es
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ir al canal en Telegram
1 744
Suscriptores
Sin datos24 horas
+67 días
-330 días
Archivo de publicaciones
#ዜና | የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቲክኒክ ኮሌጅ በሙያ ደህንነት እና ጤንነት (occupational Safty and Health) ዙሪያ ሲያስለጥናቸው የቆየውን ከአስር ስድስት(16) በላይ የኢንዱስትሪ አንቀሳቃሽ ባለሞያዎችን አስመርቋል:: ኮሌጁ ይህን ስልጠና ሲያከናውን ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን ከሽንብሮ ፕላስቲክ ፋብሪካ ጋር በመዋዋል የፋብሪካውን ከአስራ ስድስት (16 ) በላይ የሆኑ ሰራተኞችን አሰልጥኖ ማስመረቁን በወቅቱ ተጠቅሷል ። በወቅቱ ንግግር ያደረጉት የስራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊና የቴክኒክና ሞያ ኤጀንሲ ዳሬክተር ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ቢሮው በስሩ ዘርፈብዙ ስራዎችን እንደሚሰራ ጠቅሰው ከስራዎቹም መካከል የፋብሪካን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የሞያ ክፍተቶችን በመሙላት ደህንነታቸው የተጠበቀ የበቁ ዜጎችን ማብቃት ነው ብለዋል :: ቢሮው የሞያ ክፍተትን በስልጠና ማጠናከር ብቻ ሳይሆን በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች በኩል በአስተዳደሩ ለሚገኙ የተለያዩ ፋብሪካዎች መለዋወጫዎችን በማምረት የውጭ ምንዛሬን ከማስቀረት ባሻገር ከውጪ ግብዓቱ የሚመጣበትንም ጊዜ እንዲቆጠብ እያደረገ ይገኛልም በማለት ሀላፊዋ አክለው ተናግረዋል :: የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በበኩላቸው ይህ የፋብሪካ ውስጥ የሞያ ደህንነትና የጤና አጠባበቅ ስልጠና እንደ ሀገር ያለ ክፍተት መኖሩን ጠቅሰው ኮሌጁ ይህን ችግር ለመቅረፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሽንብሮ ፕላስቲክ ፋብሪካ ጋር በመዋዋል የፋብሪካውን ከአስር ስድስት (16) በላይ ሰራተኞች ማሰልጠናቸውን ተናግረዋል :: ስልጠናውን ተከታትለው የተመረቁት ስልጣኖች በበኩላቸው የወሰዱት የሞያ ደህንነትና የጤና ስልጠና ከፋብሪካ ውስጥ ስራችን ውጪም የግል ሕይወታችንን ለምን መራበት አካባቢም የሚጠቅመን ነው ብለዋል :: በምረቃና ማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይም ስልጠናቸውን ላጠናቀቁ ሰልጣኖች የእውቅና ስርተፊኬት ተሰጥቷል :: #DireTvአማርኛ |ጥር 16 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

#እንኳን_አደረሳችሁ!! ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሠላም አደረሳችሁ እያልኩ፤ በዓሉ የሠላም፣ የደስታ፣ የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!! #መልላም_የጥም
#እንኳን_አደረሳችሁ!! ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሠላም አደረሳችሁ እያልኩ፤ በዓሉ የሠላም፣ የደስታ፣ የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!! #መልላም_የጥምቀት_በዓል!! አቶ ታደለ አሰፋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን

ኮሌጁ የታዳጊና ወጣቶችን ፈጠራ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአስተዳደሩ ከሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለተወጣጡ ተማሪዎች ግንዛቤ መስጫ መድረክ አካሄደ:: በመድረኩ ለታዳጊዎች መልዕክት ያስተለፉት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ዋና ስራ ሂደት ሃላፊ አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ በንግግራቸውም በቅድሚያ የብቁ ሞያተኞችና ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች መፍለቂያ ወደ ሆነው ተቋማችን እንኳን ደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን እዚህ እንድትገኙ የሆነበት ምክንያት አሁን ላይ በንድፍ ምትማሯቸውን ትምህርቶችን በተግባር ችግሮችን ለመፍታት የምትጠቀሙበትን አግባብ ለማስገንዘብ እንዲሁም ያላችሁን የፈጠራ ሀሳብ ከወዲሁ መሰረት የምታሲዙበትን መንገድ ለማመቻቸት እንደሆነም ገልፀዋል:: ባደጉት ሀገራት ከፍተኛ ተከፋይ መሆን የሚያስችሉት የክህሎት ሙያዎች እንደሆኑ የገለፁት በኮሌጁ የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪ ኢ/ር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ እንደ ፕሮጀክት በነዚህ ጉዳዮች ላይ ድጋፍ ለማድረግ ስናስብ አስተዳደሩ ላይ ያሉ ወጣቶች የራሳቸው ሙያ ኖሯቸውና ከስራ ጋር ተገናኝተው እራሳቸውንም ሆነ ቤተሰባቸውን እንዲደግፉ ለማስቻል ነውም ብለዋል:: በመድረኩ የፈጠራ ሀሳብን ወደ ተግባር አሳድጎ ችግር ፈቺ ቢዝነሶችን እውን የማድረግን ፅንሰ ሀሳብ በተመለከት የጥናትና ቴክኖሎጂ ሽግግር አስተባባሪ በሆኑት አቶ ያሬድ ሁሉአለም አማካኝነት ግንዛቤ መፍጠር የተቻለ ሲሆን በተጨማሪም በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሂሳብ(STEM) ምንነትና በዘርፉ ያለውን ከፍተኛ አስተዋፅኦ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ለታዳጊዎቹ ግንዛቤ ሰጥተዋል:: በቀጣይም የፈጠራ ሀሳብ ያላቸውን ታዳጊዎች በመለየት ሀሳባቸው ወደ ችግር ፈቺ ቢዝነሶች መለወጥ የሚያስችላቸውን ክህሎቶች በተቋሙ እንደሚሰጣቸውም ተገልፀዋል:: በእለቱ በተካሄደው የግንዛቤ መድረክም የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህርትና እና ሰልጣኝ ተማሪ ለ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎቹ በዘርፉ ያደረጏቸውን ስኬታማ ጉዞዎች እና የህይወት ልምዳቸውን ማካፈልም ችለዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥር 9/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት የበጀት አመቱ የመጀመሪያ 6ወር የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ:: በሪፖርት መድረኩ የEASE ፕሮጀክት በ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ 6ወር ውስጥ ለማከናወን በእቅድ በተያዙ ተግባራት መነሻነት የነበረውን አፈፃፀም ጨምሮ በፕሮጀክቱ የቀጣይ ስድስት ወራት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ከፕሮጀክቱ ኢንዱስትሪ እድቫይዘሪንግ ቦርድ አባላት ጋር ውይይት ማድረግ ተችሏል:: የEASE ፕሮጀክት የ6ወር የስራ አፈፃፅም ሪፖርት በፕሮጀክቱ አስተባባሪ ኢ/ር ፋሲል ማዘንጊያ አማካኝነት ለኮሌጁ አድቫይዘሪንግ ቦርድ አባላቱ የቀረበ ሲሆን በዚህም ባለፉት 6ወራት ከተከናወኑ ተግባራት.. -የተለያዩ የሪኢኖቬሽን ስራዎች፣ -ለ8 የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራንን በቻይና በElectric Vehicle ስልጠና እንዲበቁ ማድረግ)፣ -ለኮሌጁ ሰራተኞች እንዲሁም ለሰልጣኝ ተማሪዎች የኢንተርፕሩነርሺፕ ስልጠናዎች መስጠት፣ -የኢንዱስትሪ አንቀሳቃሾችን የአቅም ግንባታ ስልጠና ስራን ጨምሮ በርካታ ቁልፍ ተግባራት መከናወናቸውን በሪፖርቱ በዝርዝር አመላክተዋል:: የኮሌጁ አመራሮችን ጨምሮ የአድቫይዘሪን ቦርድ አባላቱ በቀረበው የፕሮጀክት አፈፃፀምና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ ለፕሮጀክቱ ውጤታማነት አመላካች የሆኑ ገንቢ እስተያየቶችና ምክረ ሃሳቦችን በስፋት አንስተው ውይይት የተካሄበት የተገኙ የጋራ ውጤቶችን ለማስቀጠል በቀጣይ በተሻለ ትጋትና ቅንጅት ለመስራት ከመግባባት የተደረሰበት መድረክም ነበር:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥር 7/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር ጋር በተያያዘ በአምራች ኢንዱስትሪው ላይ የሚታየውን ክፍተት የመሙላቱ ተግባር በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአስተዳደሩ ለሚገኘው የሹምብሮ ፕላስቲክ ፋብሪካ አመራርና ሰራተኞች የሙያ ደህንነትና ጤንነት ( Occupational Safety & Health) ስልጠና በኮሌጁ መስጠት ጀመረ:: ስልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በመልዕክታቸው ተቋማችን ከዚህ ቀደም በአስተዳደሩ ተያያዥ በሆኑ የኢንጂነሪንግ ዘርፎች ተመርቀው ስራ ያልያዙ ወጣቶችን በማሰልጠን እንዱስትሪዎች ላይ በሙያ ደህንነትና ጤንነት አስተዳደር ላይ ተቀጥረው እንዲሰሩ ማመቻቸቱን አስታውሰው ይህ በዛሬው እለት የተዘጋጀው የሙያ ደህንነት ስልጠናም በዚህ አመት ለኢንዱስትሪ አንቀሳቃሽ ባለሙያዎች በስፋት ለመስጠት በእቅድ የተያዙ ስልጠናዎች አንድ አካል መሆኑንም ገልፀዋል:: የኮሌጁ ዲን አክለው ተቋማችን በሹንብሮ ፕላስቲክ ፋብሪካ በተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችና ቴክኖሎጂዎች ላይ ድጋፍ ለማድረግ አብረን እየሰራን እንገኛለን ያሉ ሲሆን የዛሬውን Occupational Safety & Health (OSH) ስልጠናን ጨምሮ በቀጣይ በተቋማችን የሚሰጡ ስልጠናዎች በድርጅቱ ላይ ከፍተኛ ለውጥ የሚያመጡ በመሆናቸው በትኩረት ስልጠናውን መውሰድ እንደሚያስፈልግም ገልፀዋል:: የEASE ፕሮጀክት በኮሌጁ የትኩረት ማዕከል አድርጎ ከሚሰራባቸው ሶስት የሙያ ዘርፎች አኳያ የOrganization Safety Health (OSH) ስልጠና ቀጥተኛ ተያያዥነት ያለው መሆኑን የገለፁት የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪ ኢ/ር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ አክለውም የOSH ስልጠናው ደረጃውን በጠበቀ መንገድ ለመስጠት የሚያችሉ የተለያዩ የደህንነት ማቴሪያሎችን በፕሮጀክቱ ግዢ በማድረግ ማሟላት መቻሉንም ገልፀዋል:: የሙያ ደህንነትና ጤንነት (Occupational Safety & Health) ስልጠናው ብቁ በሆኑ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን እማካኝነት ለቀጣይ 6 ቀናት የሚሰጥ ሲሆን በዚህም የድርጅቱ ሰራተኞች በስራ ቦታ ላይ የሚደርሱ አደጋዎችን በመለየት እና በመቆጣጠር የሰውን ህይወት እንዲሁም ንብረትን ከአደጋ መጠበቅ የሚያስችሉትን የተግባርና የንድፍ ሃሳብ ስልጠና እንደሚሰጣቸውም ተግልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥር 5/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በየጊዜው የሚዘረጉ ዲጂታል የአሰራር ሲስተሞችን በመጠቀም የአገልግሎት አሰጣጥን ማቀላጠፍ እንደሚገባ ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተቋሙን አጠቃላይ አሰራር በዲጂታል ሲስትም ለመቀየር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል:: ኮሌጁ የአገልግሎት አሰጣጡን ጨምሮ አጠቃላይ የተቋሙን አሰራር በDigital System ለመተካት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ለአመራር አባላትና ለክፍል ተጠሪዎች የግንዛቤ መድረክ አካሂዷል:: አሁን ባለንበት ዘመን ቴክኖሎጂን መጠቀም ምርጫ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ መሆኑን የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ አክለውም እንደ ተቋም ቀጣይነትን ለማረጋገጥ በዲጂታል ሲስተም ጠንካራ ተሳትፎ ማድረግና ምንሰጣቸውን አገልግሎቶች ማዘመን ይጠበቅብናልም ብለዋል:: የግንዛቤ ስልጠናው ከኢትዮ ቴሌኮም በመጡ ባለሙያዎች የተሰጠ ሲሆን በዚህም አሁን ያለው አሰራር በዲጂታል ሲስተም ሲቀየር በምን መልኩ ይሰራል የሚለውና የስራ ክፍሎች ሲስተሙን የሚያንቀሳቅሱበትን ሂደት በዝርዝር ግንዛቤ መስጠት ችለዋል:: በመድረኩ በተሰጠውን ግንዛቤ ላይ ከተሳታፊዎች በሲስተሙ አተገባር ዙሪያ ግልፅ ያልሆኑ ጉዳዮች ተነስተው ሰፊ ማብራሪያም ተሰጥቶባቸዋል:: በእለቱ ግንዛቤውን የሰጡት የኢትዮ ቴሌኮም ባለሙያዎች በቀጣይ ቀናትም ሲስተሙ የሚተገበርባቸው በሁሉም ስራ ክፍሎች ላይ በመገኘት የሲስተሙን አጠቃላይ አተገባበርና አጠቃቀምን በተመለከተ የተግባር ስልጠና እንደሚሰጡም ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥር 3/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

#እንኳን_አደረሳችሁ_አደረሰን ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ 2018 ዓ.ም የእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል(ገና) በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያልኩኝ በዓሉ የሠላም፣ የጤና፣
+1
#እንኳን_አደረሳችሁ_አደረሰን ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ 2018 ዓ.ም የእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል(ገና) በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያልኩኝ በዓሉ የሠላም፣ የጤና፣ የአንድነት፣ የመተሳሰብ እና መደጋገፍ በዓል ይሆንልን ዘንድ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ። #መልካም_የገና_በዓል!! አቶ ታደለ አሰፋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን

በገጠር ክላስተሮች የMobile Trainingን በስፋት በማዳረስ ወጣቶች በአካባቢያቸው ያለውን ሰፊ የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ:: በድሬደዋ አስተዳደር ከሚገኙ የገጠር ክላስተሮች እና የገጠር ስራ እድል ፈጠራ ተወካዮች እንዲሁም ከስልጠና ክፍል ተጠሪዎች ጋር የአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍን በተመለከት የውይይት መድረክ በኮሌጁ ተካሂዷል። በገጠር ክላስተሮች ያለው የተፈጥሮ ፀጋ በመገንዘብ በአካባቢው የሚገኙ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተግባራትን ማከናወን ያስፈልጋል ያሉት የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ል ሀላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ አክለውም የMobile Training ትግበራን በስፋትና በጥራት ተደራሽ ለማድረግ በሚኖረው ሂደት ክላስተሮችና የገጠር ስራ እድል ፈጠራ አስተባባሪዎች የሚያስፈልጉ መሰረተ ልማቶችን በማመቻቸት የስልጠናዎችን ውጤታማነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልፀዋል:: በኮሌጁ የMobile Training ሊሰጥባቸው በሚያስችሉ ዲፓርትመንቶች ላይ የተለዩ የሙያ መስኮች መኖራቸውን የገለፁት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ሂደት ሀላፊ አቶ ኤሊያስ አህመድ ሲሆኑ አክለውም በቀጣይ ከገጠር ክላስተር አስተባባሪዎችና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ነባራዊ ሁኔታ ላይ መነሻ ያደረገ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በማካሄድ በተለያዩ ዘርፎች ስልጠናዎች እንደሚሰጡም አመላክተዋል:: በመድረኩ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ በMobile Training በገጠር ክላስተሮች ላይ ያከናወናቸው ተግባራትና ያለውን መልካም ተሞክሮ በኢ/ር ህይወት እሸቱ አማካኝነት ለተሳታፊዎች ገለፃ የተደረ ሲሆን በስልጠናው የተመዘገቡ ውጤቶችን ጨምሮ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችም ቀርበው በቀጣይ ስልጠናዎች በሚሰጡበት አግባብ ላይም ውይይት ተካሂዷል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

𝗘𝗗𝗜 & 𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼-𝗜𝘁𝗮𝗹𝘆 𝗣𝗼𝗹𝘆𝘁𝗲𝗰𝗵𝗻𝗶𝗰 𝗖𝗼𝗹𝗹𝗲𝗴𝗲 (𝗘𝗜𝗣𝗖) 𝗣𝗮𝗿𝘁𝗻𝗲𝗿 𝗳𝗼𝗿 𝗘𝗻𝘁𝗿𝗲𝗽𝗿𝗲𝗻𝗲𝘂�
+3
𝗘𝗗𝗜 & 𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼-𝗜𝘁𝗮𝗹𝘆 𝗣𝗼𝗹𝘆𝘁𝗲𝗰𝗵𝗻𝗶𝗰 𝗖𝗼𝗹𝗹𝗲𝗴𝗲 (𝗘𝗜𝗣𝗖) 𝗣𝗮𝗿𝘁𝗻𝗲𝗿 𝗳𝗼𝗿 𝗘𝗻𝘁𝗿𝗲𝗽𝗿𝗲𝗻𝗲𝘂𝗿𝗶𝗮𝗹 𝗧𝗩𝗧 𝗘𝘅𝗰𝗲𝗹𝗹𝗲𝗻𝗰𝗲 Today, EDI and Ethio-Italy Polytechnic College (EIPC) signed an MoU to turn technical skills into thriving businesses! This partnership moves beyond "business as usual" by embedding an entrepreneurial ecosystem into the college. What’s coming to EIPC? ✅ New Entrepreneurial Curriculum for all students. ✅ Business Incubation & Advisory to launch real ventures. ✅ Staff Capacity Building to create expert mentors. ✅ Enterprise Support for local technology transfer. ✅ Community Ecosystem Building to drive the local economy. The goal is clear: make entrepreneurial method a core part of the TVT DNA. Together, we are creating a hub where innovation meets industry! #Entrepreneurship #EIPC #EDI #TVET #DireDawa #InnovationHub #JobCreation

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በተለያየ ዘርፍ ስኬታማ መሆን የቻሉ ሴቶችን በመጋበዝ ለኮሌጁ ሴት አሰልጣኝ መምህራንና ሴት ሰልጣኞች ልምድና ተሞክሮ የሚቀስሙበት መድረክ አካሂዷል:
+4
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በተለያየ ዘርፍ ስኬታማ መሆን የቻሉ ሴቶችን በመጋበዝ ለኮሌጁ ሴት አሰልጣኝ መምህራንና ሴት ሰልጣኞች ልምድና ተሞክሮ የሚቀስሙበት መድረክ አካሂዷል:: በመድረኩ ተገኝተው በህይወታቸው ያካበቱትን ከፍተኛ ልምድና ተሞክሮ ለተሳታፊዎች ማካፈል የቻሉት በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ድሬደዋን በመወከል የፓርላማ አባል የሆኑት ክብርት ቢፍቱ መሀመድ(ዶ/ር) እና በሀረማያ ዩኒቨርሲቲ የስነ-አዕምሮ መምህርት የሆኑት ዶ/ር ፈቲያ እንዲሁም በኮሌጁ ለረጅም አመታት በብቃት እያሰለጠኑ የሚገኙት አሰልጣኝ መምህርት ለምለም ግ/ስላሴ ሲሆኑ በዚህም በተለያዩ የስራ ሀላፊነቶች ላይ ተሰማርተው ስኬት እንዲያስመዘግቡ ያስቻላቸው የህይወት ልምዳቸውን ለተሳታፊዎች አካፍለዋል:: ኮሌጁ የተቋቋመበትን ዓላማና ተልዕኮ ለማሳካት በሚያደርገው ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴ የሴት አሰልጣኝ መምህራን እና ሰልጣኝ ተማሪዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የገለፁት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ስራ ሂደት ሀላፊ አቶ ኤሊያስ አህመድ ሲሆኑ አክለውም የዚህ መድረክ ዋና ዓላማም ከፍተኛ ጫናን ተቋቁመው ስኬታማ የሆኑ እንዲሁም በተሰማሩበት ዘርፍ ለሀገር እድገት የድርሻቸውን እያበረከቱ ከሚገኙ ሴት እህቶቻችን ተሞክሮ እንዲወስዱ ለማድረግና ወደራሳቸው ህይወት በመውስድም በተግባር እንዲጠቀሙበትም ለማስቻል መሆኑንም ገልፀዋል:: በእለቱ በተካሄደው መድረክ በተሳታፊዎችና በተጋባዥ እንግዶች መካከል ነፃ ውይይቶች የተካሄዱ ሲሆን በዚህም ሴቶች ሚገጥሟቸውን አስቸጋሪ የህይወት ጎዳናዎች በራስ መተማመን፣ በብልሃትና በጥበብ መሻገር አሸናፊ ሆነው እንዲወጡና የህይወት መንገዳቸውንም በስኬት እንዲመሩ የሚያግዛቸው መሆኑን ምክር ለግሰዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ታህሳስ 23/2018 ዓ.ም