል ጎን ተሰልፈው በየሰዓቱ የሚራገፈውን ጦር ሲረፈርፉት ሰንብተዋል፡፡ የሚልኩት የሽብር መንጋም ወልዲያን ቆረጣጥሞ በመብላት ፈንታ በእርሳስ እየተበላ የቀረባቸው እነ አቶ ጌታቸው ረዳ አልደፈር ያለቻቸው ከተማ ተደናግጣ እንዲትሸሽ ለማድረግና በየቦታው ያጋጠማቸው ሽንፈት ያሳደረባቸውን ብስጭት ለማስታገስ አስበው ትናንት ማታም ሆነ ዛሬ ወደ ንጹሐን ጎጆ ከባድ መሳሪያ በመተኮስ ላይ ይገኛሉ፡፡ የወልዲያ ወጣቶችና የጦር መሪያቸው አቶ ሙሐመድ ያሲን ግን ይህ የከባድ መሳሪያ ተኩስ ህውሓት ያጋጠመውን ከባድ ሽንፈት ከመግለጽ ባለፈ ለሽሽት የሚያነሳሳቸው አልሆነም፡፡ በየሠዓቱ የሚዘረገፈው የአሸባሪው መንጋ የቁጥሩ ብዛት ካላቸው ጥይት በላይ መሆኑን ገልጸው ተጨማሪ ሃይል ከመጠየቅ ውጭ አላፈገፈጉም፡፡ ይሄም ጥያቄያቸው ተገቢ መልስ አግኝቶ በዙሪያቸው የሚያንዣብበውን የጅብ መንጋ የሚደመሰስ ጦር ማግኘት ባይችሉም ልክ እንደ ሰሞኑ ሁሉ ዛሬም እስከዚች ሰዓት ድረስ የከበባቸውን ጅብ እንዲህ እያሉ ይረፈርፉት ይዘዋል፡፡ ዞር በል… የወልዲያን ወጣት- ላትበላው እንደ እህል ቀየህ ላይ ጨምተህ- ስንዴህን ተቀበል፡፡ ወግድ… እዳ ተሸክመህ- ለእኛ የሚወራረድ ባልሰጠኸን ዱቤ - ወልዲያን ላታነድ ከወንዶች ምድጃ- ነፍስህን አትማግድ ክላ… በየጁዎች እርሳስ- ከምታልቅ በጅምላ ዝርፊያህን ተውና- እርዳታህን ብላ፡፡ #Share

ጋይንቶች ጋር የገጠመው የሽብር ጦር ተኩሱ ሲበረታበት ሽንቱን እና እንባውን እያንጠባጠበ ‹‹እንደ ሱዳን አምባሳደር ተመልሼ እወጣ ዘንድ አንድ እድል ስጡኝ›› የሚል ልመና አቅርቦ ነበር፡፡ የጋይንት ጀግኖች ግን እንደ አፈር በሲኖትራክ ተጭኖ የመጣውን አሸባሪ አፈር አደረጉት እንጂ ተመልሶ እንዲወጣ አልፈቀዱለትም፡፡ 💪

ሚዲያዎች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ትኩረት የነፈጉት የአሸባሪው ጥቃት አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት ጆሮ ሰጥተው የሚከታተሉት በኢትዮጵያ ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ሳይሆን ኢትዮጵያን እና መንግሥትን ለመክሰስ የሚያመቻቸውን ነው፡፡ በመሆኑም በአክሱም ንጹሐን ላይ ጥቃት ደርሷል የተባለ እለት የቁጣ ድምጻቸው የተሰማው ወዲያውኑ ነበር፡፡ ጥቃቱን ለማጣራት ሲታሰብም ከኢሰመኮ ጋር በጋራ ከማጣራት ይልቅ ብቻቸውን ገብተው መመርመር ፈልገው ነበር፡፡ በስተመጨረሻ ግን ከኢሰመኮ ጋር በጋራ ባደረጉት ማጣራት በንጹሐን ላይ የደረሰውን ጥቃት በሪፖርት አጠናቅረው ይፋ ማድረግ ቻሉ፡፡ . የሚያሳዝነው ነገር ታዲያ የአክሱሙ ጥቃት ልባቸው ድረስ ተሰምቷቸው የነበሩ እኒህ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት የሌላው ጥቃት ከጆሯቸውም የማይደርስ መሆኑ ነው፡፡ እንደ አጠቃላይ በኢትዮጵያ የሚፈጸመውን የሰብዓዊ ጥሰት በመከታተል ፈንታ ‹‹የሆነ አካል በሆነ ክልል›› ውስጥ የሚያደርሰውን ጥሰት ብቻ አድፍጠው የሚጠባበቁ መሆናቸው ነው፡፡ ለነገሩ ይህ ችግር የእነሱ ብቻ ሳይሆን ህውሓት ሲንቀሳቀስ አብሮ የሚንቀሳቀሰው፣ ህውሓት ሲከስስ የሚመልሰው የኢትዮጵያ መንግሥትም ጭምር ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል አሸባሪው ሃይል አፋር ክልል ገብቶ በ210 ሕጻናት እና አዛውንት ላይ ጭፍጨፋ ማድረሱን በአልጀዚራ አማካኝነት ቀርቧል፡፡ የሚገርመው ነገር ታዲያ ከአልጀዚራ በፊት ይሄን ጥቃት መዘገብ የነበረባቸው የመንግሥት ሚዲያዎች አልጀዚራ ቦታው ድረስ ሄዶ ያጣራውንም አጀንዳቸው አላደረጉትም፡፡ በሌላ መልኩ ግን አሸባሪው መንግሥትን የሚወነጅል ክስ ሲያቀርብ ሁሉም የመንግሥት ሚዲያዎች ተመሳሳይ መልስ ሲያራግቡ ይውላሉ፡፡ ሲቀጥል ደግሞ እንደ ድርጅት የሞት ጽዋውን በመጎንጨት ላይ የሚገኘው አሸባሪ በዶክተር ደጺ አማካኝነት ‹‹የምንዋጋው እንደ ሕዝብ ነው›› ብሎ በመናገር ሽንፈቱን እና ሞቱን ለክልሉ ሕዝብ ለማከፋፈል ሞክሯል፡፡ በአፋርና በአማራ ላይ የተፈጸመው ወረራ ብሎም ኢትዮጵያን ለማፍረስ የሚደረገው ሙከራ ሕዝባዊ መሆኑን ተናግሯል፡፡ የሚገርመው ነገር ታዲያ ‹‹የአንድ ክልል ሕዝብን በሙሉ የጦር ሠራዊት የሚያደርግ›› ንግግር ሲሰጥ መንግሥትና ሚዲያዎቹ እንቅልፉቸውን ይለጥጣሉ፡፡ ጦርነቱንም ሆነ ወረራውን ‹‹ሕዝባዊ ነው›› ብሎ የተናገረው አሸባሪ በጦርነት ላይ የተገደሉበትን ታጣቂዎች አስከሬን ተከዜ ላይ ጥሎ ሱዳን ላይ ካጠመደ በኋላ ‹‹ንጹሐን ተገደሉብኝ›› የሚል ክሱን ይዞ ሲመጣ ግን ‹‹አልገደልንም›› የሚል መልስ ይዘው ከተፍ ይላሉ፡፡ እናም እንላለን…. መንግሥት የአሸባሪውን የፈጠራ ክስ ከማስተባበል ወጥቶ፣ ወራሪው ሃይል አፋር ገብቶ የጨፈጨፋቸውን ብሎም አልጀዚራ ቦታው ድረስ ሄዶ ያረጋገጠውን የ 210 ሕጻናትና አዛውንት የጅምላ ሞት እንዲሁም በሰሜን ወሎ የተፈጸመውን መጠነ ሰፊ ውድመት ለዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ይፋ ማድረግ አለበት፡፡ የአክሱሙን ጥቃት ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ ሲመረምር የነበረው ‹‹የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንም›› ያንዱን ጥቃት በንቃት ሲከታተሉ፣ ሌለኛውን ጥቃት እንዳልሰማ የሚያልፉትን እነዚያኑ ተቋማት በመጥራት በአፋር እና በአማራ ክልሎች ላይ የተፈጸመውን ጭፍጨፋ ባፋጣኝ አጣርቶ ማሳወቅ ይገባዋል፡፡ #Share

በርካታ የእምነት ተቋማትን አውድሞ አማራ ክልልን ከወረረ በኋላ ከአለውሃ ፈርጥጦ ወደ ላሊበላ ያመራው አሸባሪ የቅዱስ ላሊበላ ቤተ-መቅደስ ላይ የጥፋት እጁን እንዳያሰነዝር ያደረገው ብቸኛ ምክንያት እ
በርካታ የእምነት ተቋማትን አውድሞ አማራ ክልልን ከወረረ በኋላ ከአለውሃ ፈርጥጦ ወደ ላሊበላ ያመራው አሸባሪ የቅዱስ ላሊበላ ቤተ-መቅደስ ላይ የጥፋት እጁን እንዳያሰነዝር ያደረገው ብቸኛ ምክንያት እንደ አል-ነጃሺ ወንጀሉን የሚለጥፍበት ጦር ከስፍራው ስላልደረሰ ነው፡፡ ዛሬም ያወጣው መግለጫ ቅርሱን የመደራደሪያ እና የማስፈራሪያ መንገዱ እንዳደረገው የሚያመላክት ነው፡፡ በመሆኑም ከቀላል ትግል ይልቅ ከባድ መስዋዕትነት የሚያስከፍል ትግል የሚመስጠው መንግሥት፣ ነገ እርምጃ መውሰድ ሲጀምር አሸባሪው ሃይል ቅርሱን ይዞ ወደ መቃብሩ ከመውረድ አይመለስም፡፡ ይሄም ታሪካው ጥፋት እንዳይከሰት መላው የላሊበላ ሕዝብ ‹‹እኔን ሳትጨርስ ይሄን መቅደስ ማፍረስ አትችልም›› በሚል ሰማዕታዊ አቋም ግምብም፣ ጠባቂም መሆን ግድ ይለዋል፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ መንግሥት የሚወስደው ኦፕሬሽን ይሄን አይተኬ ቅርስ በሚታደግ መልኩ መሆን ይኖርበታል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንም የክርስትና ሃይማኖት ተከታይ በሆነ ሕዝብና በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተደብቆ ቅርስ በመዝረፍ ብሎም አገር በማውደም ላይ የተጠመደውን ይሄን "አምላክ" እና "አገር የለሽ" አሸባሪ ሃይል ማውገዝ ብቻ ሳይሆን በግልጽ ልትዋጋው ይገባል። ፌስቡክ ላይ ያጋሩት!

የጄኔራል አሳምነው መልእክት- ከሰማይ ቤት አሳዬ ደርቤ ➖➖➖➖ ጀግናን ማወደስ ጥሩ ነው፡፡ ብልህ ሕዝብ ግን ያለፈ ጀግናውን ከማወደስ በተጨማሪ ጀግንነቱን እና ዓላማውን ይወርሳል፡፡ በመሆኑም እኔን ስታወድሱ ከአማራ ያነሰ ማንነት እንደሌለኝ አትርሱ፡፡ በጎጥ ስልቻ ውስጥ ሥሜን እየጠራችሁ ዓላማዬን አታርክሱ፡፡ በእቅፋችሁ ያለውን ጀግና እያንኳሰሳችሁ በሕይወት የሌለውን አትቀስቅሱ፡፡ እናንት የዐማራ ልጆች፡- ባሁኑ ሠዓት የወረራችሁ አሸባሪ በእራሱ ሲታይ ጠንካራ ሊባል አይችልም፡፡ ይልቅስ ጥንካሬው የእናንተ ድክመት ነው፡፡ እሱ ቆርጦ ሲነሳ እናንተ ቁጭ ብላችሁ የምትጠብቁት መሆኑ ነው፡፡ እሱ ሕጻናት እና ወጣት ሳይመርጥ ከምድሩ ላይ ያገኘውን ሁሉ አፍሶ ሲመጣ እናንተ ከአርሶ አደሩ ወይም ደግሞ ከወዛደሩ እጅ ድልን የምትብቁ መሆናችሁ ነው፡፡ አንድ ነገር ልንገራችሁ? አሸባሪው የለኮሰውን ጦርነት ቀልብሳችሁ ድል ማድረግ ካልቻላችሁ በሕይወት ከምትተርፉት ይልቅ በውጊያ ላይ የሞቱት እድለኞች ናቸው፡፡ ‹‹እኔ ምን አገባኝ›› በሚል ከንቱ አስተሳሰብ ከሞት ተርፋችሁ ከህውሓት እጅ ከምትወድቁት ይልቅ ‹‹ያገባኛል›› በሚል ስሜት ታግለው ጦር ሜዳ ላይ የተዋደቁት የተሻለ ሕይወት አላቸው፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ የአማራን ደም ለማፍሰስና ኢትዮጵያን ለማፍረስ የሚታገለውን አሸባሪ በመታገልና ባለመታገል መሃከል ያለው ልዩነት ሞት እና ሕይወት ሳይሆን ምሽግና ቤት መሆኑን ማወቅ አለባችሁ፡፡ ማለትም ቆራጦቹ ጦር ሜዳ ሄደው ገዳያቸውን በመጋፈጥ በአሸናፊነት ለተሞላ ሕይወት ሲታገሉ ድልን ከሌላ እጅ የሚጠብቁት ወላዋዮች ግን ቤታቸው ተቀምጠው ገዳያቸውን እና ሞታቸውን ይጠብቃሉ፡፡ ይሄን ስላችሁ ታዲያ መላው አማራ ጦር ሜዳ ሄዶ መዋጋት አለበት እያልኩ አይደለም፡፡ ጉልበት ያለው በጉልበቱ፣ ገንዘብ ያለው በሐብቱ፣ ጭንቅላት ያለው በእውቀቱ… መዝመት አለበት ለማለት እንጂ፡፡ እራሱን እና አገሩን ያስከብር ዘንድ መርቃችሁ የምትሸኙት ወጣት እንጂ በገመድ አስራችሁ ባርነትን እና አንገት መድፋትን የምታስረክቡት ልጅ መኖር የለበትም ለማለት ነው፡፡ እናንት የዐማራ ልጆች፡- ከአሸባሪው ጋር በሚደረገው በዚህ ትግል ውስጥ ብዙ እድል ተቀምጦላችኋል፡፡ ማለትም የዘመን ነቀርሳችሁን ነቅላችሁ የምትጥሉበት፣ አሸናፊነታችሁን የምታሳዩበት፣ አገራችሁን የምታድኑበት፣ ተሸናፊ አባት በመሆን ፈንታ አሸናፊ ልጅ የምታፈሩበት፣ የሰላም አየር የምትተነፍሱበት፣ ታሪክ የምትሠሩበት፣ ጀግንነታችሁን የምታስመሰክሩበት… ምቹ ሁኔታዎችን በውስጡ ይዟል፡፡ እኒህ ሁሉ እድሎች ታዲያ በአሸባሪው ወንበር ላይ ሳይሆን በእሱ መቃብር ላይ የሚፈኩ ናቸው፡፡ በእናንተ ስንፍና እሱ ፈርጥሞ መውጣት ከቻለ ግን ከዚያ በኋላ ከምንም ውጭ ምንም የለም፡፡ አገርም፣ ክብርም፣ ሕይወትም፣ ታሪክም፣ ኩራትም አይኖርም፡፡ ይሄን የምላችሁ ታዲያ እንዳትዘናጉ ለማስጠንቀቅ እንጂ በመቃብር አፋፍ ላይ የሚገኘውን አሸባሪ እንደ ትልቅ ስጋት በመመልከት አይደለም፡፡ በወታደር ቁጥር ፈንታ በሕዝብ ቁጥር ተመክታችሁ፣ ያለ ትግል ድል ጠባቂ ሆናችሁ፣ በመላዕከ-ሞት ክንፍ ላይ ያለውን አሸባሪ ነፍስ እንዳትዘሩበት በማሰብ ነው፡፡ የገጠማችሁት ጠላት በመላው ኢትዮጵያ ልጆች የተጠላና የተተፋ ቢሆንም በዓባይና በዐቢይ የተነሳ ኢትዮጵያን በጠላትነት የፈረጁ ውጫዊ ሃይሎች ሁሉ እናንተን እንደ እንቅፋት ቆጥረው ከጎኑ መሰለፋቸውን እንዳትረሱት ለማስታወስ ነው፡፡ በተረፈ አከርካሪውን የተመታውን አሸባሪ ጭንቅላቱን ፈጥፍጣችሁ አገራችሁን ሕያው በማድረግ በሕይወት ያሉ ልጆቻችሁን ብቻ ሳይሆን ታሪክ ሠርተው ያለፉ አባቶቻችሁንም ጭምር ታኮሩ ዘንድ አደራ ብያለሁ፡፡ ሼር ያድርጉት!