Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
رفتن به کانال در Telegram
نمایش بیشتر
1 739
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+27 روز
-330 روز
آرشیو پست ها
የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር ጋር በተያያዘ በአምራች ኢንዱስትሪው ላይ የሚታየውን ክፍተት የመሙላቱ ተግባር በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአስተዳደሩ ለሚገኘው የሹምብሮ ፕላስቲክ ፋብሪካ አመራርና ሰራተኞች የሙያ ደህንነትና ጤንነት ( Occupational Safety & Health) ስልጠና በኮሌጁ መስጠት ጀመረ::
ስልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በመልዕክታቸው ተቋማችን ከዚህ ቀደም በአስተዳደሩ ተያያዥ በሆኑ የኢንጂነሪንግ ዘርፎች ተመርቀው ስራ ያልያዙ ወጣቶችን በማሰልጠን እንዱስትሪዎች ላይ በሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር ላይ ተቀጥረው እንዲሰሩ ማመቻቸቱን አስታውሰው ይህ በዛሬው እለት የተዘጋጀው የሙያ ደህንነት ስልጠናም በዚህ አመት ለኢንዱስትሪ አንቀሳቃሽ ባለሙያዎች በስፋት ለመስጠት በእቅድ የተያዙ ስልጠናዎች አንድ አካል መሆኑንም ገልፀዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለው ተቋማችን በሹንብሮ ፕላስቲክ ፋብሪካ በተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችና ቴክኖሎጂዎች ላይ ድጋፍ ለማድረግ አብረን እየሰራን እንገኛለን ያሉ ሲሆን የዛሬውን Occupational Safety & Health (OSH) ስልጠናን ጨምሮ በቀጣይ በተቋማችን የሚሰጡ ስልጠናዎች በድርጅቱ ላይ ከፍተኛ ለውጥ የሚያመጡ በመሆናቸው በትኩረት ስልጠናውን መውሰድ እንደሚያስፈልግም ገልፀዋል::
የEASE ፕሮጀክት በኮሌጁ የትኩረት ማዕከል አድርጎ ከሚሰራባቸው ሶስት የሙያ ዘርፎች አኳያ የOrganization Safety Health (OSH) ስልጠና ቀጥተኛ ተያያዥነት ያለው መሆኑን የገለፁት የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪ ኢ/ር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ አክለውም የOSH ስልጠናው ደረጃውን በጠበቀ መንገድ ለመስጠት የሚያችሉ የተለያዩ የደህንነት ማቴሪያሎችን በፕሮጀክቱ ግዢ በማድረግ ማሟላት መቻሉንም ገልፀዋል::
የሙያ ደህንነትና ጤንነት (Occupational Safety & Health) ስልጠናው ብቁ በሆኑ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን እማካኝነት ለቀጣይ 6 ቀናት የሚሰጥ ሲሆን በዚህም የድርጅቱ ሰራተኞች በስራ ቦታ ላይ የሚደርሱ አደጋዎችን በመለየት እና በመቆጣጠር የሰውን ህይወት እንዲሁም ንብረትን ከአደጋ መጠበቅ የሚያስችሉትን የተግባርና የንድፍ ሃሳብ ስልጠና እንደሚሰጣቸውም ተግልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ጥር 5/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በየጊዜው የሚዘረጉ ዲጂታል የአሰራር ሲስተሞችን በመጠቀም የአገልግሎት አሰጣጥን ማቀላጠፍ እንደሚገባ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተቋሙን አጠቃላይ አሰራር በዲጂታል ሲስትም ለመቀየር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል::
ኮሌጁ የአገልግሎት አሰጣጡን ጨምሮ አጠቃላይ የተቋሙን አሰራር በDigital System ለመተካት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ለአመራር አባላትና ለክፍል ተጠሪዎች የግንዛቤ መድረክ አካሂዷል::
አሁን ባለንበት ዘመን ቴክኖሎጂን መጠቀም ምርጫ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ መሆኑን የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ አክለውም እንደ ተቋም ቀጣይነትን ለማረጋገጥ በዲጂታል ሲስተም ጠንካራ ተሳትፎ ማድረግና ምንሰጣቸውን አገልግሎቶች ማዘመን ይጠበቅብናልም ብለዋል::
የግንዛቤ ስልጠናው ከኢትዮ ቴሌኮም በመጡ ባለሙያዎች የተሰጠ ሲሆን በዚህም አሁን ያለው አሰራር በዲጂታል ሲስተም ሲቀየር በምን መልኩ ይሰራል የሚለውና የስራ ክፍሎች ሲስተሙን የሚያንቀሳቅሱበትን ሂደት በዝርዝር ግንዛቤ መስጠት ችለዋል::
በመድረኩ በተሰጠውን ግንዛቤ ላይ ከተሳታፊዎች በሲስተሙ አተገባር ዙሪያ ግልፅ ያልሆኑ ጉዳዮች ተነስተው ሰፊ ማብራሪያም ተሰጥቶባቸዋል::
በእለቱ ግንዛቤውን የሰጡት የኢትዮ ቴሌኮም ባለሙያዎች በቀጣይ ቀናትም ሲስተሙ የሚተገበርባቸው በሁሉም ስራ ክፍሎች ላይ በመገኘት የሲስተሙን አጠቃላይ አተገባበርና አጠቃቀምን በተመለከተ የተግባር ስልጠና እንደሚሰጡም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ጥር 3/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+1
#እንኳን_አደረሳችሁ_አደረሰን
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ 2018 ዓ.ም የእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል(ገና) በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያልኩኝ በዓሉ የሠላም፣ የጤና፣ የአንድነት፣ የመተሳሰብ እና መደጋገፍ በዓል ይሆንልን ዘንድ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ።
#መልካም_የገና_በዓል!!
አቶ ታደለ አሰፋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን
በገጠር ክላስተሮች የMobile Trainingን በስፋት በማዳረስ ወጣቶች በአካባቢያቸው ያለውን ሰፊ የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ::
በድሬደዋ አስተዳደር ከሚገኙ የገጠር ክላስተሮች እና የገጠር ስራ እድል ፈጠራ ተወካዮች እንዲሁም ከስልጠና ክፍል ተጠሪዎች ጋር የአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍን በተመለከት የውይይት መድረክ በኮሌጁ ተካሂዷል።
በገጠር ክላስተሮች ያለው የተፈጥሮ ፀጋ በመገንዘብ በአካባቢው የሚገኙ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተግባራትን ማከናወን ያስፈልጋል ያሉት የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ል ሀላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ አክለውም የMobile Training ትግበራን በስፋትና በጥራት ተደራሽ ለማድረግ በሚኖረው ሂደት ክላስተሮችና የገጠር ስራ እድል ፈጠራ አስተባባሪዎች የሚያስፈልጉ መሰረተ ልማቶችን በማመቻቸት የስልጠናዎችን ውጤታማነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልፀዋል::
በኮሌጁ የMobile Training ሊሰጥባቸው በሚያስችሉ ዲፓርትመንቶች ላይ የተለዩ የሙያ መስኮች መኖራቸውን የገለፁት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ሂደት ሀላፊ አቶ ኤሊያስ አህመድ ሲሆኑ አክለውም በቀጣይ ከገጠር ክላስተር አስተባባሪዎችና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ነባራዊ ሁኔታ ላይ መነሻ ያደረገ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በማካሄድ በተለያዩ ዘርፎች ስልጠናዎች እንደሚሰጡም አመላክተዋል::
በመድረኩ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ በMobile Training በገጠር ክላስተሮች ላይ ያከናወናቸው ተግባራትና ያለውን መልካም ተሞክሮ በኢ/ር ህይወት እሸቱ አማካኝነት ለተሳታፊዎች ገለፃ የተደረ ሲሆን በስልጠናው የተመዘገቡ ውጤቶችን ጨምሮ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችም ቀርበው በቀጣይ ስልጠናዎች በሚሰጡበት አግባብ ላይም ውይይት ተካሂዷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+3
𝗘𝗗𝗜 & 𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼-𝗜𝘁𝗮𝗹𝘆 𝗣𝗼𝗹𝘆𝘁𝗲𝗰𝗵𝗻𝗶𝗰 𝗖𝗼𝗹𝗹𝗲𝗴𝗲 (𝗘𝗜𝗣𝗖) 𝗣𝗮𝗿𝘁𝗻𝗲𝗿 𝗳𝗼𝗿 𝗘𝗻𝘁𝗿𝗲𝗽𝗿𝗲𝗻𝗲𝘂𝗿𝗶𝗮𝗹 𝗧𝗩𝗧 𝗘𝘅𝗰𝗲𝗹𝗹𝗲𝗻𝗰𝗲
Today, EDI and Ethio-Italy Polytechnic College (EIPC) signed an MoU to turn technical skills into thriving businesses! This partnership moves beyond "business as usual" by embedding an entrepreneurial ecosystem into the college.
What’s coming to EIPC?
✅ New Entrepreneurial Curriculum for all students.
✅ Business Incubation & Advisory to launch real ventures.
✅ Staff Capacity Building to create expert mentors.
✅ Enterprise Support for local technology transfer.
✅ Community Ecosystem Building to drive the local economy.
The goal is clear: make entrepreneurial method a core part of the TVT DNA. Together, we are creating a hub where innovation meets industry!
#Entrepreneurship #EIPC #EDI #TVET #DireDawa #InnovationHub #JobCreation
+4
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በተለያየ ዘርፍ ስኬታማ መሆን የቻሉ ሴቶችን በመጋበዝ ለኮሌጁ ሴት አሰልጣኝ መምህራንና ሴት ሰልጣኞች ልምድና ተሞክሮ የሚቀስሙበት መድረክ አካሂዷል::
በመድረኩ ተገኝተው በህይወታቸው ያካበቱትን ከፍተኛ ልምድና ተሞክሮ ለተሳታፊዎች ማካፈል የቻሉት በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ድሬደዋን በመወከል የፓርላማ አባል የሆኑት ክብርት ቢፍቱ መሀመድ(ዶ/ር) እና በሀረማያ ዩኒቨርሲቲ የስነ-አዕምሮ መምህርት የሆኑት ዶ/ር ፈቲያ እንዲሁም በኮሌጁ ለረጅም አመታት በብቃት እያሰለጠኑ የሚገኙት አሰልጣኝ መምህርት ለምለም ግ/ስላሴ ሲሆኑ በዚህም በተለያዩ የስራ ሀላፊነቶች ላይ ተሰማርተው ስኬት እንዲያስመዘግቡ ያስቻላቸው የህይወት ልምዳቸውን ለተሳታፊዎች አካፍለዋል::
ኮሌጁ የተቋቋመበትን ዓላማና ተልዕኮ ለማሳካት በሚያደርገው ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴ የሴት አሰልጣኝ መምህራን እና ሰልጣኝ ተማሪዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የገለፁት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ስራ ሂደት ሀላፊ አቶ ኤሊያስ አህመድ ሲሆኑ አክለውም የዚህ መድረክ ዋና ዓላማም ከፍተኛ ጫናን ተቋቁመው ስኬታማ የሆኑ እንዲሁም በተሰማሩበት ዘርፍ ለሀገር እድገት የድርሻቸውን እያበረከቱ ከሚገኙ ሴት እህቶቻችን ተሞክሮ እንዲወስዱ ለማድረግና ወደራሳቸው ህይወት በመውስድም በተግባር እንዲጠቀሙበትም ለማስቻል መሆኑንም ገልፀዋል::
በእለቱ በተካሄደው መድረክ በተሳታፊዎችና በተጋባዥ እንግዶች መካከል ነፃ ውይይቶች የተካሄዱ ሲሆን በዚህም ሴቶች ሚገጥሟቸውን አስቸጋሪ የህይወት ጎዳናዎች በራስ መተማመን፣ በብልሃትና በጥበብ መሻገር አሸናፊ ሆነው እንዲወጡና የህይወት መንገዳቸውንም በስኬት እንዲመሩ የሚያግዛቸው መሆኑን ምክር ለግሰዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ታህሳስ 23/2018 ዓ.ም
ሴቶችን በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች እንዲበቁ ማስቻል ሀገራዊ ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት የሴቶችን የአመራር ክህሎት፣ በራስ መተማመን እና የውሳኔ አሰጣጥ ችሎታን ማሳደግ ላይ ያተኮረ የLeadership ስልጠና ሰጥቷል።
በEASE ፕሮጀክት በቀጣይ 5 ዓመታት ውስጥ በትኩረት ከሚያከናወኑ ተግባራት መካከል ሴቶችን በልዩ ሁኔታ የማብቃትና በሁሉም ዘርፎች የመሪነት ሚና ላይ በንቃት እዲሳተፉ ማስቻል እንደሆነ የገለፁት በኮሌጁ የEASE ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ አክለውም ወቅቱ ሴቶችን ለማብቃት ዘርፈ ብዙ ስራዎች የሚከናወኑበት ጊዜ በመሆኑ ሴት እህቶቻችን አቅማቸውን ለማሰየት ጥሩ መደላድል የሚፈጥርላቸው መሆኑንም ገልፀዋል::
በእለቱ የተዘጋጀው የLeadership ስልጠና በኮሌጁ ለሚገኙ ሴት አሰልጣኝ መምህራን እና ከየዲፓርትመንቱ ለተወጣጡ ሴት ሰልጣኝ ተማሪዎች ከሀረማያ ዩኒቨርሲቲ በመጡት ዶ/ር ፈትያ አማካኝነት ስልጠናውን በጥሩ ሁኔታ መስጠት የተቻለ ሲሆን በቀጣይም መሰል ስልጠናዎችን በተከታታይ በማዘጋጀት ሲቶችን የማብቃት ተግባራት እንደሚከናወኑም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ታህሳስ 22/2018 ዓ.ም
Repost from N/a
ሴቶችን በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች እንዲበቁ ማስቻል ሀገራዊ ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት የሴቶችን የአመራር ክህሎት፣ በራስ መተማመን እና የውሳኔ አሰጣጥ ችሎታን ማሳደግ ላይ ያተኮረ የLeadership ስልጠና ሰጥቷል።
በEASE ፕሮጀክት በቀጣይ 5 ዓመታት ውስጥ በትኩረት ከሚያከናወኑ ተግባራት መካከል ሴቶችን በልዩ ሁኔታ የማብቃትና በሁሉም ዘርፎች የመሪነት ሚና ላይ በንቃት እዲሳተፉ ማስቻል እንደሆነ የገለፁት በኮሌጁ የEASE ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ አክለውም ወቅቱ ሴቶችን ለማብቃት ዘርፈ ብዙ ስራዎች የሚከናወኑበት ጊዜ በመሆኑ ሴት እህቶቻችን አቅማቸውን ለማሰየት ጥሩ መደላድል የሚፈጥርላቸው መሆኑንም ገልፀዋል::
በእለቱ የተዘጋጀው የLeadership ስልጠና በኮሌጁ ለሚገኙ ሴት አሰልጣኝ መምህራን እና ከየዲፓርትመንቱ ለተወጣጡ ሴት ሰልጣኝ ተማሪዎች ከሀረማያ ዩኒቨርሲቲ በመጡት ዶ/ር ፈትያ አማካኝነት ስልጠናውን በጥሩ ሁኔታ መስጠት የተቻለ ሲሆን በቀጣይም መሰል ስልጠናዎችን በተከታታይ በማዘጋጀት ሲቶችን የማብቃት ተግባራት እንደሚከናወኑም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ታህሳስ 22/2018 ዓ.ም
ወጣቶችን በዲጂታል ክህሎት ማስታጠቅ የዲጂታል ኢኮኖሚውን ግንባታ በአጭር ጊዜ እውን ለማድረግ እደሚረዳ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ ለሚገኙ ሰልጣኝ ተማሪዎች የ"5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ" (5 Million Ethiopian Coders) ስልጠና እንዲወስዱ ለማስቻል የግንዛቤ መስጫ መድረክ አካሄደ::
የ5 ሚልዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ ስልጠና ዋና አላማ ወጣቶች የኮዲንግ ክህሎት በመማር የአገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ስራዎችን እንዲያገኙ ወይም የራሳቸውን ፈጠራ በመጠቀም ሀብት እንዲፈጥሩ ለማስቻል እንደሆነ የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ አክለውም የICT ዘርፉ የሀገራችን ኢኮኖሚ ሙሰሶ ተደጎ በትኩረት እየተሰራበት በመሆኑን ጭምር ወጣቶች በቀጣይ ህይወታቸው ለውጥ ሊያመጡ የሚያስችሉ መሰል ክህሎቶች ላይ ትኩረት አድርገው ቢሰሩ ተጠቃሚ ያደርጋቸዋልም ብለዋል::
ሰልጣኞች ከመደበኛ ትምህርትና ስልጠናቸው ጎን ለጎን ጊዜው የሚሰጠንን ዲጂታል ክህሎቶች መቅሰም ተፈላጊነታቸውን ይበልጥ ያሳድጋል ያሉት ደግሞ የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ስራ ሂደት ሀላፊ የሆኑት አቶ ኤሊያስ አህመድ ሲሆኑ መንግስት በነፃ ለዜጎቹ ያመቻቸውን ይህን የ"5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ" ስልጠና በአግባቡ በመጠቀም የክህሎት ባለቤትና ተወዳዳሪ መሆን እንደሚችሉም አስገንዝበዋል::
ሰልጣኞች የ"5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ" (5 Million Ethiopian Coders) ስልጠናውን ሲወስዱ ከምዝገባው ጀምሮ ስልጠናውን ተከታትለው ሰርተፊኬት እስከመውሰድ ድረስ ያለውን ሂደት በቅደም ተከተል ግንዛቤ የሰጡት በኮሌጁ የICT ዲፖርትመንት ተጠሪ የሆኑት አሰልጣኝ መ/ር አቤል ፉንታሁን ሲሆኑ በቀጣይም ለዚሁ አላማ በተዘጋጁ የዲፖርትመንቱ Labና በተቀመጠው መርሃ-ግብር መሰረት ሰልጣኞች የኮዲንግ ስልጠናውን በኮሌጁ እንደሚወስዱ ገልፀዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ታህሳስ 20/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
መልካም ስብዕና ያለው ትውልድን በመገንባት ሙስናን በዘላቂነት መከላከል እንደሚገባ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች በአለም አቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ20ኛ ጊዜ "ትውልድን በስነ-ምግባር ተቋምን በአሰራር " በሚል መሪ ቃል የዓለም የፀረ-ሙስና ቀንን በፖናል ውይይት አክብረዋል::
በክብረ በዓሉን ላይ ለሰራተኛው መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው ሙስና በባህሪው በግልፅ የማይታይና ውስብስብ የሆነ መገልጫ ያለው በመሆኑ በመንግስት አቅም ብቻ ተቆጣጥሮ ችግሩን መቅረፍ አይቻልም ያሉ ሲሆን አስተሳሰቡ የዳበረና ሙስናን የሚጠየፍ ትውልድ በመቅረፁ ረገድ እንደ ተቋም የድርሻችንን ማበርከት ይጠበቅብናልም ብለዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም ሙስና ያልተገባ ጥቅም ማግኘት ብቻ ሳይሆን እንደ ተቋም የአገልግሎት አሰጣጥን በእስታንዳርዱ መሰረት ለዜጎች አለመስጠትንም ይጨምራል ያሉ ሲሆን በዚህም የምንሰጣቸውን አገልግሎቶ ከማዘመን ጀምሮ ሁላችንም ባለንበት የስራ ዘርፍ የድርሻችንን መወጣት ስንችል ሀገር በማሻገር ሂደት ውስጥ አሻይራችንን ማሳረፍ እንችላለንም ብለዋል::
በመድረኩ ክብረ-በዓሉን አስመልክቶ የተዘጋጀው ሰነድ በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ለሰራተኛው ቀርቦ ግንዛቤ መፍጠር የተቻለ ሲሆን በቀረበው ሰነድ ላይም በተሳፊዎች ውይይት ተደርጎበታል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ታህሳስ 15/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
