cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ተውሂድ የነብያቶች ሁሉ ጥር ነው

◾️ታላቁ ኢትዮጵያዊው አሊም ሸህ መሀመድ አማነል ጃሚ አላህ ይዘንለትና እንዲህ ብሏል። ✅ የወደደ ቢወድ የጠላ ቢጠላ፦ ሰለፍዮች ማለት ፊርቀቱ ናጅያ (ከእሳት የሚድኑና ነፃ ወጪዎቹ) እነሱ ናቸው። 📚شرح فتوى الحموية (٥) https://t.me/Tawihd https://t.me/Tawihd

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
299
مشترکین
+224 ساعت
+27 روز
+730 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

هل يجزئ صيام يوم عاشوراء مفردًا؟ 📩 #السؤال : سماحة الشيخ ، صيام يوم عاشوراء من محرم ، إذا صام الشخص يوم عاشوراء من محرم فقط ، ولم يصم يومًا قبله ، ولا يومًا بعده ؛ هل يجزئه ذلك؟ 📖 #الجواب : نعم #يجزئه ؛ لكن ترك الأفضل ، الأفضل أن يصوم قبله يومًا ، أو بعده يومًا ، هذا هو الأفضل ، يعني : يصوم يومين ، التاسع والعاشر ، أو العاشر والحادي عشر ، أو يصوم الثلاثة : التاسع ، والعاشر ، والحادي عشر ، هذا أفضل ، خلافًا لليهود ، نعم. #المقدم : أحسن الله إليكم. 🎙فتاوى نور على الدرب لسماحة الشيخ ابـن بـاز رحمه
نمایش همه...
↪️ የጁመዓ ኹጥባ (ምክር) ↩️ خطبة الجمعة؛ ➴➴➴➴➴ ==================== ✅ ርዕስ፦ ➴➷➘ "«ጊዜና አሳሰሰቢነቱ » በሚል አንገብጋቢ  ወቅታዊ ርዕስ ♻️عنوان" التكريم الإسلام للمرءة " موضوع ملح حاليًا ➴➴➴➴➴ ==================== 🎙በወንድም ሪድዋን ዳውድ ሀፊዘሁሏህ 🎙 للأخ رضوان داود -حفظه الله- ➴➴➴➴➴ ==================== 🗓ሀምሌ ‐05  ‐- 2016 E.C 🕌 ባህር ዳር ከተማ መስጅደል ቡኻሪ 🕌 بمدينة بحردار [إثيوبيا]؛ في مسجد البخاري ➴➴➴➴➴ ዝርዝሩን ገብታችሁ አዳምጡ ➴➴➴➴➴ ==================== ይ ደ መ ጥ ➴➴➴➴➴ ==================== share/ሼር/አድርጉ ባረከሏሁ ፊኩም። ➴➴➴➴➴ ==================== #size መጠን 14.01 MB #length 30:43min 🕌መስጅድ:-አል-ቡኻሪ 🌎ባህር ዳር፣ ኢትዮጲያ የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ https://t.me/alateriqilhaq كن على بصيرة
نمایش همه...
ጊዜ እና አንገብጋቢነቱ.mp314.09 MB
ዓሹራ እና አፇፇሙ የጁሙዓ ኹጥባ 🎙አቡአብዲረህማን አብዱልቃዲር ሐሰን https://t.me/abuabdurahmen
نمایش همه...
ዓሹራዕ ፆም.mp38.73 MB
Audio from ጃዋር
نمایش همه...
AUD-20240714-WA0010.mp37.00 MB
Photo unavailableShow in Telegram
🥣የዐሹራእ ቀን ፆም! ለመልካም ሥራ አስተዋሽ እንሁን። ከኢብኑ ዐባስ  ተይዞ፡ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ ﴿فَإِذَا كَانَ الْعَامُ الْمُقْبِلُ - إِنْ شَاءَ اللَّهُ - صُمْنَا الْيَوْمَ التَّاسِعَ﴾ «የሚቀጥለው ዓመት ከደረስኩ በአላህ ፍቃድ የዐሹራእን ቀን ፆም ዘጠነኛውን ጨምሬ እፆማለሁ።» [ሙስሊም: 1134] ከአቢ ቀታዳ ተይዞ፡ ነቢዩ  እንዲህ ብለዋል፦ ﴿صيامُ يومِ عاشوراءَ، إنِّي أحتَسِبُ على اللَّهِ أن يُكَفِّرَ السَّنةَ الَّتي قبلَهُ﴾ «የዐሹራእ ቀን ፆም ያለፈውን አመት ኃጢአት እንደሚያብስ ከአላህ እጠብቃለሁ።» [ሙስሊም: 1162]
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
🏝 ❝አስደሳች ዜና❞ 📚 አዲስ ኪታብ በተለይ ለኡስታዞችና ለዲን ተማሪዎች 📖 ⚙️ የታላላቅ መሻይኾች ተማሪ የሆነው ዓሊም ሸይኽ ሑሰይን ቢን ሙሀመድ ቢን ዐብደላህ አል-ኢትዮጲ አስ-ስልጢይ (ሀፊዘሁላህ) ከተዘጋጁ ኪታቦች አንዱ የሆነው « እስልምና ዒሳን {ዓለይሂ ሰላም} ማላቁ እና ከእስልምና ሀይማኖት የመካድ ምክንያቶች» በሚል በዐረቢኛ የተዘጋጀ አዲስ ኪታብ በቅርቡ ገበያ ላይ ይውላል ኢንሻ አላህ!!! 📮 📔 تعظيم الإسلام لعيسى عليه السلام وأسباب الارتداد عن دين الإسلام 📝 إعداد وجمع:-             🔑 الشيخ حسين بن محمد بن عبد الله الإتيوبي السلطي 📝  አዘጋጅ:- ሸይኽ ሑሰይን ቢን ሙሀመድ ቢን ዐብደላህ አል-ኢትዮጲ አስ-ሲልጢይ (ሀፊዘሁላህ) የኪታቡን PDF ለማግኘት https://t.me/shakirsultan/1860 📌 ትምህርቱን ለመከታተል ይህን ቻናል ይቀላቀሉ 👇👇👇 🌐 https://t.me/shakirsultan
نمایش همه...
👉 የሙሐረም ወርና ሙስሊሞች የሙሐረም ወር ከሂጅሪያ ወሮች የመጀመሪያውና አላህ ለይቶ ካላቃቸው አራቱ ወራቶች አንዱ ነው ። ይህ ወር የሂጅሪያ ወር መጀመሪያ ቢሆንም ሙስሊሞች የዘመን መለወጫ ብለው በዚህ ወር መግቢያ ላይ የተለየ የሚሰሩት ነገር የለም ። ይልቁንም ሙስሊሞቸው ህይወታቸው የሰከንዶች ሽርፍራፊ ጥርቅም መሆኑንና እየአንዳንዱ ሽርፍራፊ በተቀነሰ ቁጥር ከእድሜያቸው እየተቀነሰና ወደ ቀብር እየተጠጉ መሆናቸውን ነው የሚያውቁት ። በመሆኑም በየትኛውም ዘመን ፣ አመት ፣ ወር ፣ ሳምንት ፣ ሳአት ፣ ደቂቃና ሰከንድ ለሚቀጥለው ዐለም መዘጋጀት እንዳለባቸው ያውቃሉ ። ከዚህ ዝግጅታቸው አንዱ ምንዳና ቱሩፋት አለባቸው በተባሉ ቦታና ጊዜያቶች የታዘዙትን መልካም ስራዎች መስራት ነው ። በመሆኑም በሙሐረም ወር ውስጥ የታዘዙ የአምልኮ አይነቶችን ይፈፅማሉ ምንዳውንም ከጌታቸው ይጠብቃሉ ። የሙሐረም ወር ከአራቱ የተከበሩ ወራቶች ለመሆኑ በመልእክተኛው ሐዲስ የተረጋገጠ ሲሆን ከ12ቱ አራቱ የተከበሩ መሆናቸው ደግሞ አላህ በተከበረው ቃሉ በተውባ ምእራፍ 36ው አንቀፅ እንዲ ብሎ ይነግረናል : – « إِنَّ عِدَّةَ الشُّهُورِ عِندَ اللَّهِ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا فِي كِتَابِ اللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ ۚ ذَٰلِكَ الدِّينُ الْقَيِّمُ ۚ فَلَا تَظْلِمُوا فِيهِنَّ أَنفُسَكُمْ ۚ وَقَاتِلُوا الْمُشْرِكِينَ كَافَّةً كَمَا يُقَاتِلُونَكُمْ كَافَّةً ۚ وَاعْلَمُوا أَنَّ اللَّهَ مَعَ الْمُتَّقِينَ » " የወሮች ቁጥር አላህ ዘንድ በአላህ መጽሐፍ ውስጥ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን ዐሥራ ሁለት ወር ነው ፡፡ ከእነሱ አራቱ የተከበሩ ናቸው ፡፡ ይህ ቀጥተኛው ሃይማኖት ነው ፡፡ በእነርሱ ውስጥም ነፍሶቻችሁን አትበድሉ ፡፡ አጋሪዎችንም በአንድ ላይ ኾነው እንደሚዋጉዋችሁ በአንድ ላይ ኾናችሁ ተጋደሉዋቸው ፡፡ አላህም ከሚፈሩት ጋር መኾኑን ዕወቁ ፡፡" የአላህ መልእክተኛ – ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም – የተከበሩት ወራት የተኞቹ እንደሆኑ በሚከተለው በሐዲሳቸው ነገረውናል : – عن أَبي بَكْرَةَ رضي الله عنه عَنْ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ أنه قَالَ :  " إنَّ الزَّمَانَ قَدْ اسْتَدَارَ كَهَيْئَتِهِ يَوْمَ خَلَقَ اللَّهُ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضَ السَّنَةُ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ ثَلاثٌ مُتَوَالِيَاتٌ ذُو الْقَعْدَةِ وَذُو الْحِجَّةِ وَالْمُحَرَّمُ وَرَجَبُ مُضَرَ الَّذِي بَيْنَ جُمَادَى وَشَعْبَانَ " متفق عليه አቡ በክረተ የተባለ ሶሐብይ እንዳወራው የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል ይላል : – " ዘመን አላህ ሰማይና ምድር ሲፈጥር ወደ ነበረበት ተመልሷል ። ( የሐጅ ወር አላህ በዙል ሒጃ አድርጎታል ። መሀይማኖች የቀየሩት ውድቅ ሆኖ ወደዛው ተመልሷልና ይህን ያዙ ) ። አመት አስራ ሁለት ወር ነው ። ከእነሱ ውስጥ አራቱ የተከበሩ ናቸው ። ሶስቱ ተከታታዮች ናቸው ። ዙል ቀዕዳ ፣ ዙል ሒጃ ፣ ሙሐረም , ረጀብ ደግሞ በጁማደ ሳኒና በሻዕባን መካከል ነው ። " ከእነዚህ ከአራቱ ደግሞ ሙሐረም ይበልጥ የተከበረ ወር መሆኑን ሲነግሩን የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ይላሉ : – عن أبي ذر رضي الله عنه قال :  سألت النبي – صلى الله عليه وسلم – : أي الليل خير وأي الأشهر أفضل؟ فقال : " خير الليل جوفه وأفضل الأشهر شهر الله الذي تدعونه المحرم " አቡ ዘር የተባለ ሶሐብይ – ረዲየላሁ ዐንሁ – የአላህ መልእክተኛን የትኛው ለይል ይበልጣል ? የትኛውስ ወር በላጭ ነው ብዬ ጠየቋቸው ። እሳቸውም እንዲ አሉ : – " ከለሊቱ ውስጥ በላጩ ድቅድቁ ( ከመካከለኛው በኋላ) ያለው ነው ። ከወሮች ደግሞ እናንተ ሙሐረም ብላችሁ የምትጠሩት ነው ። " በዚህ ወር ውስጥ ተወዳጅ የሆው መልካም ስራ ደግሞ ፆም ነው ። ይህንንም መልእክተኛው እንዲህ በማለት ይነግሩናል : –  عن أبي هريرة أن النبي صلى الله عليه وسلم قال :  " أفضل الصيام بعد شهر رمضان شهر الله الذي تدعونه المحرم وأفضل الصلاة بعد الفريضة قيام الليل " . رواه مسلم አቡ ሁረይራ ባወሩትና ኢማሙ ሙስሊም በዘገቡት ሐዲስ ነብዩ እንዲህ ብለዋል : – " ከፆሞች ሁሉ በላጩ ከረመዳን ወር በኋላ ሙሐረም ብላችሁ የምትጠሩት ወር ( መፆም ነው) ከሶላት ሁሉ በላጩ ከፈርድ ሶላት በኋላ የለይል ሶላት ነው ። " የአላህ መልእክተኛ በሙሐረም ወር መፆም ( የቻሉትን ማለት ነው) ከረመዳን ወር ፆም ቀጥሎ የተወደደ መሆኑን እየነገሩን ነው ። በመሆኑም አንድ ሰው በሙሐረም ወር ውስጥ የቻለውን ያክል ቢፆም በጣም ተወዳጅ ነው ። እዚህ ጋር መታወቅ ያለበት ከረመዳን ውጪ ወሩን ሙሉ መፆም እንደማይቻል ነው ። በዚህ በሙሐረም ወር የዐስረኛውን ቀን መፆም ያለፈውን አመት ወንጀል የሚያስምር መሆኑን መልእክተኛው በሚቀጥለው ሐዲሳቸው ነግረውናል ። عن أبي قَتادة رضي الله تعالى عنه ، عن الرّسول - صلّى الله عليه وسلّم - قال : " صوم عاشوراء يكفِّر السّنة الماضية " رواه النسائي አቡ ቀታዳ የተባለ ሶሐብይ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል ይላል : – " የዓሹራእ ቀንን መፆም ያለፈው አመት ወንጀል ያስምራል ። " ከእነዚህ መረጃዎች በመነሳት ሙስሊሞች በሙሐረም ወር ከፆም የበለጠ የተወደደ ስራ አለመኖሩን ያውቃሉ ። በቻሉት አቅም በፆም ወደ አላህ ይቃረባሉ ከዚህ ውጪ አላስፈላጊ አመለካከትና እምነት ከኢስላም አንፃር ቦታ የለውም ። አላህ ከተጠቃሚዮች ያድረገን ። https://t.me/bahruteka
نمایش همه...
ባህሩ ተካ - Bahiru Teka

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته قناة رسمية لمحاضرات ودروس الأستاذ بحرو تكا (أبو عبيدة) الدعوة السلفية በአላህ ፈቃድ በዚህ ቻናል የአማርኛ ትምህርቶችን እንዲሁም አጫጭር የአረብኛና የአማርኛ ፁሁፎችን እንለቃለን ከዚህ ቻናል ውጪ ከሌላ ቦታ ተወስደው ለሚለቀቁ ኦዲዮዎች እውቅና አልሰጥም

https://telegram.me/bahruteka

[3]: ከሽፍ አሽ-ሹብሃት [4]: ሙኽተሰር ሲረት አር-ረሱል [5]:መሳኢል አል-ጃሂሊየህ [6]: ኡሱል አል-ኢማን [7]: ፈዳኢል አል-ቁርኣን [8]: ፈዳኢል አል-ኢስላም [9]: መጅሙዕ አል-አ'ሃዲስ [10]: ሙኽተሰር አል-ኢንሳፍ ወ-አሽ-ሸርህ አል-ከቢር [11]: አል-ኡሱል አስ-ሰላሰህ [12]: ኣዳብ አል-መሻኢል አስ-ሶላት....የመሳሰሉ ኪታቦችን አበርክተው ከዚህ ዓለም ተለይተዋል። ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) እስከመጨረሻው አስትንፋሳቸው ደረስ ከደርዒያው አስተዳደር እንዲሁም ከሙሐመድ ብን ሰዑድና ልጁ...ከሸይኹ ጎን በመቆም ለተውሒድ ትልቅ የሆነን ዋጋ ከፍለዋል። በመጨረሻም፣ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) ከዚች ዓለም በመሞት የተለዩት በሒጅራው ቀመር አቆጣጠር፣በዙል ቀዕዳ በመጨረሻው ዕለት፣1206 ዓመተ ሒጅራ ላይ ነበር። ባጭሩ የሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) አጭር የሕይወት ታሪክ ይህን ይመስል ነበር። አላህ ተጠቃሚዎች ያድርገነ!!!!!!! @semirEnglish @semirEnglish
نمایش همه...
የሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) አጭር የሕይወት ታሪክ:
ክፍል-2 (የመጨረሻው ክፍል) ክፍል-1ን ለማግኘት⬇️ https://t.me/semirEnglish/2914 ፡ ፡ ፡ ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) የዑወናው አስተዳደር አቀባበል ካደረገላቸው በኃላ፣ሸይኹ በከፍተኛው ሞራልና ትግል ዳዕዋቸውን በቁርጠኝነት ቀጠሉ። ዑወይነህ ላይ ሲፈፀሙ የነበሩ አስቀያሚ ሽርኪያቶች ሸይኹ ሰበብ በማድረሳቸው በአላህ ፍቃድ ሊጠሩ ችለዋል። እዛው ዑወይነህ ከተማ ውስጥ ሸይኹ ከመሄዳቸው በፊት፣ መቃብሮች፣ዋሻዎች፣ዛፎች...በሙስሊም  ተብዬዎች ይመለኩ ነበር፤ሆኖምግን በዑወይነህ አስተዳደር አሚር ዑስማን ቢን መ'ዕመር...ከሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) ጎን በመሰለፍ የተለያዩ የባዕድ አምልኮ ተግባራትን በአላህ ፍቃድ ሊያስወግዱ ችለዋል። ይህ ደግሞ የሆነው፣ዑወይነህ ከተማ ብቻ ሳይሆን ዙሪያውን ጭምር ነው። ይህ በንዲህ እንዳለ፣በዑወይነህ ከተማ ውስጥ የእስልምና ህግጋት ተግባራዊ መሆን ጀመሩ። ለአብነት ያክልም...አንዲት ባለትዳር ሆና ዝሙት የፈፀመች ሴት ኢስላማዊ ህግጋት በሷ ላይ ተግባራዊ አንዲሆን ሸይኹን መጥታ ጠይቃለች። ዝሙት የፈፀምችው ሴትዮዋ ኢስላማዊ ህግጋት በሷ ላይ ተግባራዊ ኢንዲሆን መጠየቋን ተያይዞ፣ ስለ ሁኔታዋ፣ማለትም ጤነኛ ነች ወይ? ተገዳ ነው ወይ? የሚሉ ምርመራዎች ከተካሄዱ በኃላ፣እንዲሁም ወንጀሉ ከተረጋገጠ በኃላ፣ ሸይኹ ተወግራ እንድትገደል አዘዙ። የሸይኹ ዝናና ጀብድ በተለያዩ ከተሞች እየተስፋፋና እየተሰራጨ መሄድ ጀመረ። ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) "የዑወይነህ" ቆይታቸውን ካጠናቀቁ በኃላ፣ "ደርዒየህ" ወደ ተሰኘች ከተማ አቀኑ። ሸይኹ ወደ "ደርዒየህ" ማቅናታቸውን ከታወቀ በኃላ፣የአል-አህሳ አስተዳደርና እንዲሁም ብን ሱለይማን የሸይኹን ገናናነት እና ተፅኖ-ፈጣሪ መሆናቸውን ለመለየት በህዝብ መካከል ሆኖ ይከታተል ነበር። ሁኔታው አጅግ በጣም አስፈራው፤ምክንያቱም ስልጣኔ ይነጠቃል የሚል ስጋትም ጭምር አደረበት። ይህ ሱለይማን የተባለው ግለሰብ፣ለአሚር ዑስማን ስጋቱን በመግለፅ ሸይኹን እንዲገላቸው ጥያቄ አቀረበ፤ይሁንእንጂ አሚር ዑስማን የሱለይማንን ጥያቄ ለመቀበል ፍቃደኛ አንነበሩም። ሱለይማን የአሚር ዑስማንን አቋም ከተረዳ በኃላ ተሸበረ፣ተጨነቀ፣ምድር ሰፊ ከመሆኗም ጋር ጠበበችው....አሚር ዑስማን ሸይኹን ተቀበሏቸው፤ በግዛቱ የፈለጉበት ቦታ መንቀሳቀስ እንደሚችሉ አስረግጦ አሳውቋቸው። የደርዒየህ ነዋሪዎችና ህዝቦች የሸይኹን የተውሂድ ተልእኮ ተረዱ። የደርዒያው አስተዳዳሪ አሚር ሙሐመድ ብን ሰዑድ፣ ሸይኹ ወደ ግዛቱ ስለገቡ በእጅጉን ተደሰተ። አስተዳዳሪው ቀጥታ ሸይኹ የሚገኝበት ድረስ በመሄድ ጉብኝት አድርጓል። በሸይኹ የተውሒድ ጥሪም ተደስቷል። ከሸይኹም ጋር የሃሳብ ልውውጥ አድርጓል። አሚር ሙሐመድ ብን ሰዑድ ለሸይኹ ድጋፍ እንደሚያደርግላቸው ቃል ገባላቸው። ሸይኹም ለአሚሩ ዱዓ አደረጉለት። ሸይኹ ይህንን ወርቃማ የሆነውን አጋጣሚ በመጠቀም፣አያሌ የሆኑ ህዝቦችን ማስተማር ጀመሩ። የደርዒየህ እና አካባቢዋ በተውሂድ ተናወጠች፤የተውሂድ ሰንደቅዓላማ መውለብለብ ጀመረ... ምን ይሄ ብቻ የደርዒያው ዋና አስተዳዳሪ አሚር ሙሐመድ እራሱን እና ቤተሰቦቹን ይዞ እንደተማሪ ሆኖ በመቅረብ፣ ከህዝቡ ጋር በመታደም የሸይኹን ትምህርቶችን መከታተል ጀመረ። ይህ ዜና በተለያዩ አከባቢዎች ተሰራጨ። ዜናውን የሰሙ ሰዎችም ከበረከቱ ለመቋደስ፣እውቀት ለመቅሰም ወደ ደርዒየህ መሰደድ ጀመሩ። ደርዒየህ የተውሂድ ማዕከል ሆነች። ይህ በንዲህ እንዳለ፣የሸይኹ ጠላቶች በሸይኹ ላይ የተለያዩ ቅጥፈቶችን መንዛት ጀመሩ። ምን ይሄ ብቻ?! ጠንቋይ፣ ድግምተኛ፣ ሙናፊቅ (ዚንዲቅ)...በመሳሰሉ ቃላቶች በሸይኹ ላይ መንዛት ጀመሩ። በተለያዩ የውሸት ቅጥፈቶች ሸይኹን ለማሸማቀቅና ከዳዕዋው ለማሰናከል በሚክሩም፣ሙከራቸው ሳይሳካ ቀርቷል። ሸይኹ የተቺ ተቺዎች ሴራ ሳይበግራቸው ተልዕኮውን ቀጠሉ። በል እንዳውም ተቃራኒ ከሆኑ አካላቶች ጋር ጨዋነት በተሞላበት ስልት ተከራክረዋል። ከዚህም በተጨማሪ፣ከተለያዩ ከአረብ ደሴት (Arabian peninsula) የመጡ የተለያዩ ልዑካን ቡድኖችን ትክክለኛው የተውሒድ ጥሪ ካደረጉላቸው በኃላ፣ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ ህዝባቸውን ወደ ተውሒድ እንዲጠሩ አጥበቀው መክረዋል። ሸይኹ በዚህም ብቻ አላቆሙም ለአረብ ደሴት መሪዎችና ሊቃውንቶች ደብዳቤዎችነ ፃፉ። የደብዳቤው ዋና መልእክት ሽርክን እንዲሁም ኢስላም የማያውቀው ባዕድ የሆኑ አምልኮዎችን ህዝባቸውን እንዲታደጉ ነበር። ሸይኹ ደብዳቤዎችን የፃፉት ለነጅድ፣ ሪያድ፣ኸርጅ፣ ቀሲም፣ሀዬል፣ወሽም፣ ሱደይር፣አህሳ፣ መካ፣ መዲና፣ የመን...ለመሳሰሉት ሀገራቶች ፅፈው ነበር። ልብ ይበሉ! ደብዳቤው የተፃፈው በሀገሩ ለሚገኙ አስተዳደር እና ዑለማች ነው። ሸይኹ አሁንም በዚህ አላበቁም፤ከአረብ ደሴት ውጭ ለሆኑ ሀገራትም ደብዳቤዎችን ፅፈዋል፤ለምሳሌ፡ ለነ ሶሪያ፣ ኢራቅ፣ሕንድ...ለመሳሰሉት ሃገራት በደብዳቤ የዳዕዋ ጥሪ አቅርበዋል። ሸይኹ ቁርኣንና ሱንናን አብራርተዋል። ምስጋና ለአላህ የተገባ ይሁንና ዳዕዋቸው ግብ መቷል። የሸይኹን ዳዕዋ ከተቀበሉ ሀገራቶች መካከል፡ ሕንድ፣ኢንዶኔዥያ፣አፍጋኒስታን፣አፍሪካ፣ሞሮኮ፣ግብፅ፣ሶሪያ...የመሳሰሉ ሀገራቶች የሸይኹን ዳዕዋ በመቀበል ትልቅ ተፅዕኖ አድሮባቸዋል። ይህም ብቻ ሳይሆ ከሸይኹ ጎንም ጭምር ተሰልፈዋል። ሸይኹ በሒጅራው ቀመር አቆጣጢ ከ"1158" እስከ "1206" ባሉት ጊዜያት ውስጥ ትልቅ የሆነ ተግል በማድረጋቸው አመክንዮ፣ በነጅድ ሙሉበሙሉ በሚባል ደረጃ አላህ ሸይኹን ድል አጎናፀፋቸው። ሰዎች ዶሪህን፣ ቀብርን፣ እንጨትን፣ዛፍን...ማምለክ ተው። ጭፍን ተከታይነት ሚባል ነገር ጠፋ። ይህ ባህል ነው፣የአባቴ መንገድ ነው፣የአያቴ መንገድ ነው...ከማለት ሰዎች ተወገዱ። ጥርት ወዳለው እስልምና ገቡ። አላሁ አክበር ዲን እንደገና ሕያው ሆነ። ቁርኣንና ሱንና በሰዎች ላየ ተንፀባረቀ። በመልካም ማዘዝ ከመጥፎ መከልከል ተግባራዊ ስራ ሆኖ ቀጠለ፤ መስጂዶች ውስ ሰዎች ሞልተው መስገድ ጀመሩ። በሀገሪቷ ሰላምና መረጋጋት ሰፈነ። ገጠሬዎችም ከተሜዎች...በሰላም መኖር ጀመሩ። የተውሒድ ሰንደቅዓላማ ተውለበለበ። ከሸይኹ እወቀትን የቀሰሙ አካላቶች በመላው ዓረቢያ ደሴት የተውሒድ ተልዕኮን ይዘው ተሰሬጩ። ሸይኹ በሕይወት ካለፉ በኃላም ልጆቻቸው እና ተማሪዎቻቸው ዳዕዋውን በአላህ ፍቃድ ማስቀጠል ችለዋል። ከልጆቻቸው መካካል ዳዕዋውን ካስቀጠሉ እንደነ፡ ሸይኽ ኢማም ዐብዱሏህ ብን ሙሐመድ፣ ሸይኽ ሑሰይን ብን ሙሐመድ፣ ሸይኽ ዐሊይ ብን ሙሐመድ፣ሸይኽ ኢብራሂም ብን ሙሐመድ....ይገኙበታል። ከሸይኹ ከልጅ ልጆቻቸው መካከል ደግሞ፣ሸይኽ ዐብዱር-ረሕማን ብን ሐሰን፣ሸይኽ ዐሊይ ብን ሑሰይን፣ሸይኽ ሱለይማን ብን ዐብዱሏህ... ይገኙበታል። ከተማሪዎቻቸው መካከል ደግሞ፡ እንደነ ሸይኽ ሐምድ ብን ናሲር...የመሳሰሉ ይገኙበታል። ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) ለዚህ ኡማ ትልቅ የሆነን አሻራ ጥለው አልፈዋል። ለዚህም ነው ሰዎች በሺርክና በተለያዩ ባዕድ በሆኑ አምልኮ ተጨማልቀው ሳለ፣ በአላህ ፍቃድ ሸይኹ ትግል አድርገው፣የአንበሳውን ድርሻ ተጫውተው ነው ከዚች ዓለም ያለፉት። ሸይኹ ለኡማው ካበረከቱት ኪታቦች መካከል በጥቂቱ እነሆ፡ [1]: ኪታብ አት-ተውሒድ [2]: ኪታብ አል-ከባኢር
نمایش همه...
𝐒𝐞𝐦𝐢𝐫 𝐉𝐞𝐦𝐚𝐥 (𝐀𝐛𝐮 𝐇𝐚𝐟𝐬𝐚𝐡)

የሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) አጭር የሕይወት ታሪክ: ክፍል-1 አል-ሙጀዲድ ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) በሒጅራው ቀመር አቆጣጠር በ'1115 ኡነይዛ ከተሰኘች ከተማ ተወለዱ። ኡነይዛ የተሰኘችው ከተማ፣ ከሳዑዲ አረቢያ ዋና ከተማ ከሪያድ በስተ ሰሜን-ምእራብ 70 ኪሎሜትር ያክል እርቀት ላይ ትገኛለች። የሸይኹ ቤተሰቦች የተከበሩና ዑለማኦች ነበሩ። አባቱ ሸይኽ ዐብዱል-ወ'ሓብ ብን ሱለይማን (ረሂመሁላህ) ጥልቅ እውቀት እንዳላቸውና እንዲሁም አጅግ ትሁትና መልካም ሰው እንደነበሩ ይነገራል። የሙሐመድ ዐብዱል-ወ'ሓብ አባት እውቀትን የቀሰሙት፣ ከአባታቸው ከሸይኽ ሱለይማን ብን ዐሊይ እንደሆነ ታሪክ ይዘክራል። ይህ በንዲህ እንዳለ፣ሸይኽ ሱለይማን ብን ዐሊይ (ረሂመሁላህ) በጊዜው ከነበሩ ዑለማኦች፣ዋና ሊቀመንበርና ፈትዋ ሰጪ እንደሆኑ ታሪክ ያስረዳል። አል-ሙጀዲድ ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) የመጀሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን የተማሩት ከአባታቸው ነው። ይህም የሆነው እዛው በትውልድ ስፍራቸው ላይ ነበር። ሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን ዐብዱል-ወ'ሓብ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) ታንፀው ያደጉትም በአባታቸው ነበር። ሸይኹ ቁርኣንን የሃፈዙት ገና በለጋ እድሜያቸው ላይ ነበር። ይህም የሆነው 10 አመት ሆኗቸው ሳለ ነበር። ሸይኹ ተፍሲር፣ሐዲስ፣ፊቅህ...ተምረዋል። ይህ በንዲህ እንዳለ፣ ሸይኹ የሰለፎችን ኪታብ በብዛት እንደማያነቡ ይነገራል፣በተለይም የሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያና ብርቅዬ የሆነው የተማሪያቸው የኢብኑል ቀይምን ኪታቦች ማንበብ ያጓጓቸው እንደነበር የታሪክ መዛግብት ያስረዳሉ። ሸይኹ እድሜያቸው ለጉርምስና በደረሰ ጊዜ፣ከአምስቱ የኢስላም ማዕዘናት የሆነውን ሐጅን ለመፈፀም ወደ መካ አቀኑ፤ከዚያም መካ ከሚገኙ…

یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.