በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት🇪🇹
رفتن به کانال در Telegram
በሊንኮቻችን ተጨማሪ መረጃዎችን ማግኘት ይችላሉ። ፌስቡክ- https://www.facebook.com/meskan.wereda ቴሌግራም-https://t.me/meskanweredacom31 ዩቲዩብ-https://www.youtube.com/channel/UC6PBsPYR5dltyXhEJchdlaA ትዊተር-90ijTxwVTG6dwoT ኢሜል-meskanweredacommunication111@gmail.com
نمایش بیشتر813
مشترکین
+224 ساعت
+147 روز
+430 روز
آرشیو پست ها
+5
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ በምዕራብ እንቦር ቀበሌ በመንግስት እና በህብረተሰብ ተሳትፎ እየተሰራ ያለውን
የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት ኢንሼቲቭ አካል የሆነው የ8.5ኪ.ሜ ርዝመት መንገድ አሁናዊ ቁመና በወረዳው አስተባባሪዎች የአካል ምልከታ ተደረገ።
======================
ሰኔ-1/2018
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ በምዕራብ እንቦር ቀበሌ በመንግስት እና በህብረተሰብ ተሳትፎ እየተሰራ ያለውን
የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት ኢንሼቲቭ አካል የሆነው የ8.5ኪ.ሜ ርዝመት መንገድ አሁናዊ ቁመና በወረዳው አስተባባሪዎች በዛሬው እለት የአካል ምልከታ ተደርጓል።
የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሃመድ ውልጫፎ በምልከታ መርሃ ግብሩ ወቅት ተገኝተው እንዳሉት በጠቅላይ ሚነስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት ኢኒሼቲቭ የመንግስትና የህብረተሰብ ተሳትፎ አቅምን አቀናጅቶ በመጠቀምና በተገቢው በመምራት የማህበረሰብን ተጠቃሚነት የሚረጋገጥበት እንደሆነ ገልፀዋል።
የህዝብ የመልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመለየት ስራዎች ከምንጊዜውም በላይ እየተሰሩ እንደሚገኝ የገለፁት ዋና አስተዳዳሪው ህዝብ ትኮር ፕሮጀክቶች ላይ ትኩረት በማድረግ በጥራትና ባጠረ ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት እንዲውሉ ማድረግ ይገባልም ብለዋል።
https://www.facebook.com/share/p/1D5XVzXtFk/
ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ድምፅ ሰጥተዋል
+3
ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል ከተለያዩ አካባቢዎች ወደ ምስራቅ ጉራጌ ዞን ለሚገቡ እንግዶች አቀባበል ተደረገ
(ግንቦት 18/2018) 1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓልን ለማክበር ከተለያዩ አካባቢዎች ወደ የምስራቅ ጉራጌ ዞን መዲና ውቢት የሰላም ሰገነት ወደ ሆነቺው ቡታጅራ ከተማ እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
አቀባበሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን፣ የቡታጅራ ከተማ እንዲሁም የመስቃን ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት እና ፖሊስ አስተባባሪነት ነው አቀባበል የተደረገው።
በአቀባበል ፕሮግራሙ ላይ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ መሰለ ጫካ፣ የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብዱ አህመድ፣ የዞኑ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጎሳዬ፣ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የፖሊስ አባላት ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
"ድምፅ አቅም ነው አቅማችንን ለሃገር ግንባታ እንጠቀምበት"
ሃገራችንን ለማጽናት 10 ቀናቶች ቀርተውናል።
"የነገ ትልም ጅማሮ የትውልድ ዋስትና ቀን ሊደርስ 11 ቀን ይቀረዋል።
+3
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ የ12ኛ ክፍል ክልላዊ የሞዴል ፈተና በዛሬው ዕለት መሰጠት መጀመሩ ተገለፀ።
========
ግንቦት_12/2018(የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን)
በመስቃን ወረዳ የ12ኛ ክፍል ክልላዊ የሞዴል ፈተና በዛሬው ዕለት መሰጠት መጀመሩ ተገለፀ።
የመስቃን ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ከድር ሁሴን እንደገለፁት እንደ ወረዳ ከቀን 12-14 የሚሰጠው ክልል አቀፍ የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና በሁሉም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እየተሰጠ ሲሆን እንደሁም በወረዳው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከቀን 10-11 በነበሩት ጊዜያት የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ የሞዴል ፈተና መሰጠቱን ገልፀዋል ።
ሀላፊው አክለውም ተማሪዎች አሁን እየወሰዱት ያለው ሞዴል ፈተና ሲሆን ይህም ለመጨረሻው ክልላዊና ሀገራዊ ፈተና ዝግጁ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል ብለው ለዋናው ተማሪዎች በተገቢው እንዲዘጋጁ የመምህራን እና የወላጅ ክትትልና ድጋፍ ከምንጊዜውም በላይ ስለሚያስፈልጋቸው ከግናቸው ልንርቅ እንደማይገባ አፅንኦት ሰጥተው ገልፀዋል።
የመስቃን ወረዳ የፈተናና ምዘና ዝግጅት አስተዳደር ዳይሮክቶሬት ቡን መሪ አቶ ሻፊ ሃሰን እንደገለፁት በወረዳው ባለፉት ቀናቶች 2821 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎችና 2434 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ሞዴል ፈተና መሰጠቱን ገልፀው በዛሬው ዕለት 341 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ክልላዊ የሞዴል ፈተና መውሰድ መጀመራቸውን ገልፀዋል።
ዘገባው የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ነው።
"የወደፊት እጣ ፈንታችንን የምንወስንበት ያ ታላቅ ቀን ለመድረስ 12 ቀናት ብቻ ቀሩት።"
አርሰናል የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋገጠ
ግንቦት 11/2018
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ቦርንማውዝ እና ማንችስተር ሲቲ አንድ አቻ ተለያይተዋል።
ማምሻውን በቫይታሊቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጁኒየር ክሩፒ በ38ኛው ደቂቃ የቦርንማውዝን ጎል አስቆጥሯል።
አርሊንግ ሃላንድ በ95ኛው ደቂቃ ሲቲን አቻ አድርጓል።
ጨዋታው ተመጣጣኝ እና አዝናኝ ፉክክር ተደርጎበታል።
ማንችስተር ሲቲ አቻ መውጣቱን ተከትሎ አርሰናል በ82 ነጥብ አንድ ጨዋታ እየቀረው ከ22 ዓመት በኋላ የሊጉ አሸናፊ መሆኑን አረጋግጧል።
የአርሰናል የ22 ዓመት የሊጉ የዋንጫ ጥበቃ ዛሬ አብቅቷል።
በሊጉ ስድስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ማንችስተር ሲቲ በ78 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል።
በውድድር ዓመቱ 14ኛ ድሉን ያስመዘገበው ቦርንማውዝ በ56 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
ቦርንማውዝ ባለፉት 17 የሊግ ጨዋታዎች ባለመሸነፍ ድንቅ ግስጋሴ ላይ ይገኛል።
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በ38ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ይጠናቀቃል።
(ኢዜአ)
+2
#ኢትዮጵያን_ወደ_ተምሳሌት_ሀገር! በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ የ"ምረጡኝ" ቅስቀሳ በመስቃን ወረዳ በደቡብ ሸርሸራ ቀበሌ የቡና ጠጡ መርሃ ግብር ተካሂዷል።።
============
ግንቦት_11/2018 ዓ.ም(የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን)
#ኢትዮጵያን_ወደ_ተምሳሌት_ሀገር ! በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ የ"ምረጡኝ" ቅስቀሳ በመስቃን ወረዳ በደቡብ ሸርሸራ ቀበሌ በዛሬው እለት በደማቅ ሁኔታ የቡና ጠጡ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
የመስቃን ወረዳ ዋና ም/አሰተዳዳሪና ግብርና ፅ/ቤት ሀላፊ የተከበሩ አቶ ገረመው ተመስገን ፣የቀበሌው የወረዳ ደጋፊ አመራሮች፣የቀበሌው አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የቀበሌው የፓርቲ ደጋፊ አባላቶች የተገኙ ሲሆን መረሃ ግብሩ በሌሎች ቀበሌዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
#7ኛው_ሀገራዊና_ክልላዊ_ምርጫ_ሊካሄድ_13_ቀናት_ብቻ_ቀርተውታል።
******
#እኔ_ግንቦት_24_ቀን_2018 ዓ.ም መሪዬን ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ፤ እርሶስ ተዘጋጅተዋል❓
ወደ ምርጫ ጣቢያ የማይገቡ ነገሮች ምንድናቸው?
1. ማንኛውም ሰው እንደ በራሪ ወረቀት፣ ፖስተር እና በሌሎች አጭር ጽሁፍ መልክ የተዘጋጁ የምርጫ ቅስቀሳ ሰነዶችን ይዞ ወደ ምርጫ ጣቢያው መግባት አይችልም፡፡
2. ማንኛውም ሰው የጦር መሳሪያ ወይም እንደጩቤና ሴንጢ የመሳሰሉ ስለትነት ያላቸውን ወይም እንደየአካባቢው ሁኔታ ለሀይል መጠቀሚያነት የሚውሉ እንደዱላ፣ አለንጋ ፣ ቁራጭ እንጨት ወይም ብረት ወይም ሌላ ማንኛውንም ተቀጣጣይ ወይም የሚፈነዳ ጠጣር ወይም ፈሳሽ ነገር ይዞ ወደ ምርጫ ጣቢያ መግባት የለበትም።
3. የተከለከሉ ነገሮችን ወደምርጫ ጣቢያ ይዞ የመጣ መራጭ የምርጫ ጣቢያው የሰልፍ አስከባሪ በሚሰጠው መመሪያ መሰረት በአደራ አስቀምጦ መግባት አለበት።
''#ኢትዮጵያን_ወደ_ተምሳሌት_ሀገር''‼️
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ በሚካኤሎ ቀበሌ የተዘጋጀ የብልፅግና ፓርቲ የቡና ጠጡና የምርጫ ቅስቀሳ መርሃ ግብር።
+3
#ኢትዮጵያን_ወደ_ተምሳሌት_ሀገር! በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ የ"ምረጡኝ" ቅስቀሳ በመስቃን ወረዳ በሚካኤሎ ቀበሌ የቡና ጠጡ መርሃ ግብር ተካሂዷል።።
============
ግንቦት_9/2018 ዓ.ም(የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን)
#ኢትዮጵያን_ወደ_ተምሳሌት_ሀገር ! በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ የ"ምረጡኝ" ቅስቀሳ በመስቃን ወረዳ በሚካኤሎ ቀበሌ በዛሬው እለት በደማቅ ሁኔታ የቡና ጠጡ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
የመስቃን ወረዳ ዋና አሰተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሀመድ ውልጫፎ፣ የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፅ/ቤት ሀላፊ የተከበሩ አቶ መሀመድ ሳኒ፣ የብልፅግና ፅ/ቤት ም/ሀላፊና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ወንዴ ነሲቡ የቀበሌው የወረዳ ደጋፊ አመራሮች፣ የቀበሌው አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የቀበሌው የፓርቲ ደጋፊ አባላቶች የተገኙ ሲሆን መረሃ ግብሩ በሌሎች ቀበሌዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
በዛሬው ዕለት የነበረው #ኢትዮጵያን_ወደ_ተምሳሌት_ሀገር! በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ የ"ምረጡኝ" ቅስቀሳ በመስቃን ወረዳ በኦዶ ታዳጊ ማዘጋጃ ቤት የቡና ጠጡ መርሃ ግብር በቪዲዮ ሊንኩን ይጫኑት
https://www.facebook.com/share/v/1JApU36p8H/
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
