cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

GOSPEL FOR ALL PEOPLE GROUPS

ሰላም ቅዱሳን የቻናላችን ቤተሰቦች፣ በቻናሉ የሚንለቅላችሁ ፕሮግራሞች ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ስሆን፣ ሌሎችም ተጠቃሚ እንድሆኑ እንድትጋብዙ እናሳስባለን።። ✔ መንፈሳዊ መጽሐፍቶች/መጽሔቶችን ✔ ወንጌልን ስለማሰራጨት የሚመለከቱ ት/ቶችን ✔ መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት ያደረጉ ት/ቶችን ✔ የቆዩ እና አዳድስ አምልኮ መዝሙሮችን ✔ አንዳንድ ጠቃሚ አባባሎችን

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
414
مشترکین
+124 ساعت
+77 روز
+5330 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ከከበረው ስፍራ ስወርድ ክብሩን እንደሚያጣ ምንም ሳይሰስት እስካለሁበት ውርደት ስፍራ መጥቶ በቦታዬ ቆሞ ታየልኝ። የለበስኩትን ነቀፌታዬን አውልቆ ለራሱ ለበሴ ፣ በራሱ ላይ ያለውንምም ዋጋው እጅግ ውድ የሆነውን ክብሩን አለበሰኝ። ሞትንም ከሚመስል ሞት አዳነኝ ፣ የዘላለምን ሕይወት ሰጠኝ። እርሱን ተዋውቄ ለዘላለም የሁለንተናዬ እረፍት እና ደስታ ሆነኝ፣ እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ይባላል። እርሱ ነው ንጉሴ ፣ የነፍሴ ዋና ፣ ክብር ስያሻኝ ዓይኔን ወደ እርሱ አቅንቼ የማየው። የክብሬ ጥግ ፣ የሚኖረው ለእርሱ ፣ ሕይወቴን ደግሞ የሚቋጨውም በእርሱ ነው። እረፍት የሚያሻው በሙሉ ትኩረቱን ወደ ኢየሱስ ፣ ለዘለዓለሙም ያርፋል። ዓለም አታላይ እና ከንቱ ናት። በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ያሰበሰበ ግን የዘላለምን ደስታ ያጭዳል። ከጌታ ጋር መሰንበቱ ዋስትና አለውና ጊዜ ሳለ ኖረን እናተርፍበት። "ነገር ግን ቃሉን የሚማር ከሚያስተምረው ጋር መልካምን ነገር ሁሉ ይከፋፈል። አትሳቱ፤ እግዚአብሔር አይዘበትበትም። ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና፤ በገዛ ሥጋው የሚዘራ ከሥጋ መበስበስን ያጭዳልና፥ በመንፈስ ግን የሚዘራው ከመንፈስ የዘላለምን ሕይወት ያጭዳል።" ገላትያ 6 :6-8 ❤❤❤
نمایش همه...
1
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
Photo unavailableShow in Telegram
#Update “ ሃያ (20) ሄክታሩን አጥረውታል። መጋዘኖችንም እያፈረሷቸው ነው። ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ” - ቤተክርስቲያኗ የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን፣ 40 በመቶ የሚሆን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታዋን የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ‘ በጉልበት ሊወስደው ነው ’ ስትል ከሰሞኑን በተደጋጋሚ መግለጫ መስጠቷ ይታወቃል። ጉዳዩ ከምን ደረሰ ? ቤተ ክርስቲያኗ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠችው ቃል ፣ “ 20 ሄክታሩን አጥረውታል። መጋዘኖችን እያፈረሷቸው ነው። ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ” ብላለች። “ ዛሬ (ሰኞ ሐምሌ 8 ቀን 2016 ዓ/ም) ግቢ ውስጥ ገብተው በጉልበት አጥረውታል። መሳሪያ በያዙ ሰዎች እያስጠበቁት ነው ያሉት ” ስትል ገልጻለች። ይህንን ያሉት አንድ የቤተ ክርስቲያኗ አካል ፣ “ እኛም ዛሬ ለጠቅላይ ሚኒስቴሩም፣ ለኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ አመራሮችም ደብዳቤ እየላክን ነው ” ብለዋል። “ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጠዋት ነው የላከነው፣ ለአቶ ሽመልስ አብዲሳም ልከናል። ገና ምንም የሰጡት ምላሽ የለም ” ሲሉ አክለዋል። “ 40 በመቶ ገደማ ይዞታችን ነው ይወሰዳል የተባለው ” ያሉት እኝሁ አካል፣ “ አሁን ግማሹን አጥረዋል። ለሁለት ግለሰቦች ነው ይሰጣል የተባለው ” ነው ያሉት። በተጨማሪ ፣ በፍርድ ቤትም እግድ እንዲያወርድላቸው እንደጠየቁ፣ የሚጠብቁት ያስገቡትን ደብዳቤ ምላሽ እየጠበቁ እንደሆነ ገልጸዋል። “ አስቸኳይ ምላሽ የማይሰጠን ከሆነ ሰላማዊ ሰልፍ ወደ መጥራት የምናመራ ይሆናል። በሰላማዊ መንገድ ድምፃችንን እናሰማለን። ሁል ጊዜ ቤተ ክርስቲያን የምትቆመው ከሰላም ጎን ነው። የመረበሽ የማስረበሽ ዓላማ የላትም ” ብለዋል። ቅሬታ የቀረበበት የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም። ሆኖም በቀጣይ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆነ ምላሹን የምናቀርብ ይሆናል። #TikvahEthiopiaFamilyAA @tikvahethiopia
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
የኩሪፍቱ ማእከል ውስጥ በመግባት ሌላ አጥር መሳሪያ በታጠቁ አካላት ጭምር በመታገዝ ወራራ እያካሄዱ ነው https://youtu.be/56Ss0u0wzNI
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
አሸናፊው የክርስቲያን ኑሮ.pdf6.30 MB
የብሉይ ኪዳን አሰሳ.pdf2.33 MB
የይሁዳ መልዕክት.pdf4.07 KB
ግኖስቲክ
ቃሉ ዕውቀት ተብሎ ከሚተረጐም ከግሪክ ቃል የመጣ ነው። ከግሪክ ዓለም ብዙ ሰዎች ደኅንነት የሚገኘው ዕውቀትን በማግኘት ነው ብለው ያምኑ ነበር። የግኖስቲክ አስተሳሰብ ወደ ቤ.ክ. በልዩ ልዩ ዓይነት ይገባ ነበርና ሐዋርያት ተቃወሙት። የግኖስቲክ ሐሳብ ብዙና የተለያየ ነበር። ዋና ዋና ትምህርታቸው እንደሚከተለው ነው። (ሐዋርያት ትምህርቱን የተቃወሙባቸው አንቀጾች በቅንፍ ውስጥ ተጽፈዋል)። 1. ሰው በዕውቀት እግዚአብሔርን ያገኛል። ይህ ዓይነት አስተሳሰብ ግን ኵራትንና ብዙ ዓይነት የማይረባ መለፍለፍን ያስከትላል (1ጢሞ. 1፥3:4፤ 6 : 20) 2. እውነተኛው ዓለም መንፈሳዊ ነው። ይህ ዓለም የእውነተኛው ጥላ ብቻ ነው። ስለዚህ ክርስቶስ በሥጋ እንደመጣ አያምኑም (1ዮሐ. 4፥3፤ 2ዮሐ. 7)። 3. ሰው የሚድነው ከተፈጠረው ዓለም በመለየት ነው። አንዳንዶች ይህ የሚፈጸመው ሥጋን በመግዛትና በማድከም እንደሆነ አስተማሩ። ይህንም አምነው ጋብቻን፥ ልዩ ልዩ ዓይነት ምግብንም ከለከሉ (1ጢሞ 4፥3-5)። ትንሣኤም በመንፈስ እንደሆነ ተረጐሙ (2ጢሞ. 2፥18)። ሌሎች ግን እውነተኛው ዓለም መንፈሳዊ በመሆኑ ሥጋዊ ድርጊት ለውጥ እንደማያመጣ አስበው የፈለጉትን አደረጉ (2ጢሞ 36:7) 4. እግዚአብሔር መሠረታዊ የሆነ አንድ ነገርን ፈጠረ፤ ቀጥሎም ሌላ ነገር ከዚያ ወጣ፥ በኋላም ከዚህ የተለያዩ ነገሮች እየወጡ በመጨረሻ ይህ የሚታየው ዓለም ተገኘ። ስለዚህ በዓለምና በእግዚአብሔር መካከል ብዙ ደረጃዎች ይገኛሉ (ቆላ. 1፥19:20፤ 2:8-15) 5. ሰው የሚድነው በዐዋቂዎች መካከል በሚደረግ ሥርዓትና ወግ ነው ይሉ ነበር (ቆላ. 2:16-23)። “እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፥ ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።”   — ዮሐንስ 5፥24 የዘላለም ሕይወት የሚገኘው የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ፣ በማመን ፣ መታዘዝ እና በማድረግ ይገኛል። ኢየሱስ ጌታ ነው ያድናል።🙏
نمایش همه...
👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
“ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤ ካመንንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና።” — ሮሜ 13፥11 #share በማድረግ ለሌሎች አድርሱ💞🙏💞
نمایش همه...
Repost from Biblical Marriage
አብሮን የሚሰራ ሰው እንፈልጋለን! ከተለያዩ የሃገራችን ክፍል ያሉ ወጣቶች፣እጮኛሞችና ባለትዳሮች ከፍተኛ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ግልፅ ነው። ብዙ ሰዎች በተለያዩ ሱስ ውስጥ እንዳሉም ግልፅ ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ እኛ የተቻለንን እየሰራን እንገኛለን። አሁን ግን ኑ አብረን እንስራ እያልን ጥሪ እናቀርባለን! #መስፈርቶች ቢቻል:- ✅ Psychology ምሩቅ የሆነ ✅ Marriage and family counseling ምሩቅ ✅Special Needs እውቀት ያለው #ካልሆነ_ግን:- ❤️ የማማከር ፍላጎት ያለው ❤️ ከዚህ በፊት የሱስ ተጠቂ የነበረና አሁን ላይ ከዛ ሱስ የወጣ(ተሞክሮን ለማከፈል) ❤️ እድሜ ከ 18 አመት በላይ የሆነ #በጎ_ፍቃደኞች(በተወሰነ ክፍያ ሊሰራ የሚችል) 🪀 Website Developer 🪀 Graphics designer በከተሞች ደረጃ አንዳንድ #ተወካይ ሊሆን የሚችል ሰው ስለምንፈልግ አብሮን ሊሰራ ሊያገለግል የሚወድ ሊያናግረን ይችላል። ቴሌግራም አድራሻ:- @AbrishEL ስልክ ቁጥር:-0910337074 Facebook: abrishsonofjesus ልቡና ቅናቱ ያላችሁ እንዲሁ አገልግሎታችንን መርዳትና መደገፍ የምትፈልጉ ቀጥታ በመደወል ልታናግሩን ትችላላችሁ። ሰላም ይብዛላችሁ! 🩸 @Biblicalmarriage🩸
نمایش همه...
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.