AAU - Muslim Students Union
رفتن به کانال در Telegram
This is the official channel of AAU-MSU. Group: @aaumsu_discussion Youtube: youtube.com/@aaumsu Twitter: x.com/aaumsu12 Facebook: facebook.com/profile.php?id=100087931837303 Contact us: @Aaumuslimstudentsunion1 Email: aaumsu12@gmail.com
نمایش بیشتر7 071
مشترکین
+1424 ساعت
+717 روز
+48630 روز
آرشیو پست ها
የሚያሸልም ጥያቄ፦
በሰው ልጅ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ "ሎጎዬን ከሪባናችሁ ላይ አላደረጋችሁም።" - በማለት ሙስሊም ተማሪዎችን ለእስር የዳረገው ዩኒቨርስቲ ማን ይባላል?!
ከተሰጡት ምላሾች መካከል 4
ሙስሊም ጠልነት የበዛበት፤ ራስገዝ የሆነው፤ በሀገርም በአፍሪካም ስመጥር የተደረገው Addis Ababa University !
የሚያሸልም ጥያቄ፦
በሰው ልጅ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ "ሎጎዬን ከሪባናችሁ ላይ አላደረጋችሁም።" - በማለት ሙስሊም ተማሪዎችን ለእስር የዳረገው ዩኒቨርስቲ ማን ይባላል?!
ከተሰጡት ምላሾች መካከል 4
በጭቆና አንጋፋ የሆነው አዲስ አበበ ዩንቨርስቲ
አሸናፊው ማን ይሆን?!
@aaumsu
የሚያሸልም ጥያቄ፦
በሰው ልጅ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ "ሎጎዬን ከሪባናችሁ ላይ አላደረጋችሁም።" - በማለት ሙስሊም ተማሪዎችን ለእስር የዳረገው ዩኒቨርስቲ ማን ይባላል?!
ከተሰጡት ምላሾች መካከል 3
ኢትዮጵያ ውስጥ አሉ ከሚባሉ አንጋፋ እና ታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አንዱ ነው ተብሎ ብዙ ጊዜ እንደትልቅ ጀብድ የሚወራለት በሃይመኖት ጥላቻ በተሞሉ አስተዳደሮች(የኔ እምነት እንጂ የእስልምና እምነት ተከታይ ተማሪዎች መብት ሊከበር አይገባም በሚሉ) የሚመራው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
የሚያሸልም ጥያቄ፦
በሰው ልጅ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ "ሎጎዬን ከሪባናችሁ ላይ አላደረጋችሁም።" - በማለት ሙስሊም ተማሪዎችን ለእስር የዳረገው ዩኒቨርስቲ ማን ይባላል?!
ከተሰጡት ምላሾች መካከል 2
እራስ ገዝ ነኝ ብሎ የሚፎክረው,የሙስሊም ጥላቻውን መቆጣጠር አቅቶት ጥላቻው ገንፍሎ ወጥቶበት በምርቃት ቀን ሣይቀር ያስተማራቸውን ተማሪዎች ደስታን ለማደፍረስና የጀመሩትን ትግል ለማደናቀፍ ውሃ በማይቋጥር ምክንያት ሙስሊም ተማሪዎችን የሚያስረው, ስለ ዲሞክራሲ የሚደሰኩረውና ነገር ግን ፈፅሞ የማይተገብረው, በሙስሊም ጠልነቱ ፈጽሞ አቻ ያልተገኘለት, የሴኩላሪዝም ጽንሠ ሀሣብ ፈጽሞ የተምታታበትና ሁሌም ሴኩላሪዝም ብሎ የሚያዜመው አ.አ.ዩ ነው:: ሌላ ማን ሊሆን???
የሚያሸልም ጥያቄ፦
በሰው ልጅ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ "ሎጎዬን ከሪባናችሁ ላይ አላደረጋችሁም።" - በማለት ሙስሊም ተማሪዎችን ለእስር የዳረገው ዩኒቨርስቲ ማን ይባላል?!
ከተሰጡት ምላሾች መካከል 1
🤘የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲቲቲቲቲ!!!!!😡😡😡
የጥቁር ህዝቦች የነጻነት ተምሳሌት የሳይንስና የዕውቀት ማማ... ነበር ይባላል! አሁን ግን የትኩረት አቅጣጫውንና የሳይንስ ሚዛኑን ሙሉ በሙሉ የቀየረ ይመስላል እንኳን ደስ አላችሁ ዩኒቨርሲቲያችን ከዓለም ታላላቅ የምርምር ተቋማት ተርታ ሊሰለፍ የሚችልበትን አዲስ ሳይንሳዊ ግኝት አግኝቷል በጨርቅ ላይ የሎጎ አለመኖር የተማሪዎችን እግር ወደ ወህኒ ያመራል!👏👏👏👏🤬 የሚል አስገራሚ ቀመር ፐፐፐፐፐ
በሰው ልጅ ታሪክ ታይቶና ተሰምቶ በማያውቅ መልኩ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በሚል ሰበብ ሎጎዬን ከሪባናችሁ ላይ አላደረጋችሁም በሚል የህጻን ልጅ ክምችች ሙስሊም ተማሪዎችን ለእስር መዳረግ ምን የሚሉት የ21ኛው ክፍለ ዘመን የዕውቀት ደረጃ ነው? ለመሆኑ ዩኒቨርሲቲው የመማሪያ ተቋም ነው ወይስ የብራንዲንግና የሎጎ ማስታወቂያ ድርጅት? አረ ተቃጠልኩ😭😭 በኔ ጊዜም ይሔ አለመፈጠሩን እንጃ ያአላሕሕ አላሕ የስራቹን እንደሚሰጣቹ አልጠራጠርም አረ የትሔደን እንተንፍስ 🤲🤞🤬
አሸናፊ ማን ይሆን?!
@aaumsu
የሚያሸልም ጥያቄ፦
በሰው ልጅ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ "ሎጎዬን ከሪባናችሁ ላይ አላደረጋችሁም።" - በማለት ሙስሊም ተማሪዎችን ለእስር የዳረገው ዩኒቨርስቲ ማን ይባላል?!
ሽልማቱ፦ የዩኒቨርስቲው ሎጎ ያለውና "ጥያቄ አለን!" - የሚል መልዕክት የሰፈረበት ሪቫን ነው።
መልሳችሁን @Aaumuslimstudentsunion1 ላኩልን። ቀድሞ የመለሰ የሚሸለም ይሆናል።
@aaumsu
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት የተላለፈ መልዕክት!
እአሰላም አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ
የተከበራችሁና የተወደዳችሁ ተመራቂ ወንድሞቼ እና እህቶቼ፤
የዛሬው ቀን በህይወታችን ውስጥ የማይረሳ ታሪካዊ ቀን ነው። በመጀመሪያ ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፋችሁ ለዚህ ታላቅ ቀን ስላደረሳችሁ አላህ (ሱ.ወ) ምስጋና ይገባው። ሁላችሁንም እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉
ብዙ ውጣ ውረድን እና ድካምን አልፋችሁ ዛሬ ላይ ደርሳችኋል። አላህ በስራችሁም ሆነ በዕድሜያችሁ ላይ በረከትን ያድርግ። ዛሬ የሕይወታችሁን አንድ ምዕራፍ ዘግታችሁ ወደ ሌላው የሕይወት ምዕራፍ የምትሸጋገሩበት የጉዞ መጀመሪያ ነው። በቀጣይ የሕይወት ጉዟችሁ፤ ግባችሁን በጽናት፣ በትጋት እና ታላቅ አሻራን በማስቀመጥ እንድትጓዙ ምክሬን እለግሳለሁ። የተፈጠርንበትን ዋና ዓላማ እያስታወሱ፣ ለዲናችንም ሆነ ለኡመተል ኢስላም ጠቃሚ የሆኑ ስራዎችን ለመስራት መትጋት ይጠበቅባችኋል። አላህ ቀጥተኛውን መንገድ ለሁላችንም ይወፍቀን።
የዛሬው ደስታችን ከታላቅ ጀግንነት ጋር የተቆራኘ ነበር። ዛሬ የምረቃ መግቢያ በር ላይ፣ "ሃይማኖታዊ መብታችን ይከበር! የእህቶቻችን መብት ይመለስ!" የሚል ህጋዊ እና ፍትሃዊ ጥያቄን በሰላማዊ መንገድ ሪቫን በማንገባቸው ብቻ የታሰሩ ወንድም እና እህቶቻችን ነበሩ። ይህ ድርጊት ምረቃችንን የትግል እና የጽናት አውድማ አድርጎት ውሏል።
እነዚህ ጀግና ወንድም እና እህቶቻችን ላለፉት ሁለት ዓመታት ያህል መብታችን ይከበር በማለት ሳይታክቱ እና ወደ ኋላ ሳይሉ ሲጠይቁ ቆይተዋል። ዛሬም ትምህርታቸውን አጠናቀው ከዩኒቨርሲቲው በክብር ሲወጡ እንኳ፣ ያንንኑ የፍትህ እና የመብት ጥያቄ እያሰሙ፣ ለእምነታቸው ዘብ እየቆሙ መውጣታቸው ምን ያህል ለዲናቸው ክብር ቀናዒ እና ጽኑ እንደሆኑ ያሳያል። ትምህርትን አጠናቆ ዲግሪ መቀበል ብቻ ሳይሆን፣ እስከ መጨረሻው ሰዓት ድረስ ለሃቅ እና ለፍትህ ፊት ለፊት መቆም ትልቁ ምረቃ መሆኑን ዛሬ በተግባር አሳይተውናል። ስለሆነም ዛሬ የታሰሩት ለእውነት፣ ለዲናቸው ክብር እና ለእህቶቻቸው መብት ነውና በእነሱ እጅግ ልንኮራ ይገባል።
ይህንን የደስታ እና የጽናት ጊዜ እያከበርን፣ ቀጣዮቹን ጀግኖች እና የጀመዓችንን ምሰሶዎች ማመስገን እወዳለሁ፦
● ዛሬ ታላቅ ጀግንነትንና ጽናትን ያሳያችሁ ወንድም እና እህቶቼ፦ ዛሬ የታሰራችሁት ለእውነት ነው። ታሪክ የማይረሳዉን ደማቅ አሻራ ጥላችኋል፤ አላህ ምንዳችሁን በላጭ አድርጎ ይክፈላችሁ። ሁሌም አንገታችሁን ቀና አድርጉ፣ ደስተኞች ሁኑ፤ በጀነት ጸጋም ተካፋይ ያድርጋችሁ።
● የህብረቱ ፕሬዝዳንት - ማህፉዝ ነጋሽ፦ እንኳን ደስ ያለህ! በፈተና እና በውጣ ውረድ ውስጥ ሆነህ ጀመዓዉን በጥበብ እና በብልሃት ስትመራ ቆይተሃል። ለእኔም ሆነ ለሌሎች በ5 ኪሎ እና በህብረቱ የመሪነትን እና የጽናትን ትምህርት አስተምረኸናል።
● የህብረቱ ምክትል ፕሬዝዳንት - አብዱልሀሚድ አህመድ፦ የመስጂዳችን ኢማም እና ኡስታዛችን በመሆንህ፣ ለጀመዓው ያበረከትከው አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛ እና የተባረከ ነበር፤ እንኳን ደስ ያለህ።
● የህብረቱ ጸሐፊ - ዘይድ ሳዲቅ፦ እንኳን ደስ ያለህ ወንድሜ! የጀመዓው ደጋፊ እና የጀርባ አጥንት ነህ። በስራህ ታታሪ፣ ደከመኝ የማታውቅ ጀግና ነህ። በ4 ኪሎ ኢማምና አስቀሪ በመሆን ላሳለፍከው ጊዜ አላህ ስራህን ይቀበልህ።
● የ5 ኪሎ ተመራቂ ወንድም እና እህቶቼ፦ በተለይ በጀመዓ ተሳትፎ ላይ የነበራችሁ አንዋር፣ አብዱልፈታህ፣ ኡመር፣ ሐያት፣ ሆረኒየስ፣ ሂክማ፤ እንዲሁም አስቀሪዎቻችን ሙሐመድ በሺር፣ ካሊድ፣ ሀኒም፣ ሳራ... ሁላችሁንም እንኳን ደስ አላችሁ! አላህ ስራችሁን የተባረከ ያድርግ።
በኒቃብ ጉዳይ ላይ ስታግሉ ለቆያችሁ፦ ወንድሞች (አብዱረህማን እና ሌሎችም) እና እህቶች (ሃሊ እና ሌሎችም) የዛሬው ትግል የናንተ የትናንት ተጋድሎ ፍሬ ነው። ላደረጋችሁት ጽናት ምስጋናችን ይድረሳችሁ።
● በ6 ኪሎ ዶርም አብረን ላሳለፍናቸው ወንድሞች፦ አሚር፣ አቡበከር፣ አብዱልሀሚድ፣ ሰልማን እና ሌሎችም፤ አላህ ደስታችሁን እጥፍ ያድርግላችሁ።
የዛሬው የምረቃ ቀን የትግላችን ማብቂያ ሳይሆን፣ በየትኛውም የህይወት መስክ ዲናችንን እና መብታችንን ለማስከበር በጽናት የምንነሳበት አዲስ ምዕራፍ ነው። የተፈጠርንበትን ዋና ዓላማ እያስታወስን ለዲናችን እና ለኡመተል ኢስላም ጠቃሚ ስራዎችን ለመስራት አላህ ያብቃን።
በአጠቃላይ በሁሉም ካምፓስ የምትገኙ ተመራቂዎች፣ አላህ ለስኬት ያብቃችሁ።
Congratulations!
🎉🎉🎉🎉🎉🎉
✍️ ወንድማችሁ ሙሐመድ ኢድሪስ
ከታሰሩት ወንድሞች መካከል ከአንዱ የተላለፈ መልዕክት፦
"አልሐምዱሊላህ! የማይረሳን የምርቃት ፕሮግራም አሳለፍኩ። የምቆጥረው፣ የማስታውሰው፣ ለልጆቼ የምነግረውን ታሪክ አገኘሁ። አላህ ሙዚቃ እና ጫጫታ ከበዛበት መድረክ አርቆ ስለመብቴ፤ ስለአኼራዬ እየተሟገትኩ እንድውል አደረገኝ። አዲስ አለም፤ አዲስ ልምድ እንዳገኝ አደረገኝ። "የምትለብሱት ሪቫን ላይ የፈለኩት መልዕክት መቀመጥ አለበት።" - በሚል ክስ መታሰራችን ስላቅ ቢሆንም ከሐቅ ጎን ሆነን ስለታሪካዊው ሀላፊነታችን መቆማችን ደግሞ መታደል ነበር። አላህ ፍትሁን ያምጣ። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!"
@aaumsu
ታላቁ የቲክቶክ መድረክ ደረሰ _ ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ! ! !
ስለኒቃብ መጠየቅ በምርቃት ቀን እስከ ማሳሰር ከመድረሱ በፊት ጀምሮ ስላለው የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ በሰፊው ይዳሰሳል። ሕገ- መንግስቱን ጥሰው ስለሚጥሱት መብት ሕጋዊ ቦታ በሰፊው ይተነተናል። ከእኛ ስለሚጠበቀው ነገርም በደንቡን ውይይት ይደረጋል።
ሙባረክ አደም፦ በድምፃችን ይሰማ የመብት ትግል እንቅስቃሴ ፈርቀዳጅ ታጋይ፤ አክቲቪስት፤ ቲክቶከር፤ ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብዕና፤ የሂባ ፋውንዴሽን መስራች ነው። ፕሮግራማችንን በመድረክ መሪነት የሚያስተናብርልን ይሆናል።
ሙስጠፋ ሺፋ፦በድምፃችን ይሰማ የመብት ትግል እንቅስቃሴ ወቅት ለታሰሩት ጠበቃ ሆኖ አገልግሏል፤ አሁንም በጥብቃና ሙያው አንቱታን ካተረፉ ባለሙያዎች መካከል ነው። ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ሕጋዊ መሠረት ያብራራልናል።
የሕያ ኢብኑ ኑሕ፦የንፅፅር ትምህርት መምህር፤ የሒዳያ ኢስላማዊ ማህበር መስራች እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብዕና ነው። ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ ያብራራልናል።
ሁሴን ዩሱፍ፦የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፀሐፊ ሲሆን ከማን ምን ይጠበቃል የሚለውን በዝርዝር ያስቀምጣል።
መቅረት አይታሰብም። ጀመዓዎች በቻናሎቻችሁ ላይ አሰራጩት። ሁሉም ለሁሉም ያድርስ። በአንድነት በአንድ መድረክ ተሰባስበን ስለመብቶቻችን እውቀትን እንጨብጥ።
🗓 ቀን፡ ሰኞ፣ ሰኔ 22 (Monday, 29 June)
⏰ ሰዓት፡ ከምሽቱ 03፡00 ሰዓት
እውቀትን መፈለግ መብት ነው፤ እምነትንም በክብር መተግበር እንዲሁ!
የቲክቶክ ገፃችንን Follow በማድረግ ዝግጅቱን ይጠብቁ፦
https://www.tiktok.com/@aaumsu
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
ኒካህ፤ ምርቃት እና እስር በአንድ ቀን!!
በዛሬው እለት 20/10/2018 ዓ,ል ወንድማችን ፋህሚ ናሲር…ከኢኮኖሚክስ ዲፓርትመንት በተመረቀበት እለት በጌታችን አላህ ፈቃድና ውዴታ ከዚሁ ዲፓርትመንት ተመራቂ ከሆነችው እህታችን ኢክራም ሱለይማን ጋር ኒካሃቸውን አድርገዋል።
ወንድማችን በዛሬው ዕለት "ሪቫናችሁ ላይ ሎጎዬ የለም" በሚል ዩኒቨርሲቲው እንዲታሰሩ ካደረጋቸው ወንድሞች ነበር።
በአንድ ቀን ምርቃትንም፤ ትዳርንም፤ እስርንም አስተናግዷል። አሏህ ትዳራችሁን የኸይር ሁሉ መፍለቂያ ያድርገው። ለኢስላም መስዕዋት በመሆን እንደተጀመረው በዚህ ትዳር የሚወለዱ ልጆች የዑመር አይነት የዲን ታጋዮች ያድርጋቸው።
🎉بارك الله لكما وبارك عليكما وجمع بينكما في خير 🎉
@aaumsu
"በሪቫናችሁ ላይ ሎጎዬ መኖር አለበት።" - በማለት ሙስሊም ተማሪዎችን በምርቃታቸው ቀን ከእስር ቤት ያቆየው ከአለም የመጀመሪያው ዩኒቨርስቲ ማን ነው?!
+1
አሶሳ ላይ መብት የሆነው ኒቃብ አዲስ አበባ ላይ ወንጀል የሚሆነው በምን አግባብ ነው?!
አሶሳ ዩኒቨርስቲ ኒቃብ ለብሰው ተምረው ከፍተኛ ውጤት ያመጡትን ተማሪዎች ኒቃባቸውን እንደለበሱ ያስመርቃል፤ ይሸልማል። አንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ደግሞ ኒቃብ ለብሰው ሲማሩ ችግር ይፈጥራል፤ ሊመረቁ ሲመጡ ያሳስራል።
በአሶሳ ዩኒቨርስቲ ዩኒቨርስቲ ከHealth Science ከፍተኛ ውጤት ያመጣችዋ ኢማን ዲልሰባ በወርቅ ሜዳልያ ስትመረቅ፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያሉ ኒቃቢስቶች ደግሞ ኒቃብ መብት ነው ብላችሗል ተብለው ከእስር ቤት ውለዋል።
አሶሳ ላይ መብት የሆነ አዲስ አበባ ላይ ወንጀል የሚሆነው በምን አግባብ ነው?! ምንም ልዩነት የለውም። ልዩነት የአመራሮቹ ነው። የአመራሮቹ አስተሳሰብ፤ የአመራሮቹ ሙስሊም ጠልነት ነው። ሆኖም ግን አይቀጥልም። ፍትሕ ይሰፍናል።
የታሰሩት ሙሉ ለሙሉ ተፈተዋል።
ዝርዝሩን ይዘን እንመለሳለን።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
+2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተመራቂ ተማሪዎች ታሰሩ ! ! !
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች ምረቃ ፕሮግራምን እያካሄደ ባለበት ወቅት በምርቃታቸው ቀን የመረጡትን፤ የሚያስደስታቸውን፤ የምርቃት ቀኔ መልዕክት ይሁን ያሉትን በሪቫን እና ባይንደር ላይ አሳትመው ባሉበት እና የደስታ ቀናቸውን እያሳለፉ ባለበት ወቅት የግቢ በር አካባቢ ላይ ሳሉ 10 ገደማ ልጆችን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስደዋል። እንደ ምክንያትም "ሪቫኑ ላይ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሎጎ የለም!" - የሚልን አቅርበዋል።
ይህ ፈፅሞ ትክክል ያልሆነ፤ የተማሪዎችን ነፃነት የሚጋፋ፤ የደስታ ቀናቸውን የሚያደፈርስ እና ከአንድ አንጋፋ ዩኒቨርስቲ የማይጠበቅ እኩይ ተግባር ነው። መሠል የሙስሊም ተማሪዎችን ነፃነት የሚጋፋ ተግባር ኒቃብ መልበስን በመመሪያ ከመከልከል ጀምሮ እየተደጋገመ ያለና ጥሩ ወዳልሆነ አቅጣጫ የሚያመራ ነው።
ስለሆነም የታሰሩት ሙስሊም ተማሪዎች በቶሎ ተፈተው ወደ ቤተሰባቸው እንዲመለሱ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ እንጠይቃለን።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !!!
+2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተመራቂ ተማሪዎች ታሰሩ ! ! !
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች ምረቃ ፕሮግራምን እያካሄደ ባለበት ወቅት በምርቃታቸው ቀን የመረጡትን፤ የሚያስደስታቸውን፤ የምርቃት ቀኔ መልዕክት ይሁን ያሉትን በሪቫን እና ባይንደር ላይ አሳትመው ባሉበት እና የደስታ ቀናቸውን እያሳለፉ ባለበት ወቅት የግቢ በር አካባቢ ላይ ሳሉ 10 ገደማ ልጆችን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስደዋል። እንደ ምክንያትም "ሪቫኑ ላይ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሎጎ የለም!" - የሚልን አቅርበዋል።
ይህ ፈፅሞ ትክክል ያልሆነ፤ የተማሪዎችን ነፃነት የሚጋፋ፤ የደስታ ቀናቸውን የሚያደፈርስ እና ከአንድ አንጋፋ ዩኒቨርስቲ የማይጠበቅ እኩይ ተግባር ነው። መሠል የሙስሊም ተማሪዎችን ነፃነት የሚጋፋ ተግባር ኒቃብ መልበስን በመመሪያ ከመከልከል ጀምሮ እየተደጋገመ ያለና ጥሩ ወዳልሆነ አቅጣጫ የሚያመራ ነው።
ስለሆነም የታሰሩት ሙስሊም ተማሪዎች በቶሎ ተፈተው ወደ ቤተሰባቸው እንዲመለሱ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ እንጠይቃለን።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !!!
ይህ የጥያቄ አለን ትውልድ ነው። የሙስሊም ተማሪዎች መብት እስኪከበር ላያርፍ ቃልኪዳን ያሰረው።
ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
Congratulations!
ሲትራ በድሩ (economist,reader and entrepreneur )ና ኢክራም ሰኢድ (social worker, avid reader, and writer)
ከዚህ ምርቃት ቀን ቀድሞ የተሰጣችሁ ተሰጥኦ ባለቤቶች እንኳን ደስ አላችሁ :: አላህ የጀመራችሁትን ጎዳና ሁሉ ካሰባችሁት በላይ እጅግ ምቾት የበዛበት ያድርግላችሁ :: ያሰመራችሁት መስመር የሁለት አገር ስኬት ላይ የሚያደርሳችሁ ይሁን :: እናንተ ከዚህ እንድትደርሱ ሰበብ ለሆኑት ቤተሰቦችአችሁ የደስታቸው ሰበብ ያድርጋችሁ ::
እንኳን ደስስስ አላችሁ!
እንኳን ደስስስ አላችሁ!!
እንኳን ደስስስ አላችሁ!!!
✍️ ኡስማን አሊ
እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ማስተላለፍ የምትፈልጉ የጀመዓችን አባላት በ @Aaumuslimstudentsunion1 በኩል ላኩልን።
@aaumsu
Look at the image
በዛሬው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምርቃት ፕሮግራም ላይ ነው
ሪባኑን ተመልከቱት
ባይንደሩን ተመልከቱት
"She will wear her nuqab, She will also attend her education --- እንደለበሰች ትማራለች። We have a question, and we want an answer --- ጥያቄ አለን መልስም እንፈልጋለን።" - የሚል መልዕክት ነው።
በሁሉም ቦታ ስለመብታችን እንጠይቃለን። መጠየቅም ሆነ መልበስ መብታችን ነው። ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣም እንጠይቃለን።
የኔ ዕንቁ እና ጀግና እህት❤️
ነኢማ ሀሰን 🥰🥰( Law)
Be bzuu tgl ena wta wred alfesh zare lezi qen labeqash geta msgana ygebaw botaw lai megegnet balemechale yqrta teyqalew destash destaye new yene wuddd Allah bemenegdsh hulu yketelsh hulem kef beylgn🫶🫶🫶🫶
Ke AAU last year ምሩቅ እህትሽ ከወደ ወሎ congra bedgame
እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ማስተላለፍ የምትፈልጉ የጀመዓችን አባላት በ @Aaumuslimstudentsunion1 በኩል ላኩልን።
@aaumsu
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
