የሙጎ አህሉሱናህ ወልጀመዓ ስብስብ
የሚከተለው link(ሊንክ) ጆይን በማድረግ የጀመዓውን የቴሌግራም ቻናል በመቀላቀል ከሚለቀቁ ፅሁፎች ትምህርት እንውሰድ ፡፡ <<መሀበረሰቡን ከበዕድ አምልኮ አላቆ አለህን በብቸኝነት እንዲገዛ ሰበበን ማድረስ የሁላችንም ሀላፍትና ነው>> የሙጎ እና የአከባቢው የአህሉ ሱና ወልጀመዓ የቴሌግራም ቻናል ፡፡ በchannelu ያላችሁን አስተያየት በውስጥ መስመር @Abuhuzeyfa በሚል ማስተላለፍ ይችሃላል።
نمایش بیشتر- مشترکین
- پوشش پست
- ER - نسبت تعامل
در حال بارگیری داده...
در حال بارگیری داده...
ሱናን ከተረዳን በኋላ ኡስታዞች ሲቀየሩ እነሱን ትተን የተረዳነውን ሱና ሙጭጭ አድርገን መያዝ እንዳለብን ይጠቁማል።
ነጥብ ❸ የመርከዙ ሰዎች (ሙመይዓዎች) ከ8 አመት በፊት የነበራቸውን አቋም ቀይረው ዛሬ ሌላ አቋም እንደያዙ በሳዳት አንደበት ተገልጿል።
ነጥብ ➍ የሰዎች ጥፋት ግልፅ ሆኖ ሳለ እኔ ጃሂል ነኝ እያሉ የኡስታዞቻቸውን ጥፋት ለመሸፋፈን በመሻት የሚጃጃሉ ወጣቶች ትክክል እንዳልሆኑ በሳዳት ተመክሯል። ዛሬ ላይ ከእሱ በጭፍን ለሚከላከሉ ሁሉ መልዕክት ነው።
ነጥብ ❺ ኡስታዝ ተብየዎች እንደበግ ሲነዱህ የምትነዳ መሆን እንደሌለብህ ተጠቁሟል። የሚገርመው ግን ሳዳት በመርከዙ ሰዎች ጠንካራ አቋም ሲሮረው አንበሳ የሚሆኑ፤ ሳዳት ቀዝቀዝ ሲል እንደ ጀናዛ የሚሆኑ ሳዳት እንዳለው ጅላጅል ወጣቶች መኖራቸው ነው።
ነጥብ ❻ የኢብኑ መስዑድ መርከዝ ሰዎች በፊት ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚከለክሉና አሁን እንደማይከለክሉ፤ እንዲሁም ከቢድዓ ሰዎች ጋር መራራቅ እንዳለብን የሚመክሩ ነገር ግን አሁን አቋማቸው መቀየሩ በተዘዋዋሪ በሳዳት አንደበት ተመስክሯል።
ነጥብ ❼ ኡስታዞች የዱንያ ጥቅም አታሏቸው ወይም ጠመው ሲገለበጡ እኛኮ ከኡስታዞቹ አንወጣም በሚል አስተሳሰብ መጃጃል ከሱፍይ ሙሪዶች የማይሻል አካሄድ እንደሆነ ተጠቁሟል።
ነጥብ ❽ የመርከዙ ሰዎች (ሙመይዓዎች) ትናንት ኢኽዋንን ከሱፍዮች ጋር ተስማማ ብለው ሲቃወሙ የነበሩ ቢሆንም ዛሬ ተገልብጠው ራሳቸው ተዘፍቀውበታል። የሚያሳዝነው የራሳቸው ሲሆን የመስለሃ ስም እንደሚሰጡት ተገልጿል።
ነጥብ ❾ የመርከዙ ሰዎች (ሙመይዓዎች) ከኢኽዋን የተቃወሙትን ስምምነት ለራሳቸው ገብተውበት ለመስለሃ ነው ሲሉ ለራሳቸው {ለግላቸው} መስለሃ ሊሆን ለአክሲዮናቸው ለድርጅታቸው መስለሃ ሊሆን እንደሚችል ነገር ግን ለዲን መስለሃ እንዳልሆነ ተብራርቷል።
↪️ቆይ አንድ ጊዜ↩️
ሳዳት አሁን ላይ የመርከዙ ሰዎች (ሙመይዓዎች) ጠበቃ ከመሆኑ በፊት ስለ አክሲዮን እያወራ ነበር። በአሁኑ ሰዓት ግን ስለ አክሲዮን የሚያነሱ ሰዎችን ለአላህ ብለው አይደለም እያለ ነው። ለምን ይሆን? አስፈላጊ ከሆነ ለብቻ በሰፊው እመለስበታለሁ።
ነጥብ ❿ የመርከዙ ሰዎች (ሙመይዓዎች) የተውሂድ ሰዎችን እንደሚጠሉ ወደ ተውሂድና ሱና የሚጣሩ ሰዎችን እንደሚነድፉ ተጠቁሟል።
ነጥብ ⓫ ሱናን ከተረዱ በኋላ ጃሂል ነኝ እያሉ ወደኃላ ማፈግፈግ ወይም ማላገጥ የትም እንደማያደርስ ተጠቁሟል። ትናንት እነሳዳት በመርከዙ ሰዎች ሲናገሩ ከነሱ በልጦ ሲያነበንብ የነበረ ወጣት ዛሬ እነሳዳት ዝም ሲሉ ጃሂል ነኝ እነ ኢልያስን ለመናገር አቅሜ አይደለም የሚል ከሆነ እውነትም ጃሂል ነው። ግን አያዋጣም!!!
ነጥብ ⓬ ጃሂል ነኝ ከምትል ኪታብ ቅራ ስትቀራ ኡስታዞች አቋማቸውን ሲቀይሩ አሪፍ መነፅር ስለያዝክ ቻው ኡስታዝ ከተመለስክ ወደ ድሮው ተመለስ! አለበለዚያ ትቸህ ሄጃለሁ! እንደ ድሮው ጃሂል ነኝ እያልኩ በሪሞት ኮንትሮል ቆም ስትለኝ አልቆምም እገሌን ጥላ ስትለኝ አልጠላም እገሌን ውደድ ስትለኝ አልዎድም የሚል ቆራጥ ውሳኔ መያዝ እንዳለብን ተመክሯል። ለአንዳንድ ወጣቶች ወሳኝ ምክር ነው።
ነጥብ ⓭ ድሮ ሱንዮች ከሙሪድነት የወጡ ነበሩ። ሱፍዮች ብቻ ሸይኾቻቸው መጠጥ ሲጠጡ ብርዝ ነው ይሉላቸው እንደነበር ተገልጿል። ዛሬም አንዳንዶቹ ሰለፍይ ነኝ እያሉ ኡስታዞቻቸው ሲያጠፉ የፈለጉበት እንዲህ ነው እያሉ ስህተቶቻቸውን የማይቀበሉ ዘመናዊ ሙሪድ ሆነዋል።
ነጥብ ⓮ ትናንት አገሌ ሸይኽ ኢኽዋንን ሲያስጠነቅቅ ቆይቶ ዛሬ ደግሞ ስለ ኢኽዋንን ማውራት ማለት ሚሳኤል ሆኖበታል። ይሄው ስድስት ሰባት አመት ተከርችሟል የታለ አፉ ስትለው መሻይኾቹኮ ጠንቅቀው ያውቃሉ የሚሉ መሪዶች ስለመኖራቸው ተገልጿል። በነገራችን ላይ በዚህ መልኩ እየተነገረ ያለው በመርከዙ ሰዎች [በሙመይዓወች] ላይ ስለመሆኑ ጥርጥር የለም።
ነጥብ ⓯ "ትናንት ስታውቀው የነበረውን ሀቅ ዛሬ ከገለበጥከው እድገቱ ወደታች ነው" ይለናል ሳዳት ይሄ ማለትኮ መሟሟት መቅለጥ ማለት ነው። በቃ ስለ ሙመይዓዎች ጥሩ ግንዛቤ ነበረው ማለት ነው።
ነጥብ ⓰ ኡስታዝኮ እውቀታቸው ስለጨመረ መዲና ተምረው ስለመጡ ሱዳን ደርሰው ስለመጡ ብለን እያልን ከጥፋታቸው መከላከል ተገቢ አለመሆኑ ተብራርቷል። በተለይም ኢልያስ አህመድ መዲና ተምሯል መስጂደ-ነበዊ አስተምሯል እያሉ ከስህተቱ ለመከላከል የሚጥሩ ሙሪዶችን በተመለከተ ጥሩ ምክር ነው።
ነጥብ ⓱ የራሳችንን ድክመት ስንደክም ደክመናል ብለን ልናስተካክል፤ ሁሌም ያለንበት ነገር ልክ ነው እንደማይባል በሸሪዓ መመዘን እንዳለብን ተብራርቷል።
ነጥብ ⓲ ሰዎች ራሳቸውን ሚዛን አድርገው ያስቀምጡና እነሱ ሲሰሩ ጊዜ ልክ ነበሩ ሲተኙም ልክ ነበሩ እነሱ ሲተኙ ሰው ሲሰራ ደግሞ ሰው ፈጥኗል ሰው ተሳስቷል ይላሉ እውነት ለመናገር ይች ንግግር በሰዓቱ ለመርከዙ ሰዎች ብትሆንም ዛሬ ለማን እንደምትሆን አስተንትኑ! በመርከዙ ሰዎች ላይ አራስ ነብር የነበሩት አካላት አሁን ላይ ሌሎችም ሲያግዟቸው እነሱ ተኙና ሌሎችን ችኩሎች ስህተተኞች ማለት ጀመሩ
↪️የጉድ አገር አሉ አበዎች↩️
ነጥብ ⓳ ዛሬ ሰዎች አቋማቸውን የሚቀያይሩበት ጊዜ ነው። አንተ ዘንድ ሲሆን ኢኽዋኖች አስቸገሩን ይላል ሌላ ቦታ ሲሄድ እነዚህ ፅንፈኞች አስቸገሩን ይላል። አዎ ከመርከዙ ሰዎች ከፊሎቹ ተግባራቸው ከዚህ የተለየ አይደለም። ዛሬ ላይ በአንዳንዶች ቢዘነጋም የወቃሾችን ወቀሳ በማይፈሩ ጀግኖች የመርከዙ ሰዎች እየተንኮታኮቱ ነው።
ነጥብ ⓴ አንተጋ ሲሆን ሀፊዘከሏህ ወራዓክ እያለ በቃላት ቢከሽንህም እላይ ቢያጦዝህም ወደዚያ ዞር ያለ ቀን ከማጠልሸት አይቆጠብም። ከዚህ በቀላሉ ስሜታቸውን ከሚከተሉ ሰዎች ጋር መንቀሳቀስ እንደሌለብን እንገነዘባለን።
ማጠቃለያ፦ ሳዳት ከማል በዚህ ምክር ላይ ያነሳቸውን ነጥቦች ሁሉም ወጣቶች (በተለይ ሙሪዶች) ሊተገብሩት ይገባል። በተጨማሪም የመርከዙ ሰዎች ላይ እንደዚህ ጠንከር ያለ አቋም እንደሚያስፈልግ በግልፅ መረዳት ይቻላል። እነሳዳትም በነሱ ላይ በፊት እንዲሁ ጠንካሮች ነበሩ።
እርምት ያለው ➘➘➘⬇️↙️
https://t.me/AbuImranAselefybot
➚➚➚ በዚህ ያድርሰኝ
ዝም አንልም እኛ በህይወት እስካለን፤
ባለችው አቅማችን እንፋለማለን፤
ያበጠው ይፈንዳ ሲፈልግ ይተርተር፤
እውነት ይነገራል ቢጣፍጥም ቢመር።
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefyየሚጃጃሉ ወጣቶች!!! =≡=≡=≡=≡=≡=≡=> 🎙 በሳዳት ከማል አንደበት ➧ ከዚህ ምክር የተወሰኑ ነጥቦችን አጠረሰ አድርገን እንመልከት፦ ነጥብ ❶ ሳዳት በዚህ ምክር የመርከዙ ሰዎችንና እነሱን ተከትለው ሙሪድ የሆኑ ወጣቶችን በተመለከተ እያወራ መሆኑን እንገነዘባለን። ነጥብ ❷ ሱናን ከተረዳን በኋላ ኡስታዞች ሲቀየሩ እነሱን ትተን የተረዳነውን ሱና ሙጭጭ አድርገን መያዝ እንዳለብን ይጠቁማል። ነጥብ ❸ የመርከዙ ሰዎች (ሙመይዓዎች) ከ8 አመት በፊት የነበራቸውን አቋም ቀይረው ዛሬ ሌላ አቋም እንደያዙ በሳዳት አንደበት ተገልጿል። ነጥብ ➍ የሰዎች ጥፋት ግልፅ ሆኖ ሳለ እኔ ጃሂል ነኝ እያሉ የኡስታዞቻቸውን ጥፋት ለመሸፋፈን በመሻት የሚጃጃሉ ወጣቶች .... ይህንን ጨምሮ ሌሎች ⓴ ነጥቦችን በሚከተለው ሊንክ ገብተው ያንብቡ!!! ➘➴➷ ⬇️⬇️⬇️↙️↙️↙️
https://t.me/AbuImranAselefy/4867እርምት ያለው ➘➘➘⬇️↙️
https://t.me/AbuImranAselefybot➚➚➚ በዚህ ያድርሰኝ ዝም አንልም እኛ በህይወት እስካለን፤ ባለችው አቅማችን እንፋለማለን፤ ያበጠው ይፈንዳ ሲፈልግ ይተርተር፤ እውነት ይነገራል ቢጣፍጥም ቢመር። ➘➴➷➘➴➷➘➴➷
https://t.me/AbuImranAselefyhttps://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
እራስህን ሁል ጊዜ ለቁርኣንና ለሀዲስ ተጎታች አድርግ! በአንድ ነገር ላይ ከቁርኣንና ከሀዲስ ማስረጃ ሳታገኝ አቋም አትያዝ! ሁሌም ለሰዎች መልካምን ተመኝ! ለሀቅ እንጂ ለሰዎች ወጋኝ አትሁን