fa
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

رفتن به کانال در Telegram
1 743
مشترکین
+224 ساعت
+37 روز
-730 روز
آرشیو پست ها
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2015 ዓ.ም የአዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ከ የካቲት 27/ 2015 ዓ.ም ጀምሮ የሚያካሂድ መሆኑን እየገለፀ እርሶም ባሉት ጥቂት የምዝገባ ቀናት በአካል ተገኝተው እንዲመዘገቡ ይጋብዛል።

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች የ2015 ዓ.ም የመጀመሪያ 6ወር የስራ አፈፃፀምና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ተወያዩ።      በዕለቱ በተዘጋጀው መድረክ የኮሌጁን የመጀመርያ 6ወር የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ጠቅለል ባለ መልኩ  በኮሌጁ ዲ/ን የቀረበ ሲሆን ከሰራተኛውም በግማሽ አመቱ ተግዳሮት የነበሩና በቀጣይ ሊሻሻሉ ይገባል ባሏቸውን ጉዳዮች ላይ ሀሳባቸውን ለመድረኩ አካፍለዋል።    በተጨማሪም በተቋሙ በቀጣይ ትኩረት ሊደረግባቸውን የታቀዱ ተግባራትን ለኮሌጁ ማህበረሰብ የቀረቡ ሲሆን ባጠቃላይ በመድረኩ የተነሱ ሀሳቦችና ጥያቄዎች ላይ በ ኮሌጁ ዲኖች ሰፋ ያለ ማብራሪያ ተሰቶባቸው ውይይቱ ፍፃሜውን አጊዥቷል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን የካቲት 10/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአስተዳደራችን ለሚገኘው የድል ጮራ ሪፈራል ሆስፒታል የማቴሪያል ድጋፍ አደረገ።     ተቋማችን በኮሚኒቲ ሰርቪሲንግ ለሆስፒታሉ ያደረገው ድጋፍ 10 የታካሚዎች መቀመጫ ወንበሮች እና 30 የግሉኮስ መስቀያ(IV Stands) ሲሆኑ ድጋፉንም የኮሌጃችን ም/ዲን አቶ ኤልያስ አህመድ ለሆስፒታሉ ተውካዮች አስረክበውልናል።      እነዚህ የማቴሪያል ድጋፎችም በኮሌጃችን በሚገኙት የውድ ዎርክ ዲፓርትመንት፣ የማኑፋክቸሪንግ ዲፓርትመንትና ከኢ/ኤ/አ ቴክኖሎጂ ስራ ሂደት ጋር በትብብር የተመረቱ ናቸው። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ጥር 30/2015 ዓ.ም

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ  "በብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት" ተጠቃሚ ለመሆን በአስተዳደሩ የቀበሌ አንድ ማዕከላት የተመዘገቡ ወጣቶችን የሁለተኛ ዙር ሰልጣኞች በዛሬው እለት ስልጠና መስጠት ጀመረ።         በዛሬው ዕለት ለስልጠናው ወደ ኮሌጃችን የመጡት የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ሰልጣኞች በቅድሚያ ከሚወስዱት የህይወት ክህሎት ስልጠና አስቀድሞ ስለ ስልጠናው ሰፋ ያየ ግንዛቤ የተሰጣቸው ሲሆን ለሚቀጥሉት 10ቀናትም ስልጠናቸውን እየወሰዱ በተቋማችን የሚቆዩም ይሆናል።      በስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የስራ እድል ፈጠራ እና የቀበሌ አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አሚን አብዱላሂ በዚህ ዙር ዘጠኝ መቶ ሀምሳ የሚደርሱ ሰልጣኞች ወደ ስልጠና የገቡ መሆኑን ጠቅሰው ሰልጣኞች ይህን እድል በሚገባ ተጠቅመው እራሳቸውንና አገራቸውን የሚጠቅሙ ዜጎች እንዲሆኑ አሳስበዋል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ህዝብ ግንኙነት ጥር 16/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

በብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ተጠቃሚ ለመሆን በአስተዳደሩ የቀበሌ አንድ ማዕከላት የተመዘገባችሁ ሁለተኛ ዙር ሰልጣኞች ማክሰኞ ጥር 16/2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 1:30 ስልጠና የምትጀም
በብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ተጠቃሚ ለመሆን በአስተዳደሩ የቀበሌ አንድ ማዕከላት የተመዘገባችሁ ሁለተኛ ዙር ሰልጣኞች ማክሰኞ ጥር 16/2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 1:30 ስልጠና የምትጀምሩ ይሆናል። በዚህም 👉 በ06 ቀበሌ አንድ ማዕከል 👉 በ09 ቀበሌ አንድ ማዕከል 👉 በ07 ቀበሌ አንድ ማዕከል(100 ሰልጣኞች) የተመዘገባችሁ ወጣቶች ስልጠናችሁ በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሲሆን፤ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኬሽን። ጥር 15 2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለመላው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ ይላል።

የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ        በድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አዘጋጅነት ሲሰጥ የነበረውንና  "ብቃት" የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ዙር የህይወት ክህሎት ስልጠና በኮሌጃችን ወስደው  ያጠናቀቁ 353 ሰልጣኞች የምርቃት መርሃግብር በዛሬው ዕለት  በድምቀት ተካሂዷል፡፡        በዕለቱ በነበረው መርሃ ግብርም የኮሌጁ ዲኖች ለሰልጣኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልክ ያስተላለፉ ሲሆን ሰልጣኞች የወሰዱት ስልጠና በዚህ እንደማያበቃና በቀጣይ በተጨማሪ ስልጠናዎች ከተቋሙ ጋር ሚገናኙ መሆኑንም ገልፀዋል።      በዚህም የሰልጣኞች የምርቃት መርሃግብር ላይ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን የብልጽግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ ለሰልጣኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በስልጠናው ያገኙትን እውቀት በቀጣይ በስራ ላይ ለሚኖራቸው ስልጠና እንዲጠቀሙበት በማሳሰብ የሚመጡ እና የሚገጥሟቸውን ፈተናዎች በጥንካሬ በማለፍ ለራሳቸውና ለሃገራቸው የሚጠቅሙ ዜጎች እንዲሆኑ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡         የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው ባለፉት 10 ቀናት የህይወት ክህሎት ስልጠና በኮሌጆቹ ውስጥ ሲሰጣቸው የቆየ ሲሆን ይህንንም ሲያጠናቅቁ በመረጡት የሙያ ዘርፍ በአስተዳደሩ በሚገኙ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ኢንደስትሪዎች ላይ የኪስ ገንዘብ እየታሰበላቸው በተግባር እየሰሩ እውቀትና ክህሎታቸውን የሚያዳብሩ እንደሚሆን ገልጸው በስልጠና ቆይታቸውም በኮሌጆቹ የህጻናት ማቆያ ቦታዎች ተዘጋጅቶላቸው የነበረ መሆኑና በዚህም የልጅ እናት የሆኑ የፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች ስልጠናውን ሳይስተጓጎሉ እንዲወስዱ ማቻሉን በማስታወስ ለዜጎች ሁሉን ተደራሽ የሚያደርግ የስራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎች በመሰራት ላይ ለመሆናቸው ይህ መርሃግብር ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።      በተጨማሪም ሰልጣኞችን በወከል ሀሳባቸውን ያጋሩት ተሳታፊዎም ባገኙት ስልጠና ትልቅ የሂወት ልምድና ዕውቀት ያገኙ መሆኑን በመግለፅ የዚህ ፕሮጀክት  አካል ስለሆኑም ደስተኞች መሆናቸውን በመድረኩ ገልፀዋል።        በቢሮው የስራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አሚን አብዱላሂ በአጠቃላይ በዚህ ዙር በሁለቱም ኮሌጆች ሰልጥነው ካጠናቀቁ ሰልጣኞች ብዛት ስድስት መቶ ሰማንያ ዘጠኝ መሆናቸውን ገልጸው በቀጣይም ሁለተኛ ዙር ሰልጣኞችን በተመሳሳይ ተጠቃሚ የሚደረግ መሆኑን አስታውቀው ሰልጣኞቹን በማሰልጠንና ሁኔታዎችን በማመቻቸት የተሳተፉ አካላትን ሁሉ አመስግነዋል። የኢትዮ ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ህዝብ ግንኙነት ጥር 10/2015 ዓ.ም ድሬዳዋ

#ብቃት_የወጣቶች_የስራ_ላይ_ልምምድ_ፕሮጀክት የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ "ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት" ተጠቃሚ ለመሆን በአስተዳደሩ የቀበሌ አንድ ማዕከል የተመዘገቡ ወጣቶችን በዛሬው እለት በተቋሙ ስልጠና መስጠት ጀምሯል። በዛሬው እለት በኮሌጁ ስልጠናቸውን መውሰድ የጀመሩትም የ01 ቀበሌ አንድ ማዕከል፣ የ02 ቀበሌ አንድ ማዕከል(ዋናው) እና የ02 ቀበሌ ቅርንጫፍ 1(ጎሮ ) አንድ ማዕከል ናቸው። በተጨማሪም ሰልጣኞች ስልጠና ከመጀመራችው በፊት አስፈላጊውን ኦሬንቴሽን የተሰጣቸው ሲሆን ስልጠናውን ለቀጣይ 10 ቀናት በተቋማችን እየወሰዱ የሚቆዩ ይሆናል። እንዲሁም ህፃናት ልጆች ያላቸው ሰልጣኞች ከስልጠናቸው እንዳይስተጓጎሉ በማሰብ በተቋሙ የህፃናት ማቆያ በማዘጋጀት ሰልጣኞች ለቀጣይ 10 ቀናት ልጆቻቸውን አምጥተው እንዲያቆዩበት መቻችቷል።