ያሬዳውያን
የየበዓላቱ ስርአተ #ዋዜማ ፤ #ማኅሌት ፤ #ወረብ ከ፯ ቀናት በፊት እንዲሁም የየሳምንቱ መዝሙራት እና ምስባክ በጽሑፍ እና በድምጽ የሚቀርቡበት ቻናል ነው #ሁሉም_ነገር_ስለ_ማኅሌት ለማስታወቂያ እና ለማንኛውም ጥያቄ ከፈለጉን አለን በዚህ ያናግሩን 👉 @Yaredawi_admin እናመሰግናለን
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ያሬዳውያን
کانال ያሬዳውያን (@eotcmahlet) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 123 058 مشترک است و جایگاه 252 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 243 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 123 058 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 03 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 3 397 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 22 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 14.68% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.88% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 18 060 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 9 693 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 54 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“የየበዓላቱ ስርአተ #ዋዜማ ፤ #ማኅሌት ፤ #ወረብ ከ፯ ቀናት በፊት እንዲሁም የየሳምንቱ መዝሙራት እና ምስባክ በጽሑፍ እና በድምጽ የሚቀርቡበት ቻናል ነው
#ሁሉም_ነገር_ስለ_ማኅሌት
ለማስታወቂያ እና ለማንኛውም ጥያቄ ከፈለጉን
አለን በዚህ ያናግሩን 👉 @Yaredawi_admin
እናመሰግናለን”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 04 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
❝ኦ እግዚኦ አድኅን ሕዝበከ ወባርክ ርስተከ ራዓዮሙ ወአልዕሎሙ እስከ ለዓለም ወዕቀባ ለቤተ ክርስቲያኒከ ቅድስት እንተ አጥረይካ ወቤዘውካ በደሙ ክቡር ለዋሕድ ወልድከ እግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ወጸዋዕካ ትኩን ማህደረ ለነገሥት ወለመኳንንት ለዘመድ ንጹሕ ወለሕዝብ ቅዱስ እለ መጻእክሙ ወእለ ተጋባዕክሙ ወእለ ጸለይክሙ ውስተ ዛቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እለ በላዕክሙ ሥጋሁ ቅዱሰ፣ ወእለ ሰተይክሙ ደሞ ክቡረ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ይሥረይ ለክሙ ኃጢአተክሙ ዘገበርክሙ እመሂ በአእምሮ አው በኢያእምሮ በዘኀለፈ ይመሐርክሙ ወበዘይመጽዕ ይዕቀብክሙ በእንተ ሥጋሁ ሥጋ መለኮት ወበእንተ ደሙ ደመ ሕግ ወሥርዓት ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ጸባኦት ወወልደ ማርያም ንጽሕት በሕሊና ወበድንግልና ሥጋ ኅትምት ለዓለመ ዓለም አሜን❞(...)
❝አቤቱ ሕዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ እስከ ዘለዓለሙ ጠብቃቸው ከፍ ከፍም አድርጋቸው፤ በአንድ ልጅህ በጌታችን በአምላካችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በክቡር ደሙ የዋጀሃት ቤዛም የሆንካት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ጠብቃት። ለነገሥታትና ለመኳንንት ለንጹሕ ወገን ቅዱስ ለሆነ ሕዝብ ማደሪያ ትሆን ዘንድ የጠራሃት በዚህች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መጥታችሁ ተሰብስባችሁ የጸለያችሁ፣ የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋን የበላችሁ፣ ክቡር ደሙንም የጠጣችሁ በማወቅ ወይም ባለማወቅ የሠራችሁትን ኃጢአታችሁን ይቅር ይበላችሁ፡፡ ሥጋ መለኮት ስለሚባል ሥጋው፣ የሕግና የሥርዓት ደም ስለሚባል ደሙ የአሸናፊ የእግዚአብሔር ልጅ፣ በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ኅትምት የምትሆን የማርያም ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ባለፈው ይቅር ይባላችሁ በሚመጣውም ይጠብቃችሁ ለዘለዓለሙ አሜን❞(ትርጓሜ): ሕዝብን አድን - በኃጢአታቸው ከሚመጣባቸው ፍዳ፣ ኩነኔ በቸርነትህ አድናቸው ማለት ነው፡፡
❝እግዚአብሔር ይቅርታ አድራጊ ነው። እግዚአብሔር መሐሪ ይቅር ባይ ነው፡፡ ከቁጣ የራቀ፣ ምሕረቱ የበዛ፣ ጻድቅ እውነተኛ አዳኝ ማለት ነው❞— እንዲል መዝ. ፻፪፥፮ ርስትህን ባርክ - ካህናቱን አክብር ማለት ነው፡፡ ካህናቱን «ርስት» ማለቱ ካህናት አስተምረው፣ አጥምቀውና አቁርበው ርስት መንግሥተ ሰማያትን ያሰጣሉና (ማቴ. ፳፰፥፲፱)። እስከ ዘለዓለም ጠብቃቸው ከፍ ከፍም አድርጋቸው - ልዕልና ነፍስ ሰጥተህ በነፍስ በሥጋ ጠብቃቸው ሲል ነው፡፡ «ልዕልና ነፍስ» ማለት የነፍስ ከፍታ ማለት ሲሆን በነፍስ የሚገኘውን ክብር ስጣቸው ማለት ነው፡፡ በአንድ ልጅህ በጌታችን በአምላካችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ - «አንድ ልጅህ» ሲል ሃይማኖታችን ወልድ ዋህድ ማለት ሲሆን ይህም ከዓለም መፈጠር በፊት ከአብ የተወለደው፤ ከዓለም መፈጠር በኋላ ከእመቤታችን የተወለደውን አንድ ወልድ ነው ማለት ነው፡፡
❝አብ ወልድን የወለደው ነውና ዳግመኛም በማይነገር በሃሳብም በማይመረመር ግብር መንፈስ ቅዱስ ከእርሱ ወይም ከአብ ተገኝቷልና አብ ከወልድ ወልድም ከመንፈስ ቅዱስ ሳይቀድም መንፈስ ቅዱስም ከወልድ፥ ወልድም ከአብ ወደ ኋላ ሳይሆን ወልድ ለአብ ለመንፈስ ቅዱስ ቃላቸው ነው፤ መንፈስ ቅዱስም ለአብ ለወልድ እስትንፋሳቸው ነው፡፡ አብም ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ልባቸው ነው❞— ሃይማኖተ አበው ዘአቡሊዲስ ፴፱፥፯ በጥቅሉ አብ ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም። ወልድም ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፡፡ መንፈስ ቅዱስም ከአብ ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፡፡ ጥንት የሌለው ቀዳማዊ ልጅ ያለው እግዚአብሔር አብ ብቻ ነው፡፡ ዳግመኛ ወልድ አይመረመርም ማንም መርምሮ አያገኘውም፡፡ አብ ከዘመን በኋላ አልወለደውም፣ እርሱ ቀዳማዊ ወልድ ከአብ ጋር በቅድምና የነበረ ነው እንጂ የማይሞት ነው። ከማይሞት አብ ጋር ፈጣሪ ነው፤ እንደ አብ ሁሉን የፈጠረ ነው እንዲሁም መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ጋር በቅድምና የነበረ ቀዳማዊ ነው፤ በሥራውም ሁሉ ከአብ ከወልድ ጋር አንድ ነው — (ሠለስቱ ምዕት በሃይማኖተ አበው ፲፱፥፮)። በክቡር ደምህ የዋጀሃትን - ደምህን አፍስሰህ፣ ሥጋህን ቆርሰህ ያጸናሃትን ማለቱ ነው፡፡ የተቤዣችሁ (ያዳናችሁ) በሚጠፋ በወርቅ ወይም በብር እንዳይደለ ታውቃላችሁ ነውርና እድፍ እንደሌለው እንደ በግ ደም በክርስቶስ ክቡር ደም ነው እንጂ (፩ኛ ጴጥ ፩፥፲፰-፳፩)፡፡ ለነገሥታት ለመኳንንት ለንጹሕ ወገንና ቅዱስ ለሆነ ሕዝብ ማደሪያ ትሆን ዘንድ የጠራሃት - ነገሥታት መኳንንት ሥጋውንና ደሙን የሚቀበሉባት ለማለት ሲሆን ንጹሕ ወገንና ቅዱስ ሕዝብ የተባሉ እሥራኤል ዘሥጋ እና እሥራኤል ዘነፍስ ናቸው፡፡ ሁሉም አምነው ተጠምቀው ሥጋውን ደሙን የተቀበሉት ስለሆነ ለጌታችን በሥጋ ተዛምደው ያመኑት እስራኤል ዘነፍስ እና እስራኤል ዘሥጋ ይባላሉ፡፡ ሥጋ መለኮት ስለሚባል ሥጋህ - መለኮት የተዋሐደው ነፍስ የተለየው ሥጋ ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም የምንቀበለው ሥጋ ነፍስ የተለየው መለኮት የተዋሐደው ሥጋ ነውና የሕግና የሥርዓት ደም ስለሚባል ደሙ - በኦሪት እስራኤል ከግብጻውያን ባርነት ሊወጡ ሲሉ ከግብጽ ወደ ከነአን እንደሚሄዱና ለጊዜው በግብጻውያን ላይ ከታዘዘው ሞተ በኩር ወይም መቅሠፍት እንደሚድኑ ምልክት ይሆናቸው ዘንድ ጥፍሩ ያልዘረዘረ፣ ቀንዱ ያልከረከረ፣ ጠጉሩ ያላረረ ዓመት የሆነው ጠቦት አርደው እንዴት መብላት እንዳለባቸውና ደሙን በያሉበት ቤት በር ላይ እንዲቀቡ:-
❝ከደሙም ወስደው በሚበሉበት ቤት መቃኑንና ጉባኑን ወይም በሩን ይቅቡት … ደሙም ባላችሁበት ቤት ምልክት ይሆንላችኋል፡፡ ደሙንም አያለሁ እናንተንም እሠውራችኋለሁ እኔም የግብጽን ሀገር በመታሁ ጊዜ የጥፋት መቅሠፍት አይመጣባችሁም❞— ተብለው ታዘዙ እነርሱም በታዘዙት መሠረት መቃኑን ጉበኑን ቀብተው ድነዋል፡፡ የበጉ ቀንድ ያልከረከረ፣ ጠጉሩ ያላረረ፣ ጥፍሩ ያልዘረዘረ መሆኑ የክርስቶስ ምሳሌ ሲሆን፤ በጉ ምንም ነውር የሌለበት መሆኑ በጌታችን ፍፁም ሰው፥ ፍጹም አምላክ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ ስለዚህ ሌላውን ሐተታ ለጊዜው እንተወውና በደሙ ምልክትነት እሥራኤል እንደ ዳኑ ሥጋውን ደሙን የተቀበሉም ምእመናን ከሲዖል፣ ከገሃነም ይድናሉ። በኦሪት በሥርዓት የበራቸውን መግቢያ በበጉ ደም ቀብተው ከመቅሰፍት እንደ ዳኑ እኛም በጌታችን ደሙ ፈሳሽነት ድነናልና «የሕግና የሥርዓት ደም» አለው (ዘፀ ፲፪፥፯)። የአሸናፊ የእግዚአብሔር ልጅ - የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ ማለት ነው፡፡ የእግዚአብሔር አብ አባትነት የእግዚአብሔር ወልድን ልጅነት ከዚህ ብፊት የተገለጠ ሲሆን በጥቅሉ ሲፈታ ከአብ የወልድ መወለድ የመንፈስ ቅዱስ መስረጽ በእፁብ ይወሰናል እንጂ እንዲህ ነው ተብሎ አይነገረም። ከሕሊና ሁሉ በላይ ነውና አይመረመርም ምክንያቱም አብ ወልድን የወለደው መንፈስ ቅዱስን ያሰረፀው ሳይቀድም ነውና — (ሃይማኖት አበው ዘዲዮናስዮስ ፲፥፲፪)። አብ ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፥ ወድም ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፥ መንፈስ ቅዱስም ከአብ ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም እንዲል ሃይማኖተ አበው — (ዘሠለስቱ ምዕት ፲፩፥፮)። በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ኅትምት የምትሆን የማርያም ልጅ - እመቤታችን ኃጢአትን ከማሰብ፣ ከመናገር፣ ከመተግበር የተለየች መሆኗን ለመግለጽ ሲሆን በዚሁ ንጽሕናዋ አምላክን የወለደች አምላክ ከእርሷ የተወለደ መሆኗን ለመመስከር ነው፡፡ ዲ/ን ኃይለራጉኤል
❝ነአምን በቃለ ወንጌል ቅዱስ — ቅዱስ በሆነው በወንጌልህ ቃል እናምናለን❞— እያሉ እጅ እየነሡ ክንብንባቸውን እያወረዱ ይሳለማሉ በቃለ ወንጌል ማመናቸውን ይመሰክራሉ:: ክብረ ወንጌል በቅድስት ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ቅዱስ ወንጌል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ቅድሚያ የሚሰጠው ከፍ ያለ ክብር ያለው እንደሆነ የታወቀ ነው:: ስለ ክብረ ወንጌል የማይነገርበት ሥርዐት እና አምልኮ ቤተክርስቲያን የላትም:: በቅድስት ቤተክርስቲያን ቅዱስ ወንጌልን የማያሳትፍ ጸሎት፣ ቁርባን፣ መሥዋዕትና አገልግሎት የለም:: ማኅሌትና ሰዓታት ሲቆም፤ ጸሎተ ፍትሕት ሲደረስና ጸሎተ ተክሊል ሲከናወን በእነዚህ ሁሉ መስቀል ተይዞ ወንጌል ይነበባል:: በአጠቃላይ ቅዱስ ወንጌል የማይነበብበት የአገልግሎት ዘርፍም ሆነ የጸሎት ክፍል ቤተክርስቲያን የላትም። ይህም ለቅዱስ ወንጌሉ ያላትን ክብር ከፍ አድርጎ ያሳያል:: ቅዱስ ወንጌል ለሥርዐት፣ ለአምልኮት፣ ለሕግጋትና ለአገልግሎት መሠረት በመኾኑ ከሌሎቹ ሥርዓቶች የበለጠ ክብር ይሰጠዋል። ለምሳሌ:- በቅዳሴ ጊዜ ወንጌል ሲነበብ የደከመ/የታመመ እንኳን ቢሆን በዚያች በንባብ ቅጽበት ውስጥ ድካሙንም ሕመሙንም እንደምንም ችሎም ቢሆን ቆሞ እንዲያደምጥ ይታወጃል:: አዋጁን የሚያውጀው ገባሬ ሠናዩ ዲያቆን:-
❝ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን ቅዱስ ወንጌል ቆማችሁ አድምጡ!❞— የሚለው አዋጅ ከታወጀ በኋላ የተቀመጠ ካለ ቀጥ ብሎ ሕሊናውን ሰብስቦ ይቆማል:: (እዚህ ጋር ዲያቆኑ ወንጌሉን «አድምጡ» እንጂ «ስሙ» አይልም። በሁለቱ ቃላት መካከል ያለውን ልዩነት ልብ በሉ!) ዲያቆኑ ቁሙ ወአጽምዑ ማለቱ የንፍሐተ ቀርን፤ ካህኑ ወንጌል ማንበቡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፍርድ ቀን «ንዑ ኀቤየ፥ ሑሩ እምኔየ» ብሎ ፍርድ የማስተላለፉ ምሳሌ ነው:: በዚህ ጊዜ የሚደወለው ደወል የግርማ መዓቱ፤ ወንጌል ከተነበበ በኋላ መጋረጃ መዘጋቱ ሑሩ እምኔየ ብሎ ኀጥአንን የማሰናበቱ ምሳሌ ነው። (የቅዳሴ አንድምታ) ወንጌል ከተነበበም በኋላ ንፍቅ ካህን ወንጌል መስማት ክብሩ ምን ያህል እንደሆነ ሲናገር እንዲህ ይላል:-
❝ክቡር የሚሆን የወንጌልህን ቃል እንሰማ ዘንድ እንሳለመውም ዘንድ ደስ ይለን ዘንድ ለዚህ የበቃን ያደረግኸን ሁሉን የያዝህ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ ላንተ ምስጋና ይገባሃል! ዳግመኛም ክቡር የሚሆን የወንጌልህን ቃል በልቡናችን ትጽፍ ዘንድ እንለምናለን እንማልድሃለን❞— ብሎ ይማጸናል:: የቅዱስ ወንጌል ክብሩ የሚጀምረው መጽሐፉን ከማክበር ሲሆን ይኸውም አቅም ያለው ደብር የመጽሐፉን ገበታ (የውጭውን ሽፋን) በወርቅ እና በብር ያስጌጡታል አቅም የሌለው ደብር ደግሞ በወርቃማ ሱቲ (በከበረ ልብስ) ያለብሱታል:: ይህ ሁሉ ታዲያ ክብሩን ለመግለጥ ነው:: ምእመናን ቅዱስ ወንጌልን እንዴት ባለ ሁኔታ መስማት እንደሚገባቸው ሥርዓተ ቅዳሴው ሲናገር:-
❝የሰማያዊውን ንጉሥ የከበረ የወንጌሉን ቃል ለመስማት ከመጀመሪያቸው እስከ መጨረሻቸው ድረስ ከማመስገን ከመቀደስ በቀር ማድነቅና ጸጥታ ሊሆን ይገባል:: የምድራዊ ንጉሥ ደብዳቤ ሲነበብ አንድ ሰው እንኳን ለመናገር የማይደፍር ከሆነ፤ ቢናገርም ቅጣትና ግርፋት የሚያገኘው ከሆነ የሰማያዊው ንጉሥ ደብዳቤ የምትሆን ወንጌል ሲነበብ የሚናገር ምን ያህል ቅጣት ያገኘው ይሆን?❞— በማለት ወንጌል ሲነበብ ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረግ እንደሚገባው ሥርዐተ በቅዳሴያችን ያስጠነቅቃል:: ጸሎተ ወንጌል ከተፈጸመ በኋላ ንፍቅ ዲያቆን መብራት ይዞ በፊት፥ ንፍቅ ካህን ማዕጠንት ይዞ በኋላ ሆኖ ሁለቱም በቅድስት በቀኝ በኩል ዞረው በሰሜን የመቅደሱ በር ይገባሉ:: ሠራዒ ዲያቆን በቅድስቱ ላይ ሆኖ ፊቱን ወደ ምዕራብ መልሶ ቃጭል እየመታ:- «ጻዑ ንዑሰ ክርስቲያን» ይላል። ይህንንም የሚያውጅበት ምክንያት «ንዑሰ ክርስቲያን» የሚባሉት የክርስትና ሃይማኖትን በማጥናትና ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን በመከታተል ላይ ያሉት ገና ያልተጠመቁ አዲስ ክርስቲያኖች ሲሆኑ እንዲወጡ መታዘዛቸው ለመቊረብ ስለማይችሉ ነው። የጥንቱ ትምህርተ ወንጌል ሰዓት ወንጌል ከተነበበ በኋላ ኤጲስ ቆጶስ ካለ ወንጌሉን በእጁ ይዞ በክፍሎቹ የተነበበውን ለሕዝቡ ተርጉሞ ማስተማር ይገባዋል። ኤጲስ ቆጶስ ከሌለ ትርጓሜን የሚችል የተማረ ካህን እንዲያስተምር ታዝዟል (ፍትሐ ነገሥት ፲፪)። ትምህርቱ ግን ሳይበዛ ከዐሥራ ዐምስት ደቂቃ ባልበለጠ ወንጌሉንና ምስባኩን እንዲሁም የተነበቡትን መልእክታት በማቆራኘት ምስጢረ ቁርባንን ማዕከል በማድረግ አጭር ትምህርተ ወንጌል መስጠት ይገባል:: በዘመናችን ግን ወንጌል ከተነበበ በኋላ «ፃዑ ንዑሰ ክርስቲያን» ከመባሉ በፊት ትምህርተ ወንጌል መስጠት ከቆመ ዓመታት ተቆጥረዋል:: ለዚህ ብዙ ምክንያቶች መጠቀስ የሚችሉ እንደሆነ ቢገባኝም ሆኖም ግን የጥንቱን (የቀደመውን) የአባቶቻችንን ሥርዓት መሸራረፍም ሆነ ማዛነፍ ተገቢ አይደለም። እዚህ ጋር ቤተክርስቲያን የተመሠረተችው ለሁለት ዐቢይ ተልእኮ መሆኑ መታወቅ አለበት፤ ይኸውም ለቅዳሴና ለወንጌል ነው:: እነዚህ ሁለቱ የማይነጣጠሉ ሰምና ወርቅ፤ ድር እና ማግ፤ ጥርስ እና ከንፈር ሆነው የሚኖሩ የድኅነታችን ወሳኝ ጸጋዎች ናቸው:: ይልቁንም ወንጌል ደግሞ የጸጋዎች ሁሉ መግቢያ በር ነው። ሰው ሳይማር አይጠመቅም፤ ሳይጠመቅ አይቆርብም፤ ስለዚህ ጥምቀትም ቁርባንም የሚገኙት ከወንጌል ትምህርት የተነሣ ነው:: «ፃዑ» ከመባሉ በፊት ትምህርት የሚሰጥበት ምክንያት ለሁለት ዓላማ ነው። አንዱ ከሌላ ቤተ እምነት ወይም ከአምልኮተ ጣዖት የመጡ ለምሥጢረ ጥምቀት ደጅ የሚጠኑ ንዑሳነ ክርስቲያንን አስተምሮ ለመሸኘት ሲሆን፥ ለቍርባን የተዘጋጁ ምእመናን ደግሞ ፈሪሃ እግዚአብሔር ባልተለየው ልቡና፣ ትሕትና በተዋሐደው ስብእና ቀሪውን ሥርዐት እንዲከታተሉና በፍርሃትና በረዓድ ሆነው ወደ ቅዱስ ቁርባን እንዲቀርቡ ለማነቃቃት እንዲሁም ለማስጠንቀቅ ነው:: ይልቁንም እዚህ ላይ ትምህርት መስጠቱ ልዩ ጥቅም አለው። ይኸውም አንደኛ ምእመኑ በቁመት ብዛት ሰውነቱ ሳይዳከም ልቡናው ሳይደክም በትኩስ ተመስጦ በሞቀ መንፈሳዊ ኀይል ትምህርቱን በሚገባ ነቅቶ ተግቶ ይሰማል:: ሁለተኛው «ወንጌል መስማት» የከበረ የቅዳሴው አካል የድኅነት ማዕከል እንደሆነ በሚገባ እንዲገነዘብ ስለሚረዳ። እናስተውል! ዲ/ን ኃይለራጉኤል
