fa
Feedback
CUSTOMS COMMISSION JIGJIGA BRANCH/በጉምሩክ ኮሚሽን የጅግጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

CUSTOMS COMMISSION JIGJIGA BRANCH/በጉምሩክ ኮሚሽን የጅግጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

رفتن به کانال در Telegram

ራዕይ፡- "በ2022 በአገራችን ደረጃዉን የጠበቀ ዘመናዊ የጉምሩክ አስተዳደር ተገንብቶ ማየት ስ/ቁ-025-775-72-77

نمایش بیشتر
3 409
مشترکین
+324 ساعت
+107 روز
+12030 روز
آرشیو پست ها
የጉምሩክ ኮሚሽን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለሰራተኞች ሲሰጥ የቆየው የስልጠና መርሃ ግብር ተጠናቀቀ ጅግጅጋ፣ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም የጉምሩክ ኮሚሽን የሰራተኞቹን ሙያዊ አቅምና ክህሎት ለማሳደግ፣ የሥራ አፈጻጸምን ለማሻሻል እና የጀመራቸውን የሪፎርም ሥራዎች ውጤታማ ለማድረግ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በአራት ዙሮች ለጅግጅጋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሰራተኞች ሲሰጥ የቆየው የስልጠና መርሃ ግብር ተጠናቀቀ። ስልጠናው የሰራተኞችን የሙያ እውቀት ለማጠናከር፣ በሥራ ላይ የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶች በተሻለ ሁኔታ ለመፍታት እና ዘመናዊ የጉምሩክ አሠራሮችን በብቃት ለመተግበር የሚደገፍ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም ስልጠናው የሰራተኞችን የሙያ አቅም በማሳደግ የተቋሙን የለውጥ ሂደት በተግባር ለማስፈጸም እና የሪፎርም ሥራዎቹን ውጤታማ ለማድረግ የሚያግዝ ነው። የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሰራተኞችም በስልጠናው ያገኙትን እውቀትና ክህሎት በዕለት ተዕለት ሥራቸው በመተግበር፣ የኮሚሽኑን የሪፎርም አቅጣጫዎች ለማሳካት የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ ተጠቁሟል። በደንበኞች ትምህርት ቡድን ጅግጅጋ፣ ኢትዮጵያ