فریب کلاهبرداران را نخورید! تلمتریو این کانالها را شناسایی و برچسبگذاری میکند 👉 برای مشاهده برچسب، اشتراک تهیه کنید 👈
ከፍልስፍናው ጎራ <<❓>>
<<ደስታን ምን እንደሚያካትት መፈለግህን ከቀጠልክ ፈጽሞ ደስተኛ አትሆንም..! የሕይወትን ትርጉም እየፈለግህ ከሆነ ፈጽሞ ሕይወትህን አትኖርም..! >> አልበርት ካሙ ለማስታወቂያ ሥራ➝ @Naolviva
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ከፍልስፍናው ጎራ <<❓>>
کانال ከፍልስፍናው ጎራ (@phylosophy_gora) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 36 870 مشترک است و جایگاه 9 125 را در دسته ایراتیک و رتبه 901 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 36 870 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 14 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -394 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -17 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 1.84% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 0.59% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 677 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 216 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 13 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“<<ደስታን ምን እንደሚያካትት መፈለግህን ከቀጠልክ ፈጽሞ ደስተኛ አትሆንም..! የሕይወትን ትርጉም እየፈለግህ ከሆነ ፈጽሞ ሕይወትህን አትኖርም..! >>
አልበርት ካሙ
ለማስታወቂያ ሥራ➝ @Naolviva”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 15 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته ایراتیک تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 15 ژوئیه | +10 | |||
| 14 ژوئیه | +18 | |||
| 13 ژوئیه | +12 | |||
| 12 ژوئیه | 0 | |||
| 11 ژوئیه | 0 | |||
| 10 ژوئیه | 0 | |||
| 09 ژوئیه | +11 | |||
| 08 ژوئیه | +8 | |||
| 07 ژوئیه | +15 | |||
| 06 ژوئیه | +31 | |||
| 05 ژوئیه | 0 | |||
| 04 ژوئیه | 0 | |||
| 03 ژوئیه | 0 | |||
| 02 ژوئیه | +41 | |||
| 01 ژوئیه | +19 |
"ራስህን በትክክል የምትወድ ከሆነ ሌላን የምትጎዳ አይነት ሰው አትሆንም "
/ ጉተማ ቡድሀ / ሰውን ለምን እንደሚጎዱ በሚጠየቁበት ሰአት #ሥለምወደው የሚል ምላሽ የሚሰጡ ሰዎች ስህተተኛ ብቻ ሳይሆን ሀሰተኛም ናቸው ። ሰውን ለመጉዳት የምንነሳው ስለምንወደው ሳይሆን የወደድነውን የራሳችን ብቻ ለማድረግ የሚገፋን ራስወዳድነት ሥለሚጫወትብን ነው።
፧
የወደድከው ነገር ሁሉ ያንተ ካልሆነ አጥፋው የሚል ስሜት ውስጥህ ካለ...ስሜትህ ውሸት ነበር ማለት ነው። ፍሬ ከናፍር እወደዋለሁ ያልከው ነገር ያንተነቱን እንጂ እሱነቱን አልወደድከውም ማለት ነው...። አንድን ነገር ስትወደው ተፈጥሮውን አድንቅለት...ነፃ አድርገው በቃ! ያንተ መሆን ያለመሆንን ምርጫ ለሱ ብቻ ተውለት...አንተ የመኖር መብት እንዳለህ ሁሉ የምትወደው ነገርም የመኖር መብት አለው...አንተ የመምረጥ መብት እንዳለህ ሁሉ የወደድከውም የመምረጥ መብት አለው...እዚህ መሀል ማስገደድ ካለ መውደድ የለም...!!
፧
የራስህን አስተሳሰብ ስርአት ባላስያዝክበት ሁኔታ ሌላ ላይ ጣትህን ለመጠቆም እንደማትበቃው ሁሉ ራስህን መውደድህን በትክክል ባላረጋገጥክበት ሁኔታም ሌላን ልትወድ አትችልም ። የፍቅርን ትርጉም የማያውቅ እና ራሱን አፍቅሮ የማያቅ ሰው...ሥላፈቀርኳት የሌላ ሆና ማየት ሥለማልሻ አጠፋኋት ሲል ባደባባይ ይዋሻል...ራስህን አትዋሽ...!!
በትክክል ራሱን የሚወድ ሌላን የሚጎዳ ስብዕና የለውም...!!
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን..!😊| 2 | - አንተ ሰው ከየት መጣህ?
- ከግብጥ
- ምን ይዘህ?
- ጭብጥ ጥጥ
- በምን አስረህ?
- በድጋይ ልጥ
- ይህስ ሰው ዋዘኛ ነው!
- ዋዘኛስ ክራር ነው
- ክራርስ ጥዝ ጥዝ ባይ ነው
- ጥዝ ጥዝ ባይስ ንብ ነው
- ንብስ ነዳፊ ነው
- ነዳፊስ ደጋን ነው
- ደጋንስ ጠማማ ነው
- ጠማማስ መንገድ ነው
- መንገድስ ወሳጅ ነው
- ወሳጅስ ውሃ ነው
- ውሃስ ብም ብም ባይ ነው
- ብም ብም ባይስ ጎሽ ነው
- ጎሽስ ዘላይ ነው
- ዘላይስ ፌቆ ናት
- ፌቆ ስትዘል አግኝቼ በልቼ መጣሁ
- ሰባች ጎፈየች?
- ሳትታረድ መጣሁ
- የሆነስ ሆነና ስምህ ማን ነው?
- ላገር አይመች
- ማን አወጣልህ?
- ጎረቤቶች
- የናትህ ስሟ ማን ነው?
- ሳልወለድ ሞተች
- የሆነስ ሆነና እግዚሀርን አይተኸዋል አላየኸውም?
- አዎን አይቸዋለሁ
- ቀይ ነው ጥቁር?
- ተከናንቦ ነበር
- ረጅም ነው አጭር?
- ቁጭ ብሎ ነበር
ስብሀት
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊 | 652 |
| 3 | አስቄአቸው የማላውቅ እኔ ነኝ። ሲያወሩልኝ መስማት ብቻ። የሚወዱኝም በዚህ ነው። "እሱ ሰው ሲናገር ማቋረጥ አይወድም" እባልና። እኔ ግን ማውራት ስለሚደክመኝ ነው አፍ ፣ጥርስ፣ምላስ፣አገጭ፣ ጠቅላላ የፊት ጡንቻ፣ዐይኖች፣ግንባር፣እጅ ወዘተ....እነኝህን ሁሉ በአንድ ጊዜ አነቃንቄ ከእኔ ወደ ሌላ ሰው መረጃ ማስተላለፍ አድካሚ ነገር ይሆንብኛል። ያለማውራቴ ምክንያት ግን በተለያዩ ሰወች የተለያየ ትርጉም ይሰጠዋል:-
አክስቴ: "መልኬ በቃኝ ብሎ ነው"እያለች ታሽሟጥጠኛለች። የወጣልኝ አጎዶ።
አባባ: "ጨዋ ጨዋነት ነው" ይላሉ
ጋሸ: "ትዕቢት ፤ ትዕቢት ነው" ይላል
ጓደኛዬ: "መደበር ይወዳል ፣ ደባሪ ነው"ይላል
የጓደኛዬ ሴት ጓደኛ : ኩራት። ኩራት ነው። ሲበጣጠስ" ትላለች
የጋሸ ሚስት: ፍርሐት ፣ ፍርሐቱ ነው" ትላለች
ብቻ ሺህ ትርጉም ይሰጠዋል።
(ህማማትና በገና)
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊 | 636 |
| 4 | "በድሮ ጊዜ ቀስት ሲሰራ ቂጡ ላይ ለሚዛን ላባ ይገባለታል፡፡ እና አንድ ጭልፊት ጎኑን በቀስት ተመቶ ከሰማይ ላይ እየወደቀ እያለ ዞር ብሎ የተወጋበትን ቀስት ሲያይ፤ የራሱን ዐይነት ላባ ተሰክቶበት አየ፡፡ ገባህ? በወገንህ እጅ እንደ መጥፋት ቀላልና ከባድ ነገር የለም ማለት ነው፡፡"
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊 | 647 |
| 5 | መዝሙረ ሄላም... | 879 |
| 6 | بدون متن... | 1 |
| 7 | ተስፋ
ተስፋ የመኖር ምክንያት ነው።ሰውን እንዲኖር የሚያደርገው ወይም የሚገፋው መለወጥ አለመለወጡ ሳይሆን የመለወጥ ተስፋው ነው።ቢሆንም ግን ህይወት ተከታታይ መሆኗን መገንዘብ ይጠቅማል።ዛሬ የምኖረው በትናንት ምክንያት ነው።
📓አለመኖር
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን..!😊 | 904 |
| 8 | <<የዘመኑ ወጣት የአእምሮ በር የለውም። ቢኖረውም የሚያስወጣ እንጂ የሚያስገባ አይደለም። ከራሱ ዓለም ሐሳብ አውጥቶ >> ያልኩት ካልሆነ ይላል እንጂ የሌላውን ሐሳብ አይመዝንም። ሲወለድ ጀምሮ ሁሉን አውቆ የተፈጠረ ይመስለዋል። <<ያለ ብዙ ችግር ያገኘውን እውቀቱን ተፎካካሪ የሌለው ኃይል ያደርጋል። በትንሽ እውቀት ብዙ ነገር ፈታትቶ የሚገጣጥም ይመስለዋል።>>
(ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ)
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊 | 1 310 |
| 9 | ጦርነት እየተካሄደ የሚያርስ ገበሬ "ለማን ነዉ?" ሲሉት "አላህ ለሰጠዉ ይሰጣል እኔ ከደረስኩበት እበላለሁ ካልሆነ ደሞ የሚመጡት ይበሉታል" አለ አርሶ ባዶ መሬት ከመተዉ ከዚህ በላይ ምን አሪፍ ሰዉ አለ
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊 | 1 295 |
| 10 | ሦስቱ ሴቶች የዘላለም መቆያቸው ሲኦል ይሁን መንግስተ ሰማይ ለማወቅ የተረኛ መላዕኩን ምዘና እየጠበቁ ነው።
የመጀመሪያዋ እንስት ቀረበች። በምድር ህይወቷ መነኩሲት ነበረች።
ተረኛው መላዕክ " በምድር ሳለሽ ምን ያህል ግዜ ዘሙተሻል ?" ይላታል።
"አንዲትም ግዜ አልዘሞትኩም። ገዳም የገባሁትም እንዲሁ እንደተፈጠርኩ አንዳች ነገር ሳላጎድል ነው። እዛም የሚፈታተነኝ ቢበዛም ግን ተወጥቼዋለሁ።"
መላዕኩም " ማነህ የ መንግስተ ሰማያትን ቁልፍ ስጣት።" በማለት ትዕዛዝ አስተላለፈ።
ሁለተኛዋ ቀረበች
"በምድር ህይወትሽ ምን ያህል ግዜ ዘሙተሻል?"
"አንዳችም አልዘሞትኩም። ለአቅመ ሄዋን ስደርስም በወግ ማዕረግ ተዳርኩ። ከባሌ ጋር አራት ልጆች ወልደናል። ከአራት ግዜ ውጪ ከባሌም ከማንም ተነካክቼ አላውቅም።"
" የመንግስተ ሰማያትን ቁልፍ ስጣት" አለ መላዕኩም
ሦስተኛዋ ቀረበች ። እጅግ የሚያምር አቋምና መልክ አላት። ንቃትና በራስ መተማመኗም የላቀ ነው። ጡቷን በከፊል የሚያሳይ የሙት ልብስና የዳሌዋንም አስደንጋጭ ውበት የሚያጎላ ፒንክ ታይት ለብሳ ነበር።
ተመሳሳይ ጥያቄ አቀረበላት
"በጣም በልጅነቴ ስለጀመርኩ ልከኛ ቁጥራቸውን በግልፅ አላውቀውም። ግን በምድር ህይወቴ ሳለው የወሲብ ቪዲዮ እሰራ ስለነበር ቢያንስ በሁለት ቀን አንዴ የግድ እዘሙታለሁ።"
መላዕኩ እያያት ምራቁን ሲውጥ የምራቁ ጉምጉምታ ሰማየ ሰማያት ተሰማ።
ከምራቁ እየታገለም እንዲህ አለ።
"ማነህ የክፍሌን ቁልፍ ስጣት!!"
ማስታወሻ: ለአሁናዊ የግል ህይወቱ ደህንነት ሲባል የመላዕኩ ስም አልተጠቀሰም።
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊 | 1 338 |
| 11 | ሕይወት ዘላለማዊ ናት፣ አለመኖርን እንድንኖር ምርጫ እንኳን አልተሰጠንም አብዛኛው ሰው ሞት አለመኖር ይመስለዋል በተቃራኒው ግን ሞት ማለት መለየት ብቻ ነው ደግሞም ድልድይ ነው ወደ ትክክለኛ ሕይወት፤ | 1 191 |
| 12 | ሩሲያ ውስጥ የሚማር የሌላ ሃገር ዜጋ አንድ ተማሪ እንዲህ ይላል፦
"በሩሲያ ውስጥ ለአብዛኞቹ ፈተናዎች ከፍተኛው ውጤት 5 ነው ፡፡ አንድ ተማሪ ማንኛውንም ጥያቄ ካልመለሰ እና የፈተና ወረቀቱን ባዶውን ከመለሰ፣ ከ5 ውስጥ 2 ያገኛል። በሞስኮ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ቀናት ውስጥ ስለዚህ ስርዓት አላውቅም ነበርና በመገረም ዶ / ር ቴዎዶር ሜድራቭን ጠየቅኩ፦
“አንድ ተማሪ ማንኛውንም ጥያቄ ሳይመልስ እርስዎ ከ5 ውስጥ 2 ሲሰጡት ይህ ፍትሃዊ ነው? ለምን ዜሮ አይሰጡትም? ትክክለኛው መንገድ እንደዚያ አይደለምን?"
መምህሩ ሲመልሱ፦
"ለሰው ልጅ ዜሮን እንዴት መስጠት እንችላለን? ሁሉንም ትምህርቶች ለመከታተል ከጠዋቱ 1 ሰዓት ለሚነሳ ሰው ዜሮ እንዴት ልንሰጠው እንችላለን? በዚህ በቀዝቃዛ አየር ከእንቅልፉ ተነስቶ፣ የህዝብ ማመላለሻን ተጠቅሞ፣ ፈተናውን በወቅቱ ለማከናወን በመድረሱ እና ጥያቄዎቹን ለመፍታት ሞክሮ እንዴት ዜሮ እንስጠው? ብዕር፣ የማስታወሻ ደብተር፣ የጥናት ኮምፒተር ገዝቶ ለብዙ ሌሊቶች ላጠና ሰው እንዴት ዜሮ እንሰጠው ?? ሌሎች የሕይወት ዘይቤዎችን ሁሉ ትቶ ትምህርቱን ሲከታተል ለከረመ ተማሪ እንዴት ዜሮ ልንሰጠው እንችላለን? ልጄ! እዚህ አንድን ተማሪ መልሱን ባለማወቁ ብቻ ዜሮ አንሰጠውም፡፡ እኛ ቢያንስ ይህ ሰው ነው ፣ እናም አንጎል አለው የሚችለውን ሞክሯል የሚለውን እውነታ ለማክበር እንሞክራለን፡፡ ምክንያቱም እኛ የምንሰጠው ውጤት በፈተና ወረቀቱ ውስጥ ላሉት ጥያቄዎች ብቻ አይደለም ፣ ይህ የሰው ልጅ ስለሆነ እና ነጥብ ማግኘት ለሚገባው ተማሪ እውነታ አድናቆት እና አክብሮት ማሳየትም ጭምር ነው።"
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊 | 1 342 |
| 13 | እግርህ ስር የሚያደናቅፍህ ድንጋይ ተቀምጦ ዓይንህን ከድንጋዩ ለማሸሽ ብትሞክር ራስህን ማታለልህ በቅፅበት ይገለጥልሀል። ድንጋዩ የሚመታው ዓይንህን ሳይሆን እግርህን ነዋ! ብዙዎች ራሳቸውን በማታለልና በመሸንገል መንገድ ሲሄዱ እውነት እያሰናከለች ስትጥላቸው የምንመለከተውም ለዚህ ነው!
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊 | 1 230 |
| 14 | ቼ_በለው_Teshome_Mitiku_Che_Belew_ተሾመ_ምትኩ.m4a | 1 271 |
| 15 | ከአልፎሂያጁ ማስታወሻ የተቀነጨበ
(በእውቀቱ ስዩም)
በቀደም እኛ ሰፈር እሚገኘው መሬት አስተዳደር ቢሮ ጎራ አልሁ ፤
ከአስተዳዳሪው ጠረጴዛ ላይ፥ ሜትር፥ ችካልና በሶስት ጎድጓዳ ሳህኖች የተቀመጠ ናሙና አፈር ተደርድሮ ይታያል፤
“ምን እንርዳዎ ?” አለኝ አስተዳዳሪው፤
“ የሆነች ቀለል ያለች አምስት ሺ ካሬ መሬት ፈልጌ ነበር “
“የገበሬ መሬት ነው የፈለጉት?”
“ የወዛደርም ቢሆን አይደብረኝም፤”
“ አዝናለሁ ፤ ለጊዜው የሚሸጥ መሬት የለንም’
’
“ እኔም የሚሸጥ ሳይሆን የሚሰጥ መሬት ነው የምፈልገው “
“ምንስ ስለሆንክ ነው ላንተ መሬት የሚሰጥህ ?”
ሰውየው ካንቱ ወደ አንተ የተሸጋገረበት ፍጥነት አስደነቀኝ ፤
‘ እስካሁን ለናት አገሬ ካደረግሁት አስተዋጽኦ አንጻር ፤ መሬት ብቻ ሳይሆን ፥ የአየር ክልል ቢሰጠኝ አይበዛብኝም”
ሰውየው ዘበኞችን ለመጥራት ስልኩን ሲያነሳ፥ ወደ መስኮት እየጠቆምኩ፥
“ እዛ ማዳ ታጥሮ የበሰበበሰ መሬት ምን ይሰራል ?”
“የወጣቶች የስራ ፈጠራ ማእከል ልንገነባበት ነው” አለኝ ፤
“ ከገነባችሁ በሁዋላስ?”
“ አልባሌ ቦታ የሚውሉ ወጣቶች ወደ ማእከሉ እንዲገቡ ይደረጋል “
“እሺ አልባሌውን ቦታ ለኔ ስጡኝ “
2
በቀደም እኛ ሰፈር እኛ ሰፈር አስፋልት ዳር ያለ ስጋ ቤት ባለቤት ጫማ ያስጠርጋል፤ እኔ ወረፋ እየጠብቅሁ ነው፤
“ ቅድምኮ የግብረሀይሉ አባላት ሱቄን በሜትር ለከትውት ሄዱ” አለ ስጋ ሻጩ ፤
“ አይይ ! ሊያፐርሱት ነው ማለት ነው” አለ ሊስትሮው ፤
“ ሊያፈርሱት እንደሆነ በምን አወቅህ ?”
“ ታደያ በሜትር የለኩት ልብስ ሊያሰፑለት ነው?”
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊 | 1 391 |
| 16 | ሁላችንም የሰራናቸውን ስህተቶች ለምን እንደፈፀምናቸው በቂ ምክንያት ለመስጠት እና ለማስረዳት የምንጠቀምበት ሀይል፣ትክክለኛ ነገሮችን ለመስራት ከምናውለው መብለጡ አስገራሚ ነው፡፡ | 987 |
| 17 | አንዴ ጓደኛዬ ራሴን አጠፋለሁ ብሎ ተነሳ፡፡ ሁሉም
ይመክረው
ጀመር፡፡ ግን እሱ አሻፈረኝ አለ - ራሴን አጠፋለሁ አለ፡፡
ቤተሰቦቹ
ጨነቃቸው፡፡ አባቱ እየሮጡ መጡና፣ “ይሄን ልጅ
አልቻልነውም፤
ከእኛ አቅም በላይ ሆኗል…” አሉኝ፡፡ አባቱ አይወዱኝም ነበር
አሁን
ግን “ያለው ብቸኛ አማራጭ ይሄ ነው” ብለው አስበዋል…
“ችግር የለውም እመጣለሁ” አልኳቸው፡፡
ቤታቸው ሄጄ ነገሩን ከሰማሁ በኋላ “ይሄውልህ…” አልኩት፣
“ሐሳብህ በጣም ጥሩ ነው፡፡ ትክክል ነው ብዬ አላስብም፡፡
ቢሆንም ግን ራሴን አጠፋለሁ ብለህ ከተነሳህ መቼስ ምን
ማድረግ እችላለሁ፡፡ ጓደኛዬ ስለሆንክ ረዳሃለሁ፡፡ ራሴን
ካላጠፋሁ ካልክ - ጥሩ !!
ውሳኔህ ትክክል አይመስለኝም ምክንያቱም እኔ ባንተ ቦታ
ብሆን
ጨርሶ ራሴን አላጠፋም ነበር፡፡ ምክንያቱም ሞኝነት ነዋ፡፡
አንዲት
ሴት እምቢ ስላለችህ ራስህን ታጠፋለህ ? በሚሊየን
የሚቆጠሩ
ሴቶች እያሉ አንዲት ሴት እምቢ አለችኝ ብለህ ራስህን
ማጥፋት
ተገቢ ውሳኔ አይደለም፡፡
በወር ውስጥ ረስተሃት ሌላ ማፍቀርህ አይቀርም ነበር፡፡ ግን
ራሴን አጠፋለሁ ካልክ ምን ማድረግ ይቻላል … ጥሩ !!
የራስህ
ሕይወት የራስህ ነው…”
አባትዬው ይህን ሲሰሙ በጣም ተረበሹ፡፡ “ጭራሽ ራስህን
አጥፋ
ትለዋለዋህ እንዴ … እኛ እኮ ያመጣንህ ይሄን ሐሳቡን
ታስተወዋለህ ብለን ነው” አሉ አባትዬው፡፡
“እኛ ምን ስለሆንን ነው የምንረዳው ? እርስዎ ሲወልዱት
ጠይቀውታል እንዴ … ወደዚህች ምድር መምጣት
ትፈልጋለህ
ወይ ብለው ጠይቀውት ነበር ? እና አሁን ለምንድነው ራሴን
ላጥፋ ሲል የምትከለክሉት ? ራሴን ላጥፋ ካለ ፍቀዱለት”
ወደ ቤቴ ይዤው ሄድኩ…
“ና እንሂድ … ራስህን ልታጠፋ አይደለ እስኪ እስከዛው ዘና
እንበል፡፡ እንዝናና፡፡ እስቲ አንድ ለሊት አብረን አናሳልፍ፡፡ እኔጋ
እድር፡፡ ምናልባት የሆነ ቦታ እንገናኝ ይሆናል ምናልባትም
ከዚህ
በኋላ መቼም ላንገናኝ እንችላለን” አልኩት፡፡
እኔ ቤት ሆነን ቀስ በቀስ ማሰብ ጀመረ፡፡ ምክንያቱም እኔ
በምንም
መልኩ ሀሳቡን ለማስቀየር አልፈለግኩም፡፡
“አሁን የሚጮህ ሰዓት እንሙላና እንተኛ…” አልኩት፣ “ሌሊት
10
ሰዓት ሲሆን ተነስተን አንድ የሚያምር ቦታ እወስድሃለሁ፡፡
በጣም
የሚያምር ቦታ ነው፡፡ ከዚያ ቦታ ላይ በቀላሉ ዘልለህ ወንዙ
ውስጥ መፈጥፈጥ ትችላለህ … ከእኔም ጋር እዛው
እንሰነባበታለን”
ልክ 10 ሰዓት ላይ ሰዓቱ ሲጮህ ከአልጋው ጎትቼ ሳስነሳው፣
“አንተ ቆይ ምን አረግኩህ…” አለ ጮሆ፤ “ጠላቴ ነህ ወይስ
ምንድነው ? በቃ ራሴን ማጥፋት አልፈልግም !!!”
“ይሄማ ትክክል አይደለም … አንዴ ወስነህ የለ እንዴ … የምን
መወላወል ነው”
“እንዴ በቃ ራሴን አላጠፋም !!! እንድሞት ፈልገህ ነው …
አልሞትም … በቃ … አልፈልግም … ራሴን አላጠፋም …
ሕይወቴን እወዳታለሁ”
“እምቢ ካልክ አላስገድድህም” አልኩት…
እናም ራሱን አላጠፋም !!! አሁን አግብቶ ልጆች ወልዷል፡፡
መንገድ ላይ ካየኝ መንገድ አሳብሮ ነው የሚጠፋው፡፡
“አሁን ምን ተገኘና ነው” እለዋለሁ መንገድ ላይ ሳገኘው፣
“መቼም አላፈቅርም ብለኸኝ አልነበረም እንዴ … እንደገና
አፍቅረህ አረፍከው !!!”
እሱም እንዲህ ይለኛል፣ “በዕውነቱ እንኳንም ያቺ ልጅ እምቢ
አለችኝ፡፡ ለእኔ አትሆነኝም ነበር፡፡ ታሳብደኝ ነበር፡፡ እኔ አሁን
የተሻለች ልጅ ነው
ያገባሁት …”
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊 | 1 303 |
| 18 | 🙏ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው ለኢድ አል አድሃ [አረፋ] በዓል በሰላም አደረሳችሁ
❤️ EID MUBARAK 🕋
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊 | 1 164 |
| 19 | ብቸኝነት ሲሰማህ ማሰብ ከቻልክ የአሳብህ ጓደኛ ነህ። ማሰብ ካልቻልክ ብቻህን ነህ። መነጠል የስጋ ሳይሆን የአሳብ ስሜት ነው። ብቸኝነትህን አሳብህ ሲጋራ የአሳብ ጓደኛ አለህ። ብቸኝነትም ጓደኝነትም ስጋ አይደለም። የአብሮነትና የመነጠል ስሜት ነው።
ከሰው ጋር ስትሆን ለብቻህ እንደሆንክ ከተሰማህ በግርግር መሀል ብቸኛ ነህ። በስጋህ ብቻህን ሆነህ ከአሳብህ ጋር አብረህ ከሆንክ አንተማ ጓደኛ አለህ። ከቻልክ የወዳጅ አስፈላጊነትን ቀንስ። ሰው ብታጣም ያጣኸው ስጋ ነው። አብሮህ የሆነ አላቂ ነው። ዛሬ የሚቀርብህ ነገ የሚርቅ ነው። ወሳኙ ጉዳይ ህሊናህን አለማጣትህ ነው። የሌላ ስጋ ሲለይ አሳብህ ካንተ ጋር ነው።
.
መለየት የስጋ ነው። ብቻህን እንዳልሆንክ ከተሰማህ የአንተ ጓደኛ ስሜትህ ነው።
©ይስማዕከ ወርቁ
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊 | 1 276 |
| 20 | ተማሪው ረፍዶበት እያለከለከ ወደ ክፍል ሲገባ አስተማሪው በቁጣ ጠየቀው፣
"ለምን አርፍደህ መጣህ?"
" እናትና አባቴ ተጣልተው ነው"
" ታዲያ አንተ ምን አገባህ?"
" እናቴ አንዱን ጫማዬን ፣ አባቴም ሌላውን ጫማዬን ይዘው በኔ ጫማ እየተደባደቡ ስለነበረ ነው"
ባሻዬ! እንዲህ ዓይነት ትግል ነው የገጠመን። በገዛ ጥቅምህና ንብረትህ ላይ ሌላው ይወስንበታል። የዛሬውን የብልጽግና የድጋፍ ሰልፍ እኛም እንድንሳተፍበት ከሥራና ከትምህርት ቀን ውጪ ማድረግ አይቻልም ነበር?
tesfaye hailemariam
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊 | 1 135 |
این محتوا برای کاربران بالای ۱۸ سال در دسترس است
با ورود به سرویس، تأیید میکنید که ۱۸ سال یا بیشتر سن دارید.
