fa
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

رفتن به کانال در Telegram
1 740
مشترکین
-124 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
-630 روز
آرشیو پست ها
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከ ከEntrepreneurship Development Inistitut(EDI) ጋር መተባበር በBusiness Incubation center ዙሪያ ለሚመለከታቸው ባለሙያዎችና አስተባባሪዎች የስልጠና መድረክ አካሄደ:: ስልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ሀላፊና የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ል ሀላፊና ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ በንግግራቸውም የቴክኒክና ሙያ ዘርፋችን ክህሎት መር የስራ እድልን የሚመራ በመሆኑ ወጣቶች ቢዝነሳቸውን እዚሁ ኮሌጆቻችን ውስጥ እንዲያጎለብቱ ማድረግ ይጠበቅብናል ያሉ ሲሆን አክለውም ሰልጣኞች ተሰጥዕኦዋቸውን እያሳደጉ ከቢዝነሱም ተጠቃሚ የሚሆንበትን የኢንኩቤሽን ማዕከል እንዲፈጠር ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው ይህ ስልጠና የተዘጋጀበት አላማም ይህኑ ታሳቢ እድርጎ እንደሆነም ገልፀዋል:: EDI ወደ እኛ ዘርፍ ከተቀላቀለ ጊዜ ጀምሮ በርካታ ስራዎች በመስራት ዘርፉ ላይ መነቃቃት እየፈጠረ እንደሚገኝ የገለፁት ደግሞ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ በ2018 ከኢንስቲትዩቱ ጋር ዘርፈ ብዙ ስራዎችን በጋራ ለማከናወን ሰፊ እቅድ መያዙንም ገልፀዋል:: ስልጠናው ከሁለቱ ፖሊ ቴክኒኮች እና ከኤጀንሲ ለተወጣጡ ባለሙያዎች እንዲሁም አስተባባሪዎች የተሰጠ ሲሆን በዚህ ስልጠናም የBusiness Incubation center (BIC) ታሪካዊ አመጣጥ/አጀማመርና ፅንሰ-ኃሳብን ጨምሮ የቢዝነስ ኢንኩቤሽን ሴንተር ለማቋቋም እና ለማስተዳደር  መከተል የሚያስፈልገውን መሰረታዊ መርሆዎች ን ከEDI በመጡ አሰልጣኞች አማካኝነት በጥሩ አቀራረብ ለተሳታፊዎች ስልጠናውን መስጠት ተችሏል:: በዛሬው እለት ለባለሙያዎችና አስተባባሪዎች የተጀመረው ስልጠና ነገም ቀጥሎ የሚሰጥ ሲሆን በቀጣይ ለኮሌጁ ፑል አመራር አባላትና ለተመረጡ ሰልጣኝ ተማሪዎች የEntrepreneurship ስልጠና በመስጠት እንደሚቀጥልም ማወቅ ተችሏል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥቅምት 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለአዲስ ገቢ ሰልጣኞቹ የPsychometric Test እየሰጠ ይገኛል:: ይህን የPsychometric Test በሀገር አቀፍ ደረጃ በተሰጠ አቅጣጭ መሰረት በኮሌጃችንም
+9
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለአዲስ ገቢ ሰልጣኞቹ የPsychometric Test እየሰጠ ይገኛል:: ይህን የPsychometric Test በሀገር አቀፍ ደረጃ በተሰጠ አቅጣጭ መሰረት በኮሌጃችንም ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን በኮሌጁ የICT ዲፓርትነንት በሚገኝ Lab በOnline አማራጭ አዲስ ኮሌጁን ለሚቀላቀሉ ሰልጣኞች እየተሰጠ ይገኛል:: በዚህ ፈተና አዲስ ሰልጣኞች ከራሳቸው፣ከቤተሰቦቻቸውና ከጓደኞቻቸው ጋር ተመካክረው ለመምረጥ ከሚመጡት የስልጠና ዘርፍ በተጨማሪ የሰልጣኞችን የግንዛቤ፣ የስብዕናና ያላቸውን ተሰጥኦ የሚያመላክታቸው በመሆኑ ለወደፊት ውጤታማ የሚሆኑበትን የስልጠና ዘርፍ ከወዲሁ አውቀው እንዲወስኑ የሚያግዛቸው መሆኑም ተገልፇል፡፡ በእለቱ የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ የPsychometric Test አሰጣጡን በአካል ተገኝተው ያስጀመሩ ሲሆን ፈተናውን ለሚወስዱት ሰልጣኞችም ግንዛቤ የመስጠት ስራ አከናውነዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥቅምት 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም የስልጠና ዘመን አዲስ ለተቀበላቸው ሰልጣኝ ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል እና የኦረንቴሽን መድረክ አካሄደ:: ለሰልጣኝ ተማሪዎቹ በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ል ሀላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ በመልዕክታቸውም ወጣቶች የቴክኒክና ሙያ ዘርፉን መርጣችሁ እዚህ በመገኘታቸው እንኳን ደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን ወቅቱ ሚጠይቀውን ምርጫ አውቃችሁ በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለመሰልጠን ዘርፉን በመቀላቀላችሁ እጅግ እድለኞች ናችሁና እንኳን ደስ አላችሁም ብለዋል:: ለአዲስ ገቢ ሰልጣኝ ተማሪዎቹ ኦረንቴሽን የሰጡት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ በቅድሚያ ሰልጣኞች የልዩ ክህሎት ባለቤት ወደሚያደርጋችሁ ኮሌጃችሁ እንኳን በደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ለመሰልጠን እዚህ የተገኛችሁ ወጣቶች አሁን የምትገኙበት እድሜ በራሳችሁ ውሳኔ ምትወስኑበት እድሜ በመሆኑ ትክክለኛውና ጠቃሚውን መንገድ ለይታችሁ በመምረጥ የወጣትነት ጊዜያችሁን ውጤታማ ነገር ላይ እያሳለፋችሁ መሆኑን ከወዲሁ እርግጠኛ መሆን ይገባችኃልም ብለዋል:: የኮሌጁ ዲን አክለውም በኮሌጁ የትኩረት ዘርፍ ተብለው የተያዙና በዓለም ባንክ ፕሮጀክት ጭምር የሚደገፉ ሶስት የትኩረት ማዕከል የሆኑ የሙያ ዘርፎች መኖራቸውን ለሰልጣኞች ገልፀው እነርሱም የማኑፋክቸሪንግ ፣ የኤክትሪካል/እሌክትሮኒክስ እና የአውቶሞቲቭ ዘርፎች መሆናቸውን በመጥቀስ በእነዚህ ሶስት የትኩረት ዘርፎችን ምርጫቸው አድርገው ለሚቀላቀሉ ሰልጣኞች ከየትኛውም ዘርፍ በተለየ ሁኔታ እድለኞችና የላቀ ተጠቃሚ መሆናቸውንም በመድረኩ አብስረዋል:: በተጨማሪም ለአዲስ ገቢ ሰልጣኞች ስለ Biometric Test አወሳሰድ ግንዛቤ የተፈጠረላቸው ሲሆን ሰልጣኝ ተማሪዎቹ በቀጣዮቹ 3ቀናት በኮሌጁ በሚኖራቸው ቆይታ የህይወት ክህሎት(Life Skill) ስልጠና እንደሚወስዱ የተገፀ ሲሆን ጎን ለጎንም የBiometric Test የሚውስዱ ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥቅምት 24/2018 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር  የሚገኙ ሶስት ፖሊቴክኒክ ኮሌጆችን ያቀፈ ልዑካን ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የስራ ልምድ ልውውጥ ጉብኝት አካሄደ፡፡ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ  በEASE ፕሮጀክት ትግበራ ባሳየው ከፍተኛ የስራ አፈፃፀምን ጨምሮ አጠቃላይ በኮሌጁ ባስመዘገባቸው ተጨባጭ ውጤቶች ጋር ተያይዞ በሀገሪቱ የሚገኙ በርካታ ኮሌጆች ለልምድ ልውውጥ ወደ ተቋማችን እየመጡ የሚገኝ ሲሆን በዛሬው እለትም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣ አቃቂ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኮሌጅ ዲኖች እና የፕሮጀክት አስፈፃሚዎችን ጨምሮ ከአዲስ አበባ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ የምክትል ቢሮ ሀላፊና በቢሮው የተለያዩ የስራ ሀላፊዎችን ያካተተ የልዑካን ቡድን በኮሌጃችን ተገኝተው የፕሮጀክት አፈፃፀም እና የስራ ልምድ ልውውጥ አካሂደዋል:: ልዑካን ቡድኑ በኮሌጃችን በነበረው የልምድ ልውውጥ ጉብኝት መርሃ-ግብር ወቅት የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ በEASE ፕሮጀክት ያሳየውን የላቀ የስራ አፈፃፀም ሂደትን በዝርዝር የተመለከቱ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ አሁን እስከደረሰበት ደረጃ የነበረውን ሂደት እና ያከናወናቸውን ዘርፈ ብዙ የለውጥ እንቅስቃሴዎችን በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ሰፋ ያለ ገለፃና ማብራሪያም ተደርጎላቸዋል:: ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ በተደረገላቸው ገለፃና በተመለከቱት የኮሌጁ እንቅስቃሴ መነሻነት በነበረው ውይይት ወቅትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ እያከናወናቸው በሚገኘው ዘርፈ ብዙ የስራ እንቅስቃሴዎች መደነቃቸውን ገልፀው በተለይም ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት አተገባበር ላይ በአጭር ጊዜ ያሳየው የላቀ የስራ አፈፃፀም በሌሎች አቻ ኮሌጆችም ጭምር ሞዴል ተደርጎ እንዲታይ ያስቻለው መሆኑንም ገልፀዋል:: በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ የፕሮጀክቱን ማስተባበርያ ቢሮ እና በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ ዎርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን እዚህ በኮሌጁ ያገኟቸውን በርካታ ልምዶችንም ወደራሳቸው ወስደው ተግባራዊ በማድረግ እንደሚጠቀሙባቸውም ገልፀዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥቅምት 22/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

+2
2018 AMHARIC FINAL ADITED(1).mp32.79 MB

ለዲግሪ ፕሮግራም ትምህርትና ስልጠና ፈላጊዎች በሙሉ
ለዲግሪ ፕሮግራም ትምህርትና ስልጠና ፈላጊዎች በሙሉ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 ዓ.ም የትምህርትና ስልጠና ዘመን የአዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ምዝገባ ከጥቅምት 12/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 21/2018 ዓ.ም ድረስ የሚያከናውን
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 ዓ.ም የትምህርትና ስልጠና ዘመን የአዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ምዝገባ ከጥቅምት 12/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 21/2018 ዓ.ም ድረስ የሚያከናውን መሆኑን እናሳውቃለን::👇👇