fa
Feedback
ማጣላ ዋላና ሐዋርያዊት ቤተ-ክርስትያን

ማጣላ ዋላና ሐዋርያዊት ቤተ-ክርስትያን

رفتن به کانال در Telegram

“በሕይወቴ ሳለሁ ለእግዚአብሔር እቀኛለሁ፥ ለአምላኬም በምኖርበት ዘመን ሁሉ እዘምራለሁ።” — መዝሙር 104፥33

نمایش بیشتر
3 440
مشترکین
+124 ساعت
+347 روز
+12430 روز
آرشیو پست ها
_አድኖኛል_የጎፋ_አጥቢያ_ኤ_ኳየር_10_06_2016_ዓም360p.mp36.91 MB

ABY EM_mpeg4_001.mp38.40 MB

😭😭😭😭😭😭😭 በዚያች በቀራንዮ በፈጠረው ፍጡር የተገረፈበት ለኔ ሲል እኮ ነው ሕይወትን ለመስጠት መንገላታት መቁሰልህ መራብ መጠማቱ ለኔ ነው ገብቶኛል ኢየሱስ የናዝሬቱ /2* በዚያች በቀራንዮ በጎልጎታ ጌታዬ ለኔ ሲል ሲንገላታ ኃይል አለው ኃይል አለው አላማው በኔ ላይ ፍቅር ነው ፍቅር ነው /2* እኔን ለመስራት ነው ነጻነት ለመስጠት ከኃጢአት ባርነት ከሞት ወደ ሕይወት የተወጋው በጦር የተቸነከረው መከራ ስቃዩ ዋጋ አለው ለኔ ነው /2* ኃጢአቴን ሊያነጻ ከእስራቴ ፈቶ በፈጠረው ፍጡር የእሾህ አክሊል ደፍቶ ትንሳኤና ሕይወት አለኝታ የሚሆነኝ የፈሰሰው ደሙ ይችላል ሊያድነኝ /2* @matalapochurch2 Apostolic Songs

የመስቀሉ ጸጋ አንተ ምስጋናዬ ነህ 4x የሱስ ምስጋናዬ ነህ አንተ ምስጋናዬ ነህ ጌታ ምስጋናዬ ነህ አንተ ራስህ ምስጋናዬ ነህ እያሰብኩኝ ብቻ የማይቀዘቅዘውን የመስቀሉን ፍቅር እንደማያቋርጥ ምንጭ ይፈልቃል ከውስጤ ገና ብዙ መዝሙር በጨለማዬ ላይ ብርሃን ያበራ የፅድቅ ፀሐይ የደህንነቴ ምንጭ ሁሉ የፈለቀብህ ካህኔም ጌታዬ አንተ ብቻ ነህ ምክንያቴ ለምስጋና እንዲከፈት አንደበቴ 1) አሰላስላለሁ የመስቀሉን ፀጋ ባልተገባኝ መጠን ብዙ እንደሰጠኸኝ/ብዙ እንደሆንክልኝ/4* እኔ ጤና እንድሆን ደዌዮን መሸከምህን እኔ እንዳምርልህ ደም ግባት ማጣትህን እኔ እንድወደድ መጠላት መገፋትህን እኔ እንድከብር የተናቅክ መሆንህን እኔ ቀና እንድል አንገትህን መድፋትህን እኔን ለማፅደቅ ኃጢአቴን መሸከምህን የተወጋውን ጎንህን የፈሰሰውን ደምህን የጠጣኸውን መራራ ያሳለፍከውን መከራ አልረሳም ይኖራል በልቤ ታትሞ በአይኖቼ ፊት በጉልህ ተስሎ የነፍሴ ብርሃን ነህ እያት ስታበራ በነፍስህ ድካም ጸድቃለችና አሃሃሃሃ ሃሌሉያ ከዘመርኩኝ አይቀር ለዚህ ፍቅር ዘምራለሁ ከአመለኩኝ አይቀር ይህን ፍቅር ብቻ አመልካለው ከተገረምኩ አይቀር በዚህ ፍቅር እገረማለው ካወራሁኝ አይቀር ይህን ፍቅር ብቻ አወራለው የወደደኝ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በታሪኬ/በሰማይ በምድር እንዳንተ ያለ አላውቅም ጌታ @matalapochurch2

እልልታ ውዳሴ New Cover Song! እልልታ ውዳሴ ይገባዋል ለጌታ ኢየሱስ ንጉሤ እልልታ ውዳሴ ይገባዋል ለጌታ ኢየሱስ ንጉሤ ሱራፌል በሰማይ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ይላሉ ለተ ቀን ለስሙ የምስጋናን መስዋዕት ይሰዋሉ የተፈራ ንጉስ በምስጋና እጅግ የከበረ ለስሙ የሚቀና  ከዘላለም ከጥንት የነበረ እጽዋት እንስሳት ውብነቱን በግልጽ ያወሳሉ ተራሮች ባሕሮች የእጆቹን ሥራ ያወራሉ ከዋክብት ብርሃናትኃይሉን ያንፀባርቃሉ የሰማይ አዕዋፋት ማለዳ ለክብሩ ያዜማሉ እኔም የሰው ልጅ በተራዬ ግሩምነቱን ላውጅ ልናገር ሰፊ ጥልቅ ለሆነው ስለ እጹብ ድንቅ የአምላክ ፍቅር የአለምን ኃጢአት በስጋው መስቀል ሞትን ሽሮ ይመስገን ሰቶናል የክብር የመንፈስ ምሪት ኑሮ መላዕክትም ቢሆን ምንም ደም አልፈሰሰላቸውም ፍጥረታት የሞት ዕዳ ተከፈለላቸው እኔም ለኢየሱሴ እራሱን ሰውቶ ስለዚህ ላክብረው ምስጋና ለኢየሱሴ ላዳነኝ Via፦ https://youtu.be/1dts7c7Dek8?si=Jkgg0CKptpS4u24R

ሊያስጥል የሚታገል እምነትና ፍቅርን ተስፋን የሚያሳጣ የዘላለሙን ከንቱ ሚያደርግብኝ የመዳን ተስፋዬን አንዱንም አልሰማም ጠላት ሚያወራውን የተሸከሙኝን ታማኝ እጆቹን በፍጹም አለቅም ኢየሱስዬን አልጥልም  መዳኔን ከኢየሱስ ላይ ፍጹም አላነሳም ዓይኔን የምድሩን ግሳንግስ ከመትረፌ ጋራ ሃይሉ ችሎታ ከእጁ የፅድቅ ስራ አላወዳድረውም ኧሬ አይመዘንም ከዘላለም ህይወት በጭራሽ [በፍጹም] አይበልጥም ትኩስ ነው መዳኔ የማይቀዘቅዝ ዋጋው የማይቀንስ የማይደበዝዝ ማይጎድል ሙላቴ ተስፋና ዕርስቴ ውበት ሆኖልኛል ኢየሱስን ማወቄ ጉዳዬ አድርጌ አዎ አጥብቄ ይዤሃለሁ የመምጣትህን ተስፋ እጠባበቃለሁ ሲያልፍ በሚረሳ በጊዜያዊ ነገር በማግኘት በማጣት የማይነጻጸር ሞት ቢሆን ህይወት እንዳይለየኝ አውቃለሁ የእርሱ በመሆኔ ተረጋግቼአለሁ መቼም አይቀልብኝ ኢየሱስን [አምላኬን] ማወቄ ዋጋዬ ደሙ [ኢየሱስ] ነው ውድ ነው ህይወቴ [መዳኔ] @Apostolicsonglyrics @Apostolicsonglyrics @Apostolicsonglyrics

ሰበር ዜና ዋራ ቤቴል 2018 12,296 ነፍሳት ለኃጢአታቸው ስርየት በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠምቀዋል። ክብር ሁሉ ለኢየሱስ ይሁን። @zemeru በማስተዋል ዘምሩ

ምስጋና ምስጋና ይለኛል ዘምር ዘምር ይለኛል አምልክ አምልክ ይለኛል ጌታዬ ይገባዋል         እጅግ የበዛውን የእርሱን ምህረት        ማለዳ ማለዳ መቀበል ከእርሱ ፊት        ምስጋናን መጨመር እለት እለት        አስለምዶኛል ለክብሩ መቀኘት ምስጋና መልካም 3X አምልኮ መልካም 3X ዝማሬ  መልካም 3X ድል ማድረጊያ ጎዳና አሃሃ 1 ከማመስገን ጋር በፀሎት ለሚቆየው በአንተ ፊት በችግር ውስጥም ላመሰገነህ አብልጠህ መልካም ታደርጋለህ         ስለ ምህረትህ ስለጥበቃህ ስለውለታህ         ምስጋና መልካም 3X...         በችግር በደስታ በመከራ         ምስጋና መልካም 3X... 2 ወደጉድጓድ ቢጣልም ምስጋና አለ ተላልፎ ተሽጦም ምስጋና አለ ፀሎትም ቢዘገይ ምስጋና አለ ከሚያመሰግን ጋር ኢየሱስ አለ       ምስጋና መልካም.... 3 ስለሆነው ብቻ አይደለም ስለተደረገው በሁሉ ጌታን ማመስገን መልካም ነው የድልም ሁሉ ምስጢር ማሸነፊያው ምስጋና ነው የተዘጋውን ማስከፈቻው ድል ማድረጊያው        ይብዛ ይብዛ ምስጋናው        ይጨመርለት እልልታው        ቤቱን ይሙላው ደመናው        እየበዛ ክብር ሙገሳው @matalapochurch @matalapochurch

ምስጋና ምስጋና ይለኛል ዘምር ዘምር ይለኛል አምልክ አምልክ ይለኛል ጌታዬ ይገባዋል    እጅግ የበዛው የእርሱ ምህረት    ማለዳ ማለዳ መቀበል በእርሱ ፊት    ምስጋና መጨመር ዕለት ዕለት    አስለምዶኛል ለክብሩ መቀኘት ምስጋና መልካም መልካም መልካም አምልኮ » » » » ዝማሬ »         »        »        » ድል ማድረጊያ ጎዳና አሃሃ 1]ከማመስገን ጋር በፀሎት     ለሚቆየው በአንተ ፊት     በጭንቅ ውስጥ ያመሰገነህ     አብልጠህ መልካም ታደርጋለህ ስለምህረትህ ስለጥበቃህ ስለውለታህ    ምስጋና መልካም .... በችግር በደስታ በሀዘን በመከራ    ምስጋና መልካም... 2]ወደ ጉድጓድ ቢጣልም ምስጋና አለ     ተላልፎም ተሽጦ ምስጋና አለ     ፀሎትም ቢዘገይ ምስጋና አለ     ከሚያመሰግን ጋር ኢየሱስ አለ ምስጋና መልካም ....   ስለሆነው ብቻ አይደለም ስለተደረገው   በሁሉም ጌታን ማመስገን መልካም ነው   የድልን ሁሉ ምስጢር ማሸነፈያው    ምስጋና ነው የተዘጋውን ማስከፈቻው ድል ማድረጊያው ይብዛ ይብዛ ምስጋናው ይጨመርለት እልልታው ቤቱን ይሙላው ደመናው የበዛብህ ሙገሳው   ~~.. ~~    ❞በማስተዋል እንዘምር❞

እግዚአብሔር በቅድስናው ሲናገር ይሆናል ያልተለመደ አዳዲስ ነገር ደመናው ሳይታይ ንፋሱም ሳይታይ ይሞላል ሸለቆ የብረቱ መዝጊያ ይከፈታል አውቆ በኃይሉ ብዛት እና በችሎታው ብርታት አይታጣው አንዳች ያደርጋል ኢየሱስ በበረሃ ወንዞች ካዘዘ ይሁን ካለ የማይሆን ምንም የለም ​ላይፈጽም የማይናገር እግዚአብሔር ታማኝ ኪዳኑን የሚያጸና በቃሉ የሚገኝ ቢለዋወጡ ዘመናት አለ እኮ ዛሬም በብርታት በቅድስናው ተናግሯል የማይሆነውም ይሆናል ​ደጆች ተዘጋግተው ሳሉ ኢየሱስ ይመጣል ለክብሩ የሚሆን ታላላቅ ተአምራት ይሠራል በሥልጣኑ በችሎታው በአስፈሪነቱ በግርማው ይደረጋል አዲስ ነገር እርሱም ይበቅላል አሁን ​የእግዚአብሔር ድምፅ በኃይል ነው ጫካውን ይገላልጠዋል ዋላዎችን አጠንክሮ ተራራውን ያፈራርሰዋል ​ንጉሥ ሆኖ በዙፋኑ ዘላለም የሚቀመጠው የሌለውን መፍጠር ሚችል ኢየሱስ ቃሉ ሕያው ነው  ለማዳን የሚበረታ በጽድቅም የሚናገር  አለ እኮ በመሃላችን በታላቅ ክብር  ለሙታን ሕይወት ይሰጣል ዛሬም በማዳኑ ድንቅ  እኛ ካስቸገረን በላይ ኢየሱስ ትልቅ ​ከከበደን በላይ ኢየሱስ ትልቅ ካስቸገረን በላይ ኢየሱስ ትልቅ በዙፋኑ ያለው ኢየሱስ ትልቅ መፍጠር የሚችለው ኢየሱስ ትልቅ ​አንዴ ተናግሯል ኢየሱስ ኃይል የእርሱ ብቻ ነው ዝግባን ይሰብራል ድምፁ በታላቅ ክብር ነው የእሳቱን ነበልባል ቆርጦ በማዳኑ ሁሉን ፈጥሮ ሕዝቡን በሰላም ሚባርክ አቤት ድንቅ ነው የእኛ አምላክ   @matalapochurch2

🎙️𝐒𝐢𝐧𝐠𝐞𝐫 𝐌𝐞𝐥𝐚𝐤𝐮 𝐍𝐞𝐰 𝐀𝐩𝐨𝐬𝐭𝐨𝐥𝐢𝐜 𝐒𝐨𝐧𝐠 🎹𝐏𝐢𝐧𝐢𝐞𝐥 𝐒𝐭𝐮𝐝𝐢𝐨 [ እናፍቃለው ] ቀንና ለሊት የላትም እህህ እራብ ጥማት የላትም እህህ ኢየሩሳሌም መኖርያዬ ኦሆሆ መረፍያ መጽናኛዬ ኦሆሆ እስክትመጣ ድረስ እጓጓለው እስክትመጣ ድረስ እናፍቃለው እናፍቃለው ኦሆሆ እናፍቃለው እናፍቃለው ኢየሩሳሌምን እናፍቃለው እናፍቃለው ኦሆሆ እናፍቃለው እናፍቃለይሥው ውብ አገሬን እናፍቃለው እጄን ይዘህ ሰማይ አድርሰኝ በዝች ምድር ላይ እንዳትተወኝ እዝ መቅረት እኔ አልፈልግም። 2* ዓለማዬም አይደለም እስክትመጣ ድረስ እጓጓለው ከምድር ጋር ተጠብቄ ሳለሁ ዓለምንም ተከትዬ ምን እላለሁ ኢየሱስ ስመጣ 2* ባዶ ሆኜ ተቀምጨ እናፍቃለው........ ሀገሬን እኔ ናፍቅያለሁ ኢየሱሰንም ተማምኜዋለሁ አንድ ቀን ያደርሰኛል። 2* ከእርሱ ጋር ይደረገኛል ሳበኝ ወደ አንተ ሳበኝ 2* ውብ ሀገሬ አሳዬኝ ከአንተ ጋር እላይ አድረገኝ @matalapochurch @matalapochurch

New Single Song ሆሳዕና እናት አጥቢያ #ዘማሪት_ቤል_ደጉ በጉብዝና ወራቴ ላሰብህ ጉልበቴን ሳልሰስት ላገልግልህ እንደቀደሙት አባቶቼ ስራብኝ ሌላው ቀርቶ ክብርህ ብቻ ይታየኝ ላገልግልህ በእኔ ላይ አንተ ድመቅ ላገልግልህ ኑሮዬ አንተን ያሳይህ ላገልግልህ ሕይወቴን ተጠቀም ላገልግልህ ዘመኔን የእራስ አሪግ ስምህ ነው በግምባሬ ደምህ ምልክቴ ከለየኸኝ ለክብርህ በቃ ለአንተ ልኑር እንዳልጸጸት አቅሜ ጎሎ ስጨላልም ዘመኑ ነጉዶ ላስብህ በጊዜ ላስብህ በዘመኔ ላገልግልህ በጊዜ ላገልግልህ በዘመኔ ፍላጎቴ የልቤ መሻት በርትቼ ልደርስ ወደ አንተ ሙላት ከምጎትተኝ ተላቅቄ በፊትህ ልትጋ ዘወትር አምላኬ እንዳልጸጸት... መልካም እሁድ 🙏 ♡   ⎙    ⌲     ✉️  jᵒⁱⁿ ˡᶦᵏᵉ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ @matalapochurch @matalapochurch

ሰላም ለቅዱሳን በሙሉ! የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል በዘማሪት ኢየሩሳሌም መዝገቡ የተዘጋጀውንና “እንደገና ታነሳለህ” የተሰኘውን የዝማሬ ሰንዱቅ ሲያቀርብላችሁ
ሰላም ለቅዱሳን በሙሉ! የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል በዘማሪት ኢየሩሳሌም መዝገቡ የተዘጋጀውንና “እንደገና ታነሳለህ” የተሰኘውን የዝማሬ ሰንዱቅ ሲያቀርብላችሁ በታላቅ ደስታ ነው። የበጎ ስጦታ ፍጹምም በረከት ባለቤት የሆነው እግዚአብሔር በቤተክርስቲያን በኩል ለራሱ ክብር እና ለቅዱሳን መታነጽ በሚሆኑ  የዝማሬ ስጦታ እየባረከ ስላለ እናመሰግነዋለን። ዝማሬዎቹንም በታላቅ መስዋእትነት የሚያዘጋጁትንም ቅዱሳን እንባርካለን። በዚህ አድካሚ የዝማሬ አልበም መዝሙሮቹን በመቀበል በስጦታ ለቤተክርስቲያን ያበረከተችውን እህት ኢየሩሳሌምን ጨምሮ በተለያየ መንገድ የተሳተፉትን ሁሉ የቤተክርስቲያን አምላክ ኢየሱስ በማያልቀው በረከት እንዲባርክ ጸሎታችንም ምኞታችንም ነው። አልበሙ በቅርብ ቀናት ውስጥ በApostolic Songs መተግበሪያ ላይ ዝግጁ የሚሆን ሲሆን ቅዱሳን ሁሉ ዝማሬዎቹን በተለያዩ የግዢ አማራጮች በማውረድ ጸጋውን፣ ቤተክርስቲያንን እና አገልግሎቱን ትደግፉ ዘንድ በኢየሱስ ፍቅር እናስታውሳለን። የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል የካቲት 2018 ዓ.ም

የቃሊቲ እና ሳሪስ ጥምር መዘምራን ዝማሬ_አለን_እኛ
አለን እኛ የምንናፍቀው የክብርህ መገለጥ አለን እጅግ የምንጠማው የመንፈስህ ዝናብ ደመናን ሰንጥቆ ይውረድ የክብርህ እሳት ሰማያት ይከፈቱ እጅህ ትምጣልን በእውነት ልንሻገረው የከበደንን በስጋ ኃይል ያልተቻለውን ከፊታችን የገዘፈውን እንደተራራ የሆነውን የመንፈስህ ኃይል ቅባት ስነካን አድገን እንሄዳለን ወደክብርህ ዙፋን ደመናን ሰንጥቆ... ፩|ምድረ በዳው ላይ ፈሳሽ ይፈለቅ የጥማት መሬት የውሃ ምንጭ ይሁን ይለምልም ያፍራ ደረቁን ህይወት ፈቃድህንም እንዲያከናውን መንፈስህ ያውጣን ከሸለቆ ህይወት የአንተ ክብር ወደምናይበት እንደ ሌላ ሰው የሚያደርገን ጸጋህ በሙላት ይለቀቅልን ደመናን ሰንጥቆ... ፪| የደረቁ አጥንቶችም ተስፋ የቆረጥንባቸው ትንሳኤ ይሆንላቸዋል ድምፅህን ስታሰማቸው የእውሮች አይን ይገለጣል አንካሳው ይዘላል ድንቅም ይሆናል ተናገር እንጂ አንተ በስልጣን ኢየሱስ የማይቻል የለም ለአንተ ማይታዘዝ ደመናን ሰንጥቆ... አለን እኛ... ቅዱሱ መንፈስ ያለገደብ ይውረድ ሊሰወር የማይችል ታምራት ይገለጥ እጅህ በላያችን ትበርታና ትምጣ 👉                         እንድንበረታ ይወረድ እሳት ይውረድ አሜን   "   መንፈስህ ይውረድልን ይውረድልን|፰| @matalapochurch @matalapochurch

#ዘማሪ_አብርሃም_ሞላ #ዝማሬ_ላንተ_አይከብድም ላንተ አይከብድም እኔን መለወጥ |2× አያቅትህም እኔን መቀየር |2× አውቃለሁ አንተን አሳዝናለሁ ሀይልህ ከረዳኝ ግን እለወጣለሁ አውቃለሁ አንተን እበድላለሁ ምህረት ካገዘኝ ግን እቀየራለሁ ምህረት ከረዳኝ እለውጣለሁ | ፍቅርህ ካገዘኝ እቀየራለሁ |2× ህይወቴን ሳየው እራሴን ስቃኘው ሁሌም አንተን አሳዝናለሁ [እበድላለሁ] የማይለወጥ ማንኔት ጌታ ቀይረው አካሄደን አይቸግርህምና ለአንተ | ይህን ህይወቴን ማስተካከል[ማሳመር]|2× ስመስለኝ ያወኩኝ አሳዝኘሀለሁ ከፊትህ እርቅያለሁ አሳዝኘሀለሁ አንተን በድይአለሁ አለማወቀ የሄድኩበትን ዞር ብዬ ሳየው ድካም [ልፋት] ብቻ ነው የከንቱ ኑሮ ይበቃኛል አንድ አይነት ህይወት ሰልችቶኛል በአዲስ ህይወት በአዲስ ማንነት አበርታኝና ላገልግልህ አሁን [ዛሬ] እስት ወደ አንተ ልመለስ ከእግር ስር ልወደቅ እባክህ እየኝ እባክህ እየኝ እለምንሃለሁ | እባክህ እየኝ ፊትህ እወድቃለሁ | 4× jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ @matalapochurch @matalapochurch

ያነባሁትን እንባ ቆጥሮ የራሱንም ጊዜ ጠብቆ ይመጣልኛል መልሴን ይዞ ባዶ ነገሬን ሁሉ ሞልቶ ጠብቃለሁ ወደኔ እስኪመጣ ድምፀን እስክሰማ ብርሃን እስኪበራ እጥብቃለሁ ሀይሉ እስኪገለጥ እጁ እስክትመጣ ድንቅን እስከሚያደርግ ጠብቃለሁ እሱ እስኪመጣ መልሴን እስክቀበል ስፍራዬንም አለቅ እታገሳለሁ ቀኔ እስከሚደርስ ጉድጓድ ውስጥ ቢጥሉኝ ብሆን በእስር ቤት የእርሱ ቀን ሲመጣ በጊዜ ወደእኔ ሁሉም ውብ ይሆናል ይረሳል ሀዘኔ ለሚያየኝ ብመስልም ሰክሬ ማነባ ሽክሜ በዝቶብኝ ብመጣ እርሱጋ ስፍራዬንም አለቅ ትችቱ መልሴን ተቀብዬ ለምስጋና ስቆም አቤት በእርሱ ቀን ገዳዩ ሟች ነው ሊሞት ያለ ደግሞ እርሱ ንጉስ ነው አቤት በእርሱ ቀን ስንቱን ይቀይራል ያፈረ ሁሉ በኢየሱስ ይክብራል ♡   ⎙    ⌲     ✉️  jᵒⁱⁿ ˡᶦᵏᵉ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ jᵒⁱⁿ @matalapochurch @matalapochurch