የፍ/ሰ/ሰ/ት/ቤት መዝሙር ክፍል
رفتن به کانال در Telegram
ይህ ገፅ የፍኖተ ሰላም ሰ/ት/ቤት የመዝሙር ክፍል ገፅ ነው # መዝሙሮች # የበዓላት ወረብ # መልዕክቶች ይለቀቁበታል።
نمایش بیشتر1 411
مشترکین
-124 ساعت
-17 روز
+2630 روز
آرشیو پست ها
1 411
"ሁሉም በእግዚአብሔር ፍቃድ ሆነ" 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
ሰላም ውድ የሰንበት ትምህርት ቤታችን ወጣት አባላት እንደምን አመሻችሁ? አሜን አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን።
እንደ እግዚአብሔር መልካም ፍቃድ ዛሬ እሁድ ሰኔ 28/2018 ዓ.ም ከ4:00 ሰዓት ጀምሮ በሰንበት ትምህርት ቤታችን አዳራሽ የአመራር ምርጫ የተከናወነ ሲሆን። በዚህም መሰረት:- 👉👉👉
ለስራ አመራርነት፦
1-ወይንሸት ጌትነት
2-አበበ በሪሁን
3-አፈወርቅ ዮሐንስ
4-አስቴር ሻንቡ
5-መሰረት ታደሰ
6-ዲ/ን ሳሙኤል ተሾመ
7-ብሩክታዊት ዘርአይ
8-ሀብታሙ አለማየሁ
9-ይነበብ ከተማ
ለስራ አመራርነት ተጠባባቂ፦
1-ሚኒሊክ ጌታቸው
2-እፁብድንቅ ነጋ
3-ሱራፌል ጋሻው
ለአፈጻፀም ቁጥጥር እና ክትትል ክፍል
1-አባይነህ ቢያድግልኝ
2-ዲ/ን ዮሐንስ ዘሪሁን
ለአፈጻፀም ቁጥጥር እና ክትትል ክፍል ተጠባባቂ፦
1-አለምነሽ ጌቱ
2-ሚኒሊክ አዲሱ
ሆነው ተመርጠዋል።
የስራ ድልድል ግን አልተከናወነም። የስራ ድልድሉን ደግሞ በዚህ ሳምንት ውስጥ የምናሳውቅ ይሆናል።
እስከዛው ግን በፀሎት አስቡ።
መልካም ምሽት። ሰላም እደሩ።
ፈጣሪ ፍኖተ ሰላም ሰንበት ትምህርት ቤታችንን ይጠብቅልን።
አስመራጭ ኮሚቴ
1 411
ወረብ ዘሰኔ 30
ሰላም ለጽንሰትከ እንበለ ሀጢያት ወግማኔ ወለልደትከ ሰላም አመ ሰላሳሁ ለሰኔ/2/
ዮሐንስ ዘኮንከ ደመና ሰማይ ኮናኔ ደመና ሰማይ/2/
ትርጉም:- ያለ ኀጢአትና ያለ ርኵሰት ለተፈጸመ ጽንሰትህ እና በሰኔ በ30ኛው ዕለት ለሆነው ልደትህ ሰላምታ ይገባል ዮሐንስ የሰማይ ደመናን ታዝዝ ዘንድ ሥልጣን ተሰጠህ
1 411
መጥምቁ ዮሐንስ✨✨
መጥምቁ ዮሐንስ ነቢይ ወሀዋርያ
ሴቶች አልወለዱም ከቶ ያንተን አምሳያ ×2
አዝ===
የግመሏን ፀጉር " ዮሐንስ
በላይህ ደርበህ ዮሐንስ
በርሀ ሀሩሩን ዮሐንስ
በፅናትህ አልፈህ ዮሐንስ
ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትል በብርድ በቁር
ወንጌልን ሰብከሃል በይሁዳ ምድር
አዝ===
ልባችሁ አይደንግጥ ዮሐንስ
ሰዶቃውያኑ ዮሐንስ
ከሚመጣው መቅሰፍት ዮሐንስ
ተጠምቃችሁ ዳኑ ዮሐንስ
መንገዳችሁ ይመር ሳይዘጋ በሩ
ብለህ ነገርካቸው በጎ ሰራ ስሩ
አዝ===
ጎባጣውም ይቅና ዮሐንስ
የተጣመመው ዮሐንስ
ይመለስ ይታረቅ ዮሐንስ
ታዞ ለጌታው ዮሐንስ
እያልክ አስተምረህ ዘወትር ተግተህ
ከአምላክ አስታረከን መንገዱን ጠርገህ
አዝ===
ለእግዚአብሔር ታዘህ ዮሐንስ
ለህጉ ተገዝተህ ዮሐንስ
ሰናክሬም ንጉስህ ዮሐንስ
በቃልህ ገስፀህ ዮሐንስ
እስከ መጨረሻው ፀንተህ በእምነት
አንገትህ ተቀልቶ ሆንክ ሰማዕት
1 411
ምን ሰማ ዮሐንስ ✨
ምን ሰማ ዮሐንስ በማህጸን ሳለ
ህፃን ሆኖ ነቢይ ለክብር የተጠራ
እንደ እንቦሳ ጥጃ ያዘለለ ደስታ
ምን አይነት ድምጽ ነው ምን አይነት ሰላምታ
አዝ
ከተፈጥሮ በላይ ያሰገደ ክብር
እንዴት ቢገባው ነው የእናታችን ፍቅር
ሌላ ድምጽ አልሰማም ከእንግዲህ በኋላ
ለውጦኛልና የሰላምታ ቃሏ
አዝ
በረሀ ያስገባ ለብዙ ዘመናት
ምን አይነት ራዕይ እንዴት ያለ ብስራት
እንደ አዲስ ምስጋና ስልቱ የተዋበ
ተደምጦ የማያውቅ ጭራሽ ያልታሰበ
አዝ
ከሴት ከተገኙ ከደቂቀ አዳም
ድንግል ስለሆነ በህይወቱ ፍጹም
በማህጸን ሳለ ተመርጦ በጌታ
ለማዳመጥ በቃ የኪዳን ሰላምታ
ረጃጅሞቹን የቅዱስ ዮሐንስ ዝማሬዎች አገልግሎት ላይ ስለምንዘምራቸው ግጥምና ዜማቸውን እንድታጠኑ አደራ እንላለን።
ፍኖተ ሰላም ሰ/ት/ቤት ✨ @fnotesmk
1 411
መጥምቀ መለኮት ዮሐንስ
መጥምቀ መለኮት ዮሐንስ /2/
መጣ ከበረሀ ህዝቡን ሊቀድስ /2/
አዝ
ዮሐንስ ሰበከ ስለክርስቶስ
ኃጢአትን የሰራ ቶሎ እንዲመለስ
መንገዱ ይጠረግ የጎበጠው ይቅና
መድኃኒት ክርስቶስ ይገለጣልና
አዝ
በሔኖን በረሃ ድምጽህ ሲያስተጋባ
ቃልህ ውስጤን ነካኝ ፍቅርህ ልቤ ገባ
እውነት ነው ስብከትህ ፍሬ አለውና
እጆቼን ልዘርጋ ምህረት ልመና
አዝ
የዕዳ ፅህፈታችን በአምላክ ሲደመሰስ
አንተንም አየንህ ቆመህ በዮርዳኖስ
ጌታችን ሲጠመቅ ዲያብሎስ ተረታ
ነፍሳችን ዘለለች ሀሴትን ተመልታ
ፍኖተ ሰላም ሰ/ት/ቤት 🔘@fnotesmk🔘
1 411
ወአንተኒ ሕፃን
ወአንተኒ ሕፃን ነቢየ ልዑል /2/
አርኩ ለመርዓዊ ትሰመይ ትሰመይ ነቢየ ልዑል
ትርጉም፡-አንተ ህፃን የልዑል ነቢይ የሙሽራው ሚዜ ዮሐንስ ትባለለህ፡፡
ፍኖተ ሰላም
ሰ/ት/ቤት
🔘@fnotesmk
