fa
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

رفتن به کانال در Telegram
1 741
مشترکین
+224 ساعت
+37 روز
-730 روز
آرشیو پست ها
በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ 2015 በጀት አመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ሰራተኞቹ የምስጋና እውቅና ፕርግራም አካሄደ። የድሬዳዋ አስተዳደር ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ በበጀት አመቱ የተሻለ የስራ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ሰራተኞች የምስጋና እና የእውቅና መርሀ-ግብርም የተቋሙ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል ። በእለቱ ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲኖች እና በመርሀ-ግብሩ ላይም ከተጋበዙ የክብር እንግዶች በ 2015 በጀት አመት የተሻለ የስራ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ሰራተኞች የምስጋና እና የእውቅና ሰርተፍኬት እንዲሁም ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማት ተቀብለዋል። በመጨረሻም የኮሌጁ ዲን ባስተላለፉት መልዕክት በ2015 በጀት አመት የተመዘገቡ ውጤቶች የሁሉም ሰራተኞች ጥረትና ድካም የተገኘ መሆኑን በመግለፅ ከእነዚህ ሰራተኞች ውስጥ የተሻለ አፈፃፀም ያላቸውን ለይተን እውቅና ስንሰጥ ለሌላውም መነሳሳትን እንዲፈጥር በማሰብም ጭምር መሆኑን ገልፀው በቀጣይ በጀት አመትም ተቋሙ የተሻለ የስራ አፈፃፀም እንዲያስመዘግብ ሁሉም በትጋት ሊሰራ ይገባልም ብለዋል። የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መስከረም 26/1/2016 ዓ.ም

የድሬዳዋ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ያሰለጠኗቸውን ከ400 በላይ ሰልጣኞች አስመረቁ **** ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ከደረጃ እስከ ዲግሪ መርሐ-ግብር ያሰለጠኗቸውን 420 ሰልጣኞች በዛሬው ዕለት በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አዳራሽ በጋራ አስመርቀዋል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር ሀርቢ ቡህ ትምህርት እና ስልጠና ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ እድገት ቁልፍ መሳሪያ ነው ብለዋል። ሀገራችን ኢትዮጵያ ወደ ብልፅግና ለምታደርገው ጉዞ በሙያዊ ክህሎት እና በስነምግባር የታነፀ ተነሳሽነት የተላበሰ እና ከአዳዲስ ቴክኖሎጂ እና አሰራሮች ጋር ተዎህዶ መስራት የሚችል አምራች ዜጋን በጥራት እና በብዛት በመፍጠር ረገድ በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ እድገት በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልፅዋል። በመሆኑም ተማሪዎች በሰለጠኑበት የሙያ መስክ ለሀገርና ለወገን የሚጠቅም ሥራ በመስራት በሀገሪቱ የተጀመረውን የብልፅግና ጉዞ እንዲረጋገጥ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱም ነው ምክትል ከንቲባ ክቡር ሀርቢ ቡህ በመልክታቸው ያሳሰቡት። የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው በአመለካከት በእውቀት እና በክህሎት እሳድገው እንዲመረቁ ላደረጉ ለኮሌጆቹ አሰልጣኝ መምህራን የእንኳን አደረሳችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። የዛሬው ምርቃት ከወትሮ ለየት የሚያደርገውም ለመጀመሪያ ጊዜ የድሬዳዋ አስተዳደር ስራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ተጠሪ ተቋማት ከሁለቱ ኮሌጆች ጋር በቅንጅት በመስራት እንዲሁም የደረጃ ሲ እና ቢ በአንድ ላይ ማስመረቅ መቻሉ ምርቃቱን ልዩ እንደሚያደርገው ተናግረዋል። በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ከንቲባና የንግድ ኢንደስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ፣ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው፣ የድሬዳዋ ዩንቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኡባህ አደም፣ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን፣ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ እና ሌሎች የፌደራልና የአስተዳደሩ ተጋባዦች ተገኝተዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 26/2016 ዓ.ም

በዛሬው እለት የምረቃ ስነ-ስርአታችሁን የምታከናውኑ የኮሌጃችን ሰልጣኝ ተማሪዎች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ::

“በድሬዳዋ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ትምህርትና ስልጠና ተከታትላችሁ ያጠናቀቃችሁ ሰልጣኝ ተማሪዎች በምትሰማሩበት በአመለካከት፣ በዕውቀት እና በክህሎት የታነጻችሁ ብቁ ዜጋ ሆናችሁ እንደ
+3
“በድሬዳዋ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ትምህርትና ስልጠና ተከታትላችሁ ያጠናቀቃችሁ ሰልጣኝ ተማሪዎች በምትሰማሩበት በአመለካከት፣ በዕውቀት እና በክህሎት የታነጻችሁ ብቁ ዜጋ ሆናችሁ እንደማያችሁ ሙሉ እምነት አለኝ፤ በዚህም የሀገር እድገት ላይ የድርሻ ሚናችሁን ለተወጣችሁ አሰልጣኞች፣ የዘርፉ አመራሮች እና ባለሙያዎች በሙሉ በቢሮው ስም ምስጋናዬን እያቀረብኩ ስልጠና አጠናቃቂዎች ለተገባችሁ ስኬት እንኳን ደስ አላችሁ!” አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ እንደሚታወቀው በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር ካሉት ዘርፎች አንዱ የቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ስልጠና ዘርፍ እንደመሆኑ የዘርፉን ግብ እና ዓላማ፤ ለማሳካት በሚደረገው ትግል ውስጥ የማይተካ ሚና ያላቸውና ባለራዕይ የሆኑ ከዘርፉ የሚፈሩ ሰልጣኝ ተማሪዎች እንደሆኑ እሙን ነው፡፡ የድሬዳዋ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጆችም ዘርፉን በአመለካከት፣ በእውቀት እና በክህሎት የበቁ ዜጎችን በማፍራት ላይ ሲገኙ በተለይ በአሁኑ ወቅት እንደ ቢሮ በተፈጠረው ተቀራርቦ የመስራትና የመደጋገፍ ሁኔታዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድነት ሰልጣኝ ተማሪዎችን በጋራ መስከረም 26/2016 ዓ.ም በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ትልቁ አዳራሽ በድምቀት የሚያስመርቁ ይሆናል፤ በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ!!!

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለመስቀል በአል በሰላም አደረሳችሁ ይላል::

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1498ኛው የመውሊድ በአል በሰላም አደረሳችሁ ይላል::

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የዘንድሮ ተመራቂዎቹን መስከረም 26/01/2016 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ የሚያስመርቅ መሆኑን እየገለፅን ተመራቂ ተማሪዎች ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳውቃለን::