በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት🇪🇹
Ir al canal en Telegram
በሊንኮቻችን ተጨማሪ መረጃዎችን ማግኘት ይችላሉ። ፌስቡክ- https://www.facebook.com/meskan.wereda ቴሌግራም-https://t.me/meskanweredacom31 ዩቲዩብ-https://www.youtube.com/channel/UC6PBsPYR5dltyXhEJchdlaA ትዊተር-90ijTxwVTG6dwoT ኢሜል-meskanweredacommunication111@gmail.com
Mostrar más815
Suscriptores
+224 horas
+47 días
+1030 días
Archivo de publicaciones
+5
በመስቃን ወረዳ የዊጣ ታዳጊ ማዘጋጃ ቤት የተለያዩ የከተማው የውስጥ ለውስጥ መንገድ ሪዳሽ ማልበስ እና የጥገና ስራ ላይ ይገኛል።
=========
ሰኔ 9/2018ዓ.ም የመስቃን ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን
በዚህም ወደ ሶስት(4.2) ኪሎ ሜትር ሽፋን ያለው የዊጣ ከተማ በሁሉም አቅጣጫ ማለትም በሴራና፤ንቡር፤አቦቸና፤ወገሬት
ሰፈሮችን የሚያገናኝ የውስጥ ለውስጥ መንገድ የሪዳሽ ማልበስ ስራ እና ጥገና እንዲሁም የዲች ስራ በማከናውን ላይ የሚገኝ ሲሆን
መንገድ ለኢኮኖሚ፤ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ እድገት እና ትስስር ትልቅ ሚና እንዳለው የገለጹልን የመስቃን ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ም/ሃላፊ አቶ ዑስማን ናስር የከተማና የገጠር ትስስር ከማጠናከር አኳያ አምራችና ሸማች እንዲሁም በቂ የሆነ የንግድ ፍሰት እንዲኖር ከማስቻል ረገድ የጎላ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።
የመስቃን ወረዳ የዊጣ ከተማ ታዳጊ መዘጋጃ ጽ/ቤት ሃላፊ አህመኑር ከድር እየተሰራ የሚገኘው የከተማው የውስጥ ለውስት መንገድ ሪዳሽ ማልበስ እና የጥገና ስራ ለህብረተሰቡ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ምቹና የከተሞች እድገት ብሎም ትስስር የሚፈጥር ከሞሆኑ አኳያ ሚናው የጎላ ነው ብለዋል ስለሆነም በቀጣይ በልማት እቅድ ዝግጅት ላይ የሚውሉ በርካታ እቅድ እንዳላቸው ገልጸውልን የወረዳው መንግስት እንደቀድሞው ሁሉ አሁንም ድጋፉ እንዳይለየን ሲሉ ገልጸዋል።
=================
+5
በመስቃን ወረዳ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየው የ6ኛ ክፍል ሚንስትሪ ፈተና በሰላም ተጠናቀቀ።
=====================
ሰኔ-9-2018 የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየው የ6ኛ ክፍል ሚንስትሪ ፈተና በሰላምና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
በእነዚህ የፈተና ጣቢያዎች በድምሩ 2733 ተማሪዎች ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን፣ የፈተናው ሂደት በተደራጀና በተቀናጀ መልኩ ተከናውኗል።
ተማሪዎች፣ መምህራን፣ የትምህርት ቤት አመራሮች፣ ወላጆች እና የጸጥታ አካላት በአሳዩት ትብብር ፈተናው ያለምንም ችግር ተጠናቋል።
በፈተናው ወቅት የነበረው የሥራ ቅንጅትና ቁጥጥር የተማሪዎችን የፈተና ሂደት ሰላማዊና ፍትሃዊ እንዲሆን አስችሏል።
በመጨረሻም ለፈተናው ስኬታማ አፈጻጸም አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሁሉም አካላት የመስቃን ወረዳ ት/ት ቤቶች ጽ/ቤት ምስጋናውን አቅርቧል።
=================
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን!!
በተጨማሪም እነዚህ ሊንኮችን በመጫን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡
👉ፌስቡክ-https://www.facebook.com/gzmwgcao?mibextid=ZbWKwL
👉ቴሌግራም-https://t.me/meskanweredacom31
👉ዩቲዩብ-https://www.youtube.com/channel/UC6PBsPYR5dltyXhEJchdlaA
👉ቲክቶክ -tiktok.com/@meskan.woreda.gov
👉ትዊተር-90ijTxwVTG6dwoT
👉ኢሜል-meskanweredacommunication111@gmail.com
+4
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ በምስራቅ መስቃን ቀበሌ የገጠር ኮሪደር ልማት ስራ በዛሬው ዕለት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪና የተለያዩ የክልልና የዞን እንግዶች በተገኙበት ተጀመረ።
========
ሰኔ 10/2018 (የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን)
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ በምስራቅ መስቃን ቀበሌ የገጠር የኮርደርት ልማት የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሀመድ ውልጫፎ እንዲሁም የተለያዩ የክልልና የዞን እንግዶች፣ የወረዳ አመራሮች በተገኙበት በዛሬው ዕለት ተጀምሯል።
የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሀመድ ውልጫፎ የገጠር የኮሪደር ልማት እንደ ሀገር ያለው ፋይዳ ሰፊ ነው ያሉ ሲሆን በወረዳችን ለመሠረተ ልማት ዝርጋታ ምቹ ባልሆነ አሰፋፈር ምክንያት ለበርካታ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ችግሮች ሲጋለጥ የቆየውን የሀገር ባለውለታ አርሶ አደር በተዋቀረ አንድ መንደር በማሰባሰብ ከድህነት አረንቋ በማውጣት ግብርናውን በማዘመን የተሻለ ኑሮ እንዲኖር ለማስቻል አንሰራለን ብለዋል።
ዘገባው የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን።
=================
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን!!
በተጨማሪም እነዚህ ሊንኮችን በመጫን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡
👉ፌስቡክ-https://www.facebook.com/gzmwgcao?mibextid=ZbWKwL
👉ቴሌግራም-https://t.me/meskanweredacom31
👉ዩቲዩብ-https://www.youtube.com/channel/UC6PBsPYR5dltyXhEJchdlaA
👉ቲክቶክ -tiktok.com/@meskan.woreda.gov
👉ትዊተር-90ijTxwVTG6dwoT
👉ኢሜል-meskanweredacommunication111@gmail.com
+6
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅ/ቤት የ6ተኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ውልጫፎ በት/ቤቶች አሰጀምረዋል።
========
ሰኔ 8/2018(የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን)
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅ/ቤት የ6ተኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ውልጫፎ በት/ቤቶች በዛሬው እለት አሰጀምረዋል።
በመስቃን ወረዳ በሁሉም ትምህርት ቤቶች የ6ተኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና በዛሬው ዕለት መሰጠት የተጀመረ ሲሆን የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሀመድ ውልጫፎ ፣የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ የተከበሩ አቶ መሀመድ ሳኒ፣የወረዳው ትምህርት ቤቶች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር ሁሴን እንዲሁም የክልል ባለሙያዎች በትምህርት ቤት ተገኝተው አሰጀምረዋል።
በተጨማሪም ፈተና እየተሰጠባቸው ያሉ የተለያዩ ትምህርት ቤቶች በመገኘት የፈተና አሰጣጥ ሂደቱን ምልከታ አድርገዋል።
የወረዳው ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር ሁሴን እንደገለጹልን በወረዳው 2018ዓ.ም በወረዳው ባሉ 19 ማዕከላት ላይ እየተሰጠ ሲገኝ 2733 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች የመፈተኛ ጣቢያዎች ፈተና እየወሰዱ መሆኑን ገልፀዋል።
ተማሪዎች በተለያየ መልኩ ዝግጅት ሲያደርጉ መቆየታቸውን የገለፁት ኃላፊው በዛሬው ዕለትም ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መልኩ ፈተናውን መጀመራቸውን ጠቁመዋል።
+5
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ በምዕራብ እንቦር ቀበሌ በመንግስት እና በህብረተሰብ ተሳትፎ እየተሰራ ያለውን
የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት ኢንሼቲቭ አካል የሆነው የ8.5ኪ.ሜ ርዝመት መንገድ አሁናዊ ቁመና በወረዳው አስተባባሪዎች የአካል ምልከታ ተደረገ።
======================
ሰኔ-1/2018
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ በምዕራብ እንቦር ቀበሌ በመንግስት እና በህብረተሰብ ተሳትፎ እየተሰራ ያለውን
የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት ኢንሼቲቭ አካል የሆነው የ8.5ኪ.ሜ ርዝመት መንገድ አሁናዊ ቁመና በወረዳው አስተባባሪዎች በዛሬው እለት የአካል ምልከታ ተደርጓል።
የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሃመድ ውልጫፎ በምልከታ መርሃ ግብሩ ወቅት ተገኝተው እንዳሉት በጠቅላይ ሚነስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአንድ ወረዳ አንድ ፕሮጀክት ኢኒሼቲቭ የመንግስትና የህብረተሰብ ተሳትፎ አቅምን አቀናጅቶ በመጠቀምና በተገቢው በመምራት የማህበረሰብን ተጠቃሚነት የሚረጋገጥበት እንደሆነ ገልፀዋል።
የህዝብ የመልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመለየት ስራዎች ከምንጊዜውም በላይ እየተሰሩ እንደሚገኝ የገለፁት ዋና አስተዳዳሪው ህዝብ ትኮር ፕሮጀክቶች ላይ ትኩረት በማድረግ በጥራትና ባጠረ ጊዜ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት እንዲውሉ ማድረግ ይገባልም ብለዋል።
https://www.facebook.com/share/p/1D5XVzXtFk/
ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ድምፅ ሰጥተዋል
+3
ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል ከተለያዩ አካባቢዎች ወደ ምስራቅ ጉራጌ ዞን ለሚገቡ እንግዶች አቀባበል ተደረገ
(ግንቦት 18/2018) 1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓልን ለማክበር ከተለያዩ አካባቢዎች ወደ የምስራቅ ጉራጌ ዞን መዲና ውቢት የሰላም ሰገነት ወደ ሆነቺው ቡታጅራ ከተማ እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
አቀባበሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን፣ የቡታጅራ ከተማ እንዲሁም የመስቃን ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት እና ፖሊስ አስተባባሪነት ነው አቀባበል የተደረገው።
በአቀባበል ፕሮግራሙ ላይ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ መሰለ ጫካ፣ የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብዱ አህመድ፣ የዞኑ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጎሳዬ፣ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የፖሊስ አባላት ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
"ድምፅ አቅም ነው አቅማችንን ለሃገር ግንባታ እንጠቀምበት"
ሃገራችንን ለማጽናት 10 ቀናቶች ቀርተውናል።
"የነገ ትልም ጅማሮ የትውልድ ዋስትና ቀን ሊደርስ 11 ቀን ይቀረዋል።
+3
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ የ12ኛ ክፍል ክልላዊ የሞዴል ፈተና በዛሬው ዕለት መሰጠት መጀመሩ ተገለፀ።
========
ግንቦት_12/2018(የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን)
በመስቃን ወረዳ የ12ኛ ክፍል ክልላዊ የሞዴል ፈተና በዛሬው ዕለት መሰጠት መጀመሩ ተገለፀ።
የመስቃን ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ከድር ሁሴን እንደገለፁት እንደ ወረዳ ከቀን 12-14 የሚሰጠው ክልል አቀፍ የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና በሁሉም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እየተሰጠ ሲሆን እንደሁም በወረዳው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከቀን 10-11 በነበሩት ጊዜያት የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ የሞዴል ፈተና መሰጠቱን ገልፀዋል ።
ሀላፊው አክለውም ተማሪዎች አሁን እየወሰዱት ያለው ሞዴል ፈተና ሲሆን ይህም ለመጨረሻው ክልላዊና ሀገራዊ ፈተና ዝግጁ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል ብለው ለዋናው ተማሪዎች በተገቢው እንዲዘጋጁ የመምህራን እና የወላጅ ክትትልና ድጋፍ ከምንጊዜውም በላይ ስለሚያስፈልጋቸው ከግናቸው ልንርቅ እንደማይገባ አፅንኦት ሰጥተው ገልፀዋል።
የመስቃን ወረዳ የፈተናና ምዘና ዝግጅት አስተዳደር ዳይሮክቶሬት ቡን መሪ አቶ ሻፊ ሃሰን እንደገለፁት በወረዳው ባለፉት ቀናቶች 2821 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎችና 2434 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ሞዴል ፈተና መሰጠቱን ገልፀው በዛሬው ዕለት 341 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ክልላዊ የሞዴል ፈተና መውሰድ መጀመራቸውን ገልፀዋል።
ዘገባው የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ነው።
"የወደፊት እጣ ፈንታችንን የምንወስንበት ያ ታላቅ ቀን ለመድረስ 12 ቀናት ብቻ ቀሩት።"
አርሰናል የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋገጠ
ግንቦት 11/2018
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ቦርንማውዝ እና ማንችስተር ሲቲ አንድ አቻ ተለያይተዋል።
ማምሻውን በቫይታሊቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጁኒየር ክሩፒ በ38ኛው ደቂቃ የቦርንማውዝን ጎል አስቆጥሯል።
አርሊንግ ሃላንድ በ95ኛው ደቂቃ ሲቲን አቻ አድርጓል።
ጨዋታው ተመጣጣኝ እና አዝናኝ ፉክክር ተደርጎበታል።
ማንችስተር ሲቲ አቻ መውጣቱን ተከትሎ አርሰናል በ82 ነጥብ አንድ ጨዋታ እየቀረው ከ22 ዓመት በኋላ የሊጉ አሸናፊ መሆኑን አረጋግጧል።
የአርሰናል የ22 ዓመት የሊጉ የዋንጫ ጥበቃ ዛሬ አብቅቷል።
በሊጉ ስድስተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ማንችስተር ሲቲ በ78 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል።
በውድድር ዓመቱ 14ኛ ድሉን ያስመዘገበው ቦርንማውዝ በ56 ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
ቦርንማውዝ ባለፉት 17 የሊግ ጨዋታዎች ባለመሸነፍ ድንቅ ግስጋሴ ላይ ይገኛል።
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በ38ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ይጠናቀቃል።
(ኢዜአ)
+2
#ኢትዮጵያን_ወደ_ተምሳሌት_ሀገር! በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ የ"ምረጡኝ" ቅስቀሳ በመስቃን ወረዳ በደቡብ ሸርሸራ ቀበሌ የቡና ጠጡ መርሃ ግብር ተካሂዷል።።
============
ግንቦት_11/2018 ዓ.ም(የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን)
#ኢትዮጵያን_ወደ_ተምሳሌት_ሀገር ! በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ የ"ምረጡኝ" ቅስቀሳ በመስቃን ወረዳ በደቡብ ሸርሸራ ቀበሌ በዛሬው እለት በደማቅ ሁኔታ የቡና ጠጡ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
የመስቃን ወረዳ ዋና ም/አሰተዳዳሪና ግብርና ፅ/ቤት ሀላፊ የተከበሩ አቶ ገረመው ተመስገን ፣የቀበሌው የወረዳ ደጋፊ አመራሮች፣የቀበሌው አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የቀበሌው የፓርቲ ደጋፊ አባላቶች የተገኙ ሲሆን መረሃ ግብሩ በሌሎች ቀበሌዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
#7ኛው_ሀገራዊና_ክልላዊ_ምርጫ_ሊካሄድ_13_ቀናት_ብቻ_ቀርተውታል።
******
#እኔ_ግንቦት_24_ቀን_2018 ዓ.ም መሪዬን ለመምረጥ ተዘጋጅቻለሁ፤ እርሶስ ተዘጋጅተዋል❓
ወደ ምርጫ ጣቢያ የማይገቡ ነገሮች ምንድናቸው?
1. ማንኛውም ሰው እንደ በራሪ ወረቀት፣ ፖስተር እና በሌሎች አጭር ጽሁፍ መልክ የተዘጋጁ የምርጫ ቅስቀሳ ሰነዶችን ይዞ ወደ ምርጫ ጣቢያው መግባት አይችልም፡፡
2. ማንኛውም ሰው የጦር መሳሪያ ወይም እንደጩቤና ሴንጢ የመሳሰሉ ስለትነት ያላቸውን ወይም እንደየአካባቢው ሁኔታ ለሀይል መጠቀሚያነት የሚውሉ እንደዱላ፣ አለንጋ ፣ ቁራጭ እንጨት ወይም ብረት ወይም ሌላ ማንኛውንም ተቀጣጣይ ወይም የሚፈነዳ ጠጣር ወይም ፈሳሽ ነገር ይዞ ወደ ምርጫ ጣቢያ መግባት የለበትም።
3. የተከለከሉ ነገሮችን ወደምርጫ ጣቢያ ይዞ የመጣ መራጭ የምርጫ ጣቢያው የሰልፍ አስከባሪ በሚሰጠው መመሪያ መሰረት በአደራ አስቀምጦ መግባት አለበት።
''#ኢትዮጵያን_ወደ_ተምሳሌት_ሀገር''‼️
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ በሚካኤሎ ቀበሌ የተዘጋጀ የብልፅግና ፓርቲ የቡና ጠጡና የምርጫ ቅስቀሳ መርሃ ግብር።
+3
#ኢትዮጵያን_ወደ_ተምሳሌት_ሀገር! በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ የ"ምረጡኝ" ቅስቀሳ በመስቃን ወረዳ በሚካኤሎ ቀበሌ የቡና ጠጡ መርሃ ግብር ተካሂዷል።።
============
ግንቦት_9/2018 ዓ.ም(የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን)
#ኢትዮጵያን_ወደ_ተምሳሌት_ሀገር ! በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ የ"ምረጡኝ" ቅስቀሳ በመስቃን ወረዳ በሚካኤሎ ቀበሌ በዛሬው እለት በደማቅ ሁኔታ የቡና ጠጡ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
የመስቃን ወረዳ ዋና አሰተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሀመድ ውልጫፎ፣ የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፅ/ቤት ሀላፊ የተከበሩ አቶ መሀመድ ሳኒ፣ የብልፅግና ፅ/ቤት ም/ሀላፊና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ወንዴ ነሲቡ የቀበሌው የወረዳ ደጋፊ አመራሮች፣ የቀበሌው አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የቀበሌው የፓርቲ ደጋፊ አባላቶች የተገኙ ሲሆን መረሃ ግብሩ በሌሎች ቀበሌዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
