Assaye Derbie
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Assaye Derbie
تُعد قناة Assaye Derbie (@asayede) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 229 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 668 في فئة المدوّنات والمرتبة 2 379 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 229 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 11 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -160، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -5، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 34.65%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 12.67% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 932 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 803 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 25.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 12 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة المدوّنات.
14 229
المشتركون
-524 ساعات
-277 أيام
-16030 أيام
أرشيف المشاركات
14 229
እልልታ የዋጠው እሪታ
▬▬▬▬▬▬▬
➔ከሥልጣን ሽግግሩ ዋዜማ አንስቶ እስካለንበት ጊዜ ድረስ በመንግሥታዊ እልልታዎች የተዋጡትን ሕዝባዊ እሪታዎች በወግና በስንኝ የሚተርከው...
➔እንደ ሕዝብ ያከሸፍናቸውን መልካም አጋጣሚዎች፣ የቀበርናቸውን ወገኖች፣ ያስተናገድናቸውን ማንነት ተኮር ወረራዎችና ጥቃቶች፣ የተከፈሉልንን መስዋዕቶች እንዳጠቃላይም ባለፉት አራት ዓመታት ተከስተው የዘነጋናቸውን አበይት ክስተቶች፣ ከምሥልና ከቃል ማስረጃ ጋር የሚያወሳው 4ኛ መጽሐፋችን ለአንባቢያን ቀርቧል።
አከፋፋይ
➔ጃፋር መጽሐፍት መደብር ለገሐር
➔ጦቢያ መጽሐፍት ካዛንቺስ
➔በተናጠል ለሚፈልጉ ደግሞ በሁሉም የመጽሐፍት መሸጫ ሱቆች ያገኙታል።
Share & Post
14 229
የወቅቱ ፖለቲካ ግላዊ ነፃነትህን የምታጣበት እንጂ ሕዝብን ነፃ የምታወጣበት አይደለም። የእራስህን ሕይወት ከመገበር ባለፈ የሕዝብን የጅምላ ሞት ማስቀረት አትችልም።
እናም እስክንድር ነጋ እንደ ስንታየሁ ቸኮል እስር ቤት ገብቶ ያለ አስታዋሽ ከሚቀር ጥሩ ውሳኔ ወስኗል። በተረፈ ከ ብረት የጠነከረ ስብዕና ባለቤት የሆነው እስክንድር ነጋ የተረኞችን ጫና መቋቋም ተስኖት ከፓርቲው መልቀቁ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ለጥቅመኞች እንጂ ለእውነተኛ ታጋዮች ቦታ እንደሌለው ያመለክታል።
መልካም ጊዜ እስኬው።
ስላሳለፍከው የትግል ጊዜ አመሠግናለሁ።
14 229
ባንድ ቤት ፥ ሦስት ልደት🥤
ዛሬ… አሳዬ ደርቤ የተወለደበት እለት ነው። ከዚህ ባለፈም ሦስተኛ ልጄ "እቴጌ አሳዬ" አባቷ የተወለደበትን ቀን ጠብቃ ወደዚህች መሬት የመጣችበት እለት ነው፡፡
እንዳጋጣሚ ሆኖ ደግሞ እኔና እቴጌ በተወለድንበት ቀን ብዙ የለፋሁበትና ‹‹እልልታ የዋጠው እሪታ›› የሚል መጠሪያ የሰጠሁት አራተኛ መጽሐፌ (ልጄ) ከማተሚያ ማሽን ወጥቶ ከእጄ የገባበት ቀን ሆኗል፡፡
ይሄውም መጽሐፍ ከሥልጣን ሽግግሩ ዋዜማ አንስቶ ያሳለፍናቸውን ሒደቶች እንዲሁም የዩቲዩብ ሰበር ዜና ሆነው የረሳናቸውን ዓበይት ክስተቶች በስንኝና በወግ መልክ የሚተርክ ሲሆን በርካታ የምሥልና የቃል ማስረጃዎችም ተካትተውበታል፡፡
እናም በእኔና በእቴጌ የልደት ቀን የእስኪነጋ ድረስ፣ የጎዳናው እስኪቋጭ እና የሐሳብ ቀንዘሎች ታናሽ ወንድም የሆነውን አራተኛ መጽሐፌን አሳትሜ የሚጠበቅብኝን ወገናዊ ግዴታ በመወጣቴ ደስ ብሎኛል፡፡ ከሁለት ቀን በኋላ ደግሞ በሁሉም መጽሐፍት ቤቶች ውስጥ የሚገኝ ይሆናል፡፡
በተረፈ ይህ መጽሐፍ ታትሞ ለአንባቢ ይደርስ ዘንድ በተለያየ መልኩ ያገዙኝን ወዳጆቼን እያመሰገንኩ እንዲሁም መጽሐፉን የማስተዋወቅ ተግባሩን ለቀሪ ወዳጆቼ እያስረከብኩ ለእኔና ለእቴጌ ‹‹መልካም ልደት›› ፤ ለአንባቢዎቼ ደግሞ ‹‹መልካም ንባብ›› እመኛለሁ፡፡
አሳዬ ደርቤ
#Share_post
14 229
በወሎ ሥም የሚቀነቀነው ክልላዊ ጩኸት‼️
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬
➔ደቡብ ወሎ ላይ አዲስ ዞን በመመስረት ነባሩን ዞን በኦነግ ፖለቲካ የመሰልቀጥ ምኞት ያለው፤
➔በተመሳሳይ የፌስ ቡክ ሥም የተደራጀ የኦነግና የብልጽግና የሳይበር ጦር የሚያራግበው፤
➔ሕዝባዊ መሠረት የሌለው፤
➔አማራን ወደ ማይኖሪቲ አውርዶ ኦሮ፤ሚያን ብቸኛ ማጆሪቲ የማድረግ ሕልም ያለው ፤
➔የኃይማኖት ግጭት የመፍጠር ተልዕኮ የተሰጠው፤
➔የቤተ አማራዎች እትብት መቀበሪያ ምድር ወሎ መሆኗ የተዘነጋው፤
➔ትልቁን የአማራ ዞን አንዲት ወረዳ ከማታክል ልዩ ዞን ስር የማዋል እቅድ ያለው...
እናም እንላለን...
ብልጽግና ሆይ ያሰብከው ቅዠት በእኛና በፋኖዎች ዘመን ሊተገበር ስለማይችል በክልልነት ሥም ወሎን የመሰልቀጥ ምኞትህን ጥለህ ለጉራጌ የክልልነት ጥያቄ መልስ ስጥ።
14 229
የትኛውም ፖለቲከኛ በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ የአቋም መዛነፍ ሊታይበት ይችላል።
ይሄንንም ሁኔታ የተረዱ ወገኖች አስተያየት ሲሰጡ "መንጋ" እያሉ ከማንቋሸሽ ይልቅ እንደ የሱፍ ኢብራሒም እራስን መፈተሽና ይቅርታ መጠየቅ ለሁሉም ይበጃል።
በተረፈ ወዳጄ የሱፍ ኢብራሒምን ለአማራ ቀርቶ ለአገር የሚተርፍ አቅም ካላቸው ፖለቲከኞች መሀከል አንዱ እንደመሆንህ መጠን በመንግሥት በጀት ከሚታገዘውና ጥቅመኛን ካሰባሰበው የጎጠኞች መንገድ ርቀህ በያዝከው አቋም ቀጥል" ማለት እሻለሁ።
ዝንታለም አማራ‼️
14 229
አንዱ ደፋር "እባክህ አሳዬ የወሎን ጉዳይ ለእኛ ለወሎዬዎች ተውልን" የሚል ኮሜንት በተደጋጋሚ ሲሰጠኝ "የትውልድ ስፍራዬን ፌስ ቡክ ላይ ስሞላ ተሳስቼ ይሆን እንዴ?" በሚል ጥርጣሬ ፕሮፋይሌን ከፍቼ ዐየሁት።
አልተሳሳትኩም።
"ወሎ አማራ ሳይንት" መወለዴን በትክክል ሞልቻለሁ።
እናም ኮሜንቱን የሠጠኝን ልጅ አካውንት ገልጬ ስመለከት የፕሮፋይል ምሥሉ ወሎን በሚጠቀልለው የኦነግ ካርታ አሸብርቋል።
የትውልድ ቦታው ላይ ደግሞ "ወለጋ" የሚል ሥም ሰፍሯል። 😆
እኔ እምለው ግን...
የወለጋ ልጅ ከወሎ ተወላጅ በላይ በወሎ ጉዳይ ቅርብ መሆን የጀመረው ከመቼ ወዲህ ነው?
14 229
ጨለማቸውን ለሚያወዳድሩ ከንቱዎች!!
አሳዬ ደርቤ
አማራን ሊያዋርዱ ከአማራ ሕዝብ አብራክ የተወለዱ የብልጽግና ዞምቤዎች "በአማራ ክልል ከሚገኙ ዞኖች መሀከል በልማትና በእድገት ወደኋላ የቀረው የእኔ ዞን ነው›› የሚል አጀንዳ ለኩሰው የኋላ ቀርነት ውድድሩን አጧጡፈውታል፡፡
እኔ ግን እላለሁ…
አማራን ለመከፋፈል የሚውል የአበል በጀት ተመድቦላችሁ ካልሆነ በቀር በቅርቡ በሁሉም ዞኖች ስንቀሳቀስ ለብስጭት እንጂ ለምቀኝነት የሚያነሳሳ ልማት በክልሉ ውስጥ አላየሁም፡፡
በጎንደርም ሆነ በወሎ፣ በሸዋም ሆነ በጎጃም ያስተዋልኩት… እንደ ገበጣ መጫወቻ የተቆፋፈረ አስፓልት፣ ውሃ የጠማው ቧንቧ፣ መብራት የናፈቀው አምፖል፣ ግንበኛና የግንባታ ቦታ አግኝቶ የግንባታ ማቴሪያል የቸገረው ጅምር ሕንጻ፣ ጠላት ታቅፎ መንግሥት የተሰወረበት ሕዝብ፣ እንቅልፍ የለሽ ፍጥረት አዝሎ ያንቀላፋ ከተማ… እና የመሳሰሉትን ነው፡፡
ለአዲስ አበባ ካላት ቅርበትና ለኢንቨስትመንት ካላት ተመራጭነት አንጻር የተወሰነ መነቃቃት ከሚታይባት የደብረ ብርሐን ከተማ ውጭ ‹‹ምድረ ገነት›› እያልን የምናወድሳት የባሕር ዳር ከተማ እንኳን የኮብል ስቶን ዘመን ላይ ተገትራ የምትቆዝም ሆናለች፡፡ አብዛኞቹ የወሎ፣ የጎንደርና የሸዋ ከተሞችም በመሠረተ ልማት ፈንታ ‹‹የማይወረሩ ወራሪዎች›› የሚጠብቁ ሆነዋል፡፡
ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ እንደ አገር የተለኮሰው ጦርነት ‹‹የሰሜን ኢትዮጵያ›› በሚል ሥያሜ አማራ ክልል ትከሻ ላይ ከተጣለበት ጊዜ አንስቶ ለወጣቶች የሥራ እድል መፍጠሪያ ሲውል የነበረው በጀት ለሕልውና ማስቀጠያ የሚውል መሆኑ ነው፡፡ ከብአዴን ዝርፊያ የሚተርፈው በጀት አዲስ መሠረተ ልማት ለመዘርጋት ቀርቶ በወራሪዎች የወደሙትን ተቋማት ወደነበሩበት ለመመለስ የማይበቃ መሆኑ ነው፡፡
እናስ የእራስን ጥያቄ ከማቅረብ ባለፈ በሌለ ልማት ዞንን ከዞን እያወዳደራችሁ የጋራ ውድመት ከተሸከመ ሕዝብ መሀከል ተጠቃሚ ከምትፈልጉ ከክልሉ ወጣ ብላችሁ "በክላስተርና በትራክተር የሚዘራው ስንዴ በትሕ-ኦነግ ወራሪዎች የሚፈናቀሉ ወገኖችን ፍጆታ በመሸፈን ረገድ ስላለው ፋይዳ ብታስረዱን አይሻልም ወይ?
14 229
በወሎ መስመር የሚታየው የሰሞኑ እገታ የጸጥታ ችግርን ከመፍራት የመነጨ ሳይሆን "በእለት ጉርስ እጦት የቀን ሠራተኛ ለመሆን አቅደው ከተለያዩ የወሎ አካባቢዎች የሚመጡ አማራዎች የዲሞግራፊ ለውጡን እያዛቡ ስለሆነ በዚያ መስመር የሚመጣ የትኛውም ተሳፋሪ ወደ አዲስ አበባ መግባት የለበትም" የሚል ትዕዛዝ በመተላለፉ የተነሳ ነው።
14 229
➔አገር የማፍረስ ሂደቱን አጋምሰውት ስለነበር "እርሳቸው ካልተመለሱ ይህች አገር መፈራረሷ አይቀሬ ነው" የሚል ጭንቀት አልተከሰተም።
➔ከሚዲያ የተሰወሩት ከፓርላማ በተላለፈ የጥላቻ ንግግር ከሁለት ሺህ በላይ ነፍሶች ወደ ጅምላ መቃብር በገቡ ማግሥት በመሆኑ "የንጉሡ መጥፋት የእርስ በእርስ መጠፋፋት ያመጣ ይሆን" የሚል ሥጋት የተሰማው አልነበረም።
➔"የጠሚው አለመኖር በአገር እና በገዢው ፓርቲ እጣ ፈንታ ላይ የሚያስከትለው አደጋ" የሚል ትንታኔም አልተሰማም። ምክንያቱም ከሚዲያ መራቃቸውን እያወቀም፣ እኩሉ አመራር አፋኝ፣ እኩሉ ደግሞ ታፋኝ ሆኖ እርስ በእርሱ ሲጠዛጠዝ ነበር።
በመሆኑም ሶሻል ሚዲያውን የሞላው ብቸኛ ርዕስ "ምን ሆነው ጠፉ?" የሚል ቀላል ጥያቄ ነበረ። 😆
14 229
ተቀዳሚ ሙፍቲ
(የእኛ ዘመን ጌታው ሸህዬ)
አማራዎችን በሀይማኖት ከፋፍሎ ለማክሰም በርካታ ጥረት ተደርጎ ነበር።
እርስዎ ግን እሳት ላይ ቤንዚን ከማርከፍከፍ ይልቅ ውሀን መረጡ። በወንድማማች መሀከል የተፈጠረ ክስተትን ከማጋጋል ይልቅ ማሸማገልን አስቀደሙ።
እናም በእርስዎ አርቆ አሳቢነት የከሸፈውን የሃይማኖት ግጭት ሳስብ ‹‹የምን ጊዜም ታላቅ የሃይማኖት አባት›› ብዬ ላመሰግንዎ ወደድኩ፡፡
ማሳሰቢያ፡- ይህ ጽሁፍ ከመጅሊስ ጋር የሚያገናኘው ነገር ስለሌለ ስድብ አይበረታታም፡፡
14 229
ሒስ እና መወድስ
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
➔የዓመቱ ተጽዕኖ ፈጣሪ እና አነጋጋሪ ሚዲያ - ኢትዮ 360
➔›› ›› አደናጋሪ ሚዲያ- EMS
➔›› ›› የግፉአን ድምጽ- የኛ ቲቪ፣ አዲስ ድምጽና ሮሐ ሚዲያ
➔›› ›› ሐቀኛ ጋዜጠኛ- ተመስገን ደሳለኝ እና ጎበዜ ሲሳይ
➔›› ›› እውነት ጠል ጋዜጠኛ- ፋሲል የኔ ዓለም
➔›› ›› መድሎኛ ጋዜጠኛ- ግሩም ጫላ
➔›› ›› ገለልተኛ ጋዜጠኛ- ኤሊያስ መሠረት
➔›› ›› ሕዝበኛ ፓርቲ- እናት ፓርቲ እና ባልደራስ
➔›› ›› ግለኛ ፓርቲ- ኢዜማ እና አብን
➔›› ›› ቁማርተኛ ፓርቲ- ብልጽግና
➔›› ›› ድንቅ ፖለቲከኛ- ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ
➔›› ›› ጽኑ አርበኛ- ዘመነ ካሤ
➔›› ›› አሰላሳይ ልሂቅ- ረ/ፕ ትንግርቱ ገብረ ጻድቅና መስከረም አበራ
➔›› ›› መካሪ ያጣ አማካሪ- ገምቱ እስቲ 😆
➔›› ›› የሕዝብ አርቲስት - ቴዲ አፍሮ
➔›› ›› የመንግሥት አርቲስት - አቤል ሙሉጌታ
➔የዓመቱ ጥቃት ቀስቃሽና ደም አፋሳሸ የጥላቻ ንግግር ማሠራጫ ስቲዲዮ- የፓርላማው አዳራሽ
አልጨረስኩም.... 😆
14 229
የዜጎች አገራዊ ስሜት ከኀምሌ ክረምት በላይ ሲቀዘቅዝ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቋም ሆነ የዓባይን ግድብ ሦስተኛ ዙር ሙሌት ማከናወኗ ትርጉም የለሽ ዜና ይሆናል።
እናም እንላለን....
ይህቺ አገር ሚዜዋን እና አጋፋሪዋን ታገኝ ዘንድ በየስፍራው እንደ አረም እየጨፈጨፈች የበደለችውን ሕዝብ ይቅርታ መጠየቅና ካሳ ከፍላ መታረቅ ይኖርባታል።
14 229
ቀኑ ይራዘም‼️
▬▬▬▬
የተመድ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መርማሪ ኮሚሽን በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ዙሪያ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ዙሪያ ማስረጃ ያላቸው ግለሰቦች፣ ቡድኖችና ተቋማት ሁሉ እስከ ሐምሌ 24 ድረስ በእጃቸው ያሉ ማስረጃዎችን እንዲያቀርቡ ጥሪ ማድረጉ የሚደገፍ ቢሆንም የተሰጠው ቀን ግን በቂ ስላልሆነ መራዘም ይኖርበታል።
በተረፈ በርካታ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳት የደረሰብን ተጎጂዎች ሆነን ሳለ በውሸት መረጃ ተከሳሾች እንዳንሆን በተመድ ሰብዓዊ መብት ድረ ገጽ ላይ የተቀመጠውን ወይም ደግሞ ከዚህ ጽሑፍ ስር ያለውን ቅጽ ሞልተን መላክ ይኖርብናል።
https://www.ohchr.org/en/hr-bodies/hrc/ichre-ethiopa/call-for-submissions
Share
14 229
የአማራ ሕዝብ "ያለኝን አትቀማኝ" እንጂ "የሌለኝን ስጠኝ" ብሎ አይጠይቅኽም።
"ባግባቡ ምራኝ" እንጂ "ሥልጣን ስጠኝ" ብሎ አይታገልኽም።
"አትግደለኝና አታውድመኝ" ከማለት ባለፈ "ከኢትዮጵያውያን አፍ ነጥቀህ ልዩ ጥቅሜን አስከብርልኝ" አይልኽም።
እነዚህን ጥያቄዎቹን መመለስ ካልቻልክ ግን ቆሌ እና ከራማኽን ገፍፎ ማዲያት በማዲያት ያደርግኻል። ምክንያታዊና ሚዛናዊ ድጋፉን ነፍጎ የምታወራውን የማታውቅ ወፈፌ ያደርግኻል። በሥልጣንህ ልትጎዳው ስታስብ በእንባው ጎርፍ ጠራርጎ ያጠፋኻል።
↪️የአባቶቻችን አምላክ ሆይ ደማችንን የምትመልስም ሆነ እንባችንን የምታብስ አንተ ነህና ሥምህ ለዘላለም የተመሰገነ ይሁን🙏
