cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

እንተዋወስ(entewawes)

وذكر فإن الذكرى تنفع المؤمنين (አስታውስ ማስታወስ ሙኡሚኖችን ትጠቅማለችና)

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
199
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

✨ኢንሻአላህ ነገ ሰኞ ነው በፆም እንበርታ የነብያችንን ሱና ሀይ እናድርግ ሼር በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ እንሁን
نمایش همه...
✨ያለውዱ የሚሰገድ ሶላትና ያለተውሂድ የሚፈፀም ዒባዳ ከንቱ ድካም ናቸው ። ✨መብራት ከሌለበት ሰፈር ይልቅ የሚያስፈራው ተውሂድና ሱና የሌለበት ሰፈር ነው وذكر فإن الذكرى تنفع المؤمنين    (አስታውስ ማስታወስ ሙኡሚኖችን ትጠቅማለችና)
نمایش همه...
✨ጉዳይህ ዱንያ ብቻ አይሁን✨ ረሱል صلى الله عليم وسلم እንዲህ ብለዋል ፦ ሀሳቡና ጭንቁ ዱንያ የሆነ ሰው፣አላህ ጉዳዩን ይበታትንበታል ።ድህነትን በአይኑ መሀል ያደርግበታል ።ከዱንያ የተወሰነለት እንጂ አያገኝም።ጉዳይህ ዱንያ ብቻ አይሁን ሀሳቡና ጭንቀቱ አኼራ የሆነ፣መብቃቃትን በልቡ ያደርግለታል ።ጉዳዩን ይሰበስብለታል።ዱንያ የግዷን ወደሱ ትመጣለች وذكر فإن الذكرى تنفع المؤمنين    (አስታውስ ማስታወስ ሙኡሚኖችን ትጠቅማለችና) https://t.me/leihte
نمایش همه...
لااله الاالله انالله وانا اليه الرجعون ምንኛ መጨረሻ ማማር አላሁ አክበር ለዚህም ነው ሁሌም ቅድመያ ለተውሂድ በሉ ምንለው አህለሱና ወልጀምዐዎች። አላህ መጨረሻውን አሳመረለት። የኛንም መጨረሻ አላህ ያሳምርልን። አሚን አሚን t.me/yetkaru t.me/yetkaru
نمایش همه...
👍 1
وذكر فإن الذكرى تنفع المؤمنين (አስታውስ ማስታወስ ሙኡሚኖችን ትጠቅማለችና)
نمایش همه...
✨የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)የአጠጣጥ ሱና ✨ ❾ነብዩ( ሰ.ዐ.ወ )የአከባቢው ነዋሪ ለመጠጥ ከሚጠቀምበት ቦታ ይጠጡ ነበር። ➓ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በብርጭቆ ከሸክላ አፈር በተሰራ ወይም ከመዳብ አሊያም ከእንጨት በተሰራ ኩባያ ይጠጡ ነበር። ⓫ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ከላመ የገብስ ዱቄት ጋር የተዘጋጀ ውሃ ይጠጡ ነበር ። ⓬አንድ ጊዜ ከኦቾሎኒ ዱቄት ጋር የተዘጋጀ ውሃ ሲቀርብላቸው ፨የሀብታሞች መጠጥ ነው ።ሲሉ እቢታቸውን ገልፀዋል። ⓭ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በወተት የተበረዘ ማር አይጠጡም ነበር፨ሁለት ሳህኖች በአንድ ገበታ ይሉ ነበር ።እንዴት አባካኝ ትሆናላቹ ማለታቸው ነው ⓮ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሲጠጡ ተቀምጠው ነበር።ከንፈራቸውን ወደ ኩባያው ሲያስጠጉ ቢስሚላሂ ከተጎነጩ በኋላ አልሃምዱሊላህ ሶስት ጊዜ ይላሉ ።በሶስተኛው ላይ ወሽኩሩ ሊላሂ የሚለውን ያክሉ ነበር። وذكر فإن الذكرى تنفع المؤمنين    (አስታውስ ማስታወስ ሙኡሚኖችን ትጠቅማለችና) https://t.me/leihte
نمایش همه...
እንተዋወስ(entewawes)

وذكر فإن الذكرى تنفع المؤمنين (አስታውስ ማስታወስ ሙኡሚኖችን ትጠቅማለችና)

✨የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ )የአጠጣጥ ሱና✨ ⓵ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዉሃ ሲጠጡ ድምፅ አያሰሙም ነበር ።ጎርጥ እየደረጉ ጠጥተው አያውቁም ። ❷ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ንፁህና ጣፋጭ ውሃ ፍቅር ነበራቸው።እስከ ሁለት ቀን ሊያስጉዙ ከሚችል ርቀት የሚመጣ ዉሃ አዘውትረው ይጠጡ ነበር ። ⓷ከሙሚኖች ሀሉ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ )ለእናታችን አዒሻ (ረ.ዐ) ጥልቅ ፍቅር ነበራቸው ።እናታችን አዓሻ (ረ.ዐ) በጠጡበት ኩባያ ከንፈራቸውን ያረፈበትን ቦታ ፈልገው ይጠጡ ነበር። ❹ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ወተት በጣም ይወዱ ነበር።አንዳንድ ጊዜ ምንም ያልተቀላቀለበት ወተት ሲጠጡ ሎላ ጊዜ ቀዝቃዛ ውሃ ወተቱ ላይ ጨምረው ይጠጡ ነበር ። ⓹አንዳንዴ ከውሃ ማስቀመጫ ስልቻ ሲጠጡ ሌላ ግዜ ከባልዲ ይጠጡ ነበር ። ❻ሰዎች በተሰበሰቡበት የሚጠጣ ነገርእየተከፋፈለ ምናልባት የሚጠጣው ነገር ካለቀ ፣ተመልቶ ሲመጣ ከቆመበት ሰው እንዲቀጥል ያደርጉ ነበር ። ⓻ ሰዎች በተሰበሰቡበት የሚጠጣ ነገር የሚከፋፈል ከሆነ በዕድሜ ቅድመ ተከተላቸው ፤ከታላቅ ጀምረው /ከአዛውንት /እንዲሰጥ ያዙ ነበር ። ❽ነብያችን (ሰ.ዐ.ወ )እንግዶቻቸው ከጠጡ ቦኋላ በመጨረሻ እርሳቸው ይጠጡ ነበር ።ውሃ የሚየድል መጠጣት ያለበት መጨረሻ ነው ይሉ ነበር።
نمایش همه...
እህቴ 🌸⑧ የበፊት ሰዎችን ታሪክ ለማንበብ እንደምትጓጊና ታሪካቸዉን ማወቅ እንደሚያስደስትሽ አዉቃለሁ። የዛሬዉ ቀጠሯችን በእስልምና ታሪክ ዉስጥ ካለፉት እጅግ ምርጥ ከሆኑት ሴቶች መሀል የአንዷ ነዉ። ዛሬ የጀግንነት፣ የቆራጥነት ተራራ ስለሆነችዋ ሴት እናወራለን። ዛሬም በፊርዖን ቤተ መንግስት እንቆያለን። እቺ ሴት በዱንያ ላይ እንደሱ ያለ ክፉ ሰዉ አልፎ የማያዉቅ ሰዉ ሚስት ናት። የዚያ በሞኝነትና በቅጥፈት ‘እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ!’ ሲል ህዝቡ ዉስጥ ዉሸት የሚለፍፈዉ ሰዉ ሚስት ነች። ይህ ሞኝ ሰዉ እንዲያመልኩት ብሎ ሰዎችን ያስገድዳል። እምቢ ያሉትን ይገላል፣ ይቀጣል። ቤተመንግስቱ በበደል የተሞላ ነበር። እንደዚያ ከመሆኑም ጋር ግን በዚህ ቤተመንግስት ዉስጥ የሱን አምላክነትን ማይቀበሉ፣ አላህን በብቸኝነት የሚገዙ ምርጥ ባሮች ነበሩ። ከነሱ መሀል የራሱ የፊርዖን ሚስት አሲያ ቢንት መዛሂም ትገኛለች። አሲያ ኢማን በልቧ የገባዉ ገና በጠዋቱ ነበር። ግን ምን ያረጋል ባሏን ከማንም በላይ ዉሸታም፣ ከሀዲና በዳይ እንደሆነ ስለምታዉቅ ኢማኗን ደብቃ ቆየች። ነገር ግን ከጊዜ ብኋላ የተለያዩ ተዓምራትን በሙሳ እጅ ስታይ፣ ሙሳ በምን አይነት መረጃ ፊርዖንን እንደሚከራከርና የሀሩንን አንደበተ‘ርቱዕነትን ስትመለከት ኢማኗ ጨመረ። እሷ በንፁህ አዕምሮዋ ይህ የሚታመም፣ የሚደክም፣ የሚበላና የሚጠጣዉ ተራ ባሏ በፍፁም ፈጣሪ ሊሆን እንደማይችል ታዉቃለች። በሀቅ ሊገዙት የሚገባዉ ብቸኛ ፈጣሪ መኖሩን ታምናለች። ያ ፈጣሪም የሙሳና የሀሩን ጌታ ነዉ። ኢማኗን ለተወሰነ ጊዜ ከደበቀች ብኋላ ኢማኗ ከፍ ብሎ ልቧን በሙሉ መቆጣጠር ሲጀምር ፊርዖንን ፊት ለፊት አናገረችዉ። ያ የግብፅ ህዝብ ሙሉ የሚፈራዉን ጨካኝ ባሏ ፊት ቆማ ‘ፊርዖን ሆይ! (አልፈራህም!) ባንተ ክጃለዉ!’ አለችዉ። በሙሉ ራስ መተማመን ‘የሙሳና የሀሩንን አምላክ ተከትዬ ባንተ ክጃለሁ።’ አለችዉ። በዳይነቱን ፊት ለፊቱ ነገረችዉ። ፊርዖን የተዉሂድን ቃል በሚስቱ መስማቱ ለሱ ከባድ ነበር። ተቆጣ፣ ገነፈለ። እጅግ ከባድ ቅጣትን እሷን መቅጣት ጀመረ። የተለያዩ ቅጣትን ቀጣት። እሱም አልበቃ ብሎት ወታደሮቹን ወደ በረሃ ይዘዋት ወተዉ ወጥረዉ አራት ቦታ ላይ እስረዋት እንዲቀጧት አደረገ። ምግብና መጠጥንም ከለከሏት። ቀኑን ሙሉ ፀሀይ ዉስጥ አቆያት። በሁለተኛዉ ቀንም ከእምነቷ ትመለስ እንደሆነ ጠየቃት። በጭራሽ እንደማታረገዉ ስትነግረዉ አሁንም ያለምግብና መጠጥ እዚያ ፀሀይ ላይ ሲያሰቃያት ዋለ። በሶስተኛዉ ቀንም ወደ ቤቷና ወደ እምነቷ ብትመለስ እንደሚሻላት ነገራት። ቅጣቱን ልትቋቋመዉ እንደማትችል አሳወቃት። እሷ ግን ቅጣቱ ከኢማንና ከሰብር ዉጪ ሌላ ነገርን እንዳልጨመረላት ነገረችዉ። ፊርዖንም ከሷ ላይ ተስፋ በቆረጠ ጊዜ ወታደሮቹ ትልቅ ቆጥኝን ከፍ አርገዉ አንስተዉ ጭንቅላቷን እንዲፈጠፍጡት አዘዛቸዉ። በዚህ ጊዜ አላህ እሱን የጠየቀችዉን የጀነት ቤቷን አሳያትና ፈገግ እንዳለች ቆጥኙ ተወረወረ። አላህም ዝንተ ዓለም በየ ሚህራቦች በሚቀራዉ ቁርዓን ዉስጥ የምርጥ ሴቶች ምርጥ ምሳሌ እንደሆነች አወሳት። ለነዚያ ላመኑት ምርጥ ሞዴል እንደሆነች ተናገረላት። ያቺ ከጀነት በፊት የአላህን ጉርብትና የፈለገችዋን እንስት አላህም መሬትና በዉስጧ ያሉትን ነገር በሙሉ እስኪወርሳት ድረስ የምትወሳ እንቁ ሴት አድርጎ አቆያት። እህቴ! እስልምናሽ ደምሽ፣ አጥንትሽ እንደሆነ እንዳትዘነጊ። ለዚህ እስልምናሽ የምትከፊዪዉ የትኛዉ ዋጋ ቀላል ነዉ። አሲያ ኮ የግብፅ ሴቶች አለቃ ነበረች። አንድን ነገር ስትፈልግ በጣቷ መጠቆም ብቻ ይበቃት ነበር። የዱንያ ጀነት በእጆቿ ላይ ናቸዉ። ነገር ግን እሷ ዱንያን ስትመለከታት ጠፊ እንደሆነችና አላህ ጋር ያለዉ በረከት ዘላለማዊ እንደሆነ አወቀች። ዘላለማዊዉን መርጣ ጠፊዉን ተወች። እህቴ ሆይ! ዲንሽን ለዱንያ ብለሽ አትሽጪ! 🌻ከአላህ የሚያርቅሽን ሀራም ምግብን አትመገቢ! 🌷ከአላህ የሚያርቅሽን የትኛዉንም ፍቅረኛ አትቅረቢ! 🌹ኸይርሽን ሟጧ የሚበላን የትኛዉንም ስብስብ አትቀላቀዪ! 🥀እነሱ ፊት አላህን መታዘዝን የምታፍሪበትን የትኛዉንም ጀመዓ ራቂ! 🍁የአላህን ዉዴታ የሚያሳጣሽን የትኛዉንም ድርጊት አትፈፅሚ! 🍂ሁሉም ሴቶች በፋሽን ተታለዉ ሂጃባቸዉን ቢተዉ እንኳን አንቺ ግን እንዳተዩዉ! 🍃ሁሉም ሴቶች ላይፍ ነዉ እያሉ ወንድ ቢጨብጡም፣ ሙዚቃ ቢያዳምጡም፣ ከወንድ ጋር ተቃቅፈዉ ቢወጡም አንቺ ግን የአላህ ዉዴታ በመሻት ፅኚ! አዉቃለሁ! ይህን ሁላ ስታረጊ ያለጓደኛ ብቻሽን ትቀሪያለሽ። ግን ኮ አንቺ የዱንያን ጀነት ለአኼራ ጀነት ብላ የተወች የአሲያ ልጅ ነሽ። አንቺስ ልክ እንደሷ ከሰዉ ፍቅርና ቀረቤታ በፊት የአላህ ፍቅርና ቀረቤታን አትፈልጊም እንዴ? እህቴ ይህን አትርሺ! ሰዉ ብቻዉን ይሞታል፣ ብቻዉን ይቀበራል፣ ብቻዉን ይነሳል፣ ብቻዉን ይገመገማል። ዘላለማዊ የሆነዉን የአላህ ቀረቤታ ጠፊ በሆነዉ በሰዎች ቀረቤታ አትቀይሪዉ! ልክ እንደእናትሽ አሲያ በአምነትሽ ጉዳይ ላይ የማንንም ወቀሳ አትፍሪ! ከሁሉም በፊት የአላህ ዉዴታ ይቀድማል!! منقول https://t.me/leihte
نمایش همه...
እንተዋወስ(entewawes)

وذكر فإن الذكرى تنفع المؤمنين (አስታውስ ማስታወስ ሙኡሚኖችን ትጠቅማለችና)

🌹የነብዩ (ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአመጋገብ ሱና🌹 #34ነብዩ(ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከሰዎች ጋር እየበሉ ከሆነ ከገበታው የሚነሱት በመጨረሻ ነበር ። ይህንን የሚያደርጉት አንዳንድ ሰዎች ቀስ ብለው ስለሚመገብ ሌሎቹ ሲነሱ አፍረው መመገባቸውን እንዳያቆሙ ነበር ።ነብዩ (ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) እነዚህ ሰዎች እስኪጨርሱ ቀስ እያሉ እየተመገብ ይጠብቁዋቸው ነበር። #35ነብዩ(ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) በመጀመሪያዎች ሦስት ጉርሻዎች ቢስሚላህ ይሉ ነበር። #36አንድ ሰው ቢስሚላህ ሳይል ከበላ እጁን ይይዙትና ቢሰሚላህ እንዲል ያደርጉት ነበር። #37ነብዩ (ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) አንድ ሰው በግራ እጁ ሲበላ ካዩት እጁን ይይዙትና ምግቡን ያስጥሉታል፣ከዚያም በቀኝ እጁ እንዲበላ ይነግሩታል። #38አንድ አይነት ምግብ ከቀረበላቸው ከፊታቸው ብቻ ይበሉ ነበር ።ነገረ ግን ከአንድ በላይ ምግብ ከቀረበላቸው ከሰዎች ፊት ሄደው ከመብላት አይቆጠቡም ነበር። #39ነብዩ(ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) የቀይ ተምሮችን ውስጣቸውን ካፀዱ በኋላ ይበሉ ነበር ። #40በልተው ጨርሰው ከታጠቡ በኋላ በጺማቸውና በራስ ፀጉራቸው ላይ ያደርቁ ነበር። #41ዶሮ መብላት ከፈለጉ ቤታቸው ውስጥ ለብዙ ቀን ካቆዩት በኋላ አርደዋት አብስለው ይበሉ ነበር። #42ነብዩ (ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሾርባ ውሰጥ ቂጣ ከተው መብላት ይወዱ ነበር። #43ነብዩ (ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ቅቤ ከተምር ጋር መመገብ ይወዱ ነበር ።ተምርም ከወተት ጋር ይመገቡ ነበር፤ሁለቱም ምርጥ ምግቦች ናቸው ብለዋል። https://t.me/leihte
نمایش همه...
እንተዋወስ(entewawes)

وذكر فإن الذكرى تنفع المؤمنين (አስታውስ ማስታወስ ሙኡሚኖችን ትጠቅማለችና)

🌹የነብዩ ሰ.ዐ.ወ የአመጋገብ ሱና🌹 #22ነብዩ ሰ.ዐ.ወ ምግብ የያዘን የምግብ ዕቃም ሆነ መጠጥ የያዘ መጠጫን ይከድኑ ነበር።የሚከድኑበት ነገር ካጡ ካላዩ ላይ ስንጥር ያስቀምጡ ነበር። #23ተሰባስበው ለተቀመጡ ሰዎች የሚበላም ሆነ የሚጠጣ ነገር ሊያከፋፍሉ ሲፈልጉ ከቀኛቸው ይጀምሩ ነበር ።ከግሬቸው ለመጀመር ከፈለጉ ከቀኛቸው ያለውን ሰው ፍቃድ ይጠይቁ ነበር ። #24ነብዩ ሰ.ዐ.ወ ማታ የተሰራን ምግብ እስከጠዋት ፣ጠዋት የተሰራን ምግብ እሰከ ማታ አያቆዩም ነበር።(ለሚቀጥለው ምግባቸው በአላህ ላይ ይተማመኑ ነበር። #25ነብዩ ሰ.ዐ.ወ ሥጋ ወደቤት ሲያመጡ ለጎረቤት እንዲበቃ ተደርጎ እንዲሰራ ያደርጉ ነበር ። #26ነብዩ ሰ.ዐ.ወ ምግብም ላይ ሆነ መጠጥ ላይ ተንፍሰው (እፍ ብለው)አያውቁም። ምግብ ላይ መተንፈስን መጥፎ ልማድ አድርገው ይቆጥሩት ነበር ። #27ነብዩ ሰ.ዐ.ወ ሁለት ፍራፍሬዎችን በሁለት እጆችቻቸው ላይ አስቀምጠው ተራ በተራ ይመገቡ ነበር ። #28ነብዩ ሰ.ዐ.ወ ተምር ከተመገቡ በኋላ ፍሬውን በግራ እጃቸው ይጥሉት ነበር።ፍሬውን በሸሀዳ ጣታቸውና በመሀል ጣታቸው ጀርባ ላይ ላይ አድርገው ይወረውሩት ነበር። #29የማያውቁት ምግብ ከገጠማቸው አስቀድመው ስለምግቡ ይጠይቁ ነበር። #30የማያውቁት ሰው ምግብ ሲያመጣላቸው አስቀድመው እርሱ ከምግቡ እንዲበላ ያደርጉ ነበር።ይህንን ማድረግ የጀመሩት ጠላቶቻቸው መርዝ በምግብ ካበሉዋቸው ቦኋላ ነው። #31ረሱል ሰ.ዐ.ወ የጎድን አጥንት በጣም ይወዱ ነበር። #32ነብዩ ሰ.ዐ.ወ ከተጠሩበት ቤት ሲሄዱ መንገድ ላይ ሰው ካጋጠማቸው ይዘውት ይሄዱና ጠሪዎችን ፍቃድ ይጠይቁዎቸው ነበር ።ከተፈቀደላቸው ይዘውት ይገባሉ። #33ነብዩ ሰ.ዐ.ወ እንግዳቸውን በቃኝ እስኪላቸው ጠግቦ እንዲበላ ይገፋፉ ነበር። #34ይቀጥላል https://t.me/leihte/299
نمایش همه...