1 950
مشترکین
+124 ساعت
+97 روز
+2730 روز
آرشیو پست ها
1 951
#MoE
ትምህርት ሚኒስቴር የ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ለመማር ያለፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን ማስተካከል ይችላሉ ብሏል።
ሚኒስቴሩ ፤ ያልፉ ተማሪዎች ምርጫቸውን ማስተካከል የሚችሉት በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ ጥቅምት 14/2016 ዓ.ም ድረስ መሆኑን አስገንዝቧል።
በልዩ ሁኔታ በአዳማ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርሲቲዎች መማር የሚፈልጉ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና የማይሰጥ መሆኑን አውቀው ምርጫቸው ውስጥ በማካተት መመደብ እንደሚችሉም የትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። #MoE
@tikvahethiopia
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
