fa
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

رفتن به کانال در Telegram
2 485
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-157 روز
-5230 روز
آرشیو پست ها
አቶ ግርማ የሺጥላ በየትኞቹ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ሰርተዋል? በሰሜን ሸዋ ዞን ከመሃል ሜዳ ወደ ደብረ ብርሃን እየተጓዙ ባለበት ወቅት መንዝ ጓሳ አካባቢ በ“ኢ-መደበኛ ኃይሎች” በደረሰባቸው ጥቃት
አቶ ግርማ የሺጥላ በየትኞቹ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ሰርተዋል? በሰሜን ሸዋ ዞን ከመሃል ሜዳ ወደ ደብረ ብርሃን እየተጓዙ ባለበት ወቅት መንዝ ጓሳ አካባቢ በ“ኢ-መደበኛ ኃይሎች” በደረሰባቸው ጥቃት በዛሬው ዕለት የተገደሉት የአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሺጥላ፤ በክልሉ መንግስት እና ገዢ ፓርቲ በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች ለ27 ዓመታት አገልግለዋል። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በአንፆኪያ ገምዛ ወረዳ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ዘርፍ ኃላፊ በመሆን በታህሳስ 1988 ዓ.ም የአመራርነት ስራን የጀመሩት አቶ ግርማ፤ በዚያው ዓመት ሐምሌ ወር ላይ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ሆነው ተሹመዋል። በዚህ የኃላፊነት ቦታ ላይም ለሰባት ዓመት ገደማ ቆይተዋል። በጥር 1995 ዓ.ም. ከወረዳ ወደ ዞን በመሸጋገርም፤ የቀድሞው ብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) የሰሜን ሸዋ ዞን ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ መሆን ችለዋል። ለአንድ ዓመት ገደማ በዚህ ኃላፊነት ቦታ የቆዩት አቶ ግርማ፤ በጥር 1996 ዓ.ም የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሹመት አግኝተዋል። ዝርዝሩን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10750/ @EthiopiaInsiderNews

የአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሺጥላን ጨምሮ አምስት ሰዎች በ“ኢ-መደበኛ ኃይሎች” በደረሰባቸው ጥቃት መገደላቸውን የአማራ ክልል መንግስት አስታወቀ፡፡ እነዚ
የአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሺጥላን ጨምሮ አምስት ሰዎች በ“ኢ-መደበኛ ኃይሎች” በደረሰባቸው ጥቃት መገደላቸውን የአማራ ክልል መንግስት አስታወቀ፡፡ እነዚህ ኃይሎች ጥቃቱን የፈጸሙት በአቶ ግርማ ቤተሰቦች እና የግል ጥበቃዎቻቸው ላይ በሰሜን ሸዋ ዞን መንዝ ጓሳ አካባቢ መሆኑንም የክልሉ መንግስት ገልጿል፡፡ የአማራ ክልል መንግስት ይህንን ያስታወቀው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የአቶ ግርማን ሞት ይፋ ካደረጉ ከአንድ ሰዓት በኋላ ባወጣው መግለጫ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለአቶ ግርማ ሞት ተጠያቂ ያደረጉት፤ “ሐሳብን በሐሳብ ማሸነፍ ያቃታቸው” እንዲሁም “ነውጠኛ ጽንፈኞች” ሲሉ የገለጿቸውን አካላት ነው። የአማራ ክልል መንግስት በበኩሉ ጥቃቱን የፈጸሙት “ኢ-መደበኛ” እና “የሽብር ስራ እየሰሩ ያሉ ኃይሎች” ናቸው ብሏል። የክልሉ መንግስት በዚሁ መግለጫው፤ አቶ ግርማ ጥቃት የደረሰባቸው ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ 19፤ 2015 ከሰዓት በኋላ “የመንግስት እና የድርጅት ስራዎችን ሰርተው” ከመሃል ሜዳ ወደ ደብረ ብርሃን እየተጓዙ በነበረበት ወቅት መሆኑን አስታውቋል። አቶ ግርማ የተወለዱት በሰሜን ሸዋ ዞን በሚገኘው መሃል ሜዳ አካባቢ መሆኑን የግል ህይወት ታሪካቸው ያመለክታል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ዛሬ አመሻሽ ላይ ባወጡት መግለጫም፤ በአቶ ግርማ ላይ የተደረገው “አስነዋሪ እና አሰቃቂ ተግባር” የተፈጸመው፤ ተወልደው ባደጉበት አካባቢ እንደነበር ጠቅሰዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10750/ [በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ ታክሎበታል] @EthiopiaInsiderNews

የኢትዮጵያ ሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም፤ በድርቅ ምክንያት “አንድም ሰው አለመሞቱን” ማረጋገጡን አስታወቀ በኦሮሚያ፣ ሶማሌ እና ደቡብ ክልሎች የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ፤ በክልሎቹ በሚገኙ ሶስት ዞኖች
የኢትዮጵያ ሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም፤ በድርቅ ምክንያት “አንድም ሰው አለመሞቱን” ማረጋገጡን አስታወቀ በኦሮሚያ፣ ሶማሌ እና ደቡብ ክልሎች የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ፤ በክልሎቹ በሚገኙ ሶስት ዞኖች ባደረገው “የቁጥጥር ስራ” “አንድም ሰው አለመሞቱን” ማረጋገጡን የኢትዮጵያ ሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ። በድርቅ ሳቢያ ከእነዚህ ሶስት ዞኖች የተፈናቀሉ 243 ሺህ ነዋሪዎች በአሁኑ ወቅት በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ እንደሚገኙም ተቋሙ ገልጿል። የእንባ ጠባቂ ተቋም ይህንን ያስታወቀው፤ በድርቅ እና በጎርፍ ምክንያት ከሶስቱ ክልሎች ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚደረገውን ድጋፍ አስመልክቶ ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ 19፤ 2015 በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው። ተቋሙ በቦረና፣ ዳዋ እና ደቡብ ኦሞ ዞኖች “የቁጥጥር ስራ” ያከናወነው፤ ባለፈው መጋቢት ወር ወደ ስፍራዎቹ በላካቸው ሶስት ቡድኖችን አማካኝነት እንደነበር ጠቅሷል። ከመጋቢት 11 እስከ መጋቢት 25 በዞኖቹ ተሰማርተው የነበሩት ቡድኖች ትኩረት ያደረጉት፤ በድርቅ እና በጎርፍ ለተፈናቀሉ ዜጎች በሚደረገው የሰብአዊ ድጋፍ እና እርዳታ፣ መሰረታዊ የመንግስት አገልግሎቶች አሰጣጥ እንዲሁም የመልሶ የማቋቋም ስራዎች ላይ እንደነበር በዛሬው መግለጫው ላይ ተመልክቷል። በክትትሉ ውጤት መሰረት ከሶስቱ ዞኖች ውስጥ ከፍተኛው ጉዳት የደረሰው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን መሆኑን የእንባ ጠባቂ ተቋም ዋና መስሪያ ቤት የአስተዳደር በደል መከላከል ዳይሬክተር አቶ አዳነ በላይ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10744/ [ፎቶ ፋይል፦ ዩኒሴፍ ኢትዮጵያ] @EthiopiaInsiderNews

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት፤ በመስከረም አበራ ላይ 10 ተጨማሪ የምርመራ ቀናትን ፈቀደ “ሁከት እና ብጥብጥ በማነሳሳት ወንጀል” ተጠርጥራ ከሁለት ሳምንት በፊት በፖሊስ ቁጥጥር ስር በዋለች
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት፤ በመስከረም አበራ ላይ 10 ተጨማሪ የምርመራ ቀናትን ፈቀደ “ሁከት እና ብጥብጥ በማነሳሳት ወንጀል” ተጠርጥራ ከሁለት ሳምንት በፊት በፖሊስ ቁጥጥር ስር በዋለችው መስከረም አበራ ላይ አስር የምርመራ ቀናት በፍርድ ቤት ተፈቀደ። “ኢትዮ ንቃት” የተሰኘው የዩ-ቲዩብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና ባለቤት የሆነችው መስከረም፤ “ረዣዥም የጊዜ ቀጠሮ የሚጠየቅብኝ ወጥቼ የጋዜጠኝነት ስራዬን እንዳልሰራ ነው” ስትል ለፍርድ ቤት ተናግራለች። የመስከረምን ጉዳይ እየተመለከተ የሚገኘው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ለዛሬ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው፤ ፖሊስ ባለፈው የችሎት ውሎ በተፈቀዱለት የምርመራ ቀናት ያከናወናቸውን ተግባራት ለማድመጥ ነበር። በዚህም መሰረት፤ የፌደራል ፖሊስ በተሰጡት 13 የምርመራ ቀናት ያከናወናቸውን ተግባራት ለፍርድ ቤቱ በጽሁፍ አቅርቧል። መርማሪ ፖሊስ በችሎት ፊት በንባብ ባስደመጠው በዚሁ የተግባራት ዝርዝር ላይ በቀዳሚነት የተጠቀሰው፤ “ከተጠርጣሪዋ እጅ ተያዙ” በተባሉ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ላይ ተደርጓል የተባለው ምርመራ ነው። የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎቹ እንዲመረመሩ “ለሚመለከተው መስሪያ ቤት” ጥያቄ ካቀረበ በኋላ ውጤቱን መቀበሉን እና “ቀሪ የምርመራ ስራዎች እየሰራ እንደሚገኝ” ፖሊስ በዛሬው ችሎት ገልጿል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10742/ @EthiopiaInsiderNews

የኢትዮጵያ መንግስት፤ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ብሎ ከሚጠራው “ኦነግ ሸኔ” ጋር የሚያደርገውን ድርድር፤ ከነገ በስቲያ ማክሰኞ ሚያዝያ 17፤ 2015 በታንዛንያ እንደሚጀምር ጠቅላይ ሚኒስትር አብ
የኢትዮጵያ መንግስት፤ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ብሎ ከሚጠራው “ኦነግ ሸኔ” ጋር የሚያደርገውን ድርድር፤ ከነገ በስቲያ ማክሰኞ ሚያዝያ 17፤ 2015 በታንዛንያ እንደሚጀምር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አስታወቁ። የሁሉም ክልሎች ርዕሰ መስተዳድሮች፤ በትግራይ ክልል የሰፈነውን “የሰላም ጅማሮ በተግባር ለማስቀጠል” በቀጣዮቹ ቀናት ወደ መቐለ እንደሚጓዙም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያስታወቁት፤ የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት እንዲያበቃ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በተዘጋጀ የሽልማት እና የእውቅና መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር ነው። በአዲስ አበባው የወዳጅነት አደባባይ፤ ዛሬ እሁድ ሚያዝያ 15፤ 2015 በተከናወነው በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓትን ወክለው በደቡብ አፍሪካ እና ኬንያ የሰላም ንግግር ሲያደርጉ የነበሩ ልዑካን አባላት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) [በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ መረጃ ታክሎበታል]

የተመድ ዋና ጸሀፊ ወደ ትግራይ ለመጓዝ ይዘውት የነበረው እቅድ፤ በኢትዮጵያ መንግስት “ውድቅ መደረጉን” አንድ ምስጢራዊ ሰነድ አጋለጠ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ፤ ወደ
የተመድ ዋና ጸሀፊ ወደ ትግራይ ለመጓዝ ይዘውት የነበረው እቅድ፤ በኢትዮጵያ መንግስት “ውድቅ መደረጉን” አንድ ምስጢራዊ ሰነድ አጋለጠ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ፤ ወደ ትግራይ ለመጓዝ የያዙት እቅድ በኢትዮጵያ መንግስት ውድቅ በመደረጉ “ክፉኛ ተበሳጭተው” እንደነበር “ዋሽንግተን ፖስት” ጋዜጣ የተመለከተው አንድ ምስጢራዊ ሰነድ አጋለጠ። የዋና ጸሀፊው ጥያቄ በኢትዮጵያ መንግስት ተቀባይነት አለማግኘቱን በመግለጽ ለጉተሬዝ ደብዳቤ የጻፉላቸው፤ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን መሆናቸው በዚሁ ምስጢራዊ ሰነድ ይፋ ተደርጓል። ጉተሬዝ የትግራይ ጉብኝታቸው መሰረዙን ጨምሮ በሌሎች ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ የነበሯቸውን መስተጋብሮች የያዙት ምስጢራዊ ሰነዶች አፈትልከው የወጡት ከአሜሪካ መንግስት እጅ ነው። “ዲስኮርድ” በተሰኘው የመልዕክት መለዋወጫ “ሰርቨር” የተለቀቁትን እነዚህን ሰነዶች ያወጣው፤ የማሳቹሴትስ የአየር ኃይል ብሔራዊ ዘብ ባልደረባ የነበረ የ21 ዓመት ወጣት ነው። አሜሪካ “በወዳጆቿ እና አጋሮቿ ላይ ስታካሄድ የቆየችውን ስለላ ያጋለጡ ናቸው” ከተባለላቸው ሰነዶች መካከል አራቱ፤ ከጉተሬዝ ጋር የተያያዙ መሆናቸውን “ዋሽንግተን ፖስት” ትላንት ሰኞ ባወጣው ዘገባ አስታውቋል። የካቲት 10፤ 2015 የተጠናቀረ አንድ ሪፖርትን በማሳያነት የጠቀሰው ዘገባው፤ ጉተሬዝ ወደ ትግራይ ሊያደርጉት ያቀዱት ጉዞ መሰረዙን በተመለከተ፤ በወቅቱ በተመድ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩትን ታዬ ታዬ አጽቀስላሴን ለመጋፈጥ ፈልገው እንደነበር አትቷል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10705/ @EthiopiaInsiderNews

በትግራይ ክልል ያሉ የመንግስት ሰራተኞች፤ በአስር ቀናት ውስጥ ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲመለሱ ጥሪ ተላለፈ በትግራይ ክልል መንግስት ስር ባሉ መዋቅሮች ይሰሩ የነበሩ ሰራተኞች፤ በአስር ቀናት ውስጥ
በትግራይ ክልል ያሉ የመንግስት ሰራተኞች፤ በአስር ቀናት ውስጥ ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲመለሱ ጥሪ ተላለፈ በትግራይ ክልል መንግስት ስር ባሉ መዋቅሮች ይሰሩ የነበሩ ሰራተኞች፤ በአስር ቀናት ውስጥ በየመስሪያ ቤቶቻቸው ተገኝተው ሪፖርት እንዲያደርጉ ጥሪ ተላለፈ። በክልሉ ለሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች፤ ውዝፍ የሶስት ወር ደመወዝ ክፍያ መሰጠት መጀመሩም ተገልጿል። በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከተቀሰቀሰ በኋላ የትግራይን ክልልን ተቆጣጥሮ የቆየው የመከላከያ ሰራዊት፤ የመቐለ ከተማን ለቅቆ ከወጣበት ከሰኔ 2013 ዓ.ም. ጀምሮ የክልሉ መንግስት መስሪያ ቤቶች መደበኛ ስራ አቁመው ቆይተዋል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ወ/ሮ ሰብለ ካህሳይ፤ መደበኛ ስራ ተቋርጦ በቆየበት ጊዜ የክልሉ መንግስት ሰራተኞች በመስሪያ ቤቶቻቸው ይገኙ የነበረው ወጥ ባልሆነ ሁኔታ እንደነበር ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። “ፕሮግራም ወጥቶ ነበር ሰራተኛ ወደ ቢሮ ይገባ የነበረው። በሳምንት አንድ ቀንም [የሚገባ ነበር]። አንዳንድ ስራ የበዛበትም፤ ግማሽ ግማሽ ቀን ነው ስራ ይገባ የነበረው” ሲሉ ላለፉት አንድ ዓመት ከስምንት ወር ገደማ የነበረውን የስራ ሁኔታ አስረድተዋል። የፌደራል መንግስት እና ህወሓት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ከተማ በተፈራረሙት የሰላም ስምምነት መሰረት ባለፈው መጋቢት ወር አጋማሽ ላይ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር መቋቋሙን ተከትሎ፤ ሰራተኞችን በመደበኛ ሁኔታ ወደ ስራ የማስገባት እንቅስቃሴ መጀመሩን ኮሚሽነሯ አስታውቀዋል። * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10699/ @EthiopiaInsiderNews

ጋዜጠኞች ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቅዶባቸው እንዲታሰሩ መደረጉ፤ “በምንም መለኪያ ተቀባይነት የሌለው ነው” ሲል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ተቸ ከስራቸው ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር በዋሉ
ጋዜጠኞች ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቅዶባቸው እንዲታሰሩ መደረጉ፤ “በምንም መለኪያ ተቀባይነት የሌለው ነው” ሲል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ተቸ ከስራቸው ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር በዋሉ ጋዜጠኞች ላይ የቀረቡ ክሶችን፤ የፍትህ ስርዓቱ “በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ብቻ” በመመራት እንዲመለከታቸው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ጠየቀ። በቁጥጥር ስር የዋሉ ጋዜጠኞች “እንደማንኛውም ተከሳሽ” ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቅዶባቸው እንዲታሰሩ መደረጉንም፤ ምክር ቤቱ “በምንም መለኪያ ተቀባይነት የሌለው” ሲል ተችቷል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ይህን ያለው፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጋዜጠኞች ላይ የተፈጸሙ እስሮችን እና የፍርድ ቤት ሂደቶቻቸውን አስመልክቶ ዛሬ ሰኞ ሚያዝያ 9፤ 2015 ባወጣው መግለጫ ነው። ምክር ቤቱ በዚሁ መግለጫው፤ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ውስጥ የሚሰሩ ጋዜጠኞች በተደጋጋሚ “ከሕግ አግባብ ውጪ መያዝ እና መታፈናቸውን” እንዲሁም በሚሰሩባቸው ተቋማት ላይ “ያለፍርድ ቤት ማዘዣ ወረቀት ብርበራ” መፈጸሙን እንደተገነዘበ አስታውቋል። በሚዲያ አማካኝነት ተፈጽሟል በተባለ ወንጀል የተጠረጠሩት እነዚህ ጋዜጠኞች፤ በፖሊስ በቁጥጥር ስር እየዋሉ እና ወደ ፍርድ ቤት እየቀረቡ ያሉት በመገናኛ ብዙኃን አዋጁ መሰረት አለመሆኑንም ምክር ቤቱ ገልጿል። ይህ ድርጊትም “ባለሙያዎች ስራቸውን በነጻነት እንዳይሰሩ፤ እንዲሸማቀቁ እና የፕሬስ ምህዳሩ የበለጠ እንዲጠብ” እያደረገ መሆኑን በዛሬው መግለጫው ጠቅሷል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10694/ @EthiopiaInsiderNews

ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ቴዎድሮስ አስፋው፤ “ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ” በመንቀሳቀስ መጠርጠራቸውን ፖሊስ ለፍርድ ቤት ገለጸ የ“አራት ኪሎ ሚዲያ” የዩ ቲዩብ መገናኛ ብዙሃን መስራች
ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ቴዎድሮስ አስፋው፤ “ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ” በመንቀሳቀስ መጠርጠራቸውን ፖሊስ ለፍርድ ቤት ገለጸ የ“አራት ኪሎ ሚዲያ” የዩ ቲዩብ መገናኛ ብዙሃን መስራች ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና “ኢትዮ ሰላም” የተሰኘው የዩ ቲዩብ መገናኛ ብዙሃን መስራች ቴዎድሮስ አስፋው፤ “በህዝብ የተመረጠን መንግስት እና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ” በመንቀሳቀስ መጠርጠራቸውን ፖሊስ ለፍርድ ቤት አስታወቀ። ባለፈው ረቡዕ እና ሐሙስ በቁጥጥር ስር የዋሉት ቴዎድሮስ እና ዳዊት፤ ለመጀመሪያ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረቡት ዛሬ ቅዳሜ ሚያዚያ 7፤ 2015 ነው። የፌደራል ፖሊስ ሁለቱን የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ባቀረበበት ወቅት፤ የተጠረጠሩበትን የወንጀል ዝርዝር በንባብ አሰምቷል። ሁለቱ ተጠርጣሪዎች በከፈቷቸው የዩ ቲዩብ መገናኛ ብዙሃኖች፤ “ምንም አይነት የህዝብ ውክልና ሳይኖራቸው፤ የአማራ ህዝብ ግፍ ደርሶበታል በማለት ያልተገባ ወሬ አሰራጭተዋል” ሲል ወንጅሏቸዋል። በመገናኛ ብዙሃኖቻቸው “ግላዊ ፍላጎታቸውን” ሲያንጸባርቁ ነበር የተባሉት ዳዊት እና ቴዎድሮስ፤ “ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ” እንዲሁም “የአማራን ህዝብ ለአመጽ እና ለትግል ለማነሳሳት” በሚዲያ ሲቀስቅሱ ነበር ሲል ፖሊስ ለችሎት ባቀረበው እና ለተጠርጣሪዎቹም በሰጠው መማልከቻ ላይ አስፍሯል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10684/ @EthiopiaInsiderNews

በትግራይ ክልል “የቡድን ትጥቆችን የማስረከብ ሂደት” ከመጪው ሰኞ ጀምሮ እንደሚከናወን የተሃድሶ ኮሚሽን አስታወቀ በትግራይ ክልል የሚገኙ የቡድን ትጥቆችን ሰብስቦ ለመከላከያ ሰራዊት የማስረከብ ሂደት
በትግራይ ክልል “የቡድን ትጥቆችን የማስረከብ ሂደት” ከመጪው ሰኞ ጀምሮ እንደሚከናወን የተሃድሶ ኮሚሽን አስታወቀ በትግራይ ክልል የሚገኙ የቡድን ትጥቆችን ሰብስቦ ለመከላከያ ሰራዊት የማስረከብ ሂደት በመጪው ሰኞ ሚያዝያ 9፤ 2015 እንደሚጀመር ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን አስታወቀ። የኢትዮጵያ ጎረቤት በሆነችው ሱዳን ሀገር የሚገኙ ኃይሎችን ጨምሮ በተለያዩ ቦታዎች ያሉ የትግራይ ታጣቂዎችን የማሰባሰብ ስራም በአጭር ጊዜ እንደሚጀምር ኮሚሽኑ ገልጿል። የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽኑ ይህን የገለጸው፤ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ጋር ከተወያየ በኋላ ትላንት አርብ በሰጠው መግለጫ ነው። የተሃድሶ ኮሚሽኑን በኮሚሽነርነት የሚመሩት ተሾመ ቶጋ እና ሁለት ምክትሎቻቸው የተገኙበት ይህ ውይይት፤ በውጊያ ላይ የቆዩ ኃይሎችን “ትጥቅ የማስፈታት፣ እንዲበተኑ የማድረግ እና እንደገና ወደ ህብረተሰቡ የመዋሃድ” ሂደትን በተመለከተ “ቀሪ ስራዎችን በፍጥነት ማጠናቀቅ” ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር ተብሏል። የቀድሞ ታጣቂዎችን እንዲበተኑ ከማድረግ በፊት መጠናቀቅ ያለበት አንዱ ስራ “ትጥቅ ማስፈታት” መሆኑን በመግለጫው የጠቀሱት ኮሚሽነር ተሾመ ቶጋ፤ እስካሁን የተከናወነው እንደተጠበቀ ሆኖ “የቡድን መሳሪያዎችን የማስረከብ ስራ ቶሎ መጠናቀቅ እንዳለበት” ከስምምነት ላይ መደረሱን አስታውቀዋል። የቡድን መሳሪያዎችን የማስረከብ ሂደቱ፤ “ከሰኞ ጀምሮ በጣም ባጠረ ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅም” ገልጸዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10677/ @EthiopiaInsiderNews

በሚዲያ ጥፋት የተጠረጠሩ ታሳሪዎች በሙሉ፤ “ያለምንም ቅድመ ሁኔታ” ከእስር እንዲለቀቁ ኢሰመኮ አሳሰበ በመገናኛ ብዙሃን አማካኝነት ተፈጽሟል በተባለ ወንጀል የተጠረጠሩ ታሳሪዎች “በሙሉ ያለምንም ቅድ
በሚዲያ ጥፋት የተጠረጠሩ ታሳሪዎች በሙሉ፤ “ያለምንም ቅድመ ሁኔታ” ከእስር እንዲለቀቁ ኢሰመኮ አሳሰበ በመገናኛ ብዙሃን አማካኝነት ተፈጽሟል በተባለ ወንጀል የተጠረጠሩ ታሳሪዎች “በሙሉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ” ከእስር እንዲለቀቁ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አሳሰበ። የመንግስት የጸጥታ አካላት በፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎችና አባላት፣ በሚዲያ አባላት እንዲሁም በማህበረሰብ አንቂዎች ላይ ካተኮረ “እስር እና ማዋከብ” እንዲቆጠቡም ኮሚሽኑ ጠይቋል። ኢሰመኮ ይህንን ማሳሰቢያ የሰጠው፤ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች፣ የማህበረሰብ አንቂዎች እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎችን እና አባላትን “ዒላማ በማድረግ” እየተፈጸመ ያለን “እስር እና ወከባ” አስመልክቶ ዛሬ ቅዳሜ ሚያዝያ 7፤ 2015 ባወጣው መግለጫ ነው። በእነዚህ አካላት ላይ እየተፈጸመ ያለው “እስር እና ወከባ በእጅጉ አሳሳቢ” መሆኑን የገለጸው ኮሚሽኑ፤ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ብቻ ስምንት ጋዜጠኞች እና አንድ የማህበረሰብ አንቂ ለእስር መዳረጋቸውን በመግለጫው አስታውቋል። ባለፈው ረቡዕ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ የተያዘው፤ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር መስራችና የስራ አስፈጻሚ አባል የሆነው ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው በኢሰመኮ መግለጫ ላይ ከተጠቀሱ ጋዜጠኞች አንዱ ነው። የ“አራት ኪሎ ሚዲያ” መስራች እና አዘጋጅ ከሆነው ዳዊት በተጨማሪ ገነት አስማማው፣ አራጋው ሲሳይ፣ ቴዎድሮስ አስፋው፣ ጌትነት አሻግሬ፣ በየነ ወልዴ፣ ሰናይት አያሌው እና ሳሙኤል አሰፋ የተባሉ ጋዜጠኞች ባለፈው አንድ ወር ለእስር መዳረጋቸውን ኮሚሽኑ ዘርዝሯል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10661/ [በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ መረጃ ታክሎበታል] @EthiopiaInsiderNews

የኢትዮጵያን የዕዳ አከፋፈል ሽግሽግ ለማጠናቀቅ፤ አበዳሪዎቿ በአፋጣኝ ከስምምነት ላይ እንዲደርሱ የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ጥሪ አቀረቡ ኢትዮጵያ የዕዳ አከፋፈል ሽግሽግ እንዲደረግላት ባቀረበችው ጥያቄ
የኢትዮጵያን የዕዳ አከፋፈል ሽግሽግ ለማጠናቀቅ፤ አበዳሪዎቿ በአፋጣኝ ከስምምነት ላይ እንዲደርሱ የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ጥሪ አቀረቡ ኢትዮጵያ የዕዳ አከፋፈል ሽግሽግ እንዲደረግላት ባቀረበችው ጥያቄ ላይ፤ የመንግስት እና የግል አበዳሪዎች በአፋጣኝ ስምምነት ላይ እንዲደርሱ የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዴቪድ ማልፓስ ጥሪ አቀረቡ። ማልፓስ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ጋር ትላንት አርብ ሚያዝያ 6፤ 2015 በዋሽንግተን ዲሲ ከተገናኙ በኋላ ባወጡት መግለጫ፤ የኢትዮጵያ መንግስት “ኢኮኖሚያዊ መዛባቶችን እንዲያስወግድ” ማሳሰባቸውን አስታውቀዋል። አቶ አህመድ ሽዴ እና ዴቪድ ማልፓስ የተገናኙት በዋሽንግተን ዲሲ ሲካሄድ ከቆየው የዓለም ባንክ እና የአይ ኤም ኤፍ “የጸደይ ጉባኤ” ጎን ለጎን ነው። የብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የማክሮ ኢኮኖሚ አማካሪ አቶ ተክለወልድ አጥናፉን የመሳሰሉ ቁልፍ ባለስልጣናት የተሳተፉበት ስብሰባ ከዓለም አቀፍ ተቋማት እገዛ በምትሻው ኢትዮጵያ ከፍተኛ ግምት የተሰጠው ነው። ማልፓስ ከአቶ አህመድ ጋር በትላንትናው ዕለት በነበራቸው ውይይት፤ ለደሃ አገሮች ፈታኝ የሆነው ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ መነሳቱን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ “ማክሮ ኢኮኖሚያዊ መረጋጋትን ለመመለስ ያላት አንገብጋቢ ፍላጎት” “በሰፊው” ውይይት የተደረገበት ጉዳይ እንደሆነም ገልጸዋል። በዚሁ ውይይት “ድርቅ፣ የውስጥ ግጭት፣ የዕዳ ጫና እና ውስብስብ መዋቅራዊ ተግዳሮቶች“ ባሉበት አውድ ውስጥ፤ “ፈጣን እና ወሳኝ የፖሊሲ ማሻሻያዎች የሚኖራቸውን ጥቅሞች” በተመለከተ ማልፓስ አጽንኦት ሰጥተው ማንሳታቸውን በመግለጫው ተጠቅሷል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10654/ @EthiopiaInsiderNews

መንግስት “ያለምንም የህግ አግባብ” ያሰራቸውን ጋዜጠኞች “በአስቸኳይ እንዲፈታ” የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ጠየቀ መንግስት “ያለምንም የህግ አግባብ” ያሰራቸውን የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች
መንግስት “ያለምንም የህግ አግባብ” ያሰራቸውን ጋዜጠኞች “በአስቸኳይ እንዲፈታ” የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ጠየቀ መንግስት “ያለምንም የህግ አግባብ” ያሰራቸውን የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችን “በአስቸኳይ እንዲፈታ” የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ዛሬ አርብ ሚያዝያ 6፤ 2015 ባወጣው መግለጫ ጠየቀ። መንግስት በመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ላይ የሚያደርሰውን ማሸማቀቅ እንዲያቆምም ማህበሩ ተመሳሳይ ጥያቄ አቅርቧል። ማህበሩ በዛሬው መግለጫው፤ በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች የሚሰሩበት “አውድ እየጠበበ” መምጣቱን ገልጿል። ጋዜጠኞች ስራቸውን በነጻነት እንዳይሰሩ፤ “በመንግስት የጸጥታ አካላት እየተሸማቀቁ እንግልት እየደረሰባቸው” መሆኑን መታዘቡንም አመልክቷል። ለዚህም በማሳያነት የማህበሩ መስራችና የስራ አስፈጻሚ አባል የሆነውን ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻውን ጨምሮ ስድስት ጋዜጠኞች በአሁኑ ወቅት በመንግስት ኃይሎች ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ጠቅሷል። የማህበሩ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ እና የ“አራት ኪሎ ሚዲያ” መስራች ከሆነው ዳዊት በተጨማሪ መግለጫው በስም የዘረዘራቸው ጋዜጠኞች፤ አራጋው ሲሳይ፣ ገነት አስማማው፣ ጌትነት አሻግሬ፣ በየነ ወልዴ እና ቴዎድሮስ አስፋውን ነው። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10649/ @EthiopiaInsiderNews

የአማራ ክልል ወደ መደበኛ ፖሊስ የሚገቡ የክልሉ ልዩ ኃይል አባላትን በተለያዩ “ዞኖች መድቦ እያንቀሳቀሰ” መሆኑን አስታወቀ አማራ ክልል “ወደ መደበኛ የክልል ፖሊስ ስራ እንገባለን” ያሉ የአማራ ል
የአማራ ክልል ወደ መደበኛ ፖሊስ የሚገቡ የክልሉ ልዩ ኃይል አባላትን በተለያዩ “ዞኖች መድቦ እያንቀሳቀሰ” መሆኑን አስታወቀ አማራ ክልል “ወደ መደበኛ የክልል ፖሊስ ስራ እንገባለን” ያሉ የአማራ ልዩ ኃይል አባላትን፤ በክልሉ ወደሚገኙ ዞኖች መድቦ እያንቀሳቀሰ መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የአስተዳደር ጉዳዮች ክላስተር አስተባባሪ የሆኑት ዶ/ር ሰማ ጥሩነህ ተናገሩ። “በመደናገር” ወደ ተለያዩ አካባቢዎች “የተበተኑ” የልዩ ኃይል አባላትን የሚያሰባስቡ ግብረ ኃይሎች በዞን እና ወረዳ ደረጃ መቋቋማቸውን አስተባባሪው ገልጸዋል። ዶ/ር ሰማ ይህን የገለጹት፤ በአማራ ክልል ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ለክልሉ ቴሌቪዥን ጣቢያ ትላንት ረቡዕ ሚያዚያ 4፤ 2015 በሰጡት መግለጫ ነው። ዶ/ር ሰማ በአራት ቀናት ውስጥ በአማራ ክልል ወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ የሰጡ፤ ሶስተኛው የክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣን ናቸው። ሌሎቹ ባለስልጣናት እንደሰጧቸው መግለጫዎች ሁሉ የትላንቱ የዶ/ር ሰማ ማብራሪያም፤ የክልል ልዩ ኃይሎችን እንደገና ለማደራጀት በፌደራል መንግስቱ የተወሰነው ውሳኔ እና የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አባላት የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ ዋና ትኩረቱን ያደረገ ነበር። የክልል ልዩ ኃይሎችን በተመለከተ በተመለከተ የተላለፈው ውሳኔ “በሁሉም ክልሎች እየተፈጸመ ነው” ያሉት ዶ/ር ሰማ፤ “ይሄ ባለበት ሁኔታ የአማራ ክልልን ልዩ ኃይል ብቻ ባለበት እንዲቆይ ማድረግ፣ ወደ ፌደራል ጸጥታ ተቋማት እንዳይገባ መከልከል የሚቻል አይደለም” ሲሉ ተደምጠዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10639/ @EthiopiaInsiderNews

በአማራ ክልል በተካሄዱ ተቃውሞዎች ላይ በተወሰዱ “እርምጃዎች እና ጥቃቶች”፤ ሰዎች መሞታቸውን እና መጎዳታቸውን ኢሰመኮ ገለጸ የክልል ልዩ ኃይሎችን “መልሶ ለማደራጀት” በመንግስት የተላለፈውን ውሳኔ
በአማራ ክልል በተካሄዱ ተቃውሞዎች ላይ በተወሰዱ “እርምጃዎች እና ጥቃቶች”፤ ሰዎች መሞታቸውን እና መጎዳታቸውን ኢሰመኮ ገለጸ የክልል ልዩ ኃይሎችን “መልሶ ለማደራጀት” በመንግስት የተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ በአማራ ክልል በተካሄዱ ተቃውሞዎች ላይ በተወሰዱ “እርምጃዎች እና ጥቃቶች”፤ የሰዎች ሞት እና የአካል ጉዳት መከሰቱን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ። እርምጃዎቹ የተወሰዱት “በጸጥታ ኃይሎች” መሆኑን የጠቀሰው ኮሚሽኑ፤ “ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎችም” ጥቃቶች አድርሰዋል ብሏል። ኢሰመኮ ይህንን ያስታወቀው፤ የክልል ልዩ ኃይሎችን “መልሶ የማደራጀት” ውሳኔ እና ትግበራ “የሰዎችን ሰብአዊ መብቶች አደጋ ላይ በማይጥል ሁኔታ ሊከናወን እንደሚገባ” ባስታወቀበት መግለጫው ነው። ዛሬ ረቡዕ ሚያዝያ 4፤ 2015 ምሽት ላይ የወጣው የኮሚሽኑ መግለጫ፤ ልዩ ኃይሎችን በተመለከተ መንግስት ያሳለፈውን ውሳኔ ለማስፈጸም ወደ ተግባር መግባቱን ተከትሎ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የተነሱ ተቃውሞዎችን በተመለከተ ክትትል እያደረገ እንደሚገኝ ገልጿል። የኮሚሽኑ ክትትል፤ በክልሉ የተከሰተውን የጸጥታ መደፍረስ እንዲሁም በአንዳንድ አካባቢዎች የደረሱ ግጭቶች እና ጉዳቶችን ጭምር እንደሚሸፍን መግለጫው ጠቁሟል። ኢሰመኮ በዚሁ መግለጫው፤ በአማራ ክልል በሚገኙት ቆቦ፣ ባህር ዳር፣ ወረታ፣ ኮምቦልቻ፣ ደብረ ብርሃን እና መራዊ ከተሞች የተቃውሞ ሰልፎች፣ የመንገድ መዘጋት፣ የአገልግሎት መቋረጥ እንዲሁም በጸጥታ ኃይሎች መካከል ፍጥጫዎች መከሰታቸውን አመልክቷል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) * ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10634/ [በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ መረጃ ታክሎበታል] @EthiopiaInsiderNews

የቀድሞው የ“አል አይን ኒውስ” ጋዜጠኛ፤ በባህር ዳር ከተማ በመከላከያ ሰራዊት አባላት ተይዞ መወሰዱን የዓይን እማኞች ገለጹ “አራት ኪሎ ሚዲያ” የተሰኘው የዩቲዩብ መገናኛ ብዙሃን አዘጋጅ የሆነው ጋ
የቀድሞው የ“አል አይን ኒውስ” ጋዜጠኛ፤ በባህር ዳር ከተማ በመከላከያ ሰራዊት አባላት ተይዞ መወሰዱን የዓይን እማኞች ገለጹ “አራት ኪሎ ሚዲያ” የተሰኘው የዩቲዩብ መገናኛ ብዙሃን አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው፤ ዛሬ አመሻሽ ላይ በአማራ ክልል በባህር ዳር ከተማ በመከላከያ ሰራዊት አባላት ተይዞ መወሰዱን የዓይን እማኞች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። የመከላከያ ሰራዊት የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮሎኔል ጌትነት አዳነ ስለ ጋዜጠኛው መያዝ መረጃ እንደሌላቸው ገልጸዋል። ጋዜጠኛው የስራ አመራር ቦርድ አባል የሆነበት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ማህበርም በተመሳሳይ ስለ ዳዊት መያዝ እስካሁን መረጃ እንደሌለው አስታውቋል። ጋዜጠኛ ዳዊት ዛሬ ረቡዕ ሚያዝያ 4፤ 2015 አመሻሽ ላይ በመከላከያ ሰራዊት አባላት የተያዘው፤ በባህር ዳር ከተማ በሚገኘው ሆምላንድ ሆቴል ከጓደኞቹ ጋር “ሻይ እየጠጣ” ባለበት መሆኑን የዓይን እማኞቹ ገልጸዋል። ጋዜጠኛውን ወዳልታወቀ ቦታ የወሰዱት የመከላከያ ሰራዊት የኮማንዶ አባላት በሁለት “ፓትሮል” ተጭነው የመጡ መሆናቸውን የጠቆሙት የዓይን እማኞቹ፤ ከእነርሱ ውስጥ አንዱ “አንተን እንፈልግሃለን” ብሎ ዳዊትን ይዞት ወደ ተሽከርካሪዎቹ እንደወሰደው አብራርተዋል። የመከላከያ ሰራዊት አባሉ ዳዊትን ከጓደኞቹ “ነጥሎ” ከወሰደው በኋላ፤ ከሆቴሉ ቅጥር ግቢ ውጭ ከቆሙት ተሽከርካሪዎች ወደ አንደኛው ውስጥ ሲገባ መመልከታቸውንም እማኞቹ አስረድተዋል። ሆኖም በሰዓቱ “ተደናግጠው ስለነበር” በተሽከርካሪዎቹ ውስጥ ያሉት የመከላከያ ሰራዊት አባላት አጠቃላይ ቁጥር ማወቅ አለመቻላቸውንም አክለዋል። ለዝርዝሩ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10629/ @EthiopiaInsiderNews

ከአዲስ አበባ ኮንዶሚኒዬም ዕጣ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ በ“ከባድ የሙስና ወንጀል” ከተከሰሱ ግለሰቦች ውስጥ አምስቱ በፍርድ ቤት ነጻ ተባሉ የቀድሞው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክ ሙያና
ከአዲስ አበባ ኮንዶሚኒዬም ዕጣ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ በ“ከባድ የሙስና ወንጀል” ከተከሰሱ ግለሰቦች ውስጥ አምስቱ በፍርድ ቤት ነጻ ተባሉ የቀድሞው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክ ሙያና ስልጠና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱን ጨምሮ፤ ከኮንዶሚኒዬም ዕጣ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ “ከባድ የሙስና ወንጀል” ክስ የተመሰረተባቸው አምስት ግለሰቦች በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነጻ ተባሉ። በዚሁ መዝገብ ክስ ከቀረበባቸው ግለሰቦች መካከል አንድ ተከሳሽ በሌሉበት ጥፋተኛ ሲባሉ፤ ቀሪ አምስት ተከሳሾች ደግሞ የተከሰሱበት ድንጋጌ ተቀይሮ እንዲከላከሉ በፍርድ ቤቱ በይኗል። ይህን ብይን የሰጠው ዛሬ ረቡዕ ሚያዚያ 4፤ 2015 የዋለው፤ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ችሎት ነው። ችሎቱ አምስት ተከሳሾችን በነጻ ያሰናበተው፤ “ዐቃቤ ህግ ባቀረበው የሰው እና የሰነድ ማስረጃ፤ ወንጀሉን በበቂ ሁኔታ ባለማስረዳቱ” መሆኑን ገልጿል። በነጻ ከተሰናበቱት ውስጥ የአዲስ አበባ ከተማ የቴክኒክ ሙያና ስልጠና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ የነበሩት አቶ አብርሃም ሰርሞሎ እና የከተማይቱ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ቢሮ የአይሲቲ ዳይሬክቶሬይትን ሲመሩ የነበሩት አቶ ኩምሳ ቶላ ይገኙበታል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) [በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ መረጃ ይታከልበታል] @EthiopiaInsiderNews

ምስላዊ መረጃ፦ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በተያዘው ዓመት በ6.1 በመቶ ያድጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ አይ ኤም ኤፍ ተነበየ። መቀመጫውን በዋሽንግተን ዲሲ ያደረገው ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት፤ ዛሬ ማክሰኞ
ምስላዊ መረጃ፦ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በተያዘው ዓመት በ6.1 በመቶ ያድጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ አይ ኤም ኤፍ ተነበየ። መቀመጫውን በዋሽንግተን ዲሲ ያደረገው ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት፤ ዛሬ ማክሰኞ ሚያዝያ 3፤ 2015 ይፋ ባደረገው ትንበያ መሰረት በ2024 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ6.4 በመቶ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል። የድርጅቱ ትንበያ ይፋ የሆነው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት በሚሳተፉበት የዓለም ባንክ እና የአይ ኤም ኤፍ የጸደይ ስብሰባ በሚካሄድበት ወቅት ነው። ከኢትዮጵያ ጎረቤቶች መካከል መካከለኛ ገቢ ካላቸው ጎራ የምትመደበው የኬንያ ኢኮኖሚ፤ በተያዘው ዓመት 5.3 በመቶ ሊያድግ እንደሚችል የአይ ኤም ኤፍ ትንበያ ያሳያል። በሚቀጥለው ዓመት በአንጻሩ የኬንያ ኢኮኖሚ 5.4 በመቶ ዕድገት እንደሚኖረው በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ተተንብይዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @EthiopiaInsiderNews

መስከረም አበራ “ለኢ-መደበኛ አደረጃጀቶች ወታደራዊ ስልጠና እና የተኩስ ልምምድ ስትሰጥ ነበር” ሲል ፖሊስ ወነጀለ ከትላንት በስቲያ እሁድ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለችው የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዋ መ
መስከረም አበራ “ለኢ-መደበኛ አደረጃጀቶች ወታደራዊ ስልጠና እና የተኩስ ልምምድ ስትሰጥ ነበር” ሲል ፖሊስ ወነጀለ ከትላንት በስቲያ እሁድ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለችው የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዋ መስከረም አበራ፤ “ሁከት እና ብጥብጥ በማነሳሳት ወንጀል” ተጠርጥራ በፍርድ ቤት 13 የምርመራ ቀናት ተፈቀደባት። መስከረምን  ፍርድ ቤት ያቀረባት የፌደራል ፖሊስ፤ “ተጠርጣሪዋ ለኢ-መደበኛ አደረጃጀቶች ወታደራዊ ስልጠና እና የተኩስ ልምምድ ስትሰጥ ነበር” ሲል ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል። ፖሊስ ዛሬ ማክሰኞ ሚያዚያ 3፤ 2015፤ በመስከረም ላይ ውንጀላውን ያቀረበው፤ ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ነው። በችሎቱ መስከረምን ወክለው የቀረቡት ጠበቃዋ አቶ ሄኖክ አክሊሉ በበኩላቸው ፍርድ ቤቱ የደንበኛቸውን የዋስትና መብት እንዲጠብቅ ጠይቀዋል። የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዋ “የፖለቲካ ዓላማዋን ለማሳካት ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም፤ ህገ ወጥ ቡድን በማደራጀት፤ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል መረጋጋት እንዳይኖር እና ግጭት እንዲቀሰቀስ ስትሰራ ነበር” ሲል የፌደራል ፖሊስ ውንጀላውን ለፍርድ ቤቱ አሰምቷል። መስከረም “ወጣቶችን ስታደራጅ ነበር” ያለው የፌደራል ፖሊስ፤ “በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ግጭት እና ሁከት ለመቀስቀስ ስትንቀሳቀስ ነበር” ሲል የተጠረጠረችበትን ወንጀል ዝርዝር አብራርቷል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) * * ተጨማሪ መረጃ የታከለበትን ዝርዝር ዘገባ ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10599/ @EthiopiaInsiderNews

መስከረም አበራ ለሶስተኛ ጊዜ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለች “ኢትዮ ንቃት” የተሰኘው የዩ-ቲዩብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና ባለቤት የሆነችው መስከረም አበራ፤ ዛሬ እሁድ ሚያዝያ 1 አመሻሽ ላይ በፌደራ
መስከረም አበራ ለሶስተኛ ጊዜ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለች “ኢትዮ ንቃት” የተሰኘው የዩ-ቲዩብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና ባለቤት የሆነችው መስከረም አበራ፤ ዛሬ እሁድ ሚያዝያ 1 አመሻሽ ላይ በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ስር መዋሏን ባለቤቷ አቶ ፍጹም ገብረ ሚካኤል ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። መስከረም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ለእስር ስትዳረግ የዛሬው ለሶስተኛ ጊዜ ነው። በራሷም ሆነ በሌሎች መገናኛ ብዙኃን በምታቀርባቸው የፖለቲካ ትንታኔዎች ይበልጥ የምትታወቀው መስከረም፤ በአዲስ አበባ ጎሮ አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤቷ በቁጥጥር ስር የዋለችው 10 ገደማ በሚሆኑ የፌደራል ፖሊስ አባላት መሆኑን አቶ ፍጹም ገልጸዋል። መስከረም በቁጥጥር ስር ከመዋሏ በፊት፤ በመኖሪያ ቤታቸው 50 ደቂቃዎች ገደማ የወሰደ “ብርበራ” መደረጉን ባለቤቷ ተናግረዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @EthiopiaInsiderNews