fa
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

رفتن به کانال در Telegram
1 740
مشترکین
-124 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
-630 روز
آرشیو پست ها
የሳቢያን አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጉብኝት አካሄዱ:: ኮሌጁ በ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ጋር ባለው ቅንጅትና ተማሪዎች ላይ እየፈጠረ የሚገኘውን ግንዛቤ መነሻ በማድረግ ተማሪዎች ስለዘርፉ ይበልጥ እውቀት እንዲኖራቸው እንዲሁም ኮሌጁ ስልጠናዎችን የሚሰጥበት አጠቃላይ እንቅስቃሴ እንዲመለከቱ ለማድረግ በአካል ተገኝተው እንዲጎበኙ ማድረግ ተችሏል:: ከጉብኝቱ አስቀድሞ ለተማሪዎቹ ኦረንቴሽን የሰጡት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ዋና ስራ ሂደት ሀላፊ የሆኑት አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ በንግግራቸውም በቅድሚያ በቀጣይ የክህሎት ባለቤት ወደሚያደርጋችሁ ኮሌጃችሁ እንኳን በደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን አክለውም እዚህ በኮሌጃችን ላይ የሚሰጡ ስልጠናዎች ከመደበኛው ትምህርት የሚለይበት ዋነኛ ምክንያት ሰልጣኞች አምስቱንም የስሜት ህዋሶችን ተጠቅመው የሚሰለጥኑበት በመሆኑ 100% ውጤታማና ብቁ የክህሎት ባለቤት የሆነ ዜጋ የሚፈራበት ዘርፍ በመሆኑን ነውም ብለዋል:: ም/ል ዲኑ አክለውም ኮሌጁ በቀጣይ ተማሪዎቹ ከመደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን በአጫጭር ስልጠናዎች በመረጡት የሙያ መስክ በማሰልጠን የሙያ ባለቤት ለማድረግ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገልፀው ተማሪዎች በቀጣይም በኮሌጁ የሚኖራቸውን ቆይታ ራሳችሁን ለማብቃት ሊጠቀሙበት እንደሚገባም አሳስበዋል:: የሳቢያን አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በጉብኝቱ ኮሌጁ ያለውን የማሰልጠን አቅምና የማሰልጠኛ ወክሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በቀጣይም በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ ማስጀመርያ በFinishing እንዲሁም በFurniture Making ሙያ ስልጠናዎችን በተከታታይ እንደሚወስዱም ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ታህሳስ 13/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች ታህሳስ 26 አረጋውያንን ለመደገፍ በተዘጋጀው 10ኛው የሩጫ ውድድር ላይ ቲሸርቱን በመግዛት እንደሚሳተፉ አረጋግጠዋል::

የአሰልጣኝ መምህሩን አቅም መገንባት የስልጠና ጥራቱን ከማሻሻል አንጻር የላቀ ሚና እንደሚጫወት ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ሂደት በምሽት ስልጠና በተ
+7
የአሰልጣኝ መምህሩን አቅም መገንባት የስልጠና ጥራቱን ከማሻሻል አንጻር የላቀ ሚና እንደሚጫወት ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ሂደት በምሽት ስልጠና በተለያዩ ሙያዎች ስልጠና ለሚሰጡ አዲስ አሰልጣኝ መምህራን የማሰልጠን ስነ-ዘዴ (Training Methodology) ስልጠና ሰጠ:: ስልጠናው ለአሰልጣኝ መምህራኑ ከስልጠና ጥራት ጋር ተያይዞ የዘርፉን እሳቤ ተረድተው ስልጠናውን በሚፈለገው ደረጃ መስጠት እንዲያስችላቸው እንዲሁም ከምዘና ሂደት እና የምዘና ውጤት አገባብ ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ከወዲሁ ለማስቀረት ታሳቢ ያደረገ ስልጠና እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን የሚነሱ ተያያዥ ቅሬታዎችንም ለመፍታት ያግዛልም ተብሏል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ታህሳስ 11/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት ፆታን መሰረት ባደረገ ጥቃት ላይ እንዲሁም የአካባቢያዊ እና ማህበራዊ ጥበቃን አስመልክቶ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ። በመድረኩ ፆታን መሰረት ያደረገ ጥቃት (Gender-Based Violence) እና የአካባቢና ማህበራዊ ጥበቃ (Enviroment and Social safe guard) ጋር ተያይዞ በፕሮጀክቱ ቀጣይ ትግበራዎችና ተደራሽ የሚሆኑ ዝርዝር ተግባራት ላይ ለኮሌጁ የኢንዱስትሪ አድቫይዘሪንግ ቦርድ አባላት እንዲሁም የልህቀት ማዕከል ከሆኑት ሶስቱ ዲፓርትመንት ለተወጣጡ አሰልጣኝ መምህራን ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሂዷል:: በEASE ፕሮጀክት በትኩረት እንዲሰራባቸው ከሚጠበቁ ጉዳዮች መካከል የስርዓተ-ፆታ እንዲሁም አካባቢያዊና ማህበራዊ ጥበቃ በዋነኛነት እንደሚጠቀሱ ያስታወሱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ እክለውም ፆታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ጋር በተመለከተ ፕሮጀክቱ የራሱ አያያዝና ሪፖርት አቀራረብ ሂደት ያለው በመሆኑ ግንዛቤን ለመፍጠር እንዲሁም በቀጣይ በፕሮጀክቱ የሚሰሩ የሪኖቬሽን ስራዎች የአካባቢ ጥበቃን ባማከለ ሁኔታ ተግባራዊ እንዲሆኑ በሚቻልበት አግባብ ከባለድርሻ አካላት ጋር ለመወያየት ይህ መድረክ መዘጋጀቱንም ገልፀዋል:: በዕለቱ በነበረው መድረክ በቅድሚያ በEASE ፕሮጀክት ትግበራ የእስካሁን አፈፃፀምና በቀጣይ የሚከናውኑ ቁልፍ ተግባራትን አስመልክቶ የፕሮጀክቱ ዋና አስተባባሪ የሆኑት ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ ለተሳታፊዎች በዝርዝር ገለፆ አድርገዋል:: በመቀጠል በፕሮጀክቱ ትግበራ ወቅት ፆታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ሲፈጠሩ ጉዳዩ በሚስተናገድበት አግባብና ሪፖርት ከማድረግ ጀምሮ እስከ ሚሰጠው ውሳኔ ድረስ በፕሮጀክቱ ባህሪ መሰረት የተቀመጠውን የአሰራር ሂደት በዝርዝር ለተሳታፊዎች ግንዛቤ የሰጡት የEASE ፕሮጀክት የስርዓተ-ፆታና አካቶ ባለሙያ የሆኑት አቶ አዲስ አክሊሉ ሲሆኑ በተጨማሪም የፕሮጀክቱ የተለያዩ ትግበራዎች በሚከናወኑበት ወቅት የአካባቢና ማህበራዊ ጥበቃን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንዲከናወኑ በሚያመለክት ሁኔታ የተቀመጡ ዝርዝር ሂደቶችና ነጥቦች ላይም ሰፊ ገለፃን በመስጠት ለመድረኩ ተሳታፊዎች ግንዛቤ ፈጠረዋል:: በመጨረሻም በቀረቡ ጉዳዮች ላይ ከመድረኩ ተሳታፊዎች ጋር ውይይት የተካሄደ ሲሆን ለቀጠይ የፕሮጀክቱ ትግበራ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦችም የተገኙበት መድረክ ነበር:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ታህሳስ 10/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የተቋማትን አቅም በማጠናከር የተሻለ አፈጻጸም እንዲያስመዘግቡ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ የድሬዳዋ አስተዳደር አካባቢ ደንና አየር ንብረት ለውጥ ባለሰልጣን EAC ፕሮጀክት ለኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተለያዩ መሳሪያዎችን ድጋፍ አደረገ የድሬዳዋ አስተዳደር አካባቢ ደንና አየር ንብረት ለውጥ ባለሰልጣን EAC ፕሮጀክት ከሚተገብራቸው ስራዎች አንዱ የተቋማትን አቅም መገንባት መሆኑ ይታወቃል፡፡ከነዚህ ተቋማት አንዱ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡ በዚህ መሰረት በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የሚገኘው EAC ፕሮጀክት በዛሬው እለት ለኮሌጁ አምስት ዴስክ ቶፕ ኮምፒዩተሮች፣አንድ ኤልሲዲ ፕሮጀክተር እና አንድ ፕሪንተር ድጋፍ አድርጓል፡፡ በድጋፍ ርክክብ ስነ-ስርአቱ ላይ የተገኙት የአካባቢ ደንና አየር ንብረት ለውጥ ባለሰልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አብዱ መሀመድ ድጋፉ ከኮሌጁ ጋር የምንሰራቸውን ስራዎች ወደላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር በአንጻሩ ከኮሌጁ የምናገኛቸውን የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎች አሰተማማኝ ደረጃ ላይ ያደረሰ ብለዋል፡፡ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በበኩላቸው ከአካባቢ ጥበቃ EAC ፕሮጀክት የተደረገው ድጋፍ ተቋማትን በስራና በቴክኖሎጂ ለማስተሳሰር ያለው ሚና የላቀ እና በሌሎችም ተቋማት ሊለመድ የሚገባው ምሳሌ የሚሆን መልካም ተግባር ነው ብለዋል፡፡ የኮሌጁ ዲን አክለውም ያለን የስራ ግንኙነት የላቀ ደረጃ የደረሰ መሆኑን ማሳያ ሲሆን ኮሌጁም ለፕሮጀክቱ እያደረገ ያለውን ድጋፍ በአይነትና በጥራት አንዲጨምር ትልቅ ኃላፊነት ለኮሌጁ የሰጠ ነው ብለዋል፡፡ የEAC ፕሮጀክት ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ በላይነህ ደስታ የተሰጡት ድጋፎች ከኮሌጁ ጋር አብሮ ለመስራትና የፕሮጀክቱን አላማዎች በቀላሉ ከምናሳካባቸው መንገዶች አንዱ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ለስራው መሳካት የተባበሩትን አካላት ሁሉ አመስግነዋል ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር አካባቢ ደንና አየር ንብረት ለውጥ ባለሰልጣን ያደረሰን መረጃ ያመላክታል #DGC

የአርዳይታ ግብርና ቴ/ሙ/ስ/ኮሌጅ አመራሮችን ያቀፈ ልዑካን ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የስራ ልምድ ልውውጥ ጉብኝት አካሄደ፡፡ የአርዳይታ ግብርና ቴ/ሙ/ስ/ኮሌጅ የEASE ፕሮጀክት ከሚተገበርባቸው 24 የሚሆኑ የሀገሪቱ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች አንደኛው ሲሆን በዚህም የኮሌጁን ዲኖች ጨምሮ የተለያዩ የስራ ሀላፊዎችን ያካተተ የልዑካን ቡድን በኮሌጃችን ያለውን የስራ እንቅስቃሴ ለመመልከት እንዲሁም በEASE ፕሮጀክት ትግበራ ያለውን ተሞክሮ ለመውሰድ የሚያስችላቸውን የስራ ልምድ ልውውጥ በኮልጁ ማካሄድ ችለዋል:: ልዑካን ቡድኑ በኮሌጃችን በነበረው የልምድ ልውውጥ መርሃ-ግብር ወቅትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ የEASE ፕሮጀክት ትግበራን ጨምሮ ጠቅላላ በተቋም የተመዘገቡ የአፈፃፀም ውጤቶችን በዝርዝር የተመለከቱ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ ከምስረታው አንስቶ አሁን እስከደረሰበት ደረጃ የነበረውን ሂደት እና ያከናወናቸውን ዘርፈ ብዙ የለውጥ እንቅስቃሴዎችን በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ሰፋ ያለ ገለፃና ማብራሪያም ተደርጎላቸዋል:: ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ በተደረገላቸው አቀባበልና በተመለከቱት የኮሌጁ እንቅስቃሴ መነሻ በማድረግ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ እያከናወናቸው የሚገኙ ዘርፈ ብዙ የስራ እንቅስቃሴዎች አስደናቂ መሆናቸውን ገልፀው በተለይም ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት ትግበራ ካሳየው የስራ አፈፃፀም ብዙ ልምዶችን መቅሰም መቻላቸውንም ገልፀዋል:: በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ የስልጠና ዎርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በነበራቸው የልምምድ ልውውጥ መርሃ-ግብርም የተሳካ ቆይታን በኮሌጃችን ማድረግ ችለዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ታህሳስ 6/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የሰበታ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችን ያቀፈ ልዑካን ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የስራ ልምድ ልውውጥ ጉብኝት አካሄደ፡፡ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በዘርፉ ባሳየው ከፍተኛ የስራ አፈፃፀምና መነቃቃትን ጨምሮ አጠቃላይ በኮሌጁ ባስመዘገባቸው ተጨባጭ ውጤቶች ጋር ተያይዞ በርካታ ኮሌጆች ተቋማችንን መዳረሻቸው እያደረጉ የሚገኙ ሲሆን በዚህም የሰበታ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲኖች ጭምሮ የተለያዩ የስራ ሀላፊዎችን ያካተተ የልዑካን ቡድን በኮሌጃችን ተገኝተው የስራ ልምድ ልውውጥ ማካሄድ ችለዋል:: ልዑካን ቡድኑ በኮሌጃችን በነበረው የልምድ ልውውጥ መርሃ-ግብር ወቅት የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ በEASE ፕሮጀክት ጨምሮ ጠቅላላ የተቋም አፈፃፀም በዝርዝር የተመለከቱ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ አሁን እስከደረሰበት ደረጃ የነበረውን ሂደት እና ያከናወናቸውን ዘርፈ ብዙ የለውጥ እንቅስቃሴዎችን በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ሰፋ ያለ ገለፃና ማብራሪያም ተደርጎላቸዋል:: ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ በተደረገላቸው ገለፃና በተመለከቱት የኮሌጁ እንቅስቃሴ መነሻነት በነበረው ማጠቃለያ ውይይትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ እያከናወናቸው በሚገኘው ዘርፈ ብዙ የስራ እንቅስቃሴዎች አስደናቂ መሆናቸውን ገልፀው በተለይም ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት አተገባበር ላይ በአጭር ጊዜ ያሳየው የላቀ የስራ አፈፃፀም በሌሎች አቻ ኮሌጆችም ጭምር ሞዴል ተደርጎ እንዲታይ ያስቻለው መሆኑንም ገልፀዋል:: በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ የስልጠና ዎርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በነበራቸው የልምምድ ልውውጥ መርሃ-ግብርም የተሳካ ቆይታን ማድረግ ችለዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ታህሳስ 4/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ