fa
Feedback
አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

رفتن به کانال در Telegram

#የኅብርቱዋናዓላማ ፩.መንፈሳዊ መጻሕፍትን በዓላማ፤በእቅድ እንድናነባቸው፤እንድናስነብባቸው በሕይወታችን ትርጉም እንዲኖራቸው ማድረግ። ፪.ከቤተሰቦቻችን፤ዘመዶቻችን፤ወዳጆቻችን ስላነበብናቸው መጻሕፍት እነሱም ስላነበቡት መጻሕፍት ውይይት የማድረግ ልምድን ማዳበር። ፫.አንባቢ ትውልድ መፍጠር። ለአስተያየትዎ @orthokiha ይጻፉ። https://t.me/BetMetsahfte Cross @dawitfikr

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

کانال አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE (@betmetsahfte) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 17 882 مشترک است و جایگاه 1 984 را در دسته کتب و رتبه 1 900 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 17 882 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 29 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 209 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 8 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 19.94% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.77% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 562 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 388 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 22 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
#የኅብርቱዋናዓላማ ፩.መንፈሳዊ መጻሕፍትን በዓላማ፤በእቅድ እንድናነባቸው፤እንድናስነብባቸው በሕይወታችን ትርጉም እንዲኖራቸው ማድረግ። ፪.ከቤተሰቦቻችን፤ዘመዶቻችን፤ወዳጆቻችን ስላነበብናቸው መጻሕፍት እነሱም ስላነበቡት መጻሕፍት ውይይት የማድረግ ልምድን ማዳበር። ፫.አንባቢ ትውልድ መፍጠር። ለአስተያየትዎ @orthokiha ይጻፉ። https://t.me/BetMetsahfte Cross @dawit...

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 30 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته کتب تبدیل کرده‌اند.

17 882
مشترکین
+824 ساعت
+317 روز
+20930 روز
آرشیو پست ها
#ሁላችሁም_ልታነቡት_የሚገባ_መጽሐፍ ሐምሌ 8 ይጠብቁን! #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ!

#ፈላስፋው_ሰማዕት ከ ደብተራ #በአማን_ነጸረ fb ገጽ የተወሰደ ጽሑፍ! -- ጌታ መጣ፣ አስተማረ፣ ተሰቀለ፣ ሞተ፣ ተነሣ፣ ዐረገ፡፡ ሐዋርያት በጌታ መንገድ ቀጠሉ፡፡ አስተማሩ፣ መከራ ተቀበሉ፣ ዐረፉ፡፡ በዚህ መካከል የተጠረዘ መጽሐፍ የለም፡፡ ከጌታ ቀጥታ የተማረ መምህር አልነበረም፡፡ ከደቀ መዛሙርቱ የተማሩ መምህራንና ለጌታ ትምህርት የታመነ ምዕመን ግን ነበረ፡፡ ክርስትና ገና በየቤቱ በማኅበር ደረጃ ያለችበት ዘመን ነው፡፡ -- ምዕመኑ ሦስት ፈተናዎች ነበሩበት፡፡ ቀዳሚው ፈተና የውስጥ አንድነቱን የሚሸረሽረው የኖስቲኮች ትምህርት ነው፡፡ ሌላኛው ፈተና ከቤተ አይሁድና ከፈላስፎች ይመጣል፡፡ ሕይወት የሚያስከፍለው የሮም ነገሥታ ማሳደድ ሦስተኛው ፈተና ነበረ፡፡ አንድ ክርስቲያን በእነዚህ ተፈትኖ የማለፍ ግዴታ አለበት፡፡ -- በዘመኑ የነበሩ አበው ሦስት ዐበይት ትኩረቶች አላቸው፡፡ የአስተምህሮ አንድነትን ለመጠበቅ ጥረት ማድረግ፣ የቤተ ክርስቲያንን ማዕከላዊነት መጠበቅና ከዐላውያን ነገሥታት የሚመጡ ፈተናዎችን በጥብዓት መቀበል፡፡ በአስተምህሮ ረገድ መጽሐፍ ቅዱስ በአንድነት አልተጠረዘም፡፡ ዶግማዊ ድንጋጌ የለም፡፡ ትኩረቱ ምስክርነት ላይ ነው፡፡ ክርስቶስ መሲሕ ስለመሆኑና ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ተሰቅሎ ስለማዳኑ መመስከር፡፡ -- በአስተምህሮው ውስጥ ከቤተ አይሁድም፣ ከኖስቲኮችም፣ ከፈላስፎችም ስለክርስቶስ ማንነትና ከእግዚአብሔር አብ ጋራ ስላለው ግንኙነት ጥያቄ ይነሳል፡፡ ለጥያቄው የሚሰጠው መልስ የሥላሴን የማዳን ተግባር ወይም በምሥጢረ ሥላሴ ትምህርት ውጫዊ ግብር (Economic Trinity) የሚባለው ላይ ያተኩራል፡፡ አብ ወልድን ስለመላኩ፣ ወልድ ተልኮ ሥጋ ለብሶ ስለማዳኑ፣ መንፈስ ቅዱስ ስለማጽናቱ፡፡ ዘመኑ ቅድመ ኒቅያ ነው፡፡ የምሥጢረ ሥላሴ ትምህርት በውስጣዊው በኩነታዊው፣ ማለትም ስለ አብ ልብነት፣ ስለ ወወልድ ቃልነትና ስለ መንፈስ ቅዱስ እስትንፋስነት፣ ስለወላዲነት፣ ተወላዲነት፣ ሠራጺነት (Immanent Trinity) ገና በስፋት መነገር አልተጀመረም፡፡ -- የክርስቶስን ማንነት ሲናገሩ ቃል፣ ጥበብ፣ ኃይል እያሉ ይገልጡታል፡፡ ከቤተ አይሁድ ሲነጋገሩ ሦስት አማልክት አምላኪዎች እንዳይባሉ ብርቱ ጥንቃቄ ያደርጋሉ፡፡ እንደ ሰማዒውና ተከራካሪው ደረጃ ትምህርቶቻቸውን ያቀርባሉ፡፡ ሥራዎቻቸውን ስንመዘንም ይህንን ዐውድ ተረድተን ሊሆን ይገባል፡፡ እነዚያ ሊቃውንት ለኋላ ዘመን ጉባኤያት የነገረ መለኮት መነሻ ቃላትን ያቀበሉ ናቸው፡፡ -- የሰማዕቱ ቅዱስ ዮስጢኖስ ዐቢይ ተጋድሎ የሚባለው አመክንዮን ለነገረ መለኮት ማስገበር ነው፡፡ ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ፣ አርጌንስና አውቴናጎረስም ይህንን መንገድ እንደ ተከተሉት ይታመናል፡፡ በዘመኑ faith and reason ዐቢይ ርእስ ነው፡፡ -- ሰማዕቱ ሊቅ በምሥራቁም በምዕራቡም የሚታወቀውን ያህል በቤተ ክርስቲያናችን መዛግብት ስሙ ሲነሳ አይታይም፣ ወይም ገና ያልደረስንባቸውን መዛግብት ይኖሩ ይሆናል፡፡ ተዋሥኦን የተከተለው የዕቅበተ እምነት አካሔዱ ግን ለቤተ ክርስቲያናችን አዲስ አይደለም፡፡ የክርክር አርእስቱም በመካከለኛው ዘመን ካሉት የእነ አባ ጊዮርጊስ ገድላት ውስጥ ከሰፈሩት ቤተ አይሁድ ጋራ ከተያያዙ ክርክሮች ጋራ ዝምድና አያጡም፡፡ ሊቁ የሚጠቀማቸው ‹‹ወልዱ፣ ቃሉ፣ ጥበቡ፣ ኃይሉ›› እያሉ መድኅን ክርስቶስን የሚገልጡ ቃላት በመጽሐፈ ኪዳን በስፋት ይስተዋላሉ፡፡ ቃላቱ ቅድመ ኒቅያ ነገረ ክርስቶስን ገላጭ ሲሆኑ በኋላ ዘመንም ቁልፍ ሆነው በአሉታም በአዎንታም አገልግለዋል፡፡ ያንን ዘመን መረዳት የሚጨምረው ነገር አለ ካልን ይኽ መጽሐፍ መነበቡ ብዙ ያግዛል፡፡ ምስጋና ለ ዲ/ን Mesfin Tekeste N.B ደብተራ በአማን ነጸረ በኔ በኩል ለሚመጡ ልዩ ቅናሽ አድርጉ ብለውናል።መጽሐፉ @orthokiha እዘዙ ልዩ ቅናሽ ይደረግላችኃል። #አሳታሚና_አከፋፋይ የእናንተው #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ!

#መራኁት የተሰኘ መጽሐፍ በጠየቃችሁን መሰረት አስገብተናል።
#መራኁት የተሰኘ መጽሐፍ በጠየቃችሁን መሰረት አስገብተናል።

መልካም ዜና ለውድ አንባብያን #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር ንባብ ለጽድቅ ሕይወት የሚል ሞቶ አለው እንሆ በጉጉት የሚትጠብቁት #ንባብ_ለሕይወት ሐሙስ ሐምሌ 23 ይከፈተል እስከ ሐምሌ 26 ይቆያል። #
መልካም ዜና ለውድ አንባብያን #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር ንባብ ለጽድቅ ሕይወት የሚል ሞቶ አለው እንሆ በጉጉት የሚትጠብቁት #ንባብ_ለሕይወት ሐሙስ ሐምሌ 23 ይከፈተል እስከ ሐምሌ 26 ይቆያል። #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ!

አጃኢበት ነው ይላል ወሎ! በዚህ ዘመን ከተጻፉ ፥ የታሪክ መጻሕፍት በተዋጣለት የመረጃ ብቃት፤ የሚዛናዊነት ልኬት፤ የሙያ ክብርና ዋጋ ከፍ ብሎ የተገለጠበት ድንቅ የታሪክ መጽሐፍ ነው። በጠቅላላ 62
አጃኢበት ነው ይላል ወሎ! በዚህ ዘመን ከተጻፉ ፥ የታሪክ መጻሕፍት በተዋጣለት የመረጃ ብቃት፤ የሚዛናዊነት ልኬት፤ የሙያ ክብርና ዋጋ ከፍ ብሎ የተገለጠበት ድንቅ የታሪክ መጽሐፍ ነው። በጠቅላላ 620 ገጽ ያለው ደጎስ ያለ በሸጋ ሁኔታ የታተመ መጽሐፍ ነው። ይህንን መጽሐፍ final exam እንደሚፈተን ተማሪ ማስታወሻ ይዤ ነው የበላሁት ማለት ይቻላል። ሐሳቡና ጽሕፈቱ እንደ ሰምና ፈትል የሆኑለት መጽሐፍ ሳገኝ ሌሊቱን ሁሉ ላነጋበት እችላለሁ። ይህ መጽሐፍ እንደዚያ ሆኖልኛል። ጸሐፊው ቀሲስ ዶክተር መንግሥቱ ጎበዜ ናቸው። ስለሳቸው ታሪክ ከዚህ በፊት በቲክቶክ ገጼ ላይ ነግሬያችሁ ነበር። እሳቸው የተዋጣላቸው የታሪክ መምህር ተመራማሪ የቤተ ክርስቲያን ቀዳሽ ካህን ናቸው። መጽሐፋቸው በጥልቅ ምርምር ላይ የተመሰረተ በስክነትና በማስተዋል የተጻፈ ነው። ጎበዝ ይህች አገር የቆመችበት ምሰሶ በእንባጮ ሽውሽውታ የማይናወጽ ስለመሆኑ ታሪካችን ይመሰክራል። ገዝታችሁ ማንበብ ቢያቅታችሁ እንኳ ደሴ ለምትኖሩ የሀገሬ ልጆች በየሳምንቱ ለአንድ ሰው በትውስት ለመስጠት ፈቃደኛ ነኝ። በጣም አንባቢ ከበዛ 5 መጻሕፍት ጨምሬ ገዝቼ እየተዋዋሳችሁም ቢሆን ታነቡታላችሁ። ስልኬ 0920184927 ነው። ደውሉልኝ። ቢሮየ ደሴ መናፈሻ ሰፈር በሚገኘው የከፍተኛው ፍርድ ቤት ሕንፃ ፊት ለፊት በሚገኘው መንግስቱ ዘገየ ጠበቃና የሕግ አማካሪ ቢሮ ውስጥ ነው። ሸጋ ቅዳሜ! ጠበቃ መንግስቱ ዘገየ አባተ N.B ጽሑፉ እንዳለ ነው post ያደረኩት ይህን መጽሐፍ ያላነበባችሁ አንቡት #ብያንስ_በቤተ_ክርስትያናችን_ታሪክ አንድ ዓይነት አስተሳሰብ ይኑረን።

#ዘማርያም_ዘለቀ (ዲ/ን ) እንደጻፈው! ➺በአኃት አብያተ ክርስቲያናት ብቻ ሳይኾን በምሥራቅ ኦርቶዶክስ ብሎም 'ቀን ወስኖ ቅዱሳንን ማክበር ባዕድ አምልኮ ነው!' ከሚሉ ከፕሮቴስታንት አንጃዎች ሉተራውያንም አንግሊካን ቸርቾችም Saints’ Days ጭምር ቀን ተሰጥቶት June 1 ቅዱስና ሰማዕት ተብሎ የሚከበር ነው። ➔በአንግሊካን ቸርቾች በሰማዕቱ ስም የሚጠራ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን በምዕራብ አፍሪካ፦ ጋና እና በፊልጵስዩስ ከተማ(St. Justin Anglican Church in Ablekuma, Ghana, St. Justin Episcopal Church in Mankayan, Philippines & St. Justin Episcopal/Episcopalian Church in Kabacan, Philippines) አላቸው። ➔ ሃይማኖትን ለፍልስፍና ሳይኾን ፍልስፍናን ለሃይማኖት ከተጠቀሙ በወቅቱ ናኝቶ ከነበረው  የግሪክ ፍልስናንና በሐዋርያት ለተሰበከችው ለክርስትና የመገለጥ ርትዕት ሃይማኖት መካከል  ድልድይ ከኾኑ አበው አንዱ አረሚዊ ፈላሳፍ የነበረው በጥንቷ ፍላቪያ ኒያፖሊስ (አሁን የናብሉስ ከተማ፣ ፍልስጤም) ሲሆን ከአረማውያን ወላጆቹ የተወለደው ሰማዕቱ ቅዱስ ዮስጢኖስ(St. Justin Martyr (c. 100–165 AD)) ዐቃቤ እምነት ወፈላስፋ ነው። ➔እውነትን ፍለጋ ስቶይክ (Stoic)፣ ፕላቶኒክ (Platonic) እና ፓይታጎሪያን (Pythagorean) የመሳሰሉ የግሪክ ፍልስፍናዎችን አጥንቷል። ➨ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ለድኅነት እንደሚረቡ፥ ምሥጢረ ምሥጢራት ቅዱስ ቍርባን አማናዊ የመድኅነ ዓለም የኢየሱስ ክርስቶስ በአካል የመገኘት የቅዱሳን ኅብረት መኾን ይመሰክራል። ክርስትና “እውነተኛው ፍልስፍና” - "true philosophy" ይላታል። ➔የነቢያት ትንቢት ፍጻሜ፥ ብሉይ ኪዳን ጥላ በወልደ እግዚአብሔር በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መኾን ሐዲስ ኪዳን አማናዊ አካል መኾኗን ይመሰክራል። ➔ሰማዕቱ ዮስጢኖስ የሰብዓ ሊቃናትን(Septuagint) መጽሐፍ ቅዱስ መሠረት በማድረጉ ከ ፹ ወ፩ ቅዱሳት መጻሕፍት  ውስጥ "ይቤ ባሮክ..."እያለ ከመጽሐፈ ባሮክ(Dialogue with Trypho (Chapter 129), Baruch 3:35–37)፤ መጽሐፈ ኵፋሌን(Dialogue with Trypho, Chapter 81)፤ መጽሐፈ ጥበብን(Dialogue with Trypho (Chapter 129) ይጠቅሳል። ➨በቀዳማዊት ሔዋን ፋንታ ዳግሚት ሔዋን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንደተሰጠችን ይመሰክራል። "ድንግልና ያልረከሰች የመጀመሪያዋ ሔዋን የእባቡን ቃል ፀንሳ አለመታዘዝንና ሞትን ወልዳለችና። ዳግሚት ሔዋን ድንግል ማርያም ግን የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤልን ብስራት ሰምታ እምነትንና ደስታ  አስገኘች።...For Eve, who was a virgin and undefiled, having conceived the word of the serpent, brought forth disobedience and death. But the Virgin Mary received faith and joy, when the angel Gabriel announced the good tidings to her..."[Dialogue with Trypho, Chapter 100] እንዲል። ➔"የሙሴ እጆች ግን ከብደው ነበር፤ ድንጋይም ወሰዱ፥ በበታቹም አኖሩ፥ እርሱም ተቀመጠበት፤ አሮንና ሖርም አንዱ በዚህ አንዱ በዚያ ሆነው እጆቹን ይደግፉ ነበር፤ ፀሐይም እስክትገባ ድረስ እጆቹ ጠነከሩ።" ዘጸ.17፥12 በመጥቀስ የሙሴ የተዘረጉ እጆች የቅዱስ መስቀል ምሳሌ  መኾኑን(Dialogue with Trypho (Chapter 90 and 111), Chapter 90. The stretched-out hands of Moses signified beforehand the cross) በማብራራት በትእምርተ መስቀል ስናማትብ አጋንንት ድል እንደሚነሱ ብሎም ስለ መድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል አስቀድመው የተነገሩ ትንቢቶችን ጭምር (Chapter 97. Other predictions of the cross of Christ)ያብራራል እንጂ እንደ ዘመናችን ስሑታን  'አባትህ የተገደለበት ሽጉጥ' አይልም፤ አይወጣውም። ➔ በሮም ከተማ የክርስትና እምነት አስተማሪ በመሆኑ በሀሰት ተከሰሰና ከስድስት ክርስቲያኖች ጋር ተገርፎ ራሱ እንዲቀላ ተፈርዶበት በ165 ዓ.ም. ሰማዕትነትን ተቀብሏል። ➛ወልደ ተከሥተ፦ መስፍኔም በዚኽ ሰማዕት ሥራ ተከሥቷል። መጽሐፍ ማዘጋጀት ፦ እርግዝና፤ ማሳተም፦ ምጥ፤ ታትሞ ማየት፦ ልጅን ወልዶ እንደ መሳም ነውና እንኳን ማርያም ማረችኽ። በወሊድ መሞት አለና... የቀረው የፈላስፋ ሰማዕት የቅዱስ ዮስጢኖስ መጽሐፍ ሐተታ በ Tiktok platform የምንኼድበት አይደለምን? #መጽሐፉ_ታነቡት_ዘንድ_ግብዣዬ_ነው!

#ፈላስፋው_ሰማዕት_ቅዱስ_ዩስጢኖስ መጽሐፍ በስርጭ ላይ ነን! ቀድማችሁ የከፈላችሁ መጥታችሁ ውሰዱ። #አሳታሚና_አከፋፋይ #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራው
+1
#ፈላስፋው_ሰማዕት_ቅዱስ_ዩስጢኖስ መጽሐፍ በስርጭ ላይ ነን! ቀድማችሁ የከፈላችሁ መጥታችሁ ውሰዱ። #አሳታሚና_አከፋፋይ #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ!

ለቅዱስ ዩስጢኖስ መጽሐፍ ቀድመው የከፈሉ 11 ሰዎች ደርሰዋል። ቅናሹ እስከ 9:00 ብቻ ነው። ዕድሉ ተጠቀሙበት።
ለቅዱስ ዩስጢኖስ መጽሐፍ ቀድመው የከፈሉ 11 ሰዎች ደርሰዋል። ቅናሹ እስከ 9:00 ብቻ ነው። ዕድሉ ተጠቀሙበት።

#የፈላስፋው_ሰማዕት_ቅዱስ_ዩስጢኖስ መጽሐፍ 9:00 ከማተምያ ይወጣል። የሽፋን ዋጋው 1500 ብር ነው። እስከ 9:00 ቀድመው ለሚከፍሉ ለማስታወቅያ የተደረገ ቅናሽ ተጠቀሙበት 1000 ብር ብቻ ከ9:
#የፈላስፋው_ሰማዕት_ቅዱስ_ዩስጢኖስ መጽሐፍ 9:00 ከማተምያ ይወጣል። የሽፋን ዋጋው 1500 ብር ነው። እስከ 9:00 ቀድመው ለሚከፍሉ ለማስታወቅያ የተደረገ ቅናሽ ተጠቀሙበት 1000 ብር ብቻ ከ9:00 በኃላ 1200 ብር በሁሉም መደብሮች ያገኙታል። CBE 1000498547629 TELEBIRR 0925421700 KIFLOM HAILU Screenshot @orthokiha ይላኩ! #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ!

የመምህር ዮሐንስ ጌታቸው መጻሕፍት 1.ትምህርተ ጽድቅ 2.መጽሔተ ወራዙት 3.ዐይነ_ልቡና 4.ኦርቶዶክሳዊ_ነገረ_ሥላሴ በስርጭት ላይ ነን! ዋና አከፋፋይ #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማር
የመምህር ዮሐንስ ጌታቸው መጻሕፍት 1.ትምህርተ ጽድቅ 2.መጽሔተ ወራዙት 3.ዐይነ_ልቡና 4.ኦርቶዶክሳዊ_ነገረ_ሥላሴ በስርጭት ላይ ነን! ዋና አከፋፋይ #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ!

እንኳን ለቅዱስ ጳውሎስ ወጴጥሮስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ! “የጳውሎስ የመጨረሻዋ ቀን” ተራኪ፡ ገጣሚ ኤልያስ ሽታሁን ቅዱስ ጳውሎስ፣ ገጽ፡ 409

ሰው በደሉን ለማሰብ ይቸገር እንደ ሆነ እንጂ ክብሩን ግን ላይፋቅ መዝግቦ የሚያኖርበት ጥሩ የማስታወሻ ቋት አለው፡፡ አንተ አይደለም እስከ ሦስተኛው ሰማይ መነጠቅ፣ ብዙም የማይደፈር ረጅም ተራራ አን
ሰው በደሉን ለማሰብ ይቸገር እንደ ሆነ እንጂ ክብሩን ግን ላይፋቅ መዝግቦ የሚያኖርበት ጥሩ የማስታወሻ ቋት አለው፡፡ አንተ አይደለም እስከ ሦስተኛው ሰማይ መነጠቅ፣ ብዙም የማይደፈር ረጅም ተራራ አንድ ጊዜ ብትወጣ እርሱን ትረሳዋለህ? አንተ አይደለም የእስር ቤት መሠረት የሚያናውጥ መዝሙር መዘመር፣ የስብሰባ አዳራሽ በጭብጨባ የሚያናጋ ጥሩ ንግግር ብታደርግ ያን በወርቅ ቀለም ጽፈህ ታኖረዋለህ እንጂ እንዲህ በቀላሉ ትዘነጋዋለህ? ጳውሎስ ግን በኋላዬ ያለውን እረሳለሁ አለ፡፡ ብዙ ከጫፍ ደርሶ ገና ሰብስቦ ምንም እንዳልያዘ ምስኪን ራስን መቁጠር፤ እንደ ጀመረ ታናሽ መምሰል ይህ ጳውሎሳዊ ለሆነው ትሕትና መገለጫው ነው። ቅዱስ ጳውሎስ ገጽ 173 መጽሐፉ 3ኛ እትም ደርሰዋል።3ኛ እትሙ እያለቀ ነው ጥቂት ኮፒዎ አሉን መጽሐፉ የሌላችሁ እስከ ሐምሌ 5 በእጃችሁ አስገቡ።አንብቡት! ለማዘዝ @dawitfikr አናግሩት! #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_5ኪሎ_ቅድስት_ማርያም_ማኅበረ_ቅዱሳን_ሕንፃ_ግራውዱ_አጠገብ_0988888589_0954838117_ይደውሉ!

#ለመጽሐፍ_ምርቃቱ_ቀን_5_ቀናት_ብቻ_ቀሩት_ሐምሌ_4_2018_ከቀኑ_7፡00 ጀምሮ በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ሕንጻ አራተኛ ፎቅ ላይ ኹላችሁም ተጋብዛችኋል። በዚያ ቀን ቀጠሮ ይዛችሁ እንድትገኙልኝ ስል በአክብሮት ጋበዝኋችሁ🙏 👉 ለቅምሻ ያህል ከኦርቶዶክሳዊ ነገረ ሥላሴ፦ ቅዱስ አትናቴዎስ “የተለያዩ የአካል ክፍሎች ተሰብስበው ሙሉ አካልን እንደሚገነቡ፣ ሙሉ አካልም የተለያዩ ክፍሎች ውሑድ እንደ ኾነው፣ እያንዳንዱ ክፍልም የሙሉ አካሉ ክፍል ነው፡፡ ይህ ግን ስለ አምላክ ካለን ሐሳብ እጅጉን የራቀ ነው፡፡ እግዚአብሔር ምሉዕ ነው፤ የተለያዩ የአካል ክፍሎች ወይም ልዩ ልዩ የኾኑ ንጥረ ነገሮች ውሑድ አይደለም፤ ነገር ግን እርሱ ራሱ የዓለምን ሥርዓት የሠራ ነው፡፡ አምላክ የአካል ክፍሎች አለው ሲሉ ምን ዓይነት የማይረባ ነገር አምላክን ተቃርነው እንደሚናገሩ ተመልከቱ፡፡ እርሱ ከአካል ክፍሎች ከተገነባ፣ በእርግጠኝነት እርሱ ራሱን አይመስልም፣ ከማይመሳሰሉ የአካል ክፍሎችም የተገነባ ነው የሚለውን ሐሳብ ያስከትላል፡፡ እርሱ ፀሐይ ከኾነ ጨረቃ አይደለም፤ ጨረቃ ከኾነ ምድር አይደለም፤ ምድር ከኾነ ባሕር መኾን አይችልም፤ ወዘተ፡፡ … ዓይን የመስሚያ አካል አይደለም (ጆሮ)፣ የኋለኛው (የመስሚያ አካል) እጅ አይደለም፣ ሆድም ደረት አይደለም፣ እንደገና አንገትም እግር አይደለም፣ ነገር ግን እያንዳንዱ የራሱ ሥራ አለው፤ አንዱ ነጠላ ሰውነት ከእነዚህ ክፍሎች የተገነባ ነው፡፡ … ይህን ለአምላክ የሚሰጡ ከኾነ የሚከተሉትን ያመጣል፡- አንደኛ ከላይ እንዳየነው እርሱ ራሱን አይመስልም ያሰኛል፤ ኹለተኛ ተፈጥሮአዊ በኾነ ኹኔታ የአካል ክፍሎች እንደሚከፋፈሉት እርሱንም እንደገና እንዲከፋፈል እናደርገዋለን፡፡” ይላል፡፡ በመኾኑም እግዚአብሔር የአካል ክፍሎች አሉት ማለት ተገቢ አለመኾኑን ይህ ሊቅ ያትታል፡፡ እኛ ጋር ያሉ የአካል ክፍሎችን ለእግዚአብሔር ሰጥቶ መናገር ወይም ለእግዚአብሔር አካሉን ከፋፍሎ ዐይኑ የኾነ የአካል ክፍሉ ነው፣ ጆሮውም የኾነ የአካል ክፍሉ ነው፣ እጁም የኾነ የአካል ክፍሉ ነው … እያልን ልንከፋፍል አይገባም ነው ሊቁ የሚለን፡፡ ለቅምሻ ያህል ከዐይነ ልቡና መጽሐፌ፦ ቃል ሥጋ ሲኾን፣ ቃልነቱን ለቆ ሥጋ ወደ መኾን አልተለወጠም፤ ይህማ ቢኾን ፈጣሪ ፈጣሪነቱን ለቆ ፍጡር ኾነ ያሰኛል። እንዲህ ይኾናል ብሎ ማሰብ አእምሮ ካለው ከማንም የሚጠበቅ አይደለም። በመጽሐፍ "እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም" ብሎ ራሱ ባለቤቱ እንደ ተናገረው በአምላክ ዘንድ ውላጤ ፈጽሞ የለም፤ ሊኖርም አይችልም። ፈጣሪን ፍጡር ወደ መኾን ይለወጣል ብሎ የሚያምን ሰው ፈጣሪ የለም ብሎ ከሚያምን ጋር ነው ቍጥሩ ሊኾን የሚችለው። በሌላ በኲል ሥጋም ቃልን ወደ መኾን መለወጥ አይችልም። ምንም እንኳን ለፍጥረት ለውጥ ቢስማማውም በምንም መንገድ ቢኾን ፍጡር በራሱ ፈጣሪ ወደ መኾን ሊለወጥ አይችልም። ፍጡር ፈጣሪ ወደ መኾን ይለወጣል ብሎ ማሰብም ፈጣሪም ፍጡር ወደ መኾን ይለወጣል ብሎ ከማሰብ በላይ ስሕተት ነው። ፍጡር ፈጣሪ ወደ መኾን መለወጥ ከቻለ ለፍጡር የተቻለ ለፈጣሪ አይቻልም ይባል ዘንድ ተገቢ ስላልኾነ ፈጣሪም ይለወጣል ብሎ በተዘዋዋሪ እንደ ማመን ነው። በእርግጥስ ፍጡር ፈጣሪ ወደ መኾን መለወጥ ከቻለ ቀድሞ ፈጣሪ የነበረው አዲስ ከሚመጣው "ፈጣሪ" ጋር እንዴት ሊኾን ኖሯል? ይህን ውዥንብርና የተምታታ አስተሳሰብ ከየልቡናችን ልናስወግድ ይገባል። ቃል ሥጋን በተዋሐደ ጊዜ ቃልነቱን ለቋል፤ ሥጋም ቃልን በተዋሐደ ጊዜ ሥጋነቱን ለቋል የሚል ቢኖር ፈጽሞ የተወገዘ ነው። ከላይ ያነሣነውን መሠረት አድርጎ መቃርስ እንዲህ ይላል፦ "ሰውም ቢኾን አምላክነቱን አልለቀቀም፤ አምላክነቱን ለቀቀ ማለት አይገባም፤ በተዋሕዶ አንድ በኾኑት (በመለኮትና በትስብእት) መለወጥ፣ ባሕርይን መልቀቅ የለም፤ በአለበት በተዋሕዶ ጸንቶ ይኖራል እንጂ።" እንዲል። ሃይ. አበ.ዘመቃርስ 98፥15። ዲ/ን መ/ር ዮሐንስ ጌታቸው