fa
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

رفتن به کانال در Telegram
1 743
مشترکین
+224 ساعت
+37 روز
-130 روز
آرشیو پست ها
የኢንደስትሪ ቴክኒካል አዲቫይዘሪ ቦርድ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከኢንዱስትሪው ጋር ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር በማሰብ የኢንደስትሪ አዲቫይዘሪ ቦርድ አቋቁሞ የተለያዩ ስራዎችን በጋራ ሲሰራ ቆይቷል፤ በ2015 ዓ.ም ይህንን ቦርድ በአደረጃጀት ለማጠናከር በተያዘው ዕቅድ መሰረት በዛሬው ዕለት ከተለያዩ ኢንደስትሪዎች የተወጣጡ ቴክኒካል አባላትን በመያዝ የቦርዱ ቻርተር ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል በዚህም ሰብሳቢ፣ ም/ሰብሳቢ እና ጸኃፊ በመምረጥ ወደ ሰራ የሚገቡበትን አቅጣጫ አስቀምጠዋል፤ በመጨረሻም የቦርዱ አባላት በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ ዲፓርትመንት ወርክሾፖችን ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በቀጣይም ኮሌጁን በቴክኒኩ አቅጣጫ አስፈላጊ በሆኑ ነገሮች ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን መስከረም 14/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2014 የስራ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2015 ዓ.ም ዕቅድ ለኮሌጁ ቦርድ ቀርቦ ተገመገመ። በዚህም የኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ የተሰሩትን ስራዎች አድንቀው በቀጣይ በተለይም አዳዲስ ሰልጣኞችን ለመቀበል የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እንዲሁም ከኢንዱስትሪዎች ጋር የሚኖረውን ትስስር ማሻሻል ላይ ትኩረት ሊደረግ ይገባል ብለዋል። አያይዘውም በካይዘን ትግበራ ጥሩ አፈጻጸም እያሳዩ የሚገኙ የዉድ ቴክኖሎጂ እና ኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንቶችን በመዘዋወር የጎበኙ ሲሆን የዚህ ለውጥ ባለቤት የሆኑትን አሰልጣኝ መምህራንንም አበረታተዋል።

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሰራተኞች የሂስ ግለሂስ ግምገማ አካሄደ።
+9
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሰራተኞች የሂስ ግለሂስ ግምገማ አካሄደ።

በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የማኔጅመንት ኮሚቴ በኮሌጁ የትምህርትና ስልጠና እና የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ አሰጣጥ ያለበትን አሁናዊ ሁኔታ የመስክ ምልከታ አደረገ። በምልከታውም ከሰልጣኝ ተማሪዎች በትምህርትና ስልጠና አሰጣጥ ሂደቱ ላይ ያላቸውን ሀሳብና አስተያየት እንዲሁም የሚያነሷቸውን ጥያቄዎችና ቅሬታዎች መመልከት የተቻለ ሲሆን በተጨማሪም ከውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ሂደቱ ጋር በመወያየት የተነሱትን የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት በቀጣይ ዕቅድ አውጥቶ ክትትልና ምላሽ ለመስጠት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ አቅጣጫ ተቀምጧል። በተመሳሳይ በተቋም ደረጃ እየተሰሩ ያሉ ቴክኒዎሎጂዎች በተቻለ አቅምና ፍጥነት ማጠናቅ እንዲቻልና ለውጤት እንዲበቃ አቅጣጫ የተቀመጠ ሲሆን፤ ለኢንተርፕራይዞች የሚደረገው የድጋፍ አገልግሎት በተለይም በቀጥተኛ ሞያዊ ተዛምዶ ባላቸው አሰልጣኝ መምህራን የሚሰጠው ድጋፍ ውጤት ያስገኘ መሆኑን ተመልክቷል። በቀጣይም ትምህርትና ስልጠናውን በዚህ አመት በጥናት ላይ ተመስርቶ ወደ ተግባር የተገባውን የአተገባበር ስርአት በማጠናከር ለዚህም የስልጠና አስተባባሪዎችን ሚና የማጎልበት ስራ እንደሚሰራ እና ከቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ጋር ተያይዞ የተጠኑ ጥናቶችን ተግባራዊ በማድረግ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን የመለየትና የመፍታት ስራዎች ትኩረት ተሰጥቶ የሚተገበሩ ይሆናል። ድሬዳዋ ሰኔ 08/2014 ዓ.ም የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን

photo content
+9

በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የማኔጅመንት ኮሚቴ በኮሌጁ የትምህርትና ስልጠና እና የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ አሰጣጥ ያለበትን አሁናዊ ሁኔታ የመስክ ምልከታ አደረገ። በምልከታውም ከሰልጣኝ ተማሪዎች በትምህርትና ስልጠና አሰጣጥ ሂደቱ ላይ ያላቸውን ሀሳብና አስተያየት እንዲሁም የሚያነሷቸውን ጥያቄዎችና ቅሬታዎች መመልከት የተቻለ ሲሆን በተጨማሪም ከውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ሂደቱ ጋር በመወያየት የተነሱትን የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት በቀጣይ ዕቅድ አውጥቶ ክትትልና ምላሽ ለመስጠት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ አቅጣጫ ተቀምጧል። በተመሳሳይ በተቋም ደረጃ እየተሰሩ ያሉ ቴክኒዎሎጂዎች በተቻለ አቅምና ፍጥነት ማጠናቅ እንዲቻልና ለውጤት እንዲበቃ አቅጣጫ የተቀመጠ ሲሆን፤ ለኢንተርፕራይዞች የሚደረገው የድጋፍ አገልግሎት በተለይም በቀጥተኛ ሞያዊ ተዛምዶ ባላቸው አሰልጣኝ መምህራን የሚሰጠው ድጋፍ ውጤት ያስገኘ መሆኑን ተመልክቷል። በቀጣይም ትምህርትና ስልጠናውን በዚህ አመት በጥናት ላይ ተመስርቶ ወደ ተግባር የተገባውን የአተገባበር ስርአት በማጠናከር ለዚህም የስልጠና አስተባባሪዎችን ሚና የማጎልበት ስራ እንደሚሰራ እና ከቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ጋር ተያይዩየተጠኑ ተግባራዊ ጥናቶችን ተግባራዊ በማድረግ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን የመለየትና የመፍታት ስራዎች ትኩረት ተሰጥቶ የሚተገበሩ ይሆናል። ድሬዳዋ ሰኔ 08/2014 ዓ.ም የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን

photo content
+6

በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የማኔጅመንት ኮሚቴ በድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን መምሪያ በመገኘት በኮሚሽኑ የተሠሩና እምርታ ያሳዩ የሪፎርም ስራዎች አፈጻጸምን ጉብኝትና ምልከታ ማድረግ ችሏል። በጉብኝቱም በኮሚሽኑ የተወሰደው ተቋሙን የማሻሻል አልፎም የመለወጥ እንቅስቃሴ ሁሉን ያሳተፈ እና የሁሉንም የተቋሙን ሰራተኞች እና ባለድርሻ አካላት እርብርቦሽ እና ትብብር ቀምሮ ውጤታማነቱም በተግባር ያረጋገጠ መሆኑ ታይቷል። ድሬዳዋ ግንቦት 10/2014 ዓ.ም የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን

የጥናት ግኝቶች ላይ ተመስርተው የተዘጋጁ የአተገባበር ረቂቅ ሰነዶች ላይ ውይይት ተደረገ። 🗯በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ስር ከዚህ በፊት የተጀመሩ የፕሮጀክት ማዕቀፎች ማለትም የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አተገባበር ተግባራዊ ጥናትና ምርምር የጥናት ግኝቶች ላይ ተመስርቶ የተዘጋጁ የአተገባበር ረቂቅ ሰነዶች ላይ ለአመራር ፑል እና ለአጠቃላይ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን ጥናቱን ባካሄዱት የኮሌጁ A ደረጃ አሰልጣኝ መምህራን፤ የቴክኖሎጂ ሽግግር አተገባበር ተግባራዊ ጥናትና ምርምር የጥናት ግኝቶች በአሰልጣኝ መምህር ጌታቸው ወንድሙ እና አሰልጣኝ መምህር ደረጀ ተሾመ አንዲሁም የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አተገባበር ተግባራዊ ጥናትና ምርምር የጥናት ግኝቶች በአሰልጣኝ መምህር አቤል ዘገየ ቀርበው ገለጻና ውይይት ማድረግ ተችሏል፡፡ 🗯 በዚህም ተግባራዊ ጥናትና ምርምር አጥኚ አሰልጣኝ መምህራኖቹ ከተመለከቷቸው የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አተገባበር ተግባራዊ ጥናትና ምርምር የጥናት ግኝቶች በመነሳት የሚከተሉትን ምክረ ሃሳቦች አስቀምጠዋል፤ 🗯የቴክኖሎጂ ሽግግር አተገባበርን ለማሻሻል • ሊያሰራ የሚችል ማዕቀፍ እና መመሪያ ማዘጋጀት፤ • በኮሌጁ የቴ/ሽ ትግበራ፣ ክትትል እና ግምገማ የሚያደርግ የቴ/ሽ ክፍልን ማቋቋም፤ • ለዕውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት አቅም ቅድሚያ መስጠት እና ለአሰልጣኞች ቴክኖሎጂን በማሸጋገር ላይ ስልጠና መስጠት፤ • ተቋማዊ የቴክኖሎጂ ማእከላትን (ማሳያ እና መረጃ ማደራጃን ጨምሮ) ማልማት እና ማስተዋወቅ፤ • በኮሌጁ ውስጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን እና በማሳተፍ ያለውን የቴ/ሽ አቅም ማሳደግ፤ • የተቋማዊ ሀብቶችን (ቁሳቁስ እና ፋይናንሺያል) የማስፈፀም አቅምን ማሻሻል፤ 🗯 የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አተገባበርን ለማሻሻል • መዋቅር እና አስተዳደርን ማሻሻል፤ • በማህበረሰብ አገልግሎት ውስጥ ንቁ ተሳትፎን ማረጋገጥ፤ • በፍላጎት ላይ የተመሰረተ ወይም በፍላጎት የሚመራ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍን ማጠናከር፤ 🗯 በቀረበውም ምክረ ሃሳብ ላይ የኮሌጁ አመራር ፑል እና አሰልጣኝ መምህራን ሃሳብና አስተያየት የሰጡበት ሲሆን በአጭር ጊዜ ውስጥም የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አተገባበር ላይ የሚስተዋለውን ችግር በሚፈታ አግባብ ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አሳስበዋል፡፡ ድሬዳዋ ሚያዚያ 28/2014 ዓ.ም የኢትዮ ጣሊያን ኮምኒኬሽን

photo content
+9

#ኢድ_ሙባረክ
#ኢድ_ሙባረክ

photo content
+5

በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ልዩ የኢፍጣር ፕሮግራም በኮሌጃችን የውጤት ተኮር ምክትል ዲን ኢሊያስ አህመድ መኖሪያ ቤት የኮሌጁ ማኔጅመንትና ሰራተኞች በተገኙበት መልካም ጊዜ ማሳለፍ ተችሏል፡፡

በጦርነት ለተጎዱ ድጋፍ ተደረገ። ==================== ❤ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በጦርነት ምክንያት ጉዳት ለደረሰበት የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ግምቱ 1,211,283 ብር የሆነ ልዩ ልዩ የትምህርትና ስልጠና እንዲሁም ለቢሮ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ፤ ❤ ይህንንም ድጋፍ ከኮሎጁ ሁሉም የትምህርትና ስልጠና ክፍሎችና የስራ ክፍሎች መሰብሰብ የተቻለ ሲሆን በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በመገኘት የኮሌጃችን ዲን አቶ ታደለ አሠፋ ማስረከብ ችለዋል። ድሬዳዋ ሚያዚያ 21/2014 ዓ.ም የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን

በጦርነት ለተጎዱ ድጋፍ ተደረገ። ==================== ❤ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በጦርነት ምክንያት ጉዳት ለደረሰበት የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ግምቱ 1,211,283 ብር የሆነ ልዩ ልዩ የትምህርትና ስልጠና እንዲሁም ለቢሮ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ፤ ❤ ይህንንም ድጋፍ ከኮሎጁ ሁሉም የትምህርትና ስልጠና ክፍሎችና የስራ ክፍሎች መሰብሰብ የተቻለ ሲሆን በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በመገኘት የኮሌጃችን ዲን አቶ ታደለ አሠፋ ማስረከብ ችለዋል። ድሬዳዋ ሚያዚያ 21/2014 ዓ.ም የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን

photo content
+3

"አሰልጣኝ መምህር አቤል ዘገየ ወ/ገብርኤል" ============================== 🥇በድሬ ዳዋ አስተዳደር የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ባዘጋጀው የቴክኖሎጂ ውድድር የኮሌጃችን አሰልጣኝ መምህር የሆኑት ዮሴፍ እንዳልካቸው የአንደኝነት ደረጃ በማግኘታቸው የተሰማንን ደስታ መግለፃችን ይታወሳል በተያያዘም በድሬዳዋ አስተዳደር ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ በቀን 05/08/2014 ዓ.ም ባካሄደው የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር የኮሌጃችን አሰልጣኝ መምህር የሆኑት አቤል ዘገየ ወ/ገብርኤል “Improving Industry Extension Service in the Case of Ethio-Italy Poly Technic College” በሚል ርዕስ ባቀረቡት የተግባራዊ ጥናት አንደኛ መውጣት ችለዋል፤ 🥇 በዚህም በተገኘው ድርብ ድል የተሰማንን ድርብ ደስታ ለመግለጽ እንወዳለን፤ በቀጣይም ጥናቱን ወደ ተግባር ለማስገባት በልዩ ትኩረት በመስራት የዘርፉን ውጤታማነት እንደሚያሻሽል የሚጠበቅ ሲሆን ለዚህም ስኬት የኮሌጁ ማህበረሰብ ድጋፍ ወሳኝ በመሆኑ መሰል ስራዎችን እና የሚሰሩትን አሰልጣኝ መምህራን ልናበረታታቸው ይገባል። ድሬዳዋ ሚያዝያ 09/2014 ዓ.ም የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን