fa
Feedback
ያሬዳውያን

ያሬዳውያን

رفتن به کانال در Telegram

የየበዓላቱ ስርአተ #ዋዜማ ፤ #ማኅሌት ፤ #ወረብ ከ፯ ቀናት በፊት እንዲሁም የየሳምንቱ መዝሙራት እና ምስባክ በጽሑፍ እና በድምጽ የሚቀርቡበት ቻናል ነው #ሁሉም_ነገር_ስለ_ማኅሌት ለማስታወቂያ እና ለማንኛውም ጥያቄ ከፈለጉን አለን በዚህ ያናግሩን 👉 @Yaredawi_admin እናመሰግናለን

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ያሬዳውያን

کانال ያሬዳውያን (@eotcmahlet) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 123 058 مشترک است و جایگاه 252 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 243 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 123 058 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 03 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 3 397 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 22 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 14.68% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.88% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 18 060 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 9 693 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 54 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የየበዓላቱ ስርአተ #ዋዜማ ፤ #ማኅሌት ፤ #ወረብ ከ፯ ቀናት በፊት እንዲሁም የየሳምንቱ መዝሙራት እና ምስባክ በጽሑፍ እና በድምጽ የሚቀርቡበት ቻናል ነው #ሁሉም_ነገር_ስለ_ማኅሌት ለማስታወቂያ እና ለማንኛውም ጥያቄ ከፈለጉን አለን በዚህ ያናግሩን 👉 @Yaredawi_admin እናመሰግናለን

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 04 سپتامبر, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

123 058
مشترکین
+2224 ساعت
+4307 روز
+3 39730 روز
آرشیو پست ها
ሥርዓተ ማኅሌት ዘነሐሴ 28.pdf1.18 MB

ሰላም ያሬዳውያን ኪዳን በዜማ ከመጀመሪያው ጀምሮ ማወቅ ይፈልጋሉ? እንግዲያው ኪዳን የሚለውን በመጫን ማግኘት ይችላሉ ከፈለጉ ይችን ጠቅ 👉 ኪዳን

መዝሙር መድኃኔዓለም እግዚአብሔር ኀደረ ላዕሌሃ፤ ኪያሃ ዘሠምረ ሀገረ ኪያሃ ዘሠምረ ሀገረ ።

አቤቱ ሕዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ (ይ.ካ): ❝ኦ እግዚኦ አድኅን ሕዝበከ ወባርክ ርስተከ ራዓዮሙ ወአልዕሎሙ እስከ ለዓለም ወዕቀባ ለቤተ ክርስቲያኒከ ቅድስት እንተ አጥረይካ ወቤዘውካ በደሙ ክቡ
አቤቱ ሕዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ (ይ.ካ):
❝ኦ እግዚኦ አድኅን ሕዝበከ ወባርክ ርስተከ ራዓዮሙ ወአልዕሎሙ እስከ ለዓለም ወዕቀባ ለቤተ ክርስቲያኒከ ቅድስት እንተ አጥረይካ ወቤዘውካ በደሙ ክቡር ለዋሕድ ወልድከ እግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ወጸዋዕካ ትኩን ማህደረ ለነገሥት ወለመኳንንት ለዘመድ ንጹሕ ወለሕዝብ ቅዱስ እለ መጻእክሙ ወእለ ተጋባዕክሙ ወእለ ጸለይክሙ ውስተ ዛቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እለ በላዕክሙ ሥጋሁ ቅዱሰ፣ ወእለ ሰተይክሙ ደሞ ክቡረ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ይሥረይ ለክሙ ኃጢአተክሙ ዘገበርክሙ እመሂ በአእምሮ አው በኢያእምሮ በዘኀለፈ ይመሐርክሙ ወበዘይመጽዕ ይዕቀብክሙ በእንተ ሥጋሁ ሥጋ መለኮት ወበእንተ ደሙ ደመ ሕግ ወሥርዓት ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ጸባኦት ወወልደ ማርያም ንጽሕት በሕሊና ወበድንግልና ሥጋ ኅትምት ለዓለመ ዓለም አሜን❞
(...)
❝አቤቱ ሕዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ እስከ ዘለዓለሙ ጠብቃቸው ከፍ ከፍም አድርጋቸው፤ በአንድ ልጅህ በጌታችን በአምላካችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በክቡር ደሙ የዋጀሃት ቤዛም የሆንካት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ጠብቃት። ለነገሥታትና ለመኳንንት ለንጹሕ ወገን ቅዱስ ለሆነ ሕዝብ ማደሪያ ትሆን ዘንድ የጠራሃት በዚህች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መጥታችሁ ተሰብስባችሁ የጸለያችሁ፣ የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋን የበላችሁ፣ ክቡር ደሙንም የጠጣችሁ በማወቅ ወይም ባለማወቅ የሠራችሁትን ኃጢአታችሁን ይቅር ይበላችሁ፡፡ ሥጋ መለኮት ስለሚባል ሥጋው፣ የሕግና የሥርዓት ደም ስለሚባል ደሙ የአሸናፊ የእግዚአብሔር ልጅ፣ በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ኅትምት የምትሆን የማርያም ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ባለፈው ይቅር ይባላችሁ በሚመጣውም ይጠብቃችሁ ለዘለዓለሙ አሜን❞
(ትርጓሜ): ሕዝብን አድን - በኃጢአታቸው ከሚመጣባቸው ፍዳ፣ ኩነኔ በቸርነትህ አድናቸው ማለት ነው፡፡
❝እግዚአብሔር ይቅርታ አድራጊ ነው። እግዚአብሔር መሐሪ ይቅር ባይ ነው፡፡ ከቁጣ የራቀ፣ ምሕረቱ የበዛ፣ ጻድቅ እውነተኛ አዳኝ ማለት ነው❞
— እንዲል መዝ. ፻፪፥፮ ርስትህን ባርክ - ካህናቱን አክብር ማለት ነው፡፡ ካህናቱን «ርስት» ማለቱ ካህናት አስተምረው፣ አጥምቀውና አቁርበው ርስት መንግሥተ ሰማያትን ያሰጣሉና (ማቴ. ፳፰፥፲፱)። እስከ ዘለዓለም ጠብቃቸው ከፍ ከፍም አድርጋቸው - ልዕልና ነፍስ ሰጥተህ በነፍስ በሥጋ ጠብቃቸው ሲል ነው፡፡ «ልዕልና ነፍስ» ማለት የነፍስ ከፍታ ማለት ሲሆን በነፍስ የሚገኘውን ክብር ስጣቸው ማለት ነው፡፡ በአንድ ልጅህ በጌታችን በአምላካችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ - «አንድ ልጅህ» ሲል ሃይማኖታችን ወልድ ዋህድ ማለት ሲሆን ይህም ከዓለም መፈጠር በፊት ከአብ የተወለደው፤ ከዓለም መፈጠር በኋላ ከእመቤታችን የተወለደውን አንድ ወልድ ነው ማለት ነው፡፡
❝አብ ወልድን የወለደው ነውና ዳግመኛም በማይነገር በሃሳብም በማይመረመር ግብር መንፈስ ቅዱስ ከእርሱ ወይም ከአብ ተገኝቷልና አብ ከወልድ ወልድም ከመንፈስ ቅዱስ ሳይቀድም መንፈስ ቅዱስም ከወልድ፥ ወልድም ከአብ ወደ ኋላ ሳይሆን ወልድ ለአብ ለመንፈስ ቅዱስ ቃላቸው ነው፤ መንፈስ ቅዱስም ለአብ ለወልድ እስትንፋሳቸው ነው፡፡ አብም ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ልባቸው ነው❞
— ሃይማኖተ አበው ዘአቡሊዲስ ፴፱፥፯ በጥቅሉ አብ ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም። ወልድም ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፡፡ መንፈስ ቅዱስም ከአብ ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፡፡ ጥንት የሌለው ቀዳማዊ ልጅ ያለው እግዚአብሔር አብ ብቻ ነው፡፡ ዳግመኛ ወልድ አይመረመርም ማንም መርምሮ አያገኘውም፡፡ አብ ከዘመን በኋላ አልወለደውም፣ እርሱ ቀዳማዊ ወልድ ከአብ ጋር በቅድምና የነበረ ነው እንጂ የማይሞት ነው። ከማይሞት አብ ጋር ፈጣሪ ነው፤ እንደ አብ ሁሉን የፈጠረ ነው እንዲሁም መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ጋር በቅድምና የነበረ ቀዳማዊ ነው፤ በሥራውም ሁሉ ከአብ ከወልድ ጋር አንድ ነው — (ሠለስቱ ምዕት በሃይማኖተ አበው ፲፱፥፮)። በክቡር ደምህ የዋጀሃትን - ደምህን አፍስሰህ፣ ሥጋህን ቆርሰህ ያጸናሃትን ማለቱ ነው፡፡ የተቤዣችሁ (ያዳናችሁ) በሚጠፋ በወርቅ ወይም በብር እንዳይደለ ታውቃላችሁ ነውርና እድፍ እንደሌለው እንደ በግ ደም በክርስቶስ ክቡር ደም ነው እንጂ (፩ኛ ጴጥ ፩፥፲፰-፳፩)፡፡ ለነገሥታት ለመኳንንት ለንጹሕ ወገንና ቅዱስ ለሆነ ሕዝብ ማደሪያ ትሆን ዘንድ የጠራሃት - ነገሥታት መኳንንት ሥጋውንና ደሙን የሚቀበሉባት ለማለት ሲሆን ንጹሕ ወገንና ቅዱስ ሕዝብ የተባሉ እሥራኤል ዘሥጋ እና እሥራኤል ዘነፍስ ናቸው፡፡ ሁሉም አምነው ተጠምቀው ሥጋውን ደሙን የተቀበሉት ስለሆነ ለጌታችን በሥጋ ተዛምደው ያመኑት እስራኤል ዘነፍስ እና እስራኤል ዘሥጋ ይባላሉ፡፡ ሥጋ መለኮት ስለሚባል ሥጋህ - መለኮት የተዋሐደው ነፍስ የተለየው ሥጋ ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም የምንቀበለው ሥጋ ነፍስ የተለየው መለኮት የተዋሐደው ሥጋ ነውና የሕግና የሥርዓት ደም ስለሚባል ደሙ - በኦሪት እስራኤል ከግብጻውያን ባርነት ሊወጡ ሲሉ ከግብጽ ወደ ከነአን እንደሚሄዱና ለጊዜው በግብጻውያን ላይ ከታዘዘው ሞተ በኩር ወይም መቅሠፍት እንደሚድኑ ምልክት ይሆናቸው ዘንድ ጥፍሩ ያልዘረዘረ፣ ቀንዱ ያልከረከረ፣ ጠጉሩ ያላረረ ዓመት የሆነው ጠቦት አርደው እንዴት መብላት እንዳለባቸውና ደሙን በያሉበት ቤት በር ላይ እንዲቀቡ:-
❝ከደሙም ወስደው በሚበሉበት ቤት መቃኑንና ጉባኑን ወይም በሩን ይቅቡት … ደሙም ባላችሁበት ቤት ምልክት ይሆንላችኋል፡፡ ደሙንም አያለሁ እናንተንም እሠውራችኋለሁ እኔም የግብጽን ሀገር በመታሁ ጊዜ የጥፋት መቅሠፍት አይመጣባችሁም❞
— ተብለው ታዘዙ እነርሱም በታዘዙት መሠረት መቃኑን ጉበኑን ቀብተው ድነዋል፡፡ የበጉ ቀንድ ያልከረከረ፣ ጠጉሩ ያላረረ፣ ጥፍሩ ያልዘረዘረ መሆኑ የክርስቶስ ምሳሌ ሲሆን፤ በጉ ምንም ነውር የሌለበት መሆኑ በጌታችን ፍፁም ሰው፥ ፍጹም አምላክ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ ስለዚህ ሌላውን ሐተታ ለጊዜው እንተወውና በደሙ ምልክትነት እሥራኤል እንደ ዳኑ ሥጋውን ደሙን የተቀበሉም ምእመናን ከሲዖል፣ ከገሃነም ይድናሉ። በኦሪት በሥርዓት የበራቸውን መግቢያ በበጉ ደም ቀብተው ከመቅሰፍት እንደ ዳኑ እኛም በጌታችን ደሙ ፈሳሽነት ድነናልና «የሕግና የሥርዓት ደም» አለው (ዘፀ ፲፪፥፯)። የአሸናፊ የእግዚአብሔር ልጅ - የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ ማለት ነው፡፡ የእግዚአብሔር አብ አባትነት የእግዚአብሔር ወልድን ልጅነት ከዚህ ብፊት የተገለጠ ሲሆን በጥቅሉ ሲፈታ ከአብ የወልድ መወለድ የመንፈስ ቅዱስ መስረጽ በእፁብ ይወሰናል እንጂ እንዲህ ነው ተብሎ አይነገረም። ከሕሊና ሁሉ በላይ ነውና አይመረመርም ምክንያቱም አብ ወልድን የወለደው መንፈስ ቅዱስን ያሰረፀው ሳይቀድም ነውና — (ሃይማኖት አበው ዘዲዮናስዮስ ፲፥፲፪)። አብ ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፥ ወድም ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፥ መንፈስ ቅዱስም ከአብ ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም እንዲል ሃይማኖተ አበው — (ዘሠለስቱ ምዕት ፲፩፥፮)። በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ኅትምት የምትሆን የማርያም ልጅ - እመቤታችን ኃጢአትን ከማሰብ፣ ከመናገር፣ ከመተግበር የተለየች መሆኗን ለመግለጽ ሲሆን በዚሁ ንጽሕናዋ አምላክን የወለደች አምላክ ከእርሷ የተወለደ መሆኗን ለመመስከር ነው፡፡ ዲ/ን ኃይለራጉኤል

+5
#አቋቋም_ዘጳጕሜን_ሩፋኤል_#መልክአ_ሩፋኤል፡_ለገበዋቲከ_#ዚቅ፡_ውእቱ_ሊቆሙ_#Akuakuam_Ze_Pagumen.m4a5.99 MB

share 👇👇👇👇👇🇪🇹 👉@EOTCmahlet👈 👉@EOTCmahlet👈 👉@EOTCmahlet👈 🇪🇹👆👆👆👆👆👆🇪🇹 @EOTCmahlet # Join & share

✨ EU የሐበሻ ልብስ ✨ 👨‍👩‍👧‍👦 ለመላው ቤተሰብዎ የሚሆኑ ውብ እና ዘመናዊ የሐበሻ ልብሶች! 🌼 ለወንዶች፣ ለሴቶች እና ለልጆች 🌼 ከፍተኛ ጥራት ባለው ጨርቅ የተዘጋጁ 🌼 ዘመናዊ እና
✨ EU የሐበሻ ልብስ ✨ 👨‍👩‍👧‍👦 ለመላው ቤተሰብዎ የሚሆኑ ውብ እና ዘመናዊ የሐበሻ ልብሶች! 🌼 ለወንዶች፣ ለሴቶች እና ለልጆች 🌼 ከፍተኛ ጥራት ባለው ጨርቅ የተዘጋጁ 🌼 ዘመናዊ እና ባህላዊ ዲዛይኖች 🌼 ለበዓላት፣ ለቤተክርስቲያን ፕሮግራሞች ተስማሚ አዲስ አመትን በማስመልከት በልዩ ቅናሽ ዋጋ! 📲 በ 0913020450 ላይ ይደውሉ ወይም @eyoell ላይ መልዕክት ይላኩልን። 📢 ለማየት፣ ለማዘዝ እና አዳዲስ ዲዛይኖችን ለመከታተል ቻናላችንን ይቀላቀሉ! 📲 Telegram: @eyuhabeshantibeb

6 ቤት ሲሆን መልክዕ አቋቋም ደሞ እንሆ የተቀሩትን መልክዕ አቋቋም ይላካል

+1
03_ሩፋኤል_ሐዋርያ_አመላለስ_ዘመልክዕ.mp31.47 KB

#አቋቋም_ዘጳጕሜን_ሩፋኤል_#መልክአ_ሩፋኤል፡_ለቃልከ_#ዚቅ፡_ሩፋኤል_ግሩም_#Akuakuam_Ze_Pagumen.mp38.28 MB

🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷 መልክአ ሩፋኤል አቋቋም ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ መልክዕ 5 ቤት ሆነ 6 ማንሻ አለው ። ማንሻ(ማ) ሚለው 4ተኛ ቤትን ሲሆን ከማንሻው ተነስቶ ከከበሮ ጋር ይቀርባል ። ምሣሌ፦ @EOTCmahlet ሰቆቃወ ድንግል [፩]አይቴ ሀሎ ንጉሰ እስራኤል ዘተወልደ፤ [፪]ከመ ነሀብ ሎቱ አምኃ ወሰጊደ፤ [፫]እንዘ ይብሉ ሰብአ ሰገል ሰሚዖ ገሃደ፤ [፬👉]ሄሮድስ አሜሃ በእሳተ ቅንአት ነደ፤ [፭] ከመ ይቅትሉ ሕፃናተ ወኢያትረፉ አሐደ፤ [፮] እስከ ቤተልሄም ወገሊላ ሐራሁ አዖደ ፬ ቁጥር ወይም ሄሮድስ አሜሃ ማንሻ ሲሆን እንደምታዩት ሁሉም ቤት በተመሳሳይ ቃል (ደ በምትለው) ይጨርሳል። ማወቅ ያለባችሁ ከእንግዲህ የምንጠቀማቸው ቃላት 1.ጉረሮ- ማንሻን ጀምሮ ወደታች ያለ ከበሮ እና ጽናጽል አቋቋም ዜማውን ብቻ እያዜሙ ወደ ታች መውረድ ሲሆን መልክዕ ሲጀመር እና ወረብ እና ዚቅ ከተባለ በኃላ መጨረሻ ላይ ይባላል 2.ቁም -ጽናጽል እና ከበሮ ጋር መልክዕን ማለት ሲሆን የከበሮ አመታቱም ጠባቧን የከበሮ ክፍል 4ቴ ከዛ ሰፊውን የከበሮ ክፍል አንዴ // ጠባቧን የከበሮ ክፍል 2ቴ ሰፊውን የከበሮ ክፍል አንዴ ከአቋቋም ዜማ ጋር ይቀርብበታል 3. መረግድ -በብዛት ሰፊውን የከበሮ ክፍል በመጠቀም ከአቋቋም ዜማ ጋር የሚቀርብበት ነው 👇👇👇👇👇 የመልክዕ አባባል መልክዕ ምስጋና መሆኑን አይተናል ። 4 አይነት የመልክዕ አባባል አሉ ፩.አጭር የመልክዕ አባባል ፪.መካከለኛ የመልክዕ አባባል ፫.ረጅም የመልክዕ አባባል ፬.ዐቢይ ድረባ የመልክዕ አባባል @EOTCmahlet እስቲ እግዚአብሔር አምላክ እንደፈቀደ ለማየት እንሞክራለን @EOTCmahlet ፩.አጭር የመልክዕ አባባል ነገር በምሳሌ እንዲሉ አበው እንዲገባችሁ በመልክዕ ምሳሌ እንየው @EOTCmahlet @EOTCmahlet     መልክአ ሩፋኤል ሰላም ለቃልከ ዘይደምፅ እመብረቅ: ለእስትንፋስከኒ እስትንፋሰ መንፈስ ረቂቅ: ሩፋኤል ሐዋርያ ወመልአከ ጽድቅ: ይጸንሑከ እግዚኦ ዕሡራነ በዓል በጻሕቅ: ነዓ ነዓ እምሕላዌከ ምጡቅ ውስተ ቤትከ ዛቲ ክርስቶሳዊት ምርፋቅ፡፡ [፩]ሰላም ለቃልከ ዘይደምፅ እመብረቅ፤ [፪ለእስትንፋስከኒ እስትንፋሰ መንፈስ ረቂቅ፤ [፫]ሩፋኤል ሐዋርያ ወመልአከ ጽድቅ፤ [፬]ይጸንሑከ እግዚኦ ዕሡራነ በዓል በጻሕቅ፤ [፭]ነዓ ነዓ እምሕላዌከ ምጡቅ [፮]ውስተ ቤትከ ዛቲ ክርስቶሳዊት ምርፋቅ @EOTCmahlet መልክዕ ማንሻ አለው ብለናል ፣ እዚህ ጋር ማንሻው ፬ቤት ወይም ይጸንሑከ እግዚኦ ብሎ አቋቋም ይጀምራል @EOTCmahlet ያለ ከበሮና ጽናጽል  በፊት በጉረሮ 👉 ይጸንሑከ እግዚኦ ዕሡራነ በዓል በጻሕቅ: ነዓ ነዓ እምሕላዌከ ምጡቅ ውስተ ቤትከ ዛቲ ክርስቶሳዊት ምርፋቅ፡፡ @EOTCmahlet በቁም ከከበሮና ጽናጽል ጋር @EOTCmahlet 👉ይጸንሑከ እግዚኦ ዕሡራነ በዓል በጻሕቅ፤ ነዓ ነዓ እምሕላዌከ ምጡቅ ፤ይጸንሑከ እግዚኦ ዕሡራነ በዓል በጻሕቅ: ነዓ ነዓ እምሕላዌከ ምጡቅ 👉ውስተ ቤትከ ዛቲ ክርስቶሳዊት ምርፋቅ፡፡ውስተ ቤትከ ዛቲ ክርስቶሳዊት ምርፋቅ፡፡ @EOTCmahlet መረግድ፦ 👉ይጸንሑከ እግዚኦ ዕሡራነ በዓል በጻሕቅ፤ ነዓ ነዓ እምሕላዌከ ምጡቅ ፤ይጸንሑከ እግዚኦ ዕሡራነ በዓል በጻሕቅ: ነዓ ነዓ እምሕላዌከ ምጡቅ 👉ውስተ ቤትከ ዛቲ ክርስቶሳዊት ምርፋቅ፡፡ በቁም 👉ሩፋኤል ሐዋርያ ወመልአከ ጽድቅ፤ ይጸንሑከ እግዚኦ ዕሡራነ በዓል በጻሕቅ፤ ነዓ ነዓ እምሕላዌከ ምጡቅ፤ ውስተ ቤትከ ዛቲ ክርስቶሳዊት ምርፋቅ፡፡ @EOTCmahlet አመላለስ፦ ሩፋኤል ሐዋርያ/፪/ ወመልአከ ጽድቅ/፪/ መረግድ 👉ይጸንሑከ እግዚኦ ዕሡራነ በዓል በጻሕቅ፤ ነዓ ነዓ እምሕላዌከ ምጡቅ፤ ውስተ ቤትከ ዛቲ ክርስቶሳዊት ምርፋቅ፡፡ @EOTCmahlet በቁም 👉ሰላም ለቃልከ ዘይደምፅ እመብረቅ: ለእስትንፋስከኒ እስትንፋሰ መንፈስ ረቂቅ: ሩፋኤል ሐዋርያ ወመልአከ ጽድቅ: ይጸንሑከ እግዚኦ ዕሡራነ በዓል በጻሕቅ: ነዓ ነዓ እምሕላዌከ ምጡቅ ውስተ ቤትከ ዛቲ ክርስቶሳዊት ምርፋቅ፡፡ @EOTCmahlet በመረግድ 👉ሰላም ለቃልከ ዘይደምፅ እመብረቅ፤ሰላም ለቃልከ ዘይደምፅ እመብረቅ፤ ለእስትንፋስከኒ እስትንፋሰ መንፈስ ረቂቅ፤ለእስትንፋስከኒ እስትንፋሰ መንፈስ ረቂቅ፤ ሩፋኤል ሐዋርያ ወመልአከ ጽድቅ፤ ላይ ቤት ከሆነ ቁመቱ በቁም ታች ቤት ከሆነ በመረግድ ይህን ይላሉ 👇 👉ይጸንሑከ እግዚኦ ዕሡራነ በዓል በጻሕቅ፤ ነዓ ነዓ እምሕላዌከ ምጡቅ፤ ውስተ ቤትከ ዛቲ ክርስቶሳዊት ምርፋቅ፡፡ (ምርፋቅ) ብለው ከጨርሱ በኋላ ወደ ዚቅ ያመራሉ ዚቅ በቁም 👉 ሩፋኤል ግሩም: በመንፈስ ቅዱስ ሕቱም: መዓዛ ቅዳሴከ ጥዑም: ከመ ጽጌ ገዳም: ነዓ ነዓ ማዕከሌነ ቁም: በበዓልከ ባርከነ ዮም። መረግድ ዚቅ 👉ሩፋኤል ግሩም: በመንፈስ ቅዱስ ሕቱም: መዓዛ ቅዳሴከ ጥዑም: ከመ ጽጌ ገዳም: ነዓ ነዓ ማዕከሌነ ቁም: በበዓልከ ባርከነ ዮም። ወረብ እዚህ ጋር ይባላል 👉ወረብ ነዐ ነዐ ማዕከሌነ ቁም/፪/ በበዓልከ ባርከነ ዮም/፪/ ወረቡ ከተወረበና ከተዘመረ በኃላ @EOTCmahlet ዚቁ ካለቀ በኃላ ያለ ከበሮና ጽናጽል  በፊት በጉረሮ 👉 መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ መልክዕ የእመቤታችን ምሳሌ ነው 👉 መልክዕ ፭ ቤት መሆኑ ለአዳም  የ፭ሺ ፭ መቶ ዘመን ሞሳሌ ነው @EOTCmahlet 👉መልክዕ ፮ ቤት መሆኑ ጌታችንን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከ፭ሺ ፭ መቶ ዘመን ከተፈጸመ በኃላ ፮ ሺህ ዘመን ላይ ከእመቤታችን መወለዱ ምሳሌ ነው @EOTCmahlet መልክዕ ከመጨረሻ ጀምሮ ከላይ ወደ ታች እየተመረገደ መውረዱ ጌታችንን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት የመውረዱ ምሳሌ ነው @EOTCmahlet መልክዕ ከታች ሰላም ብሎ መጸንጸሉ  ስለኛ ኃጢአት ብሎ ከድንግል ማርያም ተወልዶ በማየ ዮርዳኖስ ተጠምቆ በዕለተ አርብ በዕጸ መስቀል ተሰቅሎ በ፫ኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነስቶ በ፵ኛው ቀን የማረጉ ምሳሌ ነው @EOTCmahlet ዚቅ የጌታችንን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ሲሆን ፤መልክዕ ከተባለ በኋላ ዚቅ መባሉ ከድንግል ማርያም መገኘቱ ፤መወለዱ ምሳሌ ነው 👇👇👇👇👇🇪🇹 👉@EOTCmahlet👈 👉@EOTCmahlet👈 👉@EOTCmahlet👈 🇪🇹👆👆👆👆👆👆🇪🇹 @EOTCmahlet #ይቀላቀሉ & #ለወዳጅዎ_ሼር_ያርጉ

#መልክዓ_ሩፋኤል_ለዝክረ_ስምከ_ዚቅ_#ሀበነ48k.mp313.49 MB

መልክዕ 5 ቤት ሲኖረው አቋቋሙ ይህ ነው

🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷 መልክአ ሩፋኤል አቋቋም ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ መልክዕ 5 ቤት ሆነ 6 ማንሻ አለው ። ማንሻ(ማ) ሚለው 4ተኛ ቤትን ሲሆን ከማንሻው ተነስቶ ከከበሮ ጋር ይቀርባል ። ምሣሌ፦ @EOTCmahlet መልክዓ ኢየሱስ፦ [፩]ሰላም ለዝክረ ስምከ ስመ መሃላ ዘኢይሔሱ፤ [፪]ዘአንበረ ቅድመ እግዚአብሔር በአትሮንሱ፤ [፫]ኢየሱስ ክርስቶስ ለዳዊት ባሕርየ ከርሱ፤ [፬👉]አክሊለ ስምከ እንዘ ይትቌጸል በርእሱ፤ [፭]አህጉረ ፀር ወረሰ ኢያሱ። ፬ ቁጥር ወይም አክሊለ ስምከ ማንሻ ሲሆን እንደምታዩት ሁሉም ቤት በተመሳሳይ ቃል (ሱ በምትለው) ይጨርሳል። ማወቅ ያለባችሁ ከእንግዲህ የምንጠቀማቸው ቃላት 1.ጉረሮ- ማንሻን ጀምሮ ወደታች ያለ ከበሮ እና ጽናጽል አቋቋም ዜማውን ብቻ እያዜሙ ወደ ታች መውረድ ሲሆን መልክዕ ሲጀመር እና ወረብ እና ዚቅ ከተባለ በኃላ መጨረሻ ላይ ይባላል 2.ቁም -ጽናጽል እና ከበሮ ጋር መልክዕን ማለት ሲሆን የከበሮ አመታቱም ጠባቧን የከበሮ ክፍል 4ቴ ከዛ ሰፊውን የከበሮ ክፍል አንዴ // ጠባቧን የከበሮ ክፍል 2ቴ ሰፊውን የከበሮ ክፍል አንዴ ከአቋቋም ዜማ ጋር ይቀርብበታል 3. መረግድ -በብዛት ሰፊውን የከበሮ ክፍል በመጠቀም ከአቋቋም ዜማ ጋር የሚቀርብበት ነው 👇👇👇👇👇 የመልክዕ አባባል መልክዕ ምስጋና መሆኑን አይተናል ። 4 አይነት የመልክዕ አባባል አሉ ፩.አጭር የመልክዕ አባባል ፪.መካከለኛ የመልክዕ አባባል ፫.ረጅም የመልክዕ አባባል ፬.ዐቢይ ድረባ የመልክዕ አባባል @EOTCmahlet እስቲ እግዚአብሔር አምላክ እንደፈቀደ ለማየት እንሞክራለን @EOTCmahlet ፩.አጭር የመልክዕ አባባል ነገር በምሳሌ እንዲሉ አበው እንዲገባችሁ በመልክዕ ምሳሌ እንየው @EOTCmahlet @EOTCmahlet     መልክአ ሩፋኤል [፩]ሰላም ለዝክረ ስምከ ተጸውዖ ዘቀደመ፤ [፪በአፈ አምላክ አዳም እንበለ ይሰመይ ስመ፤ [፫]ሩፋኤል ምልዓኒ ወወስከኒ ዳግመ፤ [፬]መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ [፭]ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ። @EOTCmahlet መልክዕ ማንሻ አለው ብለናል ፣ እዚህ ጋር ማንሻው ፬ቤት ወይም መንፈስ ቅዱሳዌ ብሎ አቋቋም ይጀምራል @EOTCmahlet ያለ ከበሮና ጽናጽል  በፊት በጉረሮ 👉 መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ @EOTCmahlet በቁም ከከበሮና ጽናጽል ጋር @EOTCmahlet 👉መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ 👉ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ @EOTCmahlet 👉ሩፋኤል ምልዓኒ ወወስከኒ ዳግመ፤ መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ @EOTCmahlet በመረግድ- 👉ሩፋኤል ምልዓኒ ወወስከኒ ዳግመ፤ሩፋኤል ምልዓኒ ወወስከኒ ዳግመ፤ መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ @EOTCmahlet በቁም 👉ሰላም ለዝክረ ስምከ ተጸውዖ ዘቀደመ፤በአፈ አምላክ አዳም እንበለ ይሰመይ ስመ፤ ሩፋኤል ምልዓኒ ወወስከኒ ዳግመ፤ መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ @EOTCmahlet በመረግድ 👉ሰላም ለዝክረ ስምከ ተጸውዖ ዘቀደመ፤በአፈ አምላክ አዳም እንበለ ይሰመይ ስመ፤ ሩፋኤል ምልዓኒ ወወስከኒ ዳግመ፤ ላይ ቤት ከሆነ ቁመቱ በቁም ታች ቤት ከሆነ በመረግድ ይህን ይላሉ 👇 👉መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ (አቅመ) ብለው 5ተኛ ቤቱን ከጨርሱ በኋላ ወደ ዚቅ ያመራሉ ዚቅ በቁም 👉 ሀበነ እግዚኦ አዕይንተ አእምሮ ወትረ ኪያከ ይርአያ: ወአዕዛንነሂ ቃለ ዘባሕቲትከ ይስምዓ። መረግድ 👉ዚቅ ሀበነ እግዚኦ አዕይንተ አእምሮ ወትረ ኪያከ ይርአያ: ወአዕዛንነሂ ቃለ ዘባሕቲትከ ይስምዓ። ወረብ እዚህ ጋር ይባላል 👉ወረብ ሀበነ እግዚኦ አዕይንተ አእምሮ ወትረ ኪያከ ይርአያ/፪/ ወአዕዛንነሂ ቃለ ዘባሕቲትከ ይስምዓ/፪/ ወረቡ ከተወረበና ከተዘመረ በኃላ @EOTCmahlet ዚቁ ካለቀ በኃላ ያለ ከበሮና ጽናጽል  በፊት በጉረሮ 👉 መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ ፪. መካከለኛ የመልክዕ አባባል ከአጭር መልክዕ አባባል ትንሽ ብቻ የሚለይ ሲሆን ሰላም ለዝክረ ስምከ ሚለው ን እንደማሳያ እንይ ያለ ከበሮና ጽናጽል  በፊት በጉረሮ 👉 መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ @EOTCmahlet በቁም ከከበሮና ጽናጽል ጋር @EOTCmahlet 👉መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ መረግድ 👉መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ @EOTCmahlet ቁም 👉ሩፋኤል ምልዓኒ ወወስከኒ ዳግመ፤ መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ @EOTCmahlet በመረግድ- 👉ሩፋኤል ምልዓኒ ወወስከኒ ዳግመ፤ሩፋኤል ምልዓኒ ወወስከኒ ዳግመ፤ መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ @EOTCmahlet በቁም 👉ሰላም ለዝክረ ስምከ ተጸውዖ ዘቀደመ፤በአፈ አምላክ አዳም እንበለ ይሰመይ ስመ፤ ሩፋኤል ምልዓኒ ወወስከኒ ዳግመ፤ መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ @EOTCmahlet በመረግድ 👉ሰላም ለዝክረ ስምከ ተጸውዖ ዘቀደመ፤ሰላም ለዝክረ ስምከ ተጸውዖ ዘቀደመ፤በአፈ አምላክ አዳም እንበለ ይሰመይ ስመ፤ በአፈ አምላክ አዳም እንበለ ይሰመይ ስመ፤ ሩፋኤል ምልዓኒ ወወስከኒ ዳግመ፤ ላይ ቤት ከሆነ ቁመቱ በቁም ታች ቤት ከሆነ በመረግድ ይህን ይላሉ 👇 👉መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ (አቅመ) ብለው 5ተኛ ቤቱን ከጨርሱ በኋላ ወደ ዚቅ ያመራሉ ዚቅ በቁም 👉 ሀበነ እግዚኦ አዕይንተ አእምሮ ወትረ ኪያከ ይርአያ: ወአዕዛንነሂ ቃለ ዘባሕቲትከ ይስምዓ። መረግድ 👉ዚቅ ሀበነ እግዚኦ አዕይንተ አእምሮ ወትረ ኪያከ ይርአያ: ወአዕዛንነሂ ቃለ ዘባሕቲትከ ይስምዓ። ወረብ እዚህ ጋር ይባላል 👉ወረብ ሀበነ እግዚኦ አዕይንተ አእምሮ ወትረ ኪያከ ይርአያ/፪/ ወአዕዛንነሂ ቃለ ዘባሕቲትከ ይስምዓ/፪/ ወረቡ ከተወረበና ከተዘመረ በኃላ @EOTCmahlet ዚቁ ካለቀ በኃላ ያለ ከበሮና ጽናጽል  በፊት በጉረሮ 👉 መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ፤ ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ @EOTCmahlet ✍️ማሳሰቢያ የሚደገሙትን እየደገምን የጻፍንላችሁ "👉" ምልክት ብቻ እናንተ እያያችሁ ተከተሉ 🇪🇹👇👇👇👇👇👇🇪🇹 👉@EOTCmahlet👈                  👉@EOTCmahlet👈 👉@EOTCmahlet👈 🇪🇹👆👆👆👆👆👆🇪🇹       @EOTCmahlet     # Join & share

+2
መዝሙረ_ዳዊት_አንድምታ_ትርጓሜ_በሊቀ_ሊቃውንት_ዕዝራ_ሐዲስ360p.mp4170.14 MB

☦️የሮሜ መልእክት የመጨረሻው ማብራሪያ ይሰጣል ☦️ ✔️መ/ር ነቢዩ ኤልያስ Telgram ፦ https://t.me/Terha_Tsion Youtube፦ https://youtube.com/@tserhatsion?
☦️የሮሜ መልእክት የመጨረሻው ማብራሪያ ይሰጣል ☦️ ✔️መ/ር ነቢዩ ኤልያስ Telgram ፦ https://t.me/Terha_Tsion Youtube፦ https://youtube.com/@tserhatsion?si=qh_eLZt0L3sAkacr

አስደናቂ ሥራዎቹን ተመልከቱ ከትንሽ Poster - Complex Illustrations Yonas ይባላል ። ከ3 ወራት በፊት ስለ ግራፊክስ የሚያውቀው ም ን ም ነበረ ። አሁን ላይ ግን የዓመታት ልምድ
+3
አስደናቂ ሥራዎቹን ተመልከቱ ከትንሽ Poster - Complex Illustrations Yonas ይባላል ። ከ3 ወራት በፊት ስለ ግራፊክስ የሚያውቀው ም ን ም ነበረ ። አሁን ላይ ግን የዓመታት ልምድ ያላቸው ዲዛይነሮችን የሚፈታተን ባለሙያ ሆኗል 😊 ምክንያት .... Green Bird Tech ስለተማረ ! Check his Instagram Profile Here Instagram Linkedin እዚህ Poll Vote ላይ ብዙዎቻቹ ብቁ ስለመሆናቹ እርግጠኛ መሆን እንደፈለጋቹ አይተናል ። ይሄው ምስክር 🤗 በቂ ጊዜ የለኝም ላላችሁም እንድሁ 2 ወራት ይህን ያክል መሥራት እንደሚችሉ ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ። ተማሩ ተሸለሙ የፈጠራ አቅማችሁን ዕድል ስጡት ። ራሳችሁን በኢኮኖሚ አግዙ ። _______________________ @greenbirdtechs @greenbirdtechs የለውጥዎ ክንፍ 🔑 🐥

ሥርዐተ ቅዱስ ወንጌል ካህናት ወንጌልና ኪዳን ሲያነብቡ ጥምጥማቸውን ያወልቃሉ፤ አክሊላቸውንም ያወርዳሉ ይኸውም ለአክብሮተ ወንጌል ነው:: ወንጌል በሚነበብበት ጊዜ መቆም እንጂ መቀመጥ ፈጽሞ ክልክል
ሥርዐተ ቅዱስ ወንጌል ካህናት ወንጌልና ኪዳን ሲያነብቡ ጥምጥማቸውን ያወልቃሉ፤ አክሊላቸውንም ያወርዳሉ ይኸውም ለአክብሮተ ወንጌል ነው:: ወንጌል በሚነበብበት ጊዜ መቆም እንጂ መቀመጥ ፈጽሞ ክልክል ነው። ካህኑ አንብቦ ሲጨርስ ራሱ ተሳልሞ ከንፍቅ ካህን ጀምሮ እንደ የማዕረጋቸው ያሳልማቸዋል ካህናቱ ከተሳለሙ በኋላ ምዕመናን ይሳለማሉ ኾኖም በሚሳለሙበት ጊዜ ሴቶች ክንብንባቸውን ከራሳቸው ላይ አውርደው መሳለም ይገባቸዋል፤ ንጉሥም ቢሆን እንኳ ዘውዱን ማውረድ አለበት::
❝ነአምን በቃለ ወንጌል ቅዱስ — ቅዱስ በሆነው በወንጌልህ ቃል እናምናለን❞
— እያሉ እጅ እየነሡ ክንብንባቸውን እያወረዱ ይሳለማሉ በቃለ ወንጌል ማመናቸውን ይመሰክራሉ:: ክብረ ወንጌል በቅድስት ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ቅዱስ ወንጌል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ቅድሚያ የሚሰጠው ከፍ ያለ ክብር ያለው እንደሆነ የታወቀ ነው:: ስለ ክብረ ወንጌል የማይነገርበት ሥርዐት እና አምልኮ ቤተክርስቲያን የላትም:: በቅድስት ቤተክርስቲያን ቅዱስ ወንጌልን የማያሳትፍ ጸሎት፣ ቁርባን፣ መሥዋዕትና አገልግሎት የለም:: ማኅሌትና ሰዓታት ሲቆም፤ ጸሎተ ፍትሕት ሲደረስና ጸሎተ ተክሊል ሲከናወን በእነዚህ ሁሉ መስቀል ተይዞ ወንጌል ይነበባል:: በአጠቃላይ ቅዱስ ወንጌል የማይነበብበት የአገልግሎት ዘርፍም ሆነ የጸሎት ክፍል ቤተክርስቲያን የላትም። ይህም ለቅዱስ ወንጌሉ ያላትን ክብር ከፍ አድርጎ ያሳያል:: ቅዱስ ወንጌል ለሥርዐት፣ ለአምልኮት፣ ለሕግጋትና ለአገልግሎት መሠረት በመኾኑ ከሌሎቹ ሥርዓቶች የበለጠ ክብር ይሰጠዋል። ለምሳሌ:- በቅዳሴ ጊዜ ወንጌል ሲነበብ የደከመ/የታመመ እንኳን ቢሆን በዚያች በንባብ ቅጽበት ውስጥ ድካሙንም ሕመሙንም እንደምንም ችሎም ቢሆን ቆሞ እንዲያደምጥ ይታወጃል:: አዋጁን የሚያውጀው ገባሬ ሠናዩ ዲያቆን:-
❝ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን ቅዱስ ወንጌል ቆማችሁ አድምጡ!❞
— የሚለው አዋጅ ከታወጀ በኋላ የተቀመጠ ካለ ቀጥ ብሎ ሕሊናውን ሰብስቦ ይቆማል:: (እዚህ ጋር ዲያቆኑ ወንጌሉን «አድምጡ» እንጂ «ስሙ» አይልም። በሁለቱ ቃላት መካከል ያለውን ልዩነት ልብ በሉ!) ዲያቆኑ ቁሙ ወአጽምዑ ማለቱ የንፍሐተ ቀርን፤ ካህኑ ወንጌል ማንበቡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፍርድ ቀን «ንዑ ኀቤየ፥ ሑሩ እምኔየ» ብሎ ፍርድ የማስተላለፉ ምሳሌ ነው:: በዚህ ጊዜ የሚደወለው ደወል የግርማ መዓቱ፤ ወንጌል ከተነበበ በኋላ መጋረጃ መዘጋቱ ሑሩ እምኔየ ብሎ ኀጥአንን የማሰናበቱ ምሳሌ ነው። (የቅዳሴ አንድምታ) ወንጌል ከተነበበም በኋላ ንፍቅ ካህን ወንጌል መስማት ክብሩ ምን ያህል እንደሆነ ሲናገር እንዲህ ይላል:-
❝ክቡር የሚሆን የወንጌልህን ቃል እንሰማ ዘንድ እንሳለመውም ዘንድ ደስ ይለን ዘንድ ለዚህ የበቃን ያደረግኸን ሁሉን የያዝህ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ ላንተ ምስጋና ይገባሃል! ዳግመኛም ክቡር የሚሆን የወንጌልህን ቃል በልቡናችን ትጽፍ ዘንድ እንለምናለን እንማልድሃለን❞
— ብሎ ይማጸናል:: የቅዱስ ወንጌል ክብሩ የሚጀምረው መጽሐፉን ከማክበር ሲሆን ይኸውም አቅም ያለው ደብር የመጽሐፉን ገበታ (የውጭውን ሽፋን) በወርቅ እና በብር ያስጌጡታል አቅም የሌለው ደብር ደግሞ በወርቃማ ሱቲ (በከበረ ልብስ) ያለብሱታል:: ይህ ሁሉ ታዲያ ክብሩን ለመግለጥ ነው:: ምእመናን ቅዱስ ወንጌልን እንዴት ባለ ሁኔታ መስማት እንደሚገባቸው ሥርዓተ ቅዳሴው ሲናገር:-
❝የሰማያዊውን ንጉሥ የከበረ የወንጌሉን ቃል ለመስማት ከመጀመሪያቸው እስከ መጨረሻቸው ድረስ ከማመስገን ከመቀደስ በቀር ማድነቅና ጸጥታ ሊሆን ይገባል:: የምድራዊ ንጉሥ ደብዳቤ ሲነበብ አንድ ሰው እንኳን ለመናገር የማይደፍር ከሆነ፤ ቢናገርም ቅጣትና ግርፋት የሚያገኘው ከሆነ የሰማያዊው ንጉሥ ደብዳቤ የምትሆን ወንጌል ሲነበብ የሚናገር ምን ያህል ቅጣት ያገኘው ይሆን?❞
— በማለት ወንጌል ሲነበብ ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረግ እንደሚገባው ሥርዐተ በቅዳሴያችን ያስጠነቅቃል:: ጸሎተ ወንጌል ከተፈጸመ በኋላ ንፍቅ ዲያቆን መብራት ይዞ በፊት፥ ንፍቅ ካህን ማዕጠንት ይዞ በኋላ ሆኖ ሁለቱም በቅድስት በቀኝ በኩል ዞረው በሰሜን የመቅደሱ በር ይገባሉ:: ሠራዒ ዲያቆን በቅድስቱ ላይ ሆኖ ፊቱን ወደ ምዕራብ መልሶ ቃጭል እየመታ:- «ጻዑ ንዑሰ ክርስቲያን» ይላል። ይህንንም የሚያውጅበት ምክንያት «ንዑሰ ክርስቲያን» የሚባሉት የክርስትና ሃይማኖትን በማጥናትና ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን በመከታተል ላይ ያሉት ገና ያልተጠመቁ አዲስ ክርስቲያኖች ሲሆኑ እንዲወጡ መታዘዛቸው ለመቊረብ ስለማይችሉ ነው። የጥንቱ ትምህርተ ወንጌል ሰዓት ወንጌል ከተነበበ በኋላ ኤጲስ ቆጶስ ካለ ወንጌሉን በእጁ ይዞ በክፍሎቹ የተነበበውን ለሕዝቡ ተርጉሞ ማስተማር ይገባዋል። ኤጲስ ቆጶስ ከሌለ ትርጓሜን የሚችል የተማረ ካህን እንዲያስተምር ታዝዟል (ፍትሐ ነገሥት ፲፪)። ትምህርቱ ግን ሳይበዛ ከዐሥራ ዐምስት ደቂቃ ባልበለጠ ወንጌሉንና ምስባኩን እንዲሁም የተነበቡትን መልእክታት በማቆራኘት ምስጢረ ቁርባንን ማዕከል በማድረግ አጭር ትምህርተ ወንጌል መስጠት ይገባል:: በዘመናችን ግን ወንጌል ከተነበበ በኋላ «ፃዑ ንዑሰ ክርስቲያን» ከመባሉ በፊት ትምህርተ ወንጌል መስጠት ከቆመ ዓመታት ተቆጥረዋል:: ለዚህ ብዙ ምክንያቶች መጠቀስ የሚችሉ እንደሆነ ቢገባኝም ሆኖም ግን የጥንቱን (የቀደመውን) የአባቶቻችንን ሥርዓት መሸራረፍም ሆነ ማዛነፍ ተገቢ አይደለም። እዚህ ጋር ቤተክርስቲያን የተመሠረተችው ለሁለት ዐቢይ ተልእኮ መሆኑ መታወቅ አለበት፤ ይኸውም ለቅዳሴና ለወንጌል ነው:: እነዚህ ሁለቱ የማይነጣጠሉ ሰምና ወርቅ፤ ድር እና ማግ፤ ጥርስ እና ከንፈር ሆነው የሚኖሩ የድኅነታችን ወሳኝ ጸጋዎች ናቸው:: ይልቁንም ወንጌል ደግሞ የጸጋዎች ሁሉ መግቢያ በር ነው። ሰው ሳይማር አይጠመቅም፤ ሳይጠመቅ አይቆርብም፤ ስለዚህ ጥምቀትም ቁርባንም የሚገኙት ከወንጌል ትምህርት የተነሣ ነው:: «ፃዑ» ከመባሉ በፊት ትምህርት የሚሰጥበት ምክንያት ለሁለት ዓላማ ነው። አንዱ ከሌላ ቤተ እምነት ወይም ከአምልኮተ ጣዖት የመጡ ለምሥጢረ ጥምቀት ደጅ የሚጠኑ ንዑሳነ ክርስቲያንን አስተምሮ ለመሸኘት ሲሆን፥ ለቍርባን የተዘጋጁ ምእመናን ደግሞ ፈሪሃ እግዚአብሔር ባልተለየው ልቡና፣ ትሕትና በተዋሐደው ስብእና ቀሪውን ሥርዐት እንዲከታተሉና በፍርሃትና በረዓድ ሆነው ወደ ቅዱስ ቁርባን እንዲቀርቡ ለማነቃቃት እንዲሁም ለማስጠንቀቅ ነው:: ይልቁንም እዚህ ላይ ትምህርት መስጠቱ ልዩ ጥቅም አለው። ይኸውም አንደኛ ምእመኑ በቁመት ብዛት ሰውነቱ ሳይዳከም ልቡናው ሳይደክም በትኩስ ተመስጦ በሞቀ መንፈሳዊ ኀይል ትምህርቱን በሚገባ ነቅቶ ተግቶ ይሰማል:: ሁለተኛው «ወንጌል መስማት» የከበረ የቅዳሴው አካል የድኅነት ማዕከል እንደሆነ በሚገባ እንዲገነዘብ ስለሚረዳ። እናስተውል! ዲ/ን ኃይለራጉኤል

ለበለጠ መረጃ 0925484488 ወይም 0976211621
ለበለጠ መረጃ 0925484488 ወይም 0976211621

ጻድቁ ሐብተማርያም መተናል እኛ ልጆችህ            አድነን አውጣን ከፈተና አልብሰን የብርሀንን ፋና ፃድቁ   ሰባት አክሊላትን "      " በራሱ የደፋ  "      " በጾም በፀሎቱ "      " ሰይጣንን ያጠፋ "      " ፅድቅን የታጠቀ "     " የእግዚአብሔር አገልጋይ "     " ፃድቁ አባታችን  ፃድቁ የኢትዮጵያ ሲሳይ ፃድቁ  ብርሃንን ለብሶ "   "  የእሣት  መስቀልይዞ "     " በጾም ፀሎት ሰይፍን                                              "     " ንፅህናውን መዞ "     " በደብረ ሊባኖስ "     " ለኛ የፀለየው "    " የተዋሕዶ ብርሀን አቡነ ሐብተማርያም ነው "     " የዮስትና ፀጋ "      " የፍሬ ብሩክ     "      " ለኛ ለልጆችክ "      " መመኪያ የሆንክ     "     "  በምልጃህ አድለን "     "  ፍቅርና ሰላምን "     " ፃድቁ አባታችን  አቡነ ሐብተ ማርያም ፃድቁ  ከሱራፌል ጋራ    "      " ለማቅረብ ምስጋና                                  "      " ወርቅን ተጎናጽፈክ  "     " ሀብተ ንፅሕና     "     " ሚስጥር ተካፈልክ "     " ከፅረ አርያም     "      "ፃድቁ አባታችን አቡነ ሐብተማርያም ፃድቁ  ባለመቶ ፍሬ "      " ሀብተማርያም         "      " ቤታችንን ሙላው  "      " ፍቅርና ሰላም  "     "  በደብረ ሊባኖስ "     "  ለኛ የፀለየው "     "  የተዋሕዶ ብርሀን አቡነ ሐብተማርያም ነው