fa
Feedback
በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት🇪🇹

በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት🇪🇹

رفتن به کانال در Telegram

በሊንኮቻችን ተጨማሪ መረጃዎችን ማግኘት ይችላሉ። ፌስቡክ- https://www.facebook.com/meskan.wereda ቴሌግራም-https://t.me/meskanweredacom31 ዩቲዩብ-https://www.youtube.com/channel/UC6PBsPYR5dltyXhEJchdlaA ትዊተር-90ijTxwVTG6dwoT ኢሜል-meskanweredacommunication111@gmail.com

نمایش بیشتر
839
مشترکین
-124 ساعت
+47 روز
+2930 روز
آرشیو پست ها
‎በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ "የተቀናጀ የግብርና ትጋት ለላቀ ምርታማነት" በሚል መሪ ቃል ወረዳዊ የግብርና ፅ/ቤት የ2018 የመህር ወቅት የተቀናጀ የግብርና የንቅናቄ መድረክ ማካሄድ ጀምሯ
+8
‎በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ "የተቀናጀ የግብርና ትጋት ለላቀ ምርታማነት" በሚል መሪ ቃል ወረዳዊ የግብርና ፅ/ቤት የ2018 የመህር ወቅት የተቀናጀ የግብርና የንቅናቄ መድረክ ማካሄድ ጀምሯል። ‎===== ሐምሌ _01/2018 ዓ.ም በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ "የተቀናጀ የግብርና ትጋት ለላቀ ምርታማነት" በሚል መሪ ቃል ወረዳዊ የግብርና ፅ/ቤት የንቅናቄ መድረክ በዛሬው እለት ማካሄድ ተጀመረ። በንቅናቄ መድረኩ የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ውልጫፎ፣ የመስቃን ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ሁሴን ኤርሞሎ፣የመስቃን ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ መሀመድ ሳኒ፣ የመስቃን ወረዳ ም/አስተዳዳሪ እና የግብርና ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ገረመው ተመስገንን ጨምሮ ሌሎች አስተባባሪዎች፣የወረዳ አመራሮች፣ ከቀበሌ የመጡ አመራሮች፣ የሴክተሩ የማኔጅመንት አካላት እና ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት ተገኝተውበታል። በዕለቱም በዝግጅቱ የተገኙ አካላቶች የደም ልገሳ በማድረግ ሰብዓዊ ሃላፊነት በመወጣት በከደም ለጋሹ ምንም ሳይጎድል፤ ውድ የሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት መታደግ የሚያስችለው “ደም”፣ ልዩ ስጦታነቱን በመግለፅ “ደም መለገስ የፍቅር መግለጫ እንደሆነ አሳይተዋል። #ዝርዝር መረጃ እንመለስበታለን።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት 6ኛ የፓርላማ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ የኢፌዲሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት 6ኛ የፓርላማ ዘመን፣ 5ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ፣ 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን ለእለቱ የተያዙ አጀን
+1
የፌዴሬሽን ምክር ቤት 6ኛ የፓርላማ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ የኢፌዲሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት 6ኛ የፓርላማ ዘመን፣ 5ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ፣ 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን ለእለቱ የተያዙ አጀንዳዎችን በማጽደቅ ማካሄድ ጀመረ። ምክር ቤቱ በጉባኤ አዳራሹ እያካሄደ በሚገኘው በዚህ ስብሰባ፤ መጀመሪያ የስድስተኛ የፓርላማ ዘመን፣ 5ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ 1ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ ጉባዔውን መርምሮ አጽድቋል። በመቀጠልም ምክር ቤቱ ያጸደቃቸውን ሌሎች አጀንዳዎች በዝርዝር ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ የምክር ቤቱ መረጃ ያመላክታል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መስጠፋ ሀሰን በመስቃን ወረዳ የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት አካል የሆነው የጆሌ 2እና 3 አጠቃላይ ጤና ኬላ ግንባታ አሁናዊ አፈፃፀም ያለበት ደረጃ
+5
የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መስጠፋ ሀሰን በመስቃን ወረዳ የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት አካል የሆነው የጆሌ 2እና 3 አጠቃላይ ጤና ኬላ ግንባታ አሁናዊ አፈፃፀም ያለበት ደረጃ ምልከታ አደረጉ ። ሰኔ_28/2018(የመስቃን ወረዳ መንግሰት ኮምዩኒኬሽን) የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መስጠፋ ሀሰን በመስቃን ወረዳ የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት አካል የሆነው የጆሌ 2እና 3አጠቃላይ ጤና ኬላ ግንባታ አሁናዊ አፈፃፀም ያለበት ደረጃ በዛሬው እለት አካላዊ ምልከታ አድርገዋል። በአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት ምልከታ መርሃ ግብሩ ላይ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መስጠፋ ሀሰን ፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሠረት ሽፋ፣የምስራቅ ጉራጌ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪና የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አህመድ ኑሪ ፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ት/መ/ል/መምሪያ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጎሳዬ፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ መሀመድ ሁሴን፣የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሀመድ ውልጫፎ፣ የመስቃን ወረዳ ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ሁሴን ኤርሞሎ፣ የመስቃን ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፓርት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ መሀመድ ሳኒን ጨምሮ ሌሎች የወረዳው አስተባባሪዎች፣ በፕሮግራሙ የተገኙ ከዞን ፣ ከከተማ አስተዳደር እና ከወረዳ የመጡ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የመስቃን ወረዳ አጠቃላይ አመራሮች፣ ከየቀበሌው ጥሪ የተደረገላቸው የቀበሌ ሊቀመንበሮች እና ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት ተገኝተዋል። በጉብኝት ወቅት አጠቃላይ ጤና ኬላው

በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ ከ23 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በተገኙበት ተመረ
+1
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ ከ23 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በተገኙበት ተመረቀ። ሰኔ_28/2018(የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽ በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ ከ23 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በተገኙበት በዛሬው እለት ተመርቋል። በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ ከ23 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት አካል የሆነው የመንገድና የድልድዮች ፕሮጀክት እንዲሁም የተለያዩ መሰረተ ልማቶች የዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መስጠፋ ሀሰንና ሌሎች የዞኑ የፊት አስተባባሪ አካላትና አመራሮች፣ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሀመድ ውልጫፎና ሌሎችም የፊት አስተባባሪ አካላትና አመራሮች፣ በከወረዳው ዋና አፈ-ጉባኤ ክቡር አቶ ሁሴን ኤርሞሎ እንዲሁም የቡታጅራ ከተማ ከንቲባ የተከበሩ አቶ አብዶ አህመድና ሌሎችም አመራሮችና ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የአካባቢው ማህበረሰብ በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ተመረቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል። በዝርዝር መረጃ እንመለሳለን።

በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት አካል የሆኑት የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የምልከታና የምረቃ ፕሮግራም በደመቀ ሁኔታ ተካሄደ። ሰኔ_28/2018 ( የመስቃን
+6
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት አካል የሆኑት የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የምልከታና የምረቃ ፕሮግራም በደመቀ ሁኔታ ተካሄደ። ሰኔ_28/2018 ( የመስቃን ወረዳ መንግሰት ኮሙኒኬሽን ) በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት አካል የሆኑት የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የምልከታና የምረቃ ፕሮግራም በዛሬው እለት በደመቀ ሁኔታ ተካሄዷል። በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት አካል የሆነው የጆሌ 2እና 3 አጠቃላይ ጤና ኬላ ግንባታ አሁናዊ አፈፃፀም ያለበት ደረጃ ምልከታ በማድረግ የጀመረው መረሃ ግብሩ በግድየና አቦራት እና በምዕራብ እንቦር ቀበሌዎች በመንግስትና በህብረተሠብ ቅንጅት የተሠሩ የመንገድና ድልድይ ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል። የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መስጠፋ ሀሰን የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት አካል የሆነው የጆሌ 2እና 3 አጠቃላይ ጤና ኬላ ግንባታ አሁናዊ አፈፃፀም ያለበት ደረጃ ምልከታ ባደረጉበት ወቅት እንደገለፁት ከተቀመጠለት ጊዜ አንፃር በተሻለ ፍጥነት እየተሠራ መሆኑን አንስተዋል። ለማህበረሰቡ ዘላቂ የሆኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ደረጃ በደረጃ እየፈቱ መሄድ ወሳኝ ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው በመስቃን ወረዳ በመንግስትና በህዝብ ቅንጅት በዛሬው እለት የተመለከትናቸውና የመረቅናቸው ፕሮጀክቶች እጅግ የሚያስደስቱ የአመራር ቁርጠኝነት የታየባቸው ናቸው ብለዋል። መንግስታችን ለሀገር ልማትና ግንባታ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ኢትዮጵያ ሀገራችንን ወደ ተሻላ ልዕልናና ብልፅግና ለማሻገር ከምንጊዜውም በላይ እየሰራ ይገኛል ያሉት

የመስቃን ባህልና ልማት ማህበር የማስተዋወቅና የንቅናቄ መድረክ መካሄድ ጀመረ። ሰኔ_14/2018 ዓ.ም የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና የመስቃን ልማትና ባህል ማህበር የጠቅላላ ጉባኤ ሰብሳቢ
+8
የመስቃን ባህልና ልማት ማህበር የማስተዋወቅና የንቅናቄ መድረክ መካሄድ ጀመረ። ሰኔ_14/2018 ዓ.ም የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና የመስቃን ልማትና ባህል ማህበር የጠቅላላ ጉባኤ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በተገኙበት የመስቃን ባህልና ልማት ማህበር የማስተዋወቅና የንቅናቄ መድረክ በተለያዩ ኩነቶች እየተካሄደ ነው። በመድረኩም የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ እና ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ አህመድ ኑሪ፣ የየክልል ፣ የዞን፣ የከተማና የወረዳ አመራሮች፣ የመስቃን ልማትና ባህል ማህበር የቦርድ አባላትና አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ የሚዲያ አካላት፣አርቲስቶች እና መላው የማህበረሰቡ ተወላጆች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተውበታል። ‎================== ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን!! በተጨማሪም እነዚህ ሊንኮችን በመጫን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡ 📌 ፌስቡክ-https://www.facebook.com/gzmwgcao?mibextid=ZbWKwL 📌ቴሌግራም-https://t.me/meskanweredacom31 📌 ዩቲዩብ-https://www.youtube.com/channel/UC6PBsPYR5dltyXhEJchdlaA 📌 ቲክቶክ -tiktok.com/@meskan.woreda.gov 📌 ትዊተር-90ijTxwVTG6dwoT 📌 ኢሜል-meskanweredacommunication111@gmail.com

በመስቃን ወረዳ "ከምርጫ ድል ማግስት ጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ሀሳብ በመስቃን ወረዳ አስተዳደር የ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የምስራቅ ጉራጌ ዞን አስተባባሪ አካላትና አመራሮች እንዲ
+3
በመስቃን ወረዳ "ከምርጫ ድል ማግስት ጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ሀሳብ በመስቃን ወረዳ አስተዳደር የ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የምስራቅ ጉራጌ ዞን አስተባባሪ አካላትና አመራሮች እንዲሁም የወረዳው አጠቃላይ አመራር በተገኙበት የግምገማ መድረክ መካሄድ ጀምሯል። ======================== ሰኔ 12፣ 2018 (መስቃንወረዳ መ/ኮሙኒኬሽን "ከምርጫ ድል ማግስት፤ ጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ቃል በድህረ ምርጫ ግቦች ላይ ትኩረት ያደረገ የአመራሮች መድረክ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳደር የተከበሩ አቶ ሙስጠፋ ሃሰን በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል ። መድረኩ በስኬት የተጠናቀቀውን የ7ተኛዉ ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የቅድመ ምርጫና የምርጫ ስራዎች አፈፃፀም በመገምገም በቀጣይ የድህረ ምርጫ ግቦች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑ ተመልክቷል። ለዕለቱ የተዘጋጁ ሁለት ሰነዶች እየቀረበ የሚገኝ ሲሆን በድህረ ምርጫ ማግስት የአመራር ሚና ምን መሆን አለበት በሚል ተዘጋጅቶ በወረዳው ረዳት የመንግስት ተጠሪና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ወንዴ ነሲቡ ቀርቧል እንዲሁም የሚዲያ አጠቃቀም ስርዓትና አጠቃላይ ይዘት ላይ ያተኮረ ሁለተኛው ሰነድ የመስቃን ወረዳ ረዳት የመንግስት ተጠሪ የሆኑት የተከበሩ አቶ ተሾመ አርጋ አማካኘት እየቀረበ ይገኛል። በመጨረሻ ሰነዶቹን መሰረት ያረገ ሰፋ ያለ የውይይት መድረክ ይኖራል። ዝርዝር መረጃ ይኖረናል። =================

#ዜና_ችሎት ​በህጻን ልጅ ላይ የግብረ-ስጋ ድፍረት በደል ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በፅኑ እስራት ተቀጣ። ======= ሰኔ 10/2018 ቡታጅራ (የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን) ​ተከሳሽ አቶ
#ዜና_ችሎት ​በህጻን ልጅ ላይ የግብረ-ስጋ ድፍረት በደል ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በፅኑ እስራት ተቀጣ። ======= ሰኔ 10/2018 ቡታጅራ (የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን) ​ተከሳሽ አቶ ይርጋለም ሙላቱ በሚያዝያ ወር ቀኑ በውል በማይታወቅበት ጊዜ በግምት ከቀኑ 10:00 እስከ 11:00 በሚሆንበት ጊዜ በመስቃን ወረዳ ጎይባን ቀበሌ ልዩ ቦታው ገጃ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የግል ተበዳይ የሆነችው ዕድሜዋ ከ11 እስከ 13 ዓመት በሚሆናት ህፃን ቅድስት ደምሰስ ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈፅሟል በሚል የተጣራ የምርመራ መዝገብ የደረሰው የመስቃን ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት ዐ/ህግ በተከሳሽ ላይ በ1997 ዓ/ም በስራ ላይ በዋለው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 627 (1) የተመለከተውን በመተላለፍ በህፃናት ላይ በሚፈጸም የግብረ ስጋ ድፍረት በደል ወንጀል ክስ አቅርቦበታል። ክሱ የቀረበለት የMeskan ወረዳ ፍትህ ዐ/ህግ ባቀረባቸው ማስረጃዎች ከበቂ በላይ ያስረዳ በመሆኑ ተከሳሽ መከላከያ ማስረጃ እንዲያቀርብ ብይን የተሰጠ በመሆኑ ተከሳሽ መከላከያ ማስረጃዎችን አቅርቦ የተከራከረ ሲሆን ፍ/ቤቱም ግራ ቀኙን ማስረጃ ከሰማ በኋላ መዝገቡን መርምሮ ተከሳሽ በተከሰሰበት የወንጀል ህግ ድንጋጌ ስር ጥፋተኛ ነው በማለት የጥፋተኝነት ውሳኔ አስተላልፏል ። ​በዚህ መሰረት ፍ/ቤቱ ግራ ቀኙን የቅጣት አስተያየት ከሰማ በኋላ በቀን 10/09/2018 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽን ያርማል ሌላውንም የማህበረሰብ ክፍል መሰል ወንጀሎችን ከመፈጸም እንዲቆጠቡ ያደርጋል ያለውን በ10 ዓመት ከ5 ወር እስራት እንዲቀጣ ወስኗል ። ​ማህበረሰቡ መሰል የወንጀል ድርጊቶችን ከመፈጸም እንዲቆጠብ በማለት መልዕክታችንን እናስተላልፋለን ። ​ዘገባው የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ነው።

በመስቃን ወረዳ የዊጣ ታዳጊ ማዘጋጃ ቤት የተለያዩ የከተማው የውስጥ ለውስጥ መንገድ ሪዳሽ ማልበስ እና የጥገና ስራ ላይ ይገኛል። ========= ሰኔ 9/2018ዓ.ም የመስቃን ወረዳ የመንግስት ኮሙኒ
+5
በመስቃን ወረዳ የዊጣ ታዳጊ ማዘጋጃ ቤት የተለያዩ የከተማው የውስጥ ለውስጥ መንገድ ሪዳሽ ማልበስ እና የጥገና ስራ ላይ ይገኛል። ========= ሰኔ 9/2018ዓ.ም የመስቃን ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን በዚህም ወደ ሶስት(4.2) ኪሎ ሜትር ሽፋን ያለው የዊጣ ከተማ በሁሉም አቅጣጫ ማለትም በሴራና፤ንቡር፤አቦቸና፤ወገሬት ሰፈሮችን የሚያገናኝ የውስጥ ለውስጥ መንገድ የሪዳሽ ማልበስ ስራ እና ጥገና እንዲሁም የዲች ስራ በማከናውን ላይ የሚገኝ ሲሆን መንገድ ለኢኮኖሚ፤ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ እድገት እና ትስስር ትልቅ ሚና እንዳለው የገለጹልን የመስቃን ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ም/ሃላፊ አቶ ዑስማን ናስር የከተማና የገጠር ትስስር ከማጠናከር አኳያ አምራችና ሸማች እንዲሁም በቂ የሆነ የንግድ ፍሰት እንዲኖር ከማስቻል ረገድ የጎላ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል። የመስቃን ወረዳ የዊጣ ከተማ ታዳጊ መዘጋጃ ጽ/ቤት ሃላፊ አህመኑር ከድር እየተሰራ የሚገኘው የከተማው የውስጥ ለውስት መንገድ ሪዳሽ ማልበስ እና የጥገና ስራ ለህብረተሰቡ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ምቹና የከተሞች እድገት ብሎም ትስስር የሚፈጥር ከሞሆኑ አኳያ ሚናው የጎላ ነው ብለዋል ስለሆነም በቀጣይ በልማት እቅድ ዝግጅት ላይ የሚውሉ በርካታ እቅድ እንዳላቸው ገልጸውልን የወረዳው መንግስት እንደቀድሞው ሁሉ አሁንም ድጋፉ እንዳይለየን ሲሉ ገልጸዋል። =================

በመስቃን ወረዳ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየው የ6ኛ ክፍል ሚንስትሪ ፈተና በሰላም ተጠናቀቀ። ===================== ሰኔ-9-2018 የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን በማዕከላዊ
+5
በመስቃን ወረዳ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየው የ6ኛ ክፍል ሚንስትሪ ፈተና በሰላም ተጠናቀቀ። ===================== ሰኔ-9-2018 የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየው የ6ኛ ክፍል ሚንስትሪ ፈተና በሰላምና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። በእነዚህ የፈተና ጣቢያዎች በድምሩ 2733 ተማሪዎች ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን፣ የፈተናው ሂደት በተደራጀና በተቀናጀ መልኩ ተከናውኗል። ተማሪዎች፣ መምህራን፣ የትምህርት ቤት አመራሮች፣ ወላጆች እና የጸጥታ አካላት በአሳዩት ትብብር ፈተናው ያለምንም ችግር ተጠናቋል። በፈተናው ወቅት የነበረው የሥራ ቅንጅትና ቁጥጥር የተማሪዎችን የፈተና ሂደት ሰላማዊና ፍትሃዊ እንዲሆን አስችሏል። በመጨረሻም ለፈተናው ስኬታማ አፈጻጸም አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሁሉም አካላት የመስቃን ወረዳ ት/ት ቤቶች ጽ/ቤት ምስጋናውን አቅርቧል። ================= ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን!! በተጨማሪም እነዚህ ሊንኮችን በመጫን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡ 👉ፌስቡክ-https://www.facebook.com/gzmwgcao?mibextid=ZbWKwL 👉ቴሌግራም-https://t.me/meskanweredacom31 👉ዩቲዩብ-https://www.youtube.com/channel/UC6PBsPYR5dltyXhEJchdlaA 👉ቲክቶክ -tiktok.com/@meskan.woreda.gov 👉ትዊተር-90ijTxwVTG6dwoT 👉ኢሜል-meskanweredacommunication111@gmail.com

በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ በምስራቅ መስቃን ቀበሌ የገጠር ኮሪደር ልማት ስራ በዛሬው ዕለት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪና የተለያዩ የክልልና የዞን እንግዶች በተገኙበት ተጀመረ። ========
+4
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ በምስራቅ መስቃን ቀበሌ የገጠር ኮሪደር ልማት ስራ በዛሬው ዕለት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪና የተለያዩ የክልልና የዞን እንግዶች በተገኙበት ተጀመረ። ======== ሰኔ 10/2018 (የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን) በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ በምስራቅ መስቃን ቀበሌ የገጠር የኮርደርት ልማት የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሀመድ ውልጫፎ እንዲሁም የተለያዩ የክልልና የዞን እንግዶች፣ የወረዳ አመራሮች በተገኙበት በዛሬው ዕለት ተጀምሯል። የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሀመድ ውልጫፎ የገጠር የኮሪደር ልማት እንደ ሀገር ያለው ፋይዳ ሰፊ ነው ያሉ ሲሆን በወረዳችን ለመሠረተ ልማት ዝርጋታ ምቹ ባልሆነ አሰፋፈር ምክንያት ለበርካታ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ችግሮች ሲጋለጥ የቆየውን የሀገር ባለውለታ አርሶ አደር በተዋቀረ አንድ መንደር በማሰባሰብ ከድህነት አረንቋ በማውጣት ግብርናውን በማዘመን የተሻለ ኑሮ እንዲኖር ለማስቻል አንሰራለን ብለዋል። ዘገባው የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን። ================= ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን!! በተጨማሪም እነዚህ ሊንኮችን በመጫን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡ 👉ፌስቡክ-https://www.facebook.com/gzmwgcao?mibextid=ZbWKwL 👉ቴሌግራም-https://t.me/meskanweredacom31 👉ዩቲዩብ-https://www.youtube.com/channel/UC6PBsPYR5dltyXhEJchdlaA 👉ቲክቶክ -tiktok.com/@meskan.woreda.gov 👉ትዊተር-90ijTxwVTG6dwoT 👉ኢሜል-meskanweredacommunication111@gmail.com

በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅ/ቤት የ6ተኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ውልጫፎ በት/ቤቶች አሰጀምረዋል። ======== ሰኔ 8/2018(
+6
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅ/ቤት የ6ተኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ውልጫፎ በት/ቤቶች አሰጀምረዋል። ======== ሰኔ  8/2018(የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን) በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅ/ቤት የ6ተኛ ክፍል  ሚኒስትሪ ፈተና የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ውልጫፎ በት/ቤቶች በዛሬው እለት አሰጀምረዋል። በመስቃን ወረዳ በሁሉም ትምህርት ቤቶች የ6ተኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና በዛሬው ዕለት መሰጠት የተጀመረ ሲሆን የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሀመድ ውልጫፎ ፣የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ የተከበሩ አቶ መሀመድ ሳኒ፣የወረዳው ትምህርት ቤቶች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር ሁሴን እንዲሁም የክልል ባለሙያዎች በትምህርት ቤት ተገኝተው አሰጀምረዋል። በተጨማሪም ፈተና እየተሰጠባቸው ያሉ  የተለያዩ ትምህርት ቤቶች በመገኘት የፈተና አሰጣጥ ሂደቱን ምልከታ አድርገዋል። የወረዳው ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር ሁሴን እንደገለጹልን በወረዳው 2018ዓ.ም በወረዳው ባሉ 19 ማዕከላት ላይ እየተሰጠ ሲገኝ 2733 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች የመፈተኛ ጣቢያዎች ፈተና እየወሰዱ መሆኑን ገልፀዋል። ተማሪዎች በተለያየ መልኩ ዝግጅት ሲያደርጉ መቆየታቸውን የገለፁት ኃላፊው በዛሬው ዕለትም ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መልኩ ፈተናውን መጀመራቸውን ጠቁመዋል።

በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ በምዕራብ እንቦር ቀበሌ በመንግስት እና በህብረተሰብ ተሳትፎ እየተሰራ ያለውን የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት ኢንሼቲቭ አካል የሆነው የ8.5ኪ.ሜ ርዝመት መንገድ አ
+5
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ በምዕራብ እንቦር ቀበሌ በመንግስት እና በህብረተሰብ ተሳትፎ እየተሰራ ያለውን የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት ኢንሼቲቭ አካል የሆነው የ8.5ኪ.ሜ ርዝመት መንገድ አሁናዊ ቁመና በወረዳው አስተባባሪዎች የአካል ምልከታ ተደረገ። ====================== ሰኔ-1/2018 በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ በምዕራብ እንቦር ቀበሌ በመንግስት እና በህብረተሰብ ተሳትፎ እየተሰራ ያለውን የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት ኢንሼቲቭ አካል የሆነው የ8.5ኪ.ሜ ርዝመት መንገድ አሁናዊ ቁመና በወረዳው አስተባባሪዎች በዛሬው እለት የአካል ምልከታ ተደርጓል። የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሃመድ ውልጫፎ በምልከታ መርሃ ግብሩ ወቅት ተገኝተው እንዳሉት  በጠቅላይ ሚነስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት ኢኒሼቲቭ የመንግስትና የህብረተሰብ ተሳትፎ አቅምን አቀናጅቶ በመጠቀምና በተገቢው በመምራት የማህበረሰብን ተጠቃሚነት የሚረጋገጥበት እንደሆነ ገልፀዋል። የህዝብ የመልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመለየት  ስራዎች ከምንጊዜውም በላይ እየተሰሩ እንደሚገኝ የገለፁት ዋና አስተዳዳሪው ህዝብ ትኮር ፕሮጀክቶች ላይ ትኩረት በማድረግ በጥራትና ባጠረ ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት እንዲውሉ ማድረግ ይገባልም ብለዋል። https://www.facebook.com/share/p/1D5XVzXtFk/

ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል ከተለያዩ አካባቢዎች ወደ ምስራቅ ጉራጌ ዞን ለሚገቡ እንግዶች አቀባበል ተደረገ (ግንቦት 18/2018) 1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓልን ለማ
+3
ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል ከተለያዩ አካባቢዎች ወደ ምስራቅ ጉራጌ ዞን ለሚገቡ እንግዶች አቀባበል ተደረገ (ግንቦት 18/2018) 1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓልን ለማክበር ከተለያዩ አካባቢዎች ወደ የምስራቅ ጉራጌ ዞን መዲና ውቢት የሰላም ሰገነት ወደ ሆነቺው ቡታጅራ ከተማ እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። አቀባበሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን፣ የቡታጅራ ከተማ እንዲሁም የመስቃን ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት እና ፖሊስ አስተባባሪነት ነው አቀባበል የተደረገው። በአቀባበል ፕሮግራሙ ላይ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ መሰለ ጫካ፣ የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብዱ አህመድ፣ የዞኑ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጎሳዬ፣ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የፖሊስ አባላት ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

"ድምፅ አቅም ነው አቅማችንን ለሃገር ግንባታ እንጠቀምበት" ሃገራችንን ለማጽናት 10 ቀናቶች ቀርተውናል።
"ድምፅ አቅም ነው አቅማችንን ለሃገር ግንባታ እንጠቀምበት" ሃገራችንን ለማጽናት 10 ቀናቶች ቀርተውናል።

"የነገ ትልም ጅማሮ የትውልድ ዋስትና ቀን ሊደርስ 11 ቀን ይቀረዋል።
"የነገ ትልም ጅማሮ የትውልድ ዋስትና ቀን ሊደርስ 11 ቀን ይቀረዋል።

በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ የ12ኛ ክፍል ክልላዊ የሞዴል ፈተና በዛሬው ዕለት መሰጠት መጀመሩ ተገለፀ። ======== ግንቦት_12/2018(የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን) በመስቃን ወ
+3
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ የ12ኛ ክፍል ክልላዊ የሞዴል ፈተና በዛሬው ዕለት መሰጠት መጀመሩ ተገለፀ። ======== ግንቦት_12/2018(የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን) በመስቃን ወረዳ የ12ኛ ክፍል ክልላዊ የሞዴል ፈተና በዛሬው ዕለት መሰጠት መጀመሩ ተገለፀ። የመስቃን ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ከድር ሁሴን እንደገለፁት እንደ ወረዳ ከቀን 12-14 የሚሰጠው ክልል አቀፍ የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና በሁሉም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እየተሰጠ ሲሆን እንደሁም በወረዳው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከቀን 10-11 በነበሩት ጊዜያት የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ የሞዴል ፈተና መሰጠቱን ገልፀዋል ። ሀላፊው አክለውም ተማሪዎች አሁን እየወሰዱት ያለው ሞዴል ፈተና ሲሆን ይህም ለመጨረሻው ክልላዊና ሀገራዊ ፈተና ዝግጁ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል ብለው ለዋናው ተማሪዎች በተገቢው እንዲዘጋጁ የመምህራን እና የወላጅ ክትትልና ድጋፍ ከምንጊዜውም በላይ ስለሚያስፈልጋቸው ከግናቸው ልንርቅ እንደማይገባ አፅንኦት ሰጥተው ገልፀዋል። የመስቃን ወረዳ የፈተናና ምዘና ዝግጅት አስተዳደር ዳይሮክቶሬት ቡን መሪ አቶ ሻፊ ሃሰን እንደገለፁት በወረዳው ባለፉት ቀናቶች 2821 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎችና 2434 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ሞዴል ፈተና መሰጠቱን ገልፀው በዛሬው ዕለት 341 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ክልላዊ የሞዴል ፈተና መውሰድ መጀመራቸውን ገልፀዋል። ዘገባው የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ነው።

"የወደፊት እጣ ፈንታችንን የምንወስንበት ያ ታላቅ ቀን ለመድረስ 12 ቀናት ብቻ ቀሩት።"
"የወደፊት እጣ ፈንታችንን የምንወስንበት ያ ታላቅ ቀን ለመድረስ 12 ቀናት ብቻ ቀሩት።"