ማጣላ ዋላና ሐዋርያዊት ቤተ-ክርስትያን
رفتن به کانال در Telegram
“በሕይወቴ ሳለሁ ለእግዚአብሔር እቀኛለሁ፥ ለአምላኬም በምኖርበት ዘመን ሁሉ እዘምራለሁ።” — መዝሙር 104፥33
نمایش بیشتر3 440
مشترکین
+124 ساعت
+347 روز
+12430 روز
آرشیو پست ها
😭😭😭😭😭😭😭
በዚያች በቀራንዮ
በፈጠረው ፍጡር የተገረፈበት
ለኔ ሲል እኮ ነው ሕይወትን ለመስጠት
መንገላታት መቁሰልህ መራብ መጠማቱ
ለኔ ነው ገብቶኛል ኢየሱስ የናዝሬቱ /2*
በዚያች በቀራንዮ በጎልጎታ
ጌታዬ ለኔ ሲል ሲንገላታ
ኃይል አለው ኃይል አለው
አላማው በኔ ላይ ፍቅር ነው ፍቅር ነው /2*
እኔን ለመስራት ነው ነጻነት ለመስጠት
ከኃጢአት ባርነት ከሞት ወደ ሕይወት
የተወጋው በጦር የተቸነከረው
መከራ ስቃዩ ዋጋ አለው ለኔ ነው /2*
ኃጢአቴን ሊያነጻ ከእስራቴ ፈቶ
በፈጠረው ፍጡር የእሾህ አክሊል ደፍቶ
ትንሳኤና ሕይወት አለኝታ የሚሆነኝ
የፈሰሰው ደሙ ይችላል ሊያድነኝ /2*
@matalapochurch2
Apostolic Songs
የመስቀሉ ጸጋ
አንተ ምስጋናዬ ነህ 4x
የሱስ ምስጋናዬ ነህ
አንተ ምስጋናዬ ነህ
ጌታ ምስጋናዬ ነህ
አንተ ራስህ ምስጋናዬ ነህ
እያሰብኩኝ ብቻ የማይቀዘቅዘውን የመስቀሉን ፍቅር
እንደማያቋርጥ ምንጭ ይፈልቃል ከውስጤ ገና ብዙ መዝሙር
በጨለማዬ ላይ ብርሃን ያበራ የፅድቅ ፀሐይ
የደህንነቴ ምንጭ ሁሉ የፈለቀብህ ካህኔም ጌታዬ
አንተ ብቻ ነህ ምክንያቴ
ለምስጋና እንዲከፈት አንደበቴ
1) አሰላስላለሁ የመስቀሉን ፀጋ ባልተገባኝ መጠን ብዙ እንደሰጠኸኝ/ብዙ እንደሆንክልኝ/4*
እኔ ጤና እንድሆን ደዌዮን መሸከምህን
እኔ እንዳምርልህ ደም ግባት ማጣትህን
እኔ እንድወደድ መጠላት መገፋትህን
እኔ እንድከብር የተናቅክ መሆንህን
እኔ ቀና እንድል አንገትህን መድፋትህን
እኔን ለማፅደቅ ኃጢአቴን መሸከምህን
የተወጋውን ጎንህን የፈሰሰውን ደምህን
የጠጣኸውን መራራ ያሳለፍከውን መከራ
አልረሳም ይኖራል በልቤ ታትሞ
በአይኖቼ ፊት በጉልህ ተስሎ
የነፍሴ ብርሃን ነህ እያት ስታበራ
በነፍስህ ድካም ጸድቃለችና አሃሃሃሃ ሃሌሉያ
ከዘመርኩኝ አይቀር ለዚህ ፍቅር ዘምራለሁ
ከአመለኩኝ አይቀር ይህን ፍቅር ብቻ አመልካለው
ከተገረምኩ አይቀር በዚህ ፍቅር እገረማለው
ካወራሁኝ አይቀር ይህን ፍቅር ብቻ አወራለው
የወደደኝ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ
በታሪኬ/በሰማይ በምድር እንዳንተ ያለ አላውቅም ጌታ
@matalapochurch2
እልልታ ውዳሴ
New Cover Song!
እልልታ ውዳሴ
ይገባዋል ለጌታ ኢየሱስ ንጉሤ
እልልታ ውዳሴ
ይገባዋል ለጌታ ኢየሱስ ንጉሤ
ሱራፌል በሰማይ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ይላሉ
ለተ ቀን ለስሙ የምስጋናን መስዋዕት ይሰዋሉ
የተፈራ ንጉስ በምስጋና እጅግ የከበረ
ለስሙ የሚቀና ከዘላለም ከጥንት የነበረ
እጽዋት እንስሳት ውብነቱን በግልጽ ያወሳሉ
ተራሮች ባሕሮች የእጆቹን ሥራ ያወራሉ
ከዋክብት ብርሃናትኃይሉን ያንፀባርቃሉ
የሰማይ አዕዋፋት ማለዳ ለክብሩ ያዜማሉ
እኔም የሰው ልጅ በተራዬ ግሩምነቱን ላውጅ ልናገር
ሰፊ ጥልቅ ለሆነው ስለ እጹብ ድንቅ የአምላክ ፍቅር
የአለምን ኃጢአት በስጋው መስቀል ሞትን ሽሮ
ይመስገን ሰቶናል የክብር የመንፈስ ምሪት ኑሮ
መላዕክትም ቢሆን ምንም ደም አልፈሰሰላቸውም
ፍጥረታት የሞት ዕዳ ተከፈለላቸው
እኔም ለኢየሱሴ እራሱን ሰውቶ
ስለዚህ ላክብረው ምስጋና ለኢየሱሴ ላዳነኝ
Via፦ https://youtu.be/1dts7c7Dek8?si=Jkgg0CKptpS4u24R
ሊያስጥል የሚታገል እምነትና ፍቅርን
ተስፋን የሚያሳጣ የዘላለሙን
ከንቱ ሚያደርግብኝ የመዳን ተስፋዬን
አንዱንም አልሰማም ጠላት ሚያወራውን
የተሸከሙኝን ታማኝ እጆቹን
በፍጹም አለቅም ኢየሱስዬን
አልጥልም መዳኔን
ከኢየሱስ ላይ ፍጹም አላነሳም ዓይኔን
የምድሩን ግሳንግስ ከመትረፌ ጋራ
ሃይሉ ችሎታ ከእጁ የፅድቅ ስራ
አላወዳድረውም ኧሬ አይመዘንም
ከዘላለም ህይወት በጭራሽ [በፍጹም] አይበልጥም
ትኩስ ነው መዳኔ የማይቀዘቅዝ
ዋጋው የማይቀንስ የማይደበዝዝ
ማይጎድል ሙላቴ ተስፋና ዕርስቴ
ውበት ሆኖልኛል ኢየሱስን ማወቄ
ጉዳዬ አድርጌ አዎ አጥብቄ ይዤሃለሁ
የመምጣትህን ተስፋ እጠባበቃለሁ
ሲያልፍ በሚረሳ በጊዜያዊ ነገር
በማግኘት በማጣት የማይነጻጸር
ሞት ቢሆን ህይወት እንዳይለየኝ አውቃለሁ
የእርሱ በመሆኔ ተረጋግቼአለሁ
መቼም አይቀልብኝ ኢየሱስን [አምላኬን] ማወቄ
ዋጋዬ ደሙ [ኢየሱስ] ነው ውድ ነው ህይወቴ [መዳኔ]
@Apostolicsonglyrics
@Apostolicsonglyrics
@Apostolicsonglyrics
ሰበር ዜና
ዋራ ቤቴል 2018
12,296 ነፍሳት ለኃጢአታቸው ስርየት በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠምቀዋል።
ክብር ሁሉ ለኢየሱስ ይሁን።
@zemeru
በማስተዋል ዘምሩ
ምስጋና ምስጋና ይለኛል
ዘምር ዘምር ይለኛል
አምልክ አምልክ ይለኛል
ጌታዬ ይገባዋል
እጅግ የበዛውን የእርሱን ምህረት
ማለዳ ማለዳ መቀበል ከእርሱ ፊት
ምስጋናን መጨመር እለት እለት
አስለምዶኛል ለክብሩ መቀኘት
ምስጋና መልካም 3X
አምልኮ መልካም 3X
ዝማሬ መልካም 3X
ድል ማድረጊያ ጎዳና አሃሃ
1 ከማመስገን ጋር በፀሎት
ለሚቆየው በአንተ ፊት
በችግር ውስጥም ላመሰገነህ
አብልጠህ መልካም ታደርጋለህ
ስለ ምህረትህ ስለጥበቃህ ስለውለታህ
ምስጋና መልካም 3X...
በችግር በደስታ በመከራ
ምስጋና መልካም 3X...
2 ወደጉድጓድ ቢጣልም ምስጋና አለ
ተላልፎ ተሽጦም ምስጋና አለ
ፀሎትም ቢዘገይ ምስጋና አለ
ከሚያመሰግን ጋር ኢየሱስ አለ
ምስጋና መልካም....
3 ስለሆነው ብቻ አይደለም ስለተደረገው
በሁሉ ጌታን ማመስገን መልካም ነው
የድልም ሁሉ ምስጢር ማሸነፊያው
ምስጋና ነው የተዘጋውን ማስከፈቻው ድል ማድረጊያው
ይብዛ ይብዛ ምስጋናው
ይጨመርለት እልልታው
ቤቱን ይሙላው ደመናው
እየበዛ ክብር ሙገሳው
@matalapochurch
@matalapochurch
እግዚአብሔር በቅድስናው ሲናገር
ይሆናል ያልተለመደ አዳዲስ ነገር
ደመናው ሳይታይ ንፋሱም ሳይታይ ይሞላል ሸለቆ
የብረቱ መዝጊያ ይከፈታል አውቆ
በኃይሉ ብዛት እና በችሎታው ብርታት አይታጣው አንዳች
ያደርጋል ኢየሱስ በበረሃ ወንዞች
ካዘዘ ይሁን ካለ የማይሆን ምንም የለም
ላይፈጽም የማይናገር እግዚአብሔር ታማኝ
ኪዳኑን የሚያጸና በቃሉ የሚገኝ
ቢለዋወጡ ዘመናት አለ እኮ ዛሬም በብርታት
በቅድስናው ተናግሯል የማይሆነውም ይሆናል
ደጆች ተዘጋግተው ሳሉ ኢየሱስ ይመጣል
ለክብሩ የሚሆን ታላላቅ ተአምራት ይሠራል
በሥልጣኑ በችሎታው በአስፈሪነቱ በግርማው
ይደረጋል አዲስ ነገር እርሱም ይበቅላል አሁን
የእግዚአብሔር ድምፅ በኃይል ነው
ጫካውን ይገላልጠዋል ዋላዎችን
አጠንክሮ ተራራውን ያፈራርሰዋል
ንጉሥ ሆኖ በዙፋኑ
ዘላለም የሚቀመጠው
የሌለውን መፍጠር ሚችል ኢየሱስ ቃሉ ሕያው ነው
ለማዳን የሚበረታ በጽድቅም የሚናገር
አለ እኮ በመሃላችን በታላቅ ክብር
ለሙታን ሕይወት ይሰጣል ዛሬም በማዳኑ ድንቅ
እኛ ካስቸገረን በላይ ኢየሱስ ትልቅ
ከከበደን በላይ ኢየሱስ ትልቅ
ካስቸገረን በላይ ኢየሱስ ትልቅ
በዙፋኑ ያለው ኢየሱስ ትልቅ
መፍጠር የሚችለው ኢየሱስ ትልቅ
አንዴ ተናግሯል ኢየሱስ ኃይል የእርሱ ብቻ ነው
ዝግባን ይሰብራል ድምፁ በታላቅ ክብር ነው
የእሳቱን ነበልባል ቆርጦ በማዳኑ ሁሉን ፈጥሮ
ሕዝቡን በሰላም ሚባርክ አቤት ድንቅ ነው የእኛ አምላክ
@matalapochurch2
🎙️𝐒𝐢𝐧𝐠𝐞𝐫 𝐌𝐞𝐥𝐚𝐤𝐮
𝐍𝐞𝐰 𝐀𝐩𝐨𝐬𝐭𝐨𝐥𝐢𝐜 𝐒𝐨𝐧𝐠
🎹𝐏𝐢𝐧𝐢𝐞𝐥 𝐒𝐭𝐮𝐝𝐢𝐨
[ እናፍቃለው ]
ቀንና ለሊት የላትም እህህ
እራብ ጥማት የላትም እህህ
ኢየሩሳሌም መኖርያዬ ኦሆሆ
መረፍያ መጽናኛዬ ኦሆሆ
እስክትመጣ ድረስ እጓጓለው
እስክትመጣ ድረስ እናፍቃለው
እናፍቃለው ኦሆሆ እናፍቃለው
እናፍቃለው ኢየሩሳሌምን እናፍቃለው
እናፍቃለው ኦሆሆ እናፍቃለው
እናፍቃለይሥው ውብ አገሬን እናፍቃለው
እጄን ይዘህ ሰማይ አድርሰኝ
በዝች ምድር ላይ እንዳትተወኝ
እዝ መቅረት እኔ አልፈልግም። 2*
ዓለማዬም አይደለም
እስክትመጣ ድረስ እጓጓለው
ከምድር ጋር ተጠብቄ
ሳለሁ ዓለምንም ተከትዬ
ምን እላለሁ ኢየሱስ ስመጣ 2*
ባዶ ሆኜ ተቀምጨ
እናፍቃለው........
ሀገሬን እኔ ናፍቅያለሁ
ኢየሱሰንም ተማምኜዋለሁ
አንድ ቀን ያደርሰኛል። 2*
ከእርሱ ጋር ይደረገኛል
ሳበኝ ወደ አንተ ሳበኝ 2*
ውብ ሀገሬ አሳዬኝ
ከአንተ ጋር እላይ አድረገኝ
@matalapochurch
@matalapochurch
New Single Song
ሆሳዕና እናት አጥቢያ
#ዘማሪት_ቤል_ደጉ
በጉብዝና ወራቴ ላሰብህ
ጉልበቴን ሳልሰስት ላገልግልህ
እንደቀደሙት አባቶቼ ስራብኝ
ሌላው ቀርቶ ክብርህ ብቻ ይታየኝ
ላገልግልህ በእኔ ላይ አንተ ድመቅ
ላገልግልህ ኑሮዬ አንተን ያሳይህ
ላገልግልህ ሕይወቴን ተጠቀም
ላገልግልህ ዘመኔን የእራስ አሪግ
ስምህ ነው በግምባሬ ደምህ ምልክቴ
ከለየኸኝ ለክብርህ በቃ ለአንተ ልኑር
እንዳልጸጸት አቅሜ ጎሎ
ስጨላልም ዘመኑ ነጉዶ
ላስብህ በጊዜ ላስብህ በዘመኔ
ላገልግልህ በጊዜ ላገልግልህ በዘመኔ
ፍላጎቴ የልቤ መሻት
በርትቼ ልደርስ ወደ አንተ ሙላት
ከምጎትተኝ ተላቅቄ
በፊትህ ልትጋ ዘወትር አምላኬ
እንዳልጸጸት...
መልካም እሁድ 🙏
♡ ⎙ ⌲ ✉️ jᵒⁱⁿ
ˡᶦᵏᵉ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ
jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ
@matalapochurch
@matalapochurch
ሰላም ለቅዱሳን በሙሉ!
የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል በዘማሪት ኢየሩሳሌም መዝገቡ የተዘጋጀውንና “እንደገና ታነሳለህ” የተሰኘውን የዝማሬ ሰንዱቅ ሲያቀርብላችሁ በታላቅ ደስታ ነው።
የበጎ ስጦታ ፍጹምም በረከት ባለቤት የሆነው እግዚአብሔር በቤተክርስቲያን በኩል ለራሱ ክብር እና ለቅዱሳን መታነጽ በሚሆኑ የዝማሬ ስጦታ እየባረከ ስላለ እናመሰግነዋለን። ዝማሬዎቹንም በታላቅ መስዋእትነት የሚያዘጋጁትንም ቅዱሳን እንባርካለን።
በዚህ አድካሚ የዝማሬ አልበም መዝሙሮቹን በመቀበል በስጦታ ለቤተክርስቲያን ያበረከተችውን እህት ኢየሩሳሌምን ጨምሮ በተለያየ መንገድ የተሳተፉትን ሁሉ የቤተክርስቲያን አምላክ ኢየሱስ በማያልቀው በረከት እንዲባርክ ጸሎታችንም ምኞታችንም ነው።
አልበሙ በቅርብ ቀናት ውስጥ በApostolic Songs መተግበሪያ ላይ ዝግጁ የሚሆን ሲሆን ቅዱሳን ሁሉ ዝማሬዎቹን በተለያዩ የግዢ አማራጮች በማውረድ ጸጋውን፣ ቤተክርስቲያንን እና አገልግሎቱን ትደግፉ ዘንድ በኢየሱስ ፍቅር እናስታውሳለን።
የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን
ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል
የካቲት 2018 ዓ.ም
ዝማሬ_አድኖኛል የጎፋ_አጥቢያ_ኤ ኳየርአድኖኛል አንዱ አምላክ በስጋ ተገልጦ አድኖኛል ደሙን ለእኔ አፍስሶ ዋጋ ከፍሎ አድኖኛል በውሃ ጥምቀት ዳግም ወልዶኝ አድኖኛል ቅዱሱን መንፈስ አፍስሶልኝ ስላዳነኝ ስሜ በሰማያት ተፃፈልኝ ስላዳነኝ በመላእክት ቋንቋ ተናገርኩኝ ስላዳነኝ ጠላት ከበታቼ ወደቀልኝ ስላዳነኝ የዘላለም ህይወት አገኘሁኝ ለሰው ሁሉ ሀጥያት እርሱ ስለሞተ ሲኦልን ድልነስቶ ህይወት ስላከለ ለዘላለም ተስፋ ሆነኝ ተመልክቶኝ የሞት ፍርሀት የለም ኢየሱስ ታድጓ አድኖኛል... ስላዳነኝ... ሸክም ለከበደው ና ብሎ ሚጣራ የህይወት ውሃ ሚሰጥ ሚያሳርፍ ሚያረካ ከለመለመው መስክ መቶ ስላኖረኝ ተመችቶኝ አለሁ የሱስ ስላዳነኝ ስላዳነኝ... በኢየሱስ ስም ስልጣን አጋንንትን ማዘው ሰይጣን የሚፈራኝ በፊቴ ማይቆመው የልጅነት መብቱ ስልጣኑ ስላለኝ ድፍረት ሆኖልኝ ነው ኢየሱስ ስላዳነኝ አድኖኛል... ስላዳነኝ... @ApostolicChurchOFethiopia @ApostolicChurchOFethiopia
የቃሊቲ እና ሳሪስ ጥምር መዘምራን ዝማሬ_አለን_እኛአለን እኛ የምንናፍቀው የክብርህ መገለጥ አለን እጅግ የምንጠማው የመንፈስህ ዝናብ ደመናን ሰንጥቆ ይውረድ የክብርህ እሳት ሰማያት ይከፈቱ እጅህ ትምጣልን በእውነት ልንሻገረው የከበደንን በስጋ ኃይል ያልተቻለውን ከፊታችን የገዘፈውን እንደተራራ የሆነውን የመንፈስህ ኃይል ቅባት ስነካን አድገን እንሄዳለን ወደክብርህ ዙፋን ደመናን ሰንጥቆ... ፩|ምድረ በዳው ላይ ፈሳሽ ይፈለቅ የጥማት መሬት የውሃ ምንጭ ይሁን ይለምልም ያፍራ ደረቁን ህይወት ፈቃድህንም እንዲያከናውን መንፈስህ ያውጣን ከሸለቆ ህይወት የአንተ ክብር ወደምናይበት እንደ ሌላ ሰው የሚያደርገን ጸጋህ በሙላት ይለቀቅልን ደመናን ሰንጥቆ... ፪| የደረቁ አጥንቶችም ተስፋ የቆረጥንባቸው ትንሳኤ ይሆንላቸዋል ድምፅህን ስታሰማቸው የእውሮች አይን ይገለጣል አንካሳው ይዘላል ድንቅም ይሆናል ተናገር እንጂ አንተ በስልጣን ኢየሱስ የማይቻል የለም ለአንተ ማይታዘዝ ደመናን ሰንጥቆ... አለን እኛ... ቅዱሱ መንፈስ ያለገደብ ይውረድ ሊሰወር የማይችል ታምራት ይገለጥ እጅህ በላያችን ትበርታና ትምጣ 👉 እንድንበረታ ይወረድ እሳት ይውረድ አሜን " መንፈስህ ይውረድልን ይውረድልን|፰| @matalapochurch @matalapochurch
#ዘማሪ_አብርሃም_ሞላ
#ዝማሬ_ላንተ_አይከብድም
ላንተ አይከብድም እኔን መለወጥ |2×
አያቅትህም እኔን መቀየር |2×
አውቃለሁ አንተን አሳዝናለሁ
ሀይልህ ከረዳኝ ግን እለወጣለሁ
አውቃለሁ አንተን እበድላለሁ
ምህረት ካገዘኝ ግን እቀየራለሁ
ምህረት ከረዳኝ እለውጣለሁ |
ፍቅርህ ካገዘኝ እቀየራለሁ |2×
ህይወቴን ሳየው እራሴን ስቃኘው
ሁሌም አንተን አሳዝናለሁ [እበድላለሁ]
የማይለወጥ ማንኔት
ጌታ ቀይረው አካሄደን
አይቸግርህምና ለአንተ |
ይህን ህይወቴን ማስተካከል[ማሳመር]|2×
ስመስለኝ ያወኩኝ
አሳዝኘሀለሁ ከፊትህ እርቅያለሁ
አሳዝኘሀለሁ አንተን በድይአለሁ
አለማወቀ የሄድኩበትን
ዞር ብዬ ሳየው ድካም [ልፋት] ብቻ ነው
የከንቱ ኑሮ ይበቃኛል
አንድ አይነት ህይወት ሰልችቶኛል
በአዲስ ህይወት በአዲስ ማንነት
አበርታኝና ላገልግልህ
አሁን [ዛሬ] እስት ወደ አንተ ልመለስ
ከእግር ስር ልወደቅ እባክህ እየኝ
እባክህ እየኝ እለምንሃለሁ |
እባክህ እየኝ ፊትህ እወድቃለሁ | 4×
jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ
@matalapochurch
@matalapochurch
ያነባሁትን እንባ ቆጥሮ
የራሱንም ጊዜ ጠብቆ
ይመጣልኛል መልሴን ይዞ
ባዶ ነገሬን ሁሉ ሞልቶ
ጠብቃለሁ ወደኔ እስኪመጣ
ድምፀን እስክሰማ ብርሃን እስኪበራ
እጥብቃለሁ ሀይሉ እስኪገለጥ
እጁ እስክትመጣ ድንቅን እስከሚያደርግ
ጠብቃለሁ እሱ እስኪመጣ
መልሴን እስክቀበል ስፍራዬንም አለቅ
እታገሳለሁ ቀኔ እስከሚደርስ
ጉድጓድ ውስጥ ቢጥሉኝ ብሆን በእስር ቤት
የእርሱ ቀን ሲመጣ በጊዜ ወደእኔ
ሁሉም ውብ ይሆናል ይረሳል ሀዘኔ
ለሚያየኝ ብመስልም ሰክሬ ማነባ
ሽክሜ በዝቶብኝ ብመጣ እርሱጋ
ስፍራዬንም አለቅ ትችቱ መልሴን ተቀብዬ ለምስጋና ስቆም
አቤት በእርሱ ቀን ገዳዩ ሟች ነው
ሊሞት ያለ ደግሞ እርሱ ንጉስ ነው
አቤት በእርሱ ቀን ስንቱን ይቀይራል
ያፈረ ሁሉ በኢየሱስ ይክብራል
♡ ⎙ ⌲ ✉️ jᵒⁱⁿ
ˡᶦᵏᵉ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ
jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ
@matalapochurch
@matalapochurch
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
