Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
رفتن به کانال در Telegram
نمایش بیشتر
1 740
مشترکین
-124 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
-630 روز
آرشیو پست ها
የመንግስት ሰራተኛው በለውጥ ትግበራው ሂደት ላይ የራሱን ሚና መወጣት እንዲችል ተገቢውን መረጃ መስጠትና ግንዛቤ ማስጨበጥ እንደሚገባ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በበጀት አመቱ ከመደበኛ ስራዎች ጎን ለጎን በመንግስት አቅጣጫ መሰረት ትኩረት ተደርጎባቸው በሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ ለተቋሙ ሰራተኞች የግንዛቤ መፍጠርያ መድረክ አካሄደ::
በመድረኩ ላይ እንደ ሀገር በቀጣዮቹ 2ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ ታቅደው ከተጀመሩ ቁልፍ ተግባራት መካከል እንደ ቴክኒክና ሙያ ተቋም እንዲተገበሩ ከተቀመጡ ዝርዝር ተግባራት ውስጥ በተቋም ደረጃ የተዘጋጀው እቅድና አሁን የደረሰበት አፈፃፀም ቀርቦ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ሰፊ ግንዛቤ መፍጠር ተችሏል::
ይህ የግንዛቤ መድረክ በዋናነት ያስፈለገው የመንግስት ሰራተኛው በመንግስት የሚወርዱ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ግልፅነት ተፈጥሮለት ታች ፈፃሚው ድረስ እንዲወርድ ለማስቻል ነው ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ አክለውም ሀገራችን በቴክኖሎጂ የተደገፈ የአሰራር ስርዓትን እየዘረጋች እንደምትገኝና ጊዜው ከሚሰጠን ቴክኖሎጂዎች ጋር በመጣጣም የአገልግሎት አሰጣጣችንን የተቀላጠፈ በማድረግ እንደ ተቋም የተገልጋይ እርካታን በዘላቂነት ማረጋግጥ ይጠበቅብናልም ብለዋል::
በግንዛቤ መስጫ መድረኩ በቀጣዮቹ ሁለት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ ከተቀመጡት የ100% ግቦች.. የ "1" ግቦች እና የ "መቀነስ"ግቦች ጋር ተያይዞ የሚተገበሩ ዝርዝር ተግባራት ላይ በኮሌጁ ዲን አማካኝነት ገለፃ የተደረ ሲሆን በተጨሚሪም የ5million Initiative Program በተመለከተ አጠቃላይ ሰራተኛው የሚሰለጥንበት አግባብ ላይ ሰፊ ግንዛቤ መፍጠርም ተችሏል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ታህሳስ 2/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
#ዜና /በድሬዳዋ አስተዳደር ከ 2 ሺ 4 መቶ በላይ የሚሆኑ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክትን ወደ ስራ ለማስገባት ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተደረገ
#DGC ህዳር 25/2018
ኤስ ኦ ኤስ (SOS) የህፃናት መንደር በድሬዳዋ አስተዳደር ለ አምስት ዓመታት የሚተገበር ''Green growth -empowering youth for green future project ይፋ ማድረጉ የሚታወቅ ሲሆን በዛሬው ዕለት ፕሮጀክቱን ወደ ስራ ለማስገባት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል።
በዚህም በመርሃ-ግብሩ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ፕሮጀክቱ ከቴክኒክና ሙያ ተቋማት ጋር በጋራ እንደሚሰራ እና ከ2,400 በላይ የሚሆኑ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን ገልፀዋል።
ወ/ሮ ፈጡም አያይዘውም ፕሮጀክቱ ለአምስት አመታት እንደሚቆይ እና ለወጣቶች ክህሎት መር የስራ እድል እንደሚፈጥር አመላክተዋል።
የኤስ ኦ ኤስ የህፃናት መንደር የሀረር ፕሮግራም የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ቢሮ አስተባባሪ አቶ ሚካኤል ስንታየሁ ፕሮጀክቱ ለወጣቶች ስልጠና በመስጠት ከኢንዱስትሪዎች ጋር በማስተሳሰር እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በፕሮጀክቱ ለማሰልጠን ከታቀደው ውስጥ 60% የሚሆኑት ሴቶች 5%ቱ ደግሞ አካል ጉዳተኛ ወገኖች መሆናቸውን አቶ ሚካኤል ያመላከቱ ሲሆን፤ፕሮጀክቱን ስኬታማ ለማድረግ ከግል የፋብሪካ ቀጣሪ ድርጅቶች ጋር ውይይት መደረጉን ገልፀዋል።
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በበኩላቸው ድሬዳዋ የኢንደስትሪ ከተማ መሆኗን ጠቅሰው በፕሮጀክቱ ወጣቶችን በማሰልጠን ለኢንደስትሪው የማቅረብ ስራ በስፋት እንደሚሰራ አብራርተዋል።
አቶ ታደለ አያይዘውም ፕሮጀክቱ ለድሬዳዋ ወጣቶች የስራ እድልን በመፍጠር አሁን ያለውን የሥራ አጥ ቁጥር ለመቀነስና የስራ ባህልን በማጎልበት ረገድ ትልቅ አስተዋጽዖ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
በኤደን ሳሙኤል
ፎቶ:-ሰላም አበበ
ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.diredawacommunication.org
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/DGCOMU
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/@Direcommunication
ቴሌግራም፦ https://t.me/DDGCAB
ትዊተር፦ https://twitter.com/DawaOffice
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
#ዜና /በ10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም የድሬዳዋ አስተዳደር አፈጻጸም ሪፖርት ተገመገመ
#DGC ህዳር 25/2018
10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም በሰመራ ሎጊያ ከተማ ከህዳር 6 እስከ 10 መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን ወደ ስፍራው ያቀናው የአስተዳደሩ ልዑክ ቡድን የተሳትፎ የአፈጻጸም ሪፖርት በአስተባባሪ ኮሚቴ ቀርቦ ተገምግሟል።
በመድረኩም የድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ልማት ስራ አስኪያጅ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ጀማል ኢብራሂም አስተዳደሩ በዘንድሮ የከተሞች ፎረም ከዚህ ቀደም ከነበረው ተሳትፎ የተሻለ ስራዎች ይዞ መቅረቡን ጠቅሰው በ14 ዘርፍ እና በ2 ኢንሼቲቨ የተሰሩ የልማት ስራዎችን በማቅረብ አስተዳደሩን ማስተዋወቅ የተቻለ ሲሆን በዚህም አበረታች ውጤት ማምጣት መቻሉን ተናግረዋል።
አስተባባሪ ኮሚቴ እና ልዑክ ቡድኑ የነበረውን ቅንጅታዊ ስራ የሚደነቅ መሆኑን ያነሱት ኃላፊው በፎረሙ የተሳተፉ አካላትንም በሙሉ አመስግነዋል።
በሪፖርቱም የተገኙ ልምድና ተሞክሮ በማካፈል ረገድ ከተማችን ድሬ የአንድ ማዕከል ወደ ስራ መግባቱ ከመሬት አስተዳደር ካዳስተር ስራዎች ከቤቶች ልማት ጋር በተያያዘ አስተዳደሩ ለሌሎች ከተሞች ልምድ ማካፈል እና መውሰድ መቻሉ በሪፖርቱ ተብራርቷል።
ሰላም ለማ
ምስል:- አገኘው ሸዋረጋ
ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.diredawacommunication.org
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/DGCOMU
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/@Direcommunication
ቴሌግራም፦ https://t.me/DDGCAB
ትዊተር፦ https://twitter.com/DawaOffice
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከEDI ጋር በመተባበር ዘንድሮ ስልጠናቸውን ለሚያጠናቅቁ የኮሌጁ ሰልጣኝ ተማሪዎች ስራ ፈጣሪነት ላይ ያተኮረ የኢንተፕርነርሺፕ ስልጠና ሰጠ::
የኢንተርፕርነርሺፕ ስልጠናው ላለፉት 4 ቀናት በተቋሙ ሲሰጥ የቆየ ሲሆን ወጣቶች በኮሌጁ የሚኖራቸውን ቆይታ አጠናቀው ሲወጡ ኢንዱስትሪውን ከማንቀሳቀስ ባሻገር በሰለጠኑበት የሙያ ዘርፍ የቢዝነስ ሀሳቦችን በማፍለቅ እንዴት የራሳቸውን ስራ መፍጠርና ኢኮኖሚውን መምራት እንደሚችሉ ሰፊ ግንዛቤ ያገኙበትን ስልጠና ለወጣቶቹ መስጠት ተችሏል::
በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ ለሰልጣኞች መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው ስልጠና አጠናቃቂ ወጣቶች የቀጣይ ህይወታችሁን ምዕራፍ የምትወስኑበት ወሳኝ ጊዜ ላይ እንደመሆናችሁ መጠን ከወዲሁ ስራ ፈጣሪነትን እንድትላበሱ ታስቦ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልፀው በተለይ እንደ ቴክኒክና ሙያ ሰልጣኝ ሀገር መቀየር የሚችሉና በየዘርፉ ለሚስተዋሉ ክፍተቶች መፍትሄ የሚሆኑ የቢዝነስ ሀሳቦችን በማመንጨት ስራ ፈጣሪ ዜጋ መሆን ይጠበቅባችኃልም ብለወዋል::
ሰልጣኞች ወደ ስራ አለም ከመግባታችሁ አስቀድሞ ይህን የስራ ፈጣሪነት ስልጠናን በማግኘታችሁ እድለኛ ያደርጋችኃል ያሉት ደግሞ የኮሌጁ የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ዋና ስራ ሂደት ሀላፊና ም/ል ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ አያይዘውም የተሻለ የቢዝነስ ሀሳብ ይዘው ለሚመጡ ወጣቶች በኮሌጁ የኢንኩቤሽን ሴንተር በኩል አስፈላጊውን ትብብርና ድጋፍ ለማድረግ ኮሌጁ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ መሆኑንም ገልፀዋል::
ላለፉት 4 ቀናት ለስልጠና አጠናቃቂ ወጣቶች የተሰጠውን የኢንተፕርነሺፕ ስልጠና ኮሌጁ ከEDI(Ethiopian Development Inistitut) ጋር በመተባበር ያዘጋጀ ሲሆን የስራ ፈጣሪነት ስልጠናውም ከEDI በመጡ ባለሙያዎች መስጠት ተችሏል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ህዳር 20/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ADRA Ethiopia ፕሮጀክት በኮሌጁ በSolar PV Installation & maintenance አሰልጥኖ በማህበር ላደራጃቸው ወጣቶች በSollar(የፀሀይ ብርሃን) የሚሰራ የእህል ወፍጮ ማሽን በማበርከት ወደስራ እንዲገቡ አደረገ::
በድሬዳዋ አስተዳደር ቃልቻ የገጠር ቀበሌ ውስጥ የሚገኙ እና በSolar PV Installation & maintenance (በጸሐይ ብርሃን የኃይል ምንጭ መሳሪያዎች ገጠማና ጥገና) በመሰልጠን በማህበር ለተደራጁ አስራ ስምንት ወጣቶች በጸሐይ ብርሃን ኃይል የሚሰራ የእህል ወፍጮ ማሽን የADRA Germany ዋና ሀላፊ በተገኙበት ርክክብ ተደርጏል::
ADRA ፕሮጀክት በማህበር ለተደራጁ ወጣቶች ያበረከተው በSollar የሚሰራ ዘመናዊ የወፍጮ ማሽን አጠቃላይ ከ1 ሚልየን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበት የገለፁት የADRA Germany የምስራቅ አፍሪካ ዋና አስተባባሪ አቶ ዳዊት መሃሪ ሲሆኑ አክለውም በተደረገው ድጋፍ ውስጥ የወፍጮ ማሽኑን ጨምሮ ለተለያዩ አገልግሎቶች መጠቀም የሚያስችል የ3.6 KW የሚያመነጭ የSollar Panel ተከላና የመስመር ዝርጋታ አብሮ መከናወኑን ገልፀው ወጣቶች ባገኙት መልካም እጋጣሚ ለአካባቢያቸው ማህበረሰብ አገልግሎት እየሰጡ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያግዛቸዋልም ብለዋል::
ADRA Ethiopia ፕሮጀክት ከኮሌጁ ጋር በመቀናጀት በSolar PV Installation & maintenance ስልጠና እስካሁን በተለያዩ ዙሮች ከ120 በላይ ወጣቶችን ተቀብሎ በማሰልጠንና በማብቃት ራሳቸውን ብሎም ማህበረሰባቸውን እንዲጠቅሙ በማድረጉ ረገድ ጉልህ አስተዋጾ እያበረከተ መሆኑን ያስታወሱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በበኩላቸው ይህ ለመጀመርያ ጊዜ በMobile Training አማካኝነት ወጣቶቹ ባሉበት የገጠር ክላስተር ላይ በመሄድ የተሰጠውን ውጤታማ ስልጠና እንደ ሞዴል በመውሰድ በቀጣይ በሌሎች የስልጠና ዘርፎች ላይም በስፋት ለመስራት በእቅድ መያዙንም ገልፀዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ህዳር 16/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+4
በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት አዘጋጅነት ከህዳር 11 እስከ ህዳር 14 ድረስ በጥራት መንደር ሲካሄድ የቆየው የጥራት ኤግዚቢሽን በዛሬው እለት ፍፃሜውን አጊኝቷል::
በእለቱ በነበረው የጥራት ኤግዚቢሽ መዝጊያ ላይ ለተሳታፊዎች የእውቅና ፕሮግራም የተካሄደ ሲሆን የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በጥራት ኤግዝቢሽኑ ላይ ለነበረው የላቀ ተሳትፎ የእውቅናና ሰርተፊኬት ተበርክቶለታል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ህዳር 14/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ "ጥራት በተለየ እሳቤና ፈጠራ" በሚል መሪ ቃል 14ኛውን የዓለም ጥራት ሳምንት አስመልክቶ በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው ኤግዚቢሽን ላይ እየተሳተፈ ይገኛል::
የISO የጥራት አስተዳደር ተሸላሚነትን ያገኙ ከ150 በላይ ድርጅቶችና ተቋማት በሚሳፉበት በዚህ ኤግዚቢሽን ላይ ኮሌጃችን አጠቃላይ አገልግሎቶቹን ጨምሮ የተለያዩ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎቹን እና ምርቶቹን እያስተዋወቀም ይገኛል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ህዳር 11/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
+1
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማኔጅመንት አባላት ከEDI ከመጡ ባለሙያዎች ጋር ተወያዩ::
የውይይት መድረኩ ኮሌጁ ከEntrepreneurship Development Institute(EDI) ጋር በመተባበር ለተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ሲሰጥ በቆየው የኢንተርፕርነርሺፕ ስልጠና መሰረት በቀጣይ እንደ ተቋም ወደ ተግባር ለማስገባት ያለመ መሆኑም ተገልፇል::
በዚህም በማኔጅመት ደረጃ ሊሰሩ የሚገባቸውን ተግባራት አስመልክቶ የቀጣይ ትግበራ ዝርዝር እቅድ እዘገጃጀት ላይ ውይይቶች የተካሄዱ ሲሆን የጋራ አቅጣጫ ማስቀመጥም ተችሏል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ህዳር 08/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+9
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች "ህብረ ብሄራዊ አንድነት ለሀገር እድገት" በሚል መሪ ቃል 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በጋራ በፓናል ውይይት አክብረዋል::
ዘንድሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አዘጋጅነት የሚከበረው በዓል የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቋንቋና ማንነታቸው ህገመንግስታዊ እውቅና ያገኘበት ቀን መሆኑን የጠቀሱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አክለውም ኢትዮጵያውያን በልዩነት ውስጥ ያላቸውን ጠንካራ አንድነት ይበልጥ ለማፅናት ቃልኪዳናቸውን የሚያድሱበት ዕለት መሆኑንም ገልፀዋል::
በፓናል ውይይቱ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ማጠናከር ላይ ያተኮረ ሰነድ በአቶ አበበ ዋልጋ አማካኝነት ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት የተካሄደበት ሲሆን በዓሉ እስከ ህዳር 29 ድረስ በተለያዩ ፕሮግራሞች እየተከበረ እንደሚቆይም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ህዳር 07/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
