2 485
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-157 روز
-5230 روز
آرشیو پست ها
2 485
Brand bags
Awesome quality
2900 birr
✅Free delivery
☎️ +251910159791
@ethiopiafoodengineering
2 485
Prada
Brand bags
Awesome quality
3800 birr
✅Free delivery
+251910159791
@ethiopiafoodengineering
2 485
Guess
Brand bags
Awesome quality
2800 birr
✅Free delivery
☎️ +251910159791
@ethiopiafoodengineering
2 485
FRANK MARTIN Gift sets
5 in 1 combinations
Women's Watch
Wallet
Belt
Necklace
Bracelet
3800 birr
✅Free delivery
☎️ +251910159791
@ethiopiafoodengineering
2 485
አሲዳማ መሬቶችን ለማከም ከሚፈለገው የኖራ መጠን ውስጥ እስካሁን የቀረበው 10 በመቶ ገደማ ብቻ መሆኑ ተገለጸ
በኢትዮጵያ የተለያዩ ክልሎች በአሲዳማነት የተጠቁ መሬቶችን ለማከም በዚህ ዓመት ከሚያስፈልገው የኖራ መጠን ውስጥ፤ እስካሁን ማቅረብ የተቻለው 10.3 በመቶው ብቻ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። የሲዳማ እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች የሚታረስ መሬታቸው ሙሉ ለሙሉ በአሲዳማነት እንደተጠቃም ተገልጿል።
የግብርና ሚኒስቴር ይህንን ያስታወቀው፤ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ትላንት ረቡዕ ሚያዝያ 25፤ 2015 ለተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ነው። የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የስትራቴጂክ እና እቅድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዜና ሀብተወልድ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ በአሲድ የተጠቃ መሬትን ለማከም የሚውል 1.05 ሚሊዮን ኩንታል ኖራ በተያዘው በጀት ዓመት ለማቅረብ እቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም እስካሁን ማዘጋጀት የተቻለው 110 ሺህ ኩንታል ገደማ ነው።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አሲዳማ መሬትን ለማከም የያዘው እቅድ አፈጻጸም ዝቅተኛ መሆኑ ከፓርላማው ቋሚ ኮሚቴ አባላት ጥያቄ አስነስቷል። ተስፋነሽ ተፈራ የተባሉ የቋሚ ኮሚቴው አባል፤ በሀገር ደረጃ በእርሻ መሬት ላይ እየተስፋፋ ያለውን የአሲዳማነት መጠን ለመቀነስ እና ለማከም በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዲሰራ የታቀደው ስራ አፈጻጸም “ዝቅተኛ የሆነበት ምክንያት” ላይ ማብራሪያ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።
ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10833/
@EthiopiaInsiderNews
2 485
#NationalDialogue
የሀገራዊ ምክክር ሂደት መዘግየት፤ በፓርላማ ቋሚ ኮሚቴ ስብሰባ ጥያቄ አስነሳ
በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አመቻችነት የሚካሄደው የሀገራዊ ምክክር ሂደት መዘግየት፤ በተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስብሰባ ጥያቄ አስነሳ። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕ/ር መስፍን አርዓያ፤ ህዝብ እና መንግስት ከኮሚሽኑ የሚጠብቀው “በጣም ከፍተኛ” መሆን “ትልቅ ተግዳሮት” እንደሆነ ለቋሚ ኮሚቴው ተናግረዋል።
ፕ/ር መስፍን ይህን ምላሽ የሰጡት በዋና ኮሚሽነርነት የሚመሩትን፤ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የ2015 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ሪፖርት ለቋሚ ኮሚቴው አባላት ትላንት ረቡዕ ሚያዝያ 25፤ 2015 ባቀረቡበት ወቅት ነው።
ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ እንደተግዳሮት ከለያቸው ጉዳዮች መካከል፤ ህዝቡ ከኮሚሽኑ የሚጠብቀው (public expectation) “በጣም ከፍተኛ” መሆኑ ጎልቶ የሚጠቀስ እንደሆነ ፕ/ር መስፍን ገልጸዋል። “ከመጀመሪያ ቀን ጀምሮ የት ደረሳችሁ? ምን ላይ ናችሁ? ለምን ዘገያችሁ? ለምን ቶሎ ቶሎ አትሉም? ‘የሰሜን ሁኔታ እንደዚህ ነው፤ ደቡብ እንደዚህ ነው’ የሚል ከፍተኛ የሆነ ጥያቄ አለ” ሲሉ በህዝቡ ዘንድ ያለውን ስሜት አብራርተዋል።
“የመንግስትም ፍላጎት ቶሎ እንድንሰራ ነው” ያሉት ፕ/ር መስፍን፤ “አንዳንድ ጊዜ ስራዎች ወደ እኛ ዝም ብለው በጫና መልክ ይመጣሉ” ሲሉ ተናግረዋል። ዋና ኮሚሽነሩ አለ ያሉትን “ጫና” ሲያብራሩ “ምክክር ኮሚሽኑ ይኼን ይሰራዋል፤ ይኼን ያደርገዋል፤ ይኼን ይፈጽመዋል የሚባሉ ግፊቶችም እኛ ጋር አሉ” ብለዋል።
ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10825/
@EthiopiaInsiderNews
2 485
#Wolaita
በወላይታ ዞን በድጋሚ የሚደረገው ህዝበ ውሳኔ ሰኔ 12 እንደሚካሄድ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ
“ደቡብ ኢትዮጵያ” ክልልን ለመመስረት በወላይታ ዞን በድጋሚ የሚደረገው ህዝበ ውሳኔ፤ በመጪው ሰኔ 12፤ 2015 እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። ለህዝበ ውሳኔው የመራጮች ምዝገባ የሚካሄደው፤ ድምጽ በሚሰጥበት ቀን እንደሆነም ቦርዱ ገልጿል።
ምርጫ ቦርድ ይህንን ያስታወቀው በወላይታ ዞን በድጋሚ የሚካሄደውን ህዝበ ውሳኔ አስመልክቶ፤ ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ 26፤ 2015 በአዲስ አበባ ሳፋየር ሆቴል እያደረገ ባለው የባለድርሻ አካላት ውይይት ላይ ነው። በዚህ ምክክር ላይ የነባሩ ደቡብ ክልል እና የወላይታ ዞን አመራሮች እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ተሳታፊ ሆነዋል።
በዚህ ውይይት ላይ በድጋሚ ለሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ፤ ቦርዱ ያዘጋጀውን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል። በጊዜ ሰሌዳው መሰረት ህዝበ ውሳኔው ከአንድ ወር ከ15 ቀናት በኋላ የሚካሄድ ሲሆን ውጤቱ ደግሞ በሰኔ 19 ይገለጻል። በዚህ ህዝበ ውሳኔ 998,00 መራጮች ይሳተፋሉ የሚል ግምቱን ያስቀመጠው ቦርዱ፤ የመራጮች ምዝገባ የሚከናወነው በድምጽ መስጫው ዕለት ሰኔ 12 መሆኑን አስታውቋል።
ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10819/
@EthiopiaInisderNews
2 485
ኢትዮጵያ በዓለም የፕሬስ ነጻነት ዝርዝር በ16 ደረጃዎች አሽቆለቆለች
ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት (RSF) በዓመቱ በሚያወጣው የዓለም የፕሬስ ነጻነት ዝርዝር፤ ኢትዮጵያ ዘንድሮ 130ኛ ደረጃ አገኘች። የ180 ሀገራት የፕሬስ ነጻነት በሚመዘንበት በዚህ ዝርዝር፤ ኢትዮጵያ አምና ከነበራት በ16 ደረጃዎች አሽቆልቁላለች።
መቀመጫውን በፓሪስ ፈረንሳይ ያደረገው የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅቱ፤ ይህን የሀገራት ደረጃ ላለፉት 20 ዓመታት ሲያወጣ ቆይቷል። በየሀገራቱ ያሉት ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ አውዶች፣ የህግ ማዕቀፍ እና የደህንነት ሁኔታ፤ ድርጅቱ ደረጃዎቹን ለማውጣት በጠቋሚነት የሚገለገልባቸው መመዘኛዎች ናቸው።
ዛሬ ረቡዕ ሚያዝያ 25 ይፋ በተደረገው የዘንድሮው ዝርዝር ከተገመገሙ 180 ሀገራት መካከል፤ በሰላሳ አንዱ ያለው የፕሬስ ነጻነት ሁኔታ “በጣም መጥፎ” መሆኑን ድርጅቱ ይፋ አድርጓል። በዚህ ምድብ ውስጥ ከተካተቱ ሀገራት ውስጥ የኢትዮጵያ ጎረቤት ኤርትራ ትገኝበታለች።
በሀገራቸው ያለው ሁኔታ ለፕሬስ ነጻነት “መጥፎ” የሚባል መሆኑ ከተነገረላቸው 42 ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ ተካትታለች። በኢትዮጵያ ያለው የፕሬስ ነጻነት ሁኔታ፤ በፈረንጆቹ 2022 ዓመት እንደነበረው ሁሉ “አስቸጋሪ” ሆኖ መቀጠሉን የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅቱ ገልጿል።
ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10813/
#WorldPressFreedomDay
@EthiopiaInsiderNews
2 485
የታንዛኒያው የሰላም ውይይት የመጀመሪያ ዙር ያለ ስምምነት መጠናቀቁ ተገለጸ
በኢትዮጵያ መንግስት እና ራሱን “የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት” ብሎ በሚጠራው ታጣቂ ቡድን መካከል በታንዛኒያ ሲካሄድ የነበረው የሰላም ውይይት የመጀመሪያ ዙር ዛሬ መጠናቀቁን የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የብሔራዊ ጸጥታ አማካሪ አስታወቁ። የሰላም ንግግሩ “በአመዛኙ ገንቢ” እንደነበር የገለጹት አቶ ሬድዋን ሁሴን፤ “እንደ አለመታደል ሆኖ በዚህ የውይይት ዙር ወቅት በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ አልተቻለም” ብለዋል።
አቶ ሬድዋን ሁለቱም ወገኖች ግጭቱን በዘላቂነት እና በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ውይይቶቹን መቀጠል እንደሚያስፈልግ ማመናቸውን በትዊተር ባሰራጩት አጭር መልዕክት ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት እና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት በታንዛኒያ የሰላም ውይይት ማድረግ የጀመሩት ባለፈው ሚያዝያ 17፤ 2015 ነበር። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@EthiopiaInsiderNews
2 485
በኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃን ነጻነት “በጉልህ ጥቃት ስር” እንደሚገኝ አንድ ዳሰሳ አመለከተ
ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት ብቻ 29 ጋዜጠኞች በታሰሩባት ኢትዮጵያ፤ የፕሬስ ነጻነት “ጉልህ ጥቃት” እንዳጋጠመው ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና የደቡባዊ አፍሪካ ሚዲያ ኢንስቲትዩት አስታወቁ። ባለስልጣናት የፕሬስ ነጻነትን ማፈን በሚፈልጉባቸው በምስራቅ እና ደቡባዊ አፍሪካ ሀገራት፤ በጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰው ጥቃት እየጨመረ መምጣቱንም ተቋማቱ ገልጸዋል።
ሁለቱ ተቋማት ይህን ያሉት ዛሬ ረቡዕ ሚያዝያ 25፤ 2015 ታስቦ የሚውለውን የዓለም የፕሬስ ነጻነትን በማስመልከት በጋራ ባወጡት ዳሰሳ ነው። ዳሰሳው ኢትዮጵያን ጨምሮ በ10 የአፍሪካ ሀገራት ያለውን የመገናኛ ብዙሃን ነጻነትን እና በጋዜጠኞች ላይ እየደረሱ ያሉ ጥቃቶችን በማሳያነት በማንሳት ዳሰሳ አድርጓል።
በዚሁ ዳሰሳ፤ ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት በርካታ ጋዜጠኞችን በማሰር ከኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በመለጠቅ ስሟ የተጠቀሰው ኢትዮጵያ ነች። እንደ ሁለቱ ተቋማት ዳሰሳ ከሆነ በ2022 ብቻ በኢትዮጵያ 29 ጋዜጠኞች እና የመገናኛ ብዙሃን ሰራተኞች ታስረዋል። ከእነዚህ ጋዜጠኞች አምስቱ “ከጠላት ጋር ተባብራችኋል” በሚል በትግራይ ባለስልጣናት የታሰሩ እንደነበሩ ዳሰሳው አመልክቷል።
#WorldPressFreedomDay
* ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10800/
@EthiopiaInsiderNews
2 485
ምስላዊ መረጃ፦ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ላለፉት አራት ወራት በስራ ላይ የነበረውን የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ የመሸጫ ዋጋ ከልሷል። አዲሱ ተመን ከትላንት ማክሰኞ ሚያዝያ 24፤ 2015 እኩለ ለሊት ጀምሮ እስከ ግንቦት 30፤ 2015 የሚቆይ ነው።
በአዲሱ የዋጋ ክለሳ ከፍተኛ ጭማሪ የታየው በቀላል ጥቁር ናፍጣ ላይ ነው። በዚህ የነዳጅ ምርት ላይ 8 ብር ከ17 ሳንቲም ጭማሪ ተደርጓል። የቀላል ጥቁር ናፍጣ የመሸጫ ዋጋ ላለፉት አራት ወራት ከነበረው የግብይት ተመን አኳያ ወደ 12 በመቶ ገደማ ከፍ ያለ ነው።
ከቀላል ጥቁር ናፍጣ ቀጥሎ ከፍ ያለ የዋጋ ጭማሪ የታየው በቤንዚን ላይ ነው። የአንድ ሊትር ቤንዚን የመሸጫ ዋጋ 8 ብር ከ14 ሳንቲም ጭማሪ አሳይቶ ወደ 69 ብር ከ43 ሳንቲም ከፍ ብሏል። የነጭ ናፍጣ እና ኬሮሲን የመሸጫ ዋጋ ላይም በተመሳሳይ የ3 ብር ከ78 ሳንቲም ጭማሪ ተደርጓል።
ዛሬ ይፋ በሆነው አዲሱ ተመን የአውሮፕላን ነዳጅ የመሸጫ ዋጋ ቅናሽ አሳይቷል። ባለፈው መጋቢት ወር ወደ 70.60 ብር ከፍ ብሎ የነበረው የአውሮፕላን ነዳጅ ዋጋ፤ በሊትር በአራት ብር ቀንሷል። ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ይህ የነዳጅ አይነት 78 ብር ከ87 ሳንቲም ይሸጥ ነበር።
ባለፈው ዓመት በተመሳሳይ ጊዜ የነበረውን የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ የመሸጫ ዋጋን፤ ዛሬ ከተደረገው ጭማሪ ጋር ለማነጻጸር ከታች የተያያዘውን ምስላዊ መረጃ ይመልከቱ። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@EthiopiaInsiderNews
2 485
የኢትዮጵያ መንግስት እና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት “ በቅን ልቦና እንዲደራደሩ” አሜሪካ ጥሪ አቀረበች
የኢትዮጵያ መንግስት እና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት አባላት ለሁለቱም ወገን ተቀባይነት ያለው መፍትሔ ለማምጣት በቅን ልቦና እንዲደራደሩ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ጥሪ አቀረቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከአንድ ሳምንት ገደማ በፊት ይፋ ያደረጉትን እና በታንዛኒያ የሚደረገውን ድርድር፤ አሜሪካ በበጎ እንደምትቀበለው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።
አንቶኒ ብሊንከን ራሱን “የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት” ብሎ ከሚጠራው ታጣቂ ቡድን ጋር ለተጀመረው ድርድር ድጋፋቸውን የገለጹት፤ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ግጭት የማቆም ስምምነት የተፈረመበትን ስድስተኛ ወር በማስመልከት ትላንት ማክሰኞ ሚያዝያ 24 ምሽት ባወጡት መግለጫ ነው። ብሊንከን የሰሜን ኢትዮጵያን ጦርነት ያስቆመው ስምምነት “ስኬት”፤ በኦሮሚያ ክልል “ሰላም ለማምጣት ያለውን ዕድል ይጠቁማል” የሚል እምነት አላቸው።
ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በትላንቱ መግለጫቸው፤ የፕሪቶሪያውን ስምምነት “ለሁለት ዓመታት የዘለቀውን የሰሜን ኢትዮጵያን ግጭት አቁሞ ዛሬ የቀጠለውን የሰላም እና የማገገም ሂደት ያስጀመረ” ሲሉ ገልጸውታል። በስምምነቱ ተገኝተዋል ያሏቸውን ትሩፋቶችንም ዘረዝረዋል።
ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10792/
@EthiopiaInsiderNews
2 485
ምስላዊ መረጃ፦ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ላለፉት አራት ወራት በስራ ላይ የነበረውን የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ የመሸጫ ዋጋ ከልሷል። አዲሱ ተመን ከዛሬ ማክሰኞ ሚያዝያ 24፤ 2015 እኩለ ለሊት ጀምሮ እስከ ግንቦት 30፤ 2015 የሚቆይ ነው።
በአዲሱ የዋጋ ክለሳ ከፍተኛ ጭማሪ የታየው በቀላል ጥቁር ናፍጣ ላይ ነው። በዚህ የነዳጅ ምርት ላይ 8 ብር ከ17 ሳንቲም ጭማሪ ተደርጓል። የቀላል ጥቁር ናፍጣ የመሸጫ ዋጋ ላለፉት አራት ወራት ከነበረው የግብይት ተመን አኳያ ወደ 12 በመቶ ገደማ ከፍ ያለ ነው።
ከቀላል ጥቁር ናፍጣ ቀጥሎ ከፍ ያለ የዋጋ ጭማሪ የታየው በቤንዚን ላይ ነው። የአንድ ሊትር ቤንዚን የመሸጫ ዋጋ 8 ብር ከ14 ሳንቲም ጭማሪ አሳይቶ ወደ 69 ብር ከ43 ሳንቲም ከፍ ብሏል። የነጭ ናፍጣ እና ኬሮሲን የመሸጫ ዋጋ ላይም በተመሳሳይ የ3 ብር ከ78 ሳንቲም ጭማሪ ተደርጓል።
ዛሬ ይፋ በሆነው አዲሱ ተመን የአውሮፕላን ነዳጅ የመሸጫ ዋጋ ቅናሽ አሳይቷል። ባለፈው መጋቢት ወር ወደ 70.60 ብር ከፍ ብሎ የነበረው የአውሮፕላን ነዳጅ ዋጋ፤ በሊትር በአራት ብር ቀንሷል። ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ይህ የነዳጅ አይነት 78 ብር ከ87 ሳንቲም ይሸጥ ነበር።
ባለፈው ዓመት በተመሳሳይ ጊዜ የነበረውን የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ የመሸጫ ዋጋን፤ ዛሬ ከተደረገው ጭማሪ ጋር ለማነጻጸር ከታች የተያያዘውን ምስላዊ መረጃ ይመልከቱ። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@EthiopiaInsiderNews
2 485
የነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ።
በአዲስ አበባ ከተማ በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ መደረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የዋጋ ማስተካከያው ከሚያዝያ 24 ቀን 2015 ሌሊት 6 ሰዓት ጀምሮ እስከ ግንቦት 30 ቀን 2015 ዓ.ም የሚቆይ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።
በዚሁ መሠረት፡ -
- ቤንዚን 👉 69 ነጥብ 43 ብር በሊትር
- ነጭ ናፍጣ 👉 71 ነጥብ 08 ብር በሊትር
- ኬሮሲን 👉 71 ነጥብ 08 ብር በሊትር
- የአውሮፕላን ነዳጅ 👉 66 ነጥብ 60 ብር በሊትር
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ 👉 57 ነጥብ 84 ብር በሊትር
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ 👉 56 ነጥብ 50 ብር በሊትር
መረጃው የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር / ኤፍቢሲ ነው።
@ethiopianinsider1
2 485
❤️🔥❤️🔥ልዩ ስጦታ ስጦታ ለ ሚወዱት ያበርክቱ❤️🔥❤️🔥
🎄Wooden Engraving
👉Price 1100birr
🛵Free Delivery in Addis Abeba
📞☎️0910159791
@Ethiopiafoodengineering
2 485
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ “በኢትዮጵያ ውስጣዊ ጉዳይ መግባት የሚፈልጉ” ያሏቸውን ኃይሎች፤ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳሰቡ
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ “በኢትዮጵያ ውስጣዊ ጉዳይ እየገቡ መፈትፈት የሚፈልጉ” ያሏቸውን “ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ኃይሎች” ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳሰቡ። “በመገዳደል፣ በመሰዳደብ እና በመናናቅ” ለማሳካት የሚፈለግ “የፖለቲካ ዓላማ” ውስጥ ይሳተፋሉ ያሏቸውን ባለሀብቶች፣ በውጭ ሀገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና በሀገር ውስጥ ያሉ ወጣቶችንም “ደጋግማው እንዲያስቡ” ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ይህንን ማሳሰቢያ ያስተላለፉት፤ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን የተገነባው “የሃላላ ኬላ ሪዞርት” ዛሬ ሰኞ ሚያዝያ 23፣ 2015 በተመረቀበት ወቅት ባደረጉት ንግግር ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ንግግራቸው፤ ባለፈው ሳምንት ሐሙስ የተገደሉትን የአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ የአቶ ግርማ የሺጥላን ጉዳይ አንስተዋል።
አብይ በዛሬው ንግግራቸው፤ የብልጽግና ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑትን የአቶ ግርማን ግድያ “አላግባብ መሰዋት” ሲሉ ጠርተውታል። አቶ ግርማን “ገና ሮጦ ያልጠገበ ወጣት፣ ለህዝቡ ለሀገሩ ብዙ ሊያገለግል የሚችል፣ ልጆች ቤተሰቦች ያሉት” ሲሉ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “በሰላም ቤተሰቡን ሊጠይቅ እየነዳ የሄደ፤ ጀግና መሳይ ፈሪዎች ተደብቀው በጥይት ገደሉት” ብለዋል። ይህንን ድርጊት የፈጸሙት ሰዎች፤ የሚፈልጉትን ነገር “በሀሳብ ብልጫ” “ብዙሃንን አሳምነው መከወን እንደማይሳካላቸው ያሰቡ” መሆናቸውን ተናግረዋል።
ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10784/
@EthiopiaInsiderNews
2 485
❤️🎁 በቆዳ ላይ የወዳጅ ዘመድ ፤ ፍቅረኛ ፤ ጓደኛ ፎቶ እንዲህ በሚያስደንቅ መልኩ ያሰሩ፡፡❤️🎁
👉Size 40*50=1,200 ብር
50*60=1,700 ብር
60*75=2,400 ብር
75*90=3200 ብር
🛵Free Delivery Everywhere in Addis Ababa
🦋❤️Leather Engravings🦋❤️
👉ለ ምርቃት 🎓🧑🎓
👉ለ ሰርግ 💍💐
👉 ለ ልደት 🎂
👉ለ ወዳጅዎ እና ለ ፍቅረኛዎ🎁💝
📞 +251910159791
@EthiopiaFoodengineering
🎁❤️ ልብ የሚገዙ ስጦታዎችን ለሚወዱት ያበርክቱ..
2 485
❤️🎁 በቆዳ ላይ የወዳጅ ዘመድ ፤ ፍቅረኛ ፤ ጓደኛ ፎቶ እንዲህ በሚያስደንቅ መልኩ ያሰሩ፡፡❤️🎁
👉Size 40*50=1,200 ብር
50*60=1,700 ብር
60*75=2,400 ብር
75*90=3200 ብር
🛵Free Delivery Everywhere in Addis Ababa
🦋❤️Leather Engravings🦋❤️
👉ለ ምርቃት 🎓🧑🎓
👉ለ ሰርግ 💍💐
👉 ለ ልደት 🎂
👉ለ ወዳጅዎ እና ለ ፍቅረኛዎ🎁💝
📞 +251910159791
🎁❤️ ልብ የሚገዙ ስጦታዎችን ለሚወዱት ያበርክቱ..
2 485
የዩኒቨርሲቲ ምሩቃንን አሰልጥኖ ወደ ውጭ ሀገር ለስራ ለማሰማራት እንቅስቃሴ መጀመሩን የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ገለጸ
የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲ ምሩቃንን አሰልጥኖ ወደ ውጭ ሀገር ለስራ ለማሰማራት እንቅስቃሴ መጀመሩን አስታወቀ። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 85 ሺህ ዜጎችን ወደ ውጭ ሀገር ለስራ ለማሰማራት አቅዶ ማከናወን የቻለው 66 በመቶ ብቻ ነው ብሏል። በዚህ ጊዜ ውስጥ ስድስት ሚሊዮን ዜጎች በስራ ፈላጊነት መመዘገባቸውንም ሚኒስቴሩ ገልጿል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ይህን የገለጸው ትላንት ሐሙስ ሚያዝያ 19፤ 2015 የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸሙን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበበት ወቅት ነው። የስራ እና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪያት ካሚል፤ በስራ እድል ፈጠራ፣ በቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና እንዲሁም በውጭ ሀገር ስራ ስምሪት ላይ መስሪያ ቤታቸው ያከናወናቸውን ስራዎች ለፓርላማው አብራርተዋል።
የሚኒስትሯን ሪፖርት ተከትሎ ጥያቄዎችን ከሰነዘሩ የፓርላማ አባላት አንዱ የሆኑት አቶ ዮሃንስ መስፍን፤ “የውጭ ሀገር የስራ አማራጮችን ተጠቅሞ ለዜጎች ብቁ ስራ ዕድል ለመፍጠር ምን ታስቧል?” የሚል ጥያቄ አቅርበዋል። በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የአሰሪ እና ሰራተኛ ጉዳይ ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታው አቶ አሰግድ ጌታቸው ለዚህ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፤ ከውጭ ሀገር ስራ ስምሪት ጋር በተያያዘ የመዳረሻ ሀገራትን ለማበራከት ጥናት መጀመሩን ተናግረዋል።
ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10778/
@EthiopiaInsiderNews
2 485
የፌደራል ፖሊስ “የፍርድ ቤቶችን ውሳኔዎች እና ትዕዛዞችን አይፈጽምም” የሚሉ ቅሬታዎች በፓርላማ ስብሰባ ላይ ቀረቡ
የፌደራል ፖሊስ፤ በፍርድ ቤቶች የተላለፉ ውሳኔዎች እና ትዕዛዞችን “ያለመፈጸም እና የመንጓተት አካሄድን ይከተላል” የሚሉ ቅሬታዎች በተወካዮች ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ ቀረቡ። የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ለቅሬታዎቹ በሰጡት ምላሽ፤ የፍርድ ቤት ትዕዛዝን አለማክበር በተቋማቸው የማይታለፍ “ቀይ መስመር ነው” ብለዋል።
ቅሬታዎቹ እና ምላሾቹ የተደመጡት፤ የፌደራል ፖሊስ የ2015 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ትላንት ሐሙስ ሚያዚያ 19፤ 2015 በተገመገመበት ወቅት ነው። በዚሁ ስብሰባ ጥያቄያቸውን ያቀረቡት አቶ አዳነ ማንዴ የተባሉ የምክር ቤት አባል፤ በፍርድ ቤት ውሳኔ ያገኙ ጉዳዮች “አልፎ አልፎ ሳይፈጸሙ የሚንከባለሉ እና የሚቀሩ” መኖራቸውን ከቀረቡ ቅሬታዎች መረዳታቸውን ገልጸዋል።
የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ አዳነ፤ በፍርድ ቤቶች የስራ ግምገማ ወቅት “ካጋጠሙ ዋነኛ ችግሮች” በሚል ከተነሱ ጉዳዮች ውስጥ የውሳኔዎች ተፈጻሚ አለመሆን አንዱ እንደነበር አስታውሰዋል። ሌላኛዋ የቋሚ ኮሚቴው አባል ፋናዬ መለሰ በበኩላቸው “ፍርድ ቤት ቀርበው፤ ፍርድ ቤቱ ጥፋት አላገኘሁባቸውም ብሎ በነጻ ያሰናበታቸውን ግለሰቦች ፖሊስ ‘አልፈታም’ ሲል እና መልሶ ሲያስር ይስተዋላል” ብለዋል። “ጉዳዩን ዜጎች ከሚያቀርቡት ቅሬታ በተጨማሪ በፍርድ ቤቶች ላይ ባደረግነው የመስክ ምልከታ ማረጋገጥ ችለናል” ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል።
ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10773/
@EthiopiaInsiderNews
