cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ኦርቶዶክስ ተማሪዎች (አርበኞቹ!!)

❝ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ፥ መልካም ነው እነሆም፥ ያማረ ነው።❞ መዝሙር 133: 1 ይህ መንፈሳዊ ቻናል ለኢትዮዮጵያ ተማሪዎች ስለ ሀይማኖታችን አዳዲስ ነገሮች የምናውቅበት ህብረትና አንድነት የምንፈጥርበት የተለያዩ ነገሮች የምንማማርበት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናላችን ነው። አስተያየት ጥቆማ ወይም ጥያቄ ካላቹ ከታች ባለው አድርሱን: @Am_Olan_K @yoTod_776

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
317
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

6፤ ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይኾናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፥ ኀያል አምላክ፥ የዘለዓለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል። 7፤ ከዛሬ ዠምሮ እስከ ዘለዓለም ድረስ በፍርድና በጽድቅ ያጸናውና ይደግፈው ዘንድ በዳዊት ዙፋንና በመንግሥቱ ላይ አለቅነቱ ይበዛል፥ ለሰላሙም ፍጻሜ የለውም። የእግዚአብሔር ቅንአት ይህን ያደርጋል። ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ 9፥ 6-7 እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሠላም አደረሳችሁ!!
نمایش همه...
#ይድረስ_ለሴቶች_እህቶቼ_አንብቡት ወንዶችም አንብባችሁ ለእህቶቻችን ሼር ሼር ሼር በማድረግ አጋሩ አዲስ ተች ስልክ የገዛችውን ልጅ አባቷ ሲያያት . . . . . . . ›› አባት ፡ “”ስልኩን ስትገዢ በመጀመሪያ ያደረግሽው ምንድነው ? “” ብሎ ጠየቃት፡፡ ልጅ ፡ “”በመጀመሪያ ያደረኩት . . . ስክሪኑ እንዳይጫጫር መከላከያ ስቲከር ለጠፍኩበት . . . “” አባት ፡ “” እንደዚ እንድታደርጊው የገፋፋሽ ሰው እለ ?”” ልጅ ፡ “” የለም ! ! ! “” አባት ፡ “”ያመረቱትን እንደ ማንቋሸሽ አይሆንም ግን . . .”” ልጅ ፡ “”ኧረ አባዬ ! እንደውም የሚመክሩን እንድንለጥፍበት ነው ! ”” አባት ፡ “” የሸፈንሽው ግን ርካሽ ስለሆነ ወይም ስለሚያስጠላ ነው ??? “” ልጅ ፡ “”” በነገራችን ላይ የሸፈንኩት . . . እንዳይበላሽብኝ እና ብዙ ግዜ እንዲያገለግለኝ ስለምፈልግ ነው ! “” አባት ፡ “”” ስትሸፍኝው . . . ውበቱን አልቀነሰውም “” ልጅ ፡ “”” እንደውም በጣም አምሮበታል በዛ ላይ እንዳይበላሽ ይከላከልልኛል “” አባት ፡ በአባትነት ዓይን እያያት “”” አንድ ጥያቄ ብጠይቅሽስ. . . ከስልክሽ የሚበልጠውን ገላሽን እንድትሸፍኝው . . . እሺ ትይኛለሽ ወይ ??? `` ሁሌም አባታችን እግዚአብሔር ይጠይቀናል በሰው ላይ አድሮ . . . . ብቻ በብዙ ነገር ራሳችንን እንድንሸፍን ይጠይቀናል ! 👉🏼 የምናስተውል ካለን መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል"፤ 👉🏼 ሴቶች በሚገባ ልብስ ከእፍረትና ራሳቸውን ከመግዛት ጋር ሰውነታቸውን ይሸፍኑ (1 ኛ ጢሞ 2፥9) 👉🏼 በሚሞት ስጋችሁ ሐጢያት አይንገስ ብልቶቻችሁን የፅድቅ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር አቅርቡ (ሮሜ 6፥12-14) 👉🏼 ከሴት ጋር አለመገናኘት መልካም ነው ካልተቻለ ዝሙትን ለመከላከል በአንድ ይፅና ከዚህ ውጭ ጉዞ ወደ እሳት ነው (1ኛ ቆሮ 7፥1) 👉🏼 ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱ ያፈርሰዋል ቤተ መቅደሱም እናንተው ናችሁ (1ኛ ቆሮ 3፥17) 👉🏼 የወንድ ልብስ የለበሰች ሴት በአምላክ ዘንድ የተጠላች ናት (ዘዳ 22፥5; ዘፀ 39፥28) 👉🏼 ፀጉሯን ሳትሸፍን የምትፀልይ ሴት እራሷን ያዋረደች ናት(1ኛ ቆሮ 11፥5) እንድናስተውል እና እንደ እግዚአብሔር ቃል እንድንኖር እግዚአብሔር ይርዳን አሜን
نمایش همه...
.....አብዛኛዎቹ ቀመሮች እስካሁንም ወደፊትም ከጥቂት ኢትዮጵያውያን ውጭ ማንም ተመራምሮ የማያገኛቸው ሲሆኑ ከዓለም ሀገራት በተለየ ለኢትዮጵያውያ ብቻ የታደሉ የኢትዮጵያ ብርቅዬ ሀብቶች ናቸው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ጊዜው ደርሶ የዚህ ቀመር ምስጢር በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ምድር ሲዙረጋ ዛሬ ኢትዮጵያውያን ወደ አሜሪካና አውሮፓ ለመሄድ የሚናፍቁትን ያክል ያን ጊዜ የሁሉም ሀገር ዜጋ ኢትዮጵያ ለመግባት ይናፍቃል። ይህም የሚሆነው ያን ጊዜ ኢትዮጵያ ዓለም ላይ የሌለ የፈጠራ ሥራ ውጤት ባለቤት የምትሆንበት ፣ ትምህርት አይገባቸውም የሚባሉት ሰዎች በጥቂት አመታት ውስጥ የብዙ ዕውቀት ባለቤት የሚሆንበት ፣የሰውን ልጅ አይምሮ በደስታ የሚመስጥ ፣ ያሬዳዊ ጣዕመ ዜማ ከአሁኑ በተለየ መንገድ የሚሰማበት ፣ ሀገር እንድትሆን ለብዙ አመታት የተደከመበት ውጤታማ ቀመር ስላላት ነው። 🇨🇬( ፌላሌምሌሞንም ገፅ ፲፭)🇨🇬 ........................"ለማንኛውም እንካ ይሄ የትምህርት መድኃኒት ሠላሳና አርባ ዓመት ደክመህ የማትጨርሰውን ትምህርት አንድ አመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ እንድትሸመድድ የሚያስችል ነው።" አሉኝ ብርሌ የጨበጠውብ እጃቸውን ወደኔ በመዘርጋት። ይህን መድኃኒት የቀመሰ ሰው የሚጠበቅበት ሁሉንም የትምህርት አይነቶች ያለመምህር አንድ ጊዜ ማንበብ ወይም ሲነበቡ ማዳመጥ ብቻ ነው። ቅድም እንደነገርኩህ ይህ አሠራር በኢትዮጵያ ምድር ሲዘረጋ አንደኛ ደረጃ ፣ሁለተኛ ደረጃ ፣ ከፍተኛ ትምህርት (ዮኒቨርስቲ ) ፣ዲፕሎማ ፣ዲግሪ ፣ ዶክትሬት ፣ማስተርስ በሚባሉ የትምህርት ዓይነት የምንደክመው አሥራ ሁለት አመት እስኪሞላን ድረስ ብቻ ነው። ከዚያ በኋላ በዚህ የረቀቀ ጥበብ ሁሉም የሀገሪቱ ዜጋ ዕድሜው ለአቅመ ትምህርት ከሚደርስበት ከአራትና አምስት ዓመቱ ጀምሮ የሚማረው ትምህርት ዕውቅ ተመራማሪ የሚሆንበት እድል ያጎናፅፈዋል አሉኝ አንዱን በፈሳሽ የተሞላ ብርሌ አንስተው እያቀበሉኝ። ይህ የሚሆንበት ሁሉም ኢትዮጵያውያን ይህንን ጸጋ የሚላበሱበት ዘመን ወደፊት የሚመጣው ዘመነ ቴዎድሮስ ሲሆን የጊዜው እርዝመትም 40 ዘመን እንደሆነ ይነገርለታል አሉኝ። ከእጃቸው ተቀብዬ ያለምንም ማቅማማት ጨለጥኩት። 🇨🇬{ፌላሌምሌሞንም ገፅ፲፱} 🇨🇬
نمایش همه...
እባካችሁ<< ይህን መልእክት ካስተላለፍክ በሕይወትህ አንድ ለውጥ ታያለህ ካላስተላለፍክ ትጎዳለህ>> የሚል በሰው በሚጫወቱ የአህዛብ እና የመናፍቃን ድርሰትን ሼር ከማድረግ ተቆጠቡ። ቆይ ምኑ ነው ሀይማኖታዊ ቅርጽ ያለው ፈውስ አይፈጸምም እያልኩ አይደለም ግን እስኪ ደራሲው ምን ማለት እንደፈለገ እዩት።"አንዱ ኦፌሰር ለ 13 ሰው ልኮ ከ13 ቀን በኋላ ማእረግ ተጨመረለት" ይላል በርግጥ እንደዚህ አይነቱን ከቤተክርስቲያን ያፈነገጠ መልእክት ሳይሆን ቤተክርስቲያንናችን የምታስተምረውን ነገር ለሰው ማካፈል ጥሩ ነገር ሳይሆን ማድረግ ያለብን ነገርም ነው ።ትምህርት እና ሕይወት ያገኘንበትን ነገር ለሌሎች አለማካፈል ብቻዬን ልብላ እንደማለት ነው። ግን እንዚህ አይነት ነገሮችን ሼር ስናደርግ በጽሁፉ እንደገለጸው ማእረግ ለማግኘት ወይም ማንኛውንም ምድራዊ ጥቅም ለማግኘት ነው እንዴ...???ይህን ካሰባችሁ ሼር ባታደርጉት ይሻላል። የእኛ ጥቅም ሰማያዊ እናም መንፈሳዊ በረከት ነው ከዚህ ውጪ ካሰብን በሌላ ቋንቋ ለአገልግሎታችን ከፈጣሪ ጉቦ እየጠየቅን ነው ።ሌላው "አንዱ ሼር ሳያደርግ ቀርቶ 13 ቀን ከሰረ" ይለናል ይህ ደግሞ ፍጹም ውሸት ኢ -ኦርቶዶክሳዊ ነገር ነው ። ፈጣሪ ማንንም አስገድዶ አያሰራም፣ ስላልሰራለት ማንንም አይቀጣም በራሱ ዋጋውን አጣ እንጂ እንኳን ይቺን ስንት ስራ ብትሰራ በራስህ ፍቃድ እንጂ ተገደህ አይደለም ካልፈለክ መተወት መብትህ ነው ።ከሰራህ ዋጋ አለህ ካልሰራህ ያ ዋጋ ወይም በረከት ቀረብህ ለሌላ ለሚሰራ ይተላለፋል አለቀ ።ከዚህ ቀጥሎ ያለው ነው የጸሐፊውን ማንነት የሚያሳብቀው እና ፍጹም ከቤተክርስቲያን ትምህርት ተቃራኒ የሚናገረው የመጀመሪያው<< እኔ አምላክህ ነኝ ከሕይወትህ 30 ደቂቃ #ብቻ ስጠኝ >> የሚለው ነው ።እንደዚህ ነው እንዴ የተማርነው ፈጣሪ ከሕይወታችን 30 ደቂቃ ብቻ እንድንሰጠው ነው ያዘዘን ..?? በምድር ሳላችሁ በእያንዳዷ ደቂቃ ሁሉ ሀሳባችሁ ስለክርስቶስ ይሁን ነው እኮ የተባልነው። እንደው ይህን ባትችሉ በቀን 7 ጊዜ ለጸሎት ቁሙ በየእቅስቃሴያችሁ ሁሉ ፈጣሪን ከማመስገን አትዘናጉ ነው የተባልነው ወገኖቼ 30 ደቂቃ እንኳን ለሕይወት ዘመን ለግማሽ ቀንም በጣም ጥቂት ነው ።ይበቃል ካልን ለእኛ ክርስቲያን ስማችን እንጂ ግብራችን አይደለም። ቀጥሎ ደግሞ ፍጥጥ ያለ ውሸት መባል የሚያንሰውን አምላካችሁ አላችሁ ይለናል እሱም <<ጸልይ አልልህም >> ይሄንንስ ከዲያብሎስ ውጪ ማንም አላላውም ። ሳታቋርጡ ጸልዩ 1ኛ ተሰ 5፥17 ወደፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ ሉቃ 22፥46 ሳይታክቱም ዘወትር ሊጸልዩ እንደሚገባቸው....ሉቃ 18፥1 እና በጣም ብዙ ስለጸሎት የተነገረንን ረስተን ነው ይህን ፈጣሪ ጸልይ አልልህም ይላችኋል የሚል መልእክት ለሰው ሼር የምናደርገው...??ከዛ እባክህ ይህን መልእክት ላክ ህልምህ እውን ይሆናል ምናምን የሚሉ ነገሮች አሉ አሁንም ልንገራችሁ ለአንድ ሰው የሆነ ነገር ስናካፍል እሱ ይጠቅመዋል ብለን እንጂ እኛ ለመጠቀም ብለን አይደለም ።ትምህርት ወይም ምክር ከሆነ ሼር ያደረከው ያደረስክለት ሰው ከመልእክቱ እንዲጠቀምበት ብለህ እንጂ ያንተ ህልም እንዲሳካልህ አስበህ መሆን የለበትም ።ሲጀመር ይሄ ሃይማኖታዊ አይሉት ግብረ ገብነት አይሉት በጎ ፍቃድ አይሉት ምንድነው ቆይ እንደው ከሃይማኖታዊ ነገር የወጣ ቢሆን እንኳን የሚያስታላልፈው መልእክት ለራስ ጥቅም ሲሆን ብቻ ሰውን መርዳት እና ራስ ወዳድነትን ነው የሚሰብከው ።እናም ይህን እና እንደዚህ አይነት መልእክቶችን በየዋህነት ሼር የምታደርጉ ወንድምና እህቶቼ እያስተዋላችሁ ገና እባክህ ለማንበብና ለማስተላለፍ ሞክር ሲል ይህ የኦርቶዶክስ ወይም ቤተክርስቲያናዊ መልእክት አይደለም ወይም በጣም አጠራጣሪ ነው ማለት ትችላላችሁ ።ቤተክርስቲያን <<እባክህ ሼር አድርግ ለራስህ ጥቅም ነው>> ብላ የምታስተላለው ምንም ነገር የላትም ።
نمایش همه...
አምስቱ ቅንዋተ መስቀል ችንካሮች ሳዶር፣ አላዶር፣ ዳናት፣ አዴራ እና ሮዳስ ይባላሉ። ትርጉማቸውም እንዲህ ነው፦ እየሱስ ክርስቶስ 1. ሳዶር፦ ሳዶር ማለት ቀኝ እጁ የተቸነከረበት ነው። 2. አላዶር፦ አላዶር ማለት ግራ እጁ የተቸነከሩበት ነው። 3. ዳናት፦ ዳናቴ ማለት እግሮቹ የቸችነከሩበት ነው። 4. ሮዳስ፦ ሮዳስ ማለት ከወገቡ (እምብርቱን) አጣብቆ እንዲይዘው የተቸነከሩበት ነው። 5. አዴራ፦ አዴራ ማለት ደረቱን አጣብቆ እንዲይዘው የተቸነከሩበት ነው። 💚💛❤
نمایش همه...
ስለ ኢትዮጲያ ትንሳኤ የሚመሰክር ቆየት ያለ ድንቅ የበገና መዝሙር።
نمایش همه...
ጾም ስግደቱ ሲቆም; ፀሎቱም ተረሳ እኛም መሞት; ጀመርን አንተ ስትነሳ
نمایش همه...
"ቃል ሥጋ ኮነ" በመዠመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። ይህ በመዠመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ። በቃሉም ትዕዛዝ ምድርን ፈጠረ። አባትህን አዳም በርሷ አሳደረ አርሱ ግን ሳተና በደለ ቃልም ሥጋ ሆነ፣ ለአዳም ሲል ተሰቀለ ላንተ ለልጁ ሕይወትን አደለህ ይህን ድንቅ ነገር ተምረህ በሥጋ ደስታ ሰክረህ በመንፈስ ታድሰህ በርትተህ ደግሞ ወጣህና አስኳላ ገባህ። እርሱም ይህን አስተማረህ፦ አንተም ገርሞህ እየሰማህ፣ ባእድ ቃላቱ እያማለሉህ፣ ማድመጥህን ቀጠልህ። በመጀመሪያ ባዶነት ነበረ ቢግ ባንግም በባዶነት ዘንድ ነበረ ቢግ ባንግም አቧራ ነበረ በግራቪቲም ትዕዛዝ ፕላኔት ፈጠረ ፕላኔትም ውሃን አቆረ በውሃው ውስጥ ሴልን አሳደረ ሴልም ሳተና ተቀየረ አዲሱ ዝርያ በሚዩቴሽን ተፈጠረ ሴልም አሣ ሆነ። ታሪክም ተቀየረ ሴል እግር አወጣ ወደ የብስም ወጣ አሳ አዞ ኾነ "ቃል ሥጋ ኮነ" የሚለው ተኰነነ። ከልብህ ከልብሽ፣ ከልቤ ተነነ ከህይወት ራቅነ በእውቀት ጠፋነ በክህደት ዘለቅነ "ግኖስቲኮስ" ተቀበልነ ሳይንስም አለነ፦ አሳ አዞ ሆነ አዞ "ፕራይሜት" ሆነ ፕራይሜት ጦጣ፣ ጦጣም ሰው ሆነ እኛ ሰዎች ክስተት ነነ የባሕር ውስጥ ሴል የሚዩቴሽኑ ውጤት የስህተት ልጆች ነነ ከዝብርቅርቅ ከኬኦስ የመጣን ከዩኒቨርስ አንጻር ነጥብ የማንሆን ዋጋ የሌለን ከንቱ ፍጥረት ነን "ኢንሲግኒፊካንት" ነን ብለን አመን የፈረንጁን ትምህርት፣ የአላዋቂውን እውቀት በአበደ አእምሮ የፈጠረውን "ምጥቀት" እኔ ክቡሩ፣ አመሳለ እግዚእ ፍጥረት አምኜ ተቀብዬ አስፍሬ በወረቀት ቃል ሥጋ ኮነ የሚለው ተኰነነ ወረቀት ዲግሪ ኮነ ዲግሪ እውቀት ኮነ ጥበብ ተኮነነ ከዓለም በነነ ጠፋ፣ ተበተነ ወደ አርያም፣ ወደ ፈጣሪው ሄደ ነጎደ ሰውስ አበደ ፈጣሪውን ካደ ሰው ከዝንጀሮ ይመጣል የሚለውን ቃል አንተ የአገሬ ቂል ከቃል ሥጋ መሆን ልታስማማ ስትጥር እንዲሁ ስትጃጃል እንዲሁ ስንጃጃል አዘነብን ቃል አዘነብን ክርስቶስ ራቀን መንፈስ ቅዱስ ጨለመ ልባችን ገባ ከቤታችን ጥንተ ጠላታችን ወረረ ሀገራችን ወረረ ልባችንን አደረ በቤታችን ጥል ክርክር ቅናትን አለመስማማት ፍቅር ማጣትን ራስ ወዳድነትን ዘራብን ጥፋቱስ የራሳችን የማይድን ቁስል ስናክም የማያድግ ችግኝ ስናርም ወልጋዳ ቲዮሪን፣ ስንከረክም የአውሮፓን የበሰበሰ ቲዮረም በሀገሬ ጸበል ልናለመልም ብስብሱን ዛፍ ልናደርግ ለምለም አጉል ህልም ስናልም እኛ ለኛ ኖረን አናውቅም። ፈረንጁ'ንኳ ከደረሰበት መድረሱን አልቻልንም አንችልምም ነገሩ እንዴት ሆኖ? ቃል ሥጋ ኮነ ሚለው ከተኮነነ የኛ ነገር'ኮ አበቃ፥ ተነነ፥ በነነ፥ በዚሁ ቀረነ። ይኸው አሁንም ስናዘግም አለነ። ቃል ግን በርግጥ፣ ሥጋ ኮነ!!
نمایش همه...
☀️ግንቦት ፩ ^ እንኳን ለቅድስት ድንግል በክልኤ ማርያም ወላዲተ አምላክ #የልደት በዓል አደረሳችሁ ፤ እንኳን አደረሰን !
نمایش همه...