fa
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام Assaye Derbie

کانال Assaye Derbie (@asayede) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 337 مشترک است و جایگاه 2 647 را در دسته وبلاگ‌ها و رتبه 2 350 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 337 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 25 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -108 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -4 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 38.62% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 12.61% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 538 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 808 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 33 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 26 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته وبلاگ‌ها تبدیل کرده‌اند.

14 337
مشترکین
-424 ساعت
-317 روز
-10830 روز
آرشیو پست ها
የዜጎች አገራዊ ስሜት ከኀምሌ ክረምት በላይ ሲቀዘቅዝ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቋም ሆነ የዓባይን ግድብ ሦስተኛ ዙር ሙሌት ማከናወኗ ትርጉም የለሽ ዜና ይሆናል። እናም እንላለን.... ይህቺ አገር ሚዜዋን እና አጋፋሪዋን ታገኝ ዘንድ በየስፍራው እንደ አረም እየጨፈጨፈች የበደለችውን ሕዝብ ይቅርታ መጠየቅና ካሳ ከፍላ መታረቅ ይኖርባታል።

ቀኑ ይራዘም‼️ ▬▬▬▬ የተመድ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መርማሪ ኮሚሽን በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ዙሪያ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ዙሪያ ማስረጃ ያላቸው ግለሰቦች፣ ቡድኖችና ተቋማት ሁሉ እስከ ሐምሌ 24 ድረስ በእጃቸው ያሉ ማስረጃዎችን እንዲያቀርቡ ጥሪ ማድረጉ የሚደገፍ ቢሆንም የተሰጠው ቀን ግን በቂ ስላልሆነ መራዘም ይኖርበታል። በተረፈ በርካታ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳት የደረሰብን ተጎጂዎች ሆነን ሳለ በውሸት መረጃ ተከሳሾች እንዳንሆን በተመድ ሰብዓዊ መብት ድረ ገጽ ላይ የተቀመጠውን ወይም ደግሞ ከዚህ ጽሑፍ ስር ያለውን ቅጽ ሞልተን መላክ ይኖርብናል። https://www.ohchr.org/en/hr-bodies/hrc/ichre-ethiopa/call-for-submissions Share

የአማራ ሕዝብ "ያለኝን አትቀማኝ" እንጂ "የሌለኝን ስጠኝ" ብሎ አይጠይቅኽም። "ባግባቡ ምራኝ" እንጂ "ሥልጣን ስጠኝ" ብሎ አይታገልኽም። "አትግደለኝና አታውድመኝ" ከማለት ባለፈ "ከኢትዮጵያውያን
የአማራ ሕዝብ "ያለኝን አትቀማኝ" እንጂ "የሌለኝን ስጠኝ" ብሎ አይጠይቅኽም። "ባግባቡ ምራኝ" እንጂ "ሥልጣን ስጠኝ" ብሎ አይታገልኽም። "አትግደለኝና አታውድመኝ" ከማለት ባለፈ "ከኢትዮጵያውያን አፍ ነጥቀህ ልዩ ጥቅሜን አስከብርልኝ" አይልኽም። እነዚህን ጥያቄዎቹን መመለስ ካልቻልክ ግን ቆሌ እና ከራማኽን ገፍፎ ማዲያት በማዲያት ያደርግኻል። ምክንያታዊና ሚዛናዊ ድጋፉን ነፍጎ የምታወራውን የማታውቅ ወፈፌ ያደርግኻል። በሥልጣንህ ልትጎዳው ስታስብ በእንባው ጎርፍ ጠራርጎ ያጠፋኻል። ↪️የአባቶቻችን አምላክ ሆይ ደማችንን የምትመልስም ሆነ እንባችንን የምታብስ አንተ ነህና ሥምህ ለዘላለም የተመሰገነ ይሁን🙏

photo content

ለዲያቆን ዳኒ የምስጋና ጥያቄ የአለቃ ገብረ ሐና መልስ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ አለቃ ገብረ ሐና አጼ ቴዎድሮስን የሚያስቆጣ ሤራ ውስጥ ይሳተፋሉ። ይሄውም ሤራ ከንጉሡ ጆሮ መድረሱን በሰሙ ጊዜ ሸሽተው ወደ ዘጌ ገዳም ያመራሉ። በገዳም ቆይታቸውም ርሐብ ባገሩ ይገባና ይቸገራሉ፡፡ አንድ ቀን ታዲያ ለወስፋት ማስታገሻ የምትሆን ቁራሽ ዳቦ ከአገልጋያቸው ጋር ተካፍለው ከበሉ በኋላ ዲያቆኑ ከመቀመጫው ተነስቶ ‹‹ጌታዬ ስብሐት ብዬ ምስጋና ላቅርብ?›› ብሎ ሲጠይቃቸው አለቃ የሰጡት መልስ እንዲህ የሚል ነበረ፡፡ "ተው ልጅ ቀለዳችሁብኝ ብሎ ይቆጣል፡፡"😆 ምን ለማለት ፈልጌ ነው? የእኛ ፈጣሪ ከነፍስ የሚፈልቅን እውነተኛ ስሜት መጋራት የሚወድ እንጂ እንደ ብልጽግና መሪ ከምላስ በሚመነጭ ተራ ውዳሴና አድናቆት የሚፈነድቅ ባለመሆኑ...የአልጋ ቁራኛ ሆነው ሳለ ‹‹ጤናየን ሰጠኸኝ›› እያሉ ከሚሸነግሉት አስመሳዮች ይልቅ ‹‹ፈውስህን ላክልኝ›› የሚሉትን መጎብኘት ይመርጣል፡፡ ባዶ ሞሰብ ታቅፈው፣ በመንግሥት አልባ ምድር ላይ በጠላት መሀከል ቆመው፣ የሚሰማቸውን እውነተኛ የአደጋ ስሜት እርሱ በፈጠረው ልብ ውስጥ ሸሽገው... ‹‹ስለሰጠኸን ሰላምና ጸጋ እናመሰግንኻለን›› እያሉ ከሚደልሉት ተዋንያን ይልቅ በመቅሰፍቱ ዘመን እሪታቸውን፣ በመናው ዘመን እልልታቸውን ለሚያቀርቡ ፍጡራን ምላሽ ይሰጣል፡፡ እናስ ወንድም ዳኒ፦ በሁለት ሳምንት ውስጥ ከሁለት ሺህ በላይ ወገኑን በጅምላ የቀበረ፣ አገሩ ጠፍቶት የተደናገረ፣ የእለት ጉርስ አጥቶ የተቸገረ ሕዝብ፣ በልቡ የታቆረውንና ‹‹አፍነህ ያዘው›› ብሎ መንግሥት የከለከለውን ዋይታውን ትቶ በመመሪያ የወረደውንና በልቡ የሌለውን እልልታ ቢያቀልጥ "አሾፋችሁብኝ" ብሎ አይቆጣም ወይ? ትናንት ‹‹ማዕቀብ ሊጣልብህ ነው›› የሚል መረጃ ሲሰማ ‹‹የምዕራቡ ዓለም መሪዎች በመንግሥታችን ላይ የሚያደርጉትን ጫና እንቃወማለን›› እያልን የምንጮህበትን እድል ያመቻቸልን መንግሥት፣ ዛሬ ደግሞ "የሰማዩ ጌታ ተቆጥቶብኻል›› የሚል ትንቢት የተነገረው በሚመስል መልኩ ያዘጋጀውን የእልልታ መርሐ ግብር ተቀብለን ‹‹ይሄን የመሰለ መንግሥት የሰጠኸን አምላክ ሆይ እናመሰግንኻለን›› ስንል ቢሰማን "ማንን ነው የምታታልሉት?" ብሎ በመብረቅ አይመታንም ወይ? 😆

ፓትርያርኩ አማራ ቢሆኑ ኖሮ ለሃይማኖት እና ለግብረ ገብነት ቦታ የሌላቸው የትሕ▬ኦነግ ኃይሎች "down down" በሚል ተቃውሞ ሥልጣናቸውን ለመንጠቅ ይጋጋጡ ነበር። የኔው አማራ ግን... ባላመነበት
ፓትርያርኩ አማራ ቢሆኑ ኖሮ ለሃይማኖት እና ለግብረ ገብነት ቦታ የሌላቸው የትሕ▬ኦነግ ኃይሎች "down down" በሚል ተቃውሞ ሥልጣናቸውን ለመንጠቅ ይጋጋጡ ነበር። የኔው አማራ ግን... ባላመነበት ጉዳይ ማንም የማይነዳው፣ ተነጥሎ ማሰብ የሚቻለው፣ ሕግጋት የሚገዛው፣ የዘር ፖለቲካ እምነቱን ያልቀማው በመሆኑ አልፎ አልፎ የዘር ጉዳይ ለሚጫናቸው ፖትርያርክ ጠበቃ ሆኖ በመሟገት ላይ ይገኛል። በጣም ነው የምኮራብህ አንተ ሕዝብ!

ከራሳቸው ሥም ይልቅ የሕዝብን ጥቅም አስቀድመው፣ ብሎም "ኢትዮጵያን ለመታደግ ለብልጽግና ማደግደግ" የሚል አቋም ይዘው፣ አገር በማፍረሱም ሆነ በመቀለሱ ሒደት ውስጥ የአቅማቸውን በማበርከት ላይ ከሚገኙ ሦስት ዓይና አዋቂና ታዋቂ ሰዎች መሀከል አንዳንዶቹን ስናስታውስ... ➔ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ ➔ሙዓዘ ጥበባት ➔ሰርጸ ፍሬ ስብሐት ➔ረ/ፕ ነቢዩ ባዬ ➔ረ/ፕ አበባው አያሌው ➔ዶክተር ምሕረት ደበበ ➔አርቲስት ደበበ እሸቱ ➔ፕሮፌሰር ብርሐኑ ነጋ ➔ዶክተር በለጠ ሞላ ➔ዶክተር¿ ዮናስ ዘውዴ . . . እውቅናችሁን እና ክብራችሁን አሳልፋችሁ የሰጣችሁት ሥርዓት እውን ከሚያደርገው አገራዊ ስኬትም ሆነ መንኮታኮት ጀርባ ሥማችሁን በቀለም ወይንም በደም ጽፎ ታሪክ ይዘክራችኋል።

photo content

የአማራ ክልል ምክር ቤት የአፈና ውሎ ቀጥሏል፣ የሚያሣዝነኝ ነገር ቢኖር ቢያንስ ቢያንስ መናገርና ሃሣብህን መግለፅ ከምትችልበት ሁኔታ እንዴት የማትችልበት እጣፈንታ ይቀየራል። እኔ በኢህአዴግ ጊዜ በ
የአማራ ክልል ምክር ቤት የአፈና ውሎ ቀጥሏል፣ የሚያሣዝነኝ ነገር ቢኖር ቢያንስ ቢያንስ መናገርና ሃሣብህን መግለፅ ከምትችልበት ሁኔታ እንዴት የማትችልበት እጣፈንታ ይቀየራል። እኔ በኢህአዴግ ጊዜ በማንኛውም አጋጣሚ ሃሣቤን ከመግለፅ ተገድቤም ታፍኘም አላውቅም። ለውጥ ብዬ ለለውጥ ታግዬ መጣ በተባለው የለውጥ ዘመን ግን የህግ ጥሠት አለ ሰነ ስረአት ይከበር ብዬ በመከራከሬ የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ከምክር ቤቱ አዳራሽ በፖሊስ ተይዠ እንድወጣ ትዛዝ ከተሠጠ በኋላ በምክር ቤቱ አባላት በተፈጠረ ጫጫት ፖሊስ ገብቶ ሣያወጣኝ ቢቀርም ነገሩ ግን እንዳልተፈፀመ አድርጌ አልወስደውም። በመሠረቱ እኔ ሁሉንም ነገር ለመሆን የወሠንኩኝ ሠው መሆኔን ያላውቁ ሠዎች ጉዳዩን የተለያዬ ሠበብ አስባብ እየፈጠሩ ለማደናገር ቢሞክሩም አይሣካላቸውም። እኔ የአማራ ህዝብ ሞት እስከሚቆምና ጥያቄዎቹ እስከሚመለሱ ትግሉ የጠዬቀውን ዋጋ ሁሉ እከፍላለሁ።ይህንን ትግል ያለ ማቋረጥ በማንኛውም ያልተመቸ ሁኔታ ሣደርግ ስራ አጥቸ ጦም አዳሪ እንደምሆን ፣ታስሬ እንደምሠቃይ ፣ቀጥሎም የመጨረሻውን የሞት ፅዋ እንደምቀምስ በመዘጋት አይደለም። መኪናና እጀባ የጎድልብናል ብለው የአማራን ህዝብ በግዞት አስይዘው እንደሚቀልዱት ግን ለመቀለድ አልወሠንኩም። እኔ በምክር ቤቱ ውሎ ሃሣቤን ለመግለፅ እጀን ሣወጣ ብውልም እድል የሠጠኝ አካል የለም ። ሠው በህጋዊ መድረክ ከተከለከለ የሚጠቀመው የትግል መድረክ ያገኘውንና በእጁ ያለውን እድል ይሆናል። በመጨረሻም የታፈንኩት እኔ ብቻ ሳልሆን የአማራ ህዝብም ነው። በተረፈ እኔ የማቀርበው ሃሣብ የዚህን ያህል ሚዛን ተሠጥቶት የሚፈራ መሆኑን አልገመትኩም ነበር ከዛሬ ስብሰባ የገባኝ ነገር ተከራክረው እኔን ማሸነፍ እንደማይችሉ ነው። ሃሣብና እውነት ያሸንፋል !! ጉልበትና አፈና ይሸነፋል።

በባሕር አቋርጦ አረብ ከመግባት በላይ ሸኖን አልፎ ሸገር መግባት የማይቻል ሆኗል፡፡ እናም መንገደኞች ከሚሰቃዩ ‹‹የሸኔ መታወቂያ የሌለው ሰው ፊንፊኔ መግባት አይችልም›› የሚል አዋጅ ለምን አይተላለፍም?

ኢትዮጵያ ተወረረች የሚባለው የቱ ክልል ሲወረር ነው? ▬▬▬ በባለፈው ጄኔራል አልቡርሃን "መሬት የመውረር ዓላማ አንግበው ኢትዮጵያ ላይ ጦርነት ከከፈቱ ታጣቂዎቼ መሀከል ሰባት ተገደሉብኝ" እያለ ሲደነፋ ከመከላከያ መሪዎች የተሠጠው መልስ "እርምጃውን የወሰዱት የአካባቢው ታጣቂዎች ይሆናሉ እንጂ እኔ እርምጃውን ልወስድ ቀርቶ መረጃውም የደረሰኝ ዘግይቶ ነው" የሚል ነበረ። ዛሬ ደግሞ የኢፌድሪ መከላከያ ሠራዊት ገጽ ላይ እንዲህ የሚል ዜና ተለጥፏል። "ከአራት ቀናት በፊት ወደ ሶማሌ ክልል አፍዴር ዞን የገባው የአልሸባብ ታጣቂ "ሁልሁል" በሚባል ንዑስ ቀበሌ በሶማሌ ልዩ ኃይልና ታጣቂ ከተከበበ በኋላ ለወሬ ነጋሪ ሳይተርፍ ሙሉ ለሙሉ መደምሰሱን የክልሉ መንግሥት አስታወቀ!" 😆 እኔ እምለው ግን... በሱዳን ታጣቂ የሚወረረው አማራ ክልል ከሆነ፣ በአልሸባብ አሸባሪ ወረራ የሚፈጸምበት ሶማሌ ክልል ከሆነ፣ በደቡብ ሱዳን ታጣቂ የሚደፈረው ጋምቤላ ክልል ከሆነ.... "ኢትዮጵያ ተወረረች" የሚባለው የትኛው አካባቢ ለጥቃት ሲጋለጥ ነው? ደግሞስ ውጫዊ ጠላቶች ጦርነት ሲከፍቱ አደጋውን ወደ ጸጋ ቀይሮ የሕዝብን አንድነትና አለሁ ባይነት ማሳየት የሚገባው መንግሥት... ጥቃቱን ለክልሎች እያስረከበ በመከላከያ ሠራዊቱ ላይ ተስፋ የማያሳድሩና በተገፊነት ስሜት ለአገራቸው ያላቸውን ፍቅር የሚወረውሩ ክልሎች እየፈጠረ ኢትዮጵያን ታሪክ ሲያደርጋት ሕዝቡ ተመልካች ሆኖ የሚታደመው እስከ መቼ ድረስ ነው? በ13 ተሽከርካሪ የተጫነ የአልሸባብ ታጣቂ ድንበር ሰብሮ ወረራ ሲፈጽም የጦር ሥምሪትና መረጃ መስጠት የሚገባው መንግሥት እራሱን ከሚዲያ ሰውሮ "የአፋልጉኝ ማስታወቂያ" ሲያወጣ አስበው እስቲ...😆

photo content

አዲስ አበባን ስናስባት‼️ አሳዬ ደርቤ አዲስ አበባ ትናንት ▬▬▬▬▬▬▬ ➔ማንነትን ሳትጠይቅ ዜጎችን በዜግነታቸው የምታኖር፤ ➔ጉልበት ያለውን በጉልበቱ፣ የተሻለ የትምህርት ዝግጅት ያለውን በወረቀቱ፣ ብቃት ያለውን በብቃቱ የምትቀጥር ➔ከሌሎች ክልሎች የሚመጡ ዜጎችን ‹‹የክፍለ ሐገር ልጆች›› በሚል መጠሪያ ተቀብላ እርድናን የምታስተምር፤ ➔ድሃውንም ሆነ ሐብታሙን በአቅሙ ልክ አብልታ የምታሳድር ➔‹‹በ97ቱ ምርጫ ድምጽ የነፈግኩት መንግሥት ምንም ቢሠራ አይጥመኝም›› እያለች የምትጎርር ➔‹‹ሰፈሬን እና ቤቴን ሰጥቼ ኮንዶሚንየም አልቀበልም›› በሚል አቋም ከመንግሥት ጋር የምትከራከር ➔ከኢትዮጵያም አልፋ የአፍሪካና የዓለም ከተማ ለመሆን የምትሞክር ➔በቻርተር የሚያስተዳድራትን ሥርዓት በዘረኛነት ፈርጃ ከግንቦት ሰባቶች ጋር የምታሤር አዲስ አበባ ዛሬ ▬▬▬▬▬▬ ➔በክልል ሕገ መንግሥት የምትተዳደር ➔ለወለደቻቸው ልጆቿ ባዕድነትን የምታስተምር ➔መቶ ፐርሰንት ድምጿን በሠጠችው ዘረኛ መንግሥት አንገቷን ታንቃ የምታጣጥር ➔በዜግነት ማሰብን ተነፍጋ ማንነቷን ፍለጋ ዘር የምትቆጥር ➔ከእለት ጉርሷ ቀንሳ የሠራችው የጋራ መኖሪያ ቤት በቤተሰብ ሲከፋፈል እያየች ቁጭ ብላ የምታማርር ➔‹‹አገራዊ ለውጥ ያመጣል›› የሚል እምነት ካሳደረችበት መንግሥት የዲሞግራፊ ለውጥ ተቀብላ ልጆቿን የምታባርር፤ ➔መኖሪያ ቤቷን ለቅቃ ወደ ኪራይ ቤት ካመራች በኋላ ‹‹ለማይረባ እቃ ይሄን ያህል ብር አልከፍልም›› እያለች ጫኚና አውራጅ ጋር የምትከራከር ➔አራዳ ልጆቿ ‹‹የሴተኛ አዳሪ ልጆች›› እና ‹‹ወራሪዎች›› ሲባሉ አፏን ከፍታ የምታዳምጥ ➔ከክልሎች በላቀ መልኩ በዘር ፖለቲካ የምትናጥ ➔ፍቅር በሠጠቻቸው መሪዎች ‹‹ጥላቻ አለብሽ›› እየተባለች የምትንጓጠጥ ➔‹‹ጥጋቤን እና ርሐብሺን ብቻ ሳይሆን ቋንቋየን መቻል አለብሽ›› በሚል አሀዳዊ ሥርዓት እንደ ሻሜት የምትናጥ እናም እልኻለሁ… ከዘረኝነት የጸዳችና የሁሉም የነበረች ከተማን በተረኝነት አስተሳሰብ ለማንም የማትሆን ከተማ በማድረግ ላይ የሚገኝ መንግሥት… ዜጎችን በዜግነታቸው የምታኖርና የሁሉም የሆነች አገር እውን ያደርጋል ብሎ ለማሰብ እንደነ ሲሳይ አጌና ሦስት ዓይና መሆን ይጠይቃል፡፡😆

ጋበዝኳችሁ

ለዶክተር ሲሳይ መንግሥቴ አሳዬ ደርቤ ➔በከንቲባዋ በኩል ከባድ ግልምጫ ቢያጋጥምህም፣ አድናቆትና ሽንገላ የለመደውን መድረክ በሐቅ ድምጽ ሞግተኸዋል፡፡ ➔ማለት ያለብህን በጥያቄ መልክ አቅርበህ የመሪዎ
ለዶክተር ሲሳይ መንግሥቴ አሳዬ ደርቤ ➔በከንቲባዋ በኩል ከባድ ግልምጫ ቢያጋጥምህም፣ አድናቆትና ሽንገላ የለመደውን መድረክ በሐቅ ድምጽ ሞግተኸዋል፡፡ ➔ማለት ያለብህን በጥያቄ መልክ አቅርበህ የመሪዎችን ማንነት በግልጽ አሳይተኸናል፡፡ ➔ልክ እንደ ዶክተር ደሳለኝ እና ክርስቲያን ታደለ በአዲስ አበባ ምክር ቤት ውስጥ የመረጠህ ሕዝብ ድምጽ ሆነኻል፡፡ ➔የብልጽግና ወኪል ሆኖ ምክር ቤት ከገቡ በኋላ ሕዝብን ማገልገልና ለሕዝብ መታገል እንደሚቻል አስተምረኻል፡፡ ➔ከሆነ ጊዜ አንስቶ በሶሻል ሚዲያ የምታራምዳቸው ሐሳቦችም፣ ሕዝባዊ አንድነትን የሚያጠናክሩና እውነትን የሚናገሩ ሆነዋልና በዚሁ አቋምህ ትቀጥል ዘንድ እመኛለሁ፡፡ አክባሪህ!

የሕፃን መራሹ ሥርዓት ዋነኛ ስጋት የሆኑት አዛውንት እስካሁን አልተፈቱም አይደል?
የሕፃን መራሹ ሥርዓት ዋነኛ ስጋት የሆኑት አዛውንት እስካሁን አልተፈቱም አይደል?

ደስታህን ተረከበኝ‼️ ▬▬▬▬▬▬ ➔በሕልውናው ትግሉ ወቅት ለሄዊ ስንቅና ትጥቅ ያላቀበለ የለተሰንበትን ድል መካፈል አይችልም›› ከተባለ... ➔አገራቸውን ለማፍረስ የተነሱ አሸባሪዎችን የሚጠላ፣ የአገራቸውን ሥም ያስጠሩ አትሌቶችን ማድነቅ የማይችል ከሆነ… ➔የጎይተቶምን ደስታ ለመጋራት የጌታቸው ረዳ ደቀ-መዝሙር ሆኖ መገኘት የሚጠይቅ ከሆነ… ➔አሸባሪ ኃይሎች በማይካድራ፣ በጪና፣ በጋሸና፣ በአጋምሳ፣ በቆቦ፣ በአንጾኪያ፣ በኮምቦልቻ የፈጸሙትን አረመኔያዊ ድርጊት ሲያወግዝ የከረመ ሰው፣ አገር የወከሉ አትሌቶች በአሜሪካ ኦሪገን የፈጸሙትን ገድል መካፈል የማይችል ከሆነ… ➔በመንገዳቸው ሁሉ ያገኙትን ሕይወትና ንብረት እያወደሙ ደብረ ሲና ድረስ የመጡ አሸባሪዎችን እንደ እናቱ ገዳይ የሚጠላ አካል ከትግራይ የወጡ አትሌቶችን መውደድ አይችልም›› ከተባለ… ➔በተፈጸመበት ጭፍጨፋ ፈንታ ያልፈጸመውንና ያልተፈጸመውን ጀኖ ሳይድ አምኖ የአሉላ ሰሎሞንን የትዊተር ዘመቻ ያልተቀላቀለ ፣ስለ ለተሰንበት የመናገር ሞራል የለውም›› ከተባለ… ደስታህን እንጂ የጅራፍ ፖለቲካህንና የአዞ እንባህን ልጋራህ አልችልም፡፡ ወደትናንት ከተመለስን ላጠፋኸው ሕይወትና ሐብት ካሳ ከመክፈል ባለፈ ወቀሳ የምታቀርብበት ሞራል የለህም፡፡ (በተረፈ ያን ሁሉ ኀዘን ለብቻዬ ሳስተናግድ ከርሜ ደስታህን መጋራቴ እንዳሳፈረኝ ልደብቅህ አልሻም።)

"አገሩን ጥሎ ከሄደ በኋላ ባንድራውን መርሳት የተሳነው የአሀዳዊያን አትሌት በአንድ እግሩ ቤልጀምን፣ በሌለኛው እግሩ ኢትዮጵያን ወክሎ በተሳተፈበት ሩጫ የነሐስ ሜዳሊያ አግኝቷል!" 😆
"አገሩን ጥሎ ከሄደ በኋላ ባንድራውን መርሳት የተሳነው የአሀዳዊያን አትሌት በአንድ እግሩ ቤልጀምን፣ በሌለኛው እግሩ ኢትዮጵያን ወክሎ በተሳተፈበት ሩጫ የነሐስ ሜዳሊያ አግኝቷል!" 😆

በዓለም አትሌቲክስ የማራቶን ውድድር ላይ አትሌት ታምራት ቶላና አትሌት ሞስነት ገረመው ሁለተኛውን ወርቅ እና ብር ለአገራቸው አስገኝተዋል።
በዓለም አትሌቲክስ የማራቶን ውድድር ላይ አትሌት ታምራት ቶላና አትሌት ሞስነት ገረመው ሁለተኛውን ወርቅ እና ብር ለአገራቸው አስገኝተዋል።