cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

መሳጭ ትረካዎች እና ሌሎችም🎧

መሳጭ ትረካዎች በአዩ

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
241
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ስንብት በዘናጭ ፊደላት በደማቅ ቀለማት ፍቅርሽን ለማድመቅ የተንተባተብኩት ፊትትሽ ተሰይሜ የተንቀጠቀጥኩት ፍቅር እኮ ነዉ ያልኩት የቃል ሽንገላ እንጂ አልነበረም እዉነት ....
نمایش همه...
ከመሰናክል ባሻገር! “በአንድ እንቅፋት ምክንያት ተስፋ በመቁረጥ የሕይወታችሁን ከመከተል ማቆም ማለት የመኪናችሁ አንዱ ጎማ ስለተነፈሰ ብቻ ሌሎቹን ሶስት ጎማዎች በስለት በመቅደድ ማስተንፈስ እንደማለት ነው” - ካልታወቀ ምንጭ ሰሞኑን ካልተሳካው ሙከራ፣ ከተዘጋው የእድል በር፣ ከተቋረጠው የሰው ተስፋ፣ ከባከነው ንብረት . . . ባሻገር የሚሄድ ማንነት እንዲኖራችሁ ጸሎቴ ነው፡፡ Dr.eyob መልካም ቀን!
نمایش همه...
የምንኖረው ባለማወቅ ጥልቅ ውስጥ ነው
نمایش همه...
#ካነበብኩት የሳይኮሎጂ ፕሮፌሰሩ ወደ ክፍል ገብቶ የእለቱን ወሳኝ ትምርት ለመጀመር ወደ ቦርድ እንደዞረ ፉጨት ሰማ። ወደ ተማሪዎቹ ዞሮ ማን እንዳፏጨ ጠየቀቃቸው። ሁሉም ዝም አሉ። ፕሮፊሰሩ ተረጋግቶ ፣ እስክሪቢቶውን ወደ ኪሱ እየከተተ "የዛሬው ሌክቸር እዚ ላይ ያበቃል" አለና ፈገግ ብሎ "ነገር ግን መጀመሪያ አንድ ታሪክ እነግራችኋለው" አላቸው። ሁሉም በጉጉት መጠበቅ ጀመሩ። □ □ □ "ትላንት ቤቴ እንቅልፍ ስላስቸገረኝ ዝም ብዬ ተነስቼ ነዳጅ ሞልቼ በዛውም ልናፈስ ብዬ ከመሽ ወጣሁ። ነዳጅ ከሞላሁ በኋላ ከትራፌክ ነጻ የሆነው መንገድ ላይ እየተንሸራሸርኩ እያለ ከሆነ ድግስ ቦታ የወጣች የምትመስል ቆንጂዬ ወጣት አየሁ። መኪናዬን አዙሬ እርዳታ እንደምትፈልግ ጠየኳት" ታክሲ እንዳጣች እና ቤቷ እንዳደርሳት ጠየቀችኝ። ጋቢና ገባች ... ማውራት ጀመርን ... ውበት ብቻ ሳይሆን ባወራነው ርእስ ሁሉ በጣም ስማርት የሆነ ጭንቅላት እንዳላት ከምታወራው ነገር መገመት ቻልኩ። ቤቷ እንደደረስን በጣም ጥሩ ሰው እንደሆንኩ ነገረችኝ። እኔም ጥሩ አስተሳሰብ እንዳላት ነግሬያት በሌላ ጊዜ ተገናኝተን ሻይ ቡና እንድንል ጠየኳት። በሀሳቤም ተስማማች። ዩኒቨርስቲ ፕሮፌሰር እንደሆንኩ አውርተን። ስልክ ተለዋወጥን። ◎ ◎ ◎ እና..ልንለያይ ስንል አንድ ነገር ላስቸግርህ ስትለኝ ምንም ችግር የለውም አልኳት። "ወንድሜ አንተ የምታስተምርበት ዩኒቨርስቲ ውስጥ ተማሪ ነው። በኛ ግንኙነት እንዳይጎዳ ቃል ግባልኝ !" አለችኝ። ...ችግር የለም ብዬ ስሙን ጠየኳት ስሙንም ነገረችኝ።ምናልባት ብዙ ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው ውስጥ ስለሚማሩና ተመሳሳይ ስም ሊኖራቸው ስለሚችል ወንድምሽን እንዴት ልለየው እችላለሁ ? ስል ጠየኳት። እሷም:- ወንድሜ አንድ መለያ ባህሪ አለው። በሱ ታውቀዋለህ። ፉጨት ማፏጨት ያዘወትራል" አለችኝ። ... ከዛ ሁሉም ተማሪ ወደ አፏጨው ልጅ ዞሮ ማየት ጀመረ። ◊ ◊ ◊ ፕሮፌሰሩም :- "የሳይኮሎጂ PHDዬን ተምሬ እንጂ ገዝቼ አይደለም ያገኘውት። ና ውጣ" ብሎ ጆሮውን ይዞ ከክፍል አስወጣው 😀
نمایش همه...
ገጣሚ:-ገ/ክርስቶስ ደስታ "ዞሮ ዞሮ ከቤት" @ethiopiagetem
نمایش همه...
የወንድ ልጅ ኋላው! (አሌክስ አብርሃም) ትዝ ይለኛል የስምንተኛ ክፍል ተማሪ ሁኘ ለመጀመሪያ ጊዜ ከኋላየ ከምትቀመጥ ልጅ ክፉ ፍቅር ያዘኝ ! በእርግጥ እኔ ማለት (ጉራ ቢመስላችሁም ይምሰላችሁ እንጅ) የዛሬን አያርገውና ብእርን እንደምንሽር ተጠቅሜ ከሰማይ ወፍ የማወርድ ልጅ ነበርኩ ! አለ አይደል ዝም ብየ የፍቅር ደብዳቤ ፅፌ ባዶ ሜዳ ላይ ቁሜ ባነብ ከሰማይ ላይ ሁለት ንስር ፣አራት እርግብና ዘጠኝ ቁራ ... እንዲሁም አንድ የኢትዮጵያን ሰማይ አቋርጦ በሚያልፍ አውሮፕላን ተሳፍራ የምትጓዝ ፈረንሳዊት ልጃገረድ ዱብ ዱብ ይሉ ነበር ! (ያኔ ቴክኖሎጅው አልነበረም እንጅ ይሄን ሳደርግ ላይቭ ገብቸ አሳያችሁ ነበር ) ግን ለዛች ልጅ እንኳን ቃል አውጣቶ ሃሳብን በደብዳቤ ማስፈር ይቅርና እስክርቢቶ ለመጨበጥ እንኳን እጀ እየተንቀጠቀጠ እንቢ አለኝ !ሁኖ የማያውቀውን እጀን ያልበኝ ጀመረ ! ፍቅር እንደዛሬው ቀላል ነገር አልነበረም ወገኖቸ ! በዚህም ምክንያት የልጅቱን ትኩረት ለማግኘት ሌላ መላ መዘየድ ነበረብኝ …ችግሩ ግን ልጅቱ ከኋላየ ስለምትቀመጥ ከኋላ የሚያዩንን ሴቶች ለማማለል የሚረዳ ምንም አይነት መላ ማግኘት አለመቻሌ ነበር ! ደግሞ ከፊቷ ተቀምጨ ዙረህ እያት እያት የሚለኝ ነገር ነበር… ፍርሃት እንደማጅራት ቆልፍ ግራና ቀኝ ይዞ የጋሪ ፈረስ አስመሰለኝ እንጅ ! ለመጀመሪያ ጊዜ እግዚአብሔር ሰውን ሲፈጥረው እንደመኪና ስፖኪዮ ቢገጥምለት ምናለበት ብየ የተመኘሁበት ጊዜ ነበር !ለምንድነው ግን ሴቶች የወንድን ልጅ የኋላ ታሪክ እንጅ የኋላ ሰውነት በትኩረት የማይመለከቱት??? እንዴ ኧረ <የኋላው ከሌለ የለም የፊቱ> እህቶቸ !((((ውበትሽ እንደአደይ አበባ ምናምን ስትሉ …‹‹ለበፊቷ ፍቅረኛህም እንደዚህ ትላት ነበር ? … የምታፈቅረኝ ከሆነ ለማንም ሴት ያላልከውን <ብራንድ ኒው> ነገር ….እኔ እንደሌሎች ሴቶች አይደለሁም ›› ምናምን ! መፅሃፍ ባገላብጥ ከዛ በፊት ያፈቀሩ ሰዎችን ብጠይቅ በቃ ወንድ ልጅ ከኋላው አማላይ የመሆን ተስፋ እንደሌለው ተረዳሁ ! (((ከኋላም ከፊትም አማላይ የመሆን ተስፋ ያላቸው አገርና ሴት ብቻ መሆናቸው የገባኝ በዛ እድሜ ነበር !))) ‹‹በጃንሆይ ጊዜ በግ ሰባት ብር ጠጅ …›› ሲሉን የአገርን ኋላ ዞረው እያስቃኙን ነው! ‹‹ትልቅ ነበርን ትልቅም እንሆናለን›› የሚሉት አባባልም አገርን ከኋላዋም ከፊቷም የማድነቅ ሱስ የወለደው መፎክር ነው ! እና ይችን ያፈቀርኳትንና ከኋላየ የምትቀመጥ ልጅ ለማማለል ማጅራቴን ማስዋብ ፈለኩ …በዚች አለም ላይ ለማጅራት ማስዋቢያ ተብሎ የተሰራ ምንም ነገር አጣሁ! የወንድ ልጅ ማጅራት ለመመታት እንጅ ለመፈቀር ያላደለው ሚስኪን አካል ነው ! ማን ለማንጅራት ዘፈነ …? ደግሞ ክፋቱ …እኛ አበሾች የፈለገ ቢያምርብን ቢስማማን ጉልበትና ማጅራታችን የሚጠቁረው ነገር ! ተሰቃየሁ በፍቅር … በዚች ዓለም ላይ በዓይን ፍቅር እንደመሰቃየት ከባድ ነገር የለም የሚሉ ወንዶች ገጥመውኛል … እንደኔ እንደኔ ከባዱ ነገር በሚያፈቅሯት ሴት አይን ስር ተጥዶ እየታዩ መዋል ነው! ከማየት መታየት ከባድ ነው! ‹‹ከህዝብ አይን ማምለጥ አይቻልም›› የሚሉ ካድሬዎች ራሱ በሚጠላቸው ህዝብ አይን ስር ቁመው እንዲህ የተጨነቁ በሚያፈቅራቸው ህዝብ እይታ ውስጥ ቢከርሙ ምን ሊሆኑ ነው! ቃል መተንፈስ አቅቶኝ …እንደታፈንኩ ጊዜ ነጎደ… የትምህርት ዓመቱም አለቀ ….ወደሃይኩል ስንገባ ተለያየን! ከአይኗ ስር ዘወር ስል ፍቅሩም ቀለል አለኝ! የልጅነት ፍቅር ገር ነው ! በቃ አደግን ! ለዓመታት ትኑር ትሙት ረሳኋት! ባለፈው ቅዳሜ ማታ ድንገት ቴሌቪዥን ስከፍት ፣ ስምንተኛ ክፍል ካፈቀርኳት ልጅ ኋላ ይቀመጥ የነበረና ሰሞኑን ‹‹ጃኖው ከደረቷ›› በሚል ነጠላ ዜማው ታዋቂ የሆነው ደግሰው ደበበ (ዳጊ ዲ ) በቴሌቪዥን ቀርቦ ስለሙዚቃ ስራው እያወራ ደረስኩ … በመጨረሻም ስለሚስቱ ተጠየቀ ‹‹ እ በስራህ የሚስትህ ድጋፍ ከፍተኛ እንደሆነ ስትገልፅ ይሰማል ….ሚስትህ ጋር እንዴት ተዋወቃችሁ… ከዛ በፊት ግን እስቲ ሚስትህ እዚህ አለች እስቲ ወደመድረክ ….›› በጭብጨባ ታጅባ እንደቬሎ የተንዘረፈፈ የአበሻ ቀሚስ ለብሳ የስምንተኛ ክፍል ፍቅሬ ማህሌት ብቅ አለች ! ‹‹እ ሚስቴ ጋር እስከአሁን አልተዋወቅንም ህይወት ሒደት ነው …›› አለ በፈገግታ እያያት! ታዳሚው አጨበጨበ!ምነው ፈጣሪ ለዚህ ህዝብ አራት አራት አራት ጥንድ እጅ ባበቀለለት ….አጨብጭቦ አይጠግብምኮ! ‹‹ለመጀመሪያ ጊዜ እንዴት ተዋወቃችሁ ካልከኝ …እ…ስምንተኛ ክፍል ከፊቴ ነበር የምትቀመጠው … እና ከኋላዋ ማጅራቷ ላይ የበቀሉት ስስ ፀጉሮውች በመስኮት ከሚገባው ብርሃን ጋር ተዳምረው ልዩ ወርቃማ ፀዳልና ውበት ነበር የሚፈጥሩት …አሁን ማን ያምነኛል …ማጅራቷን አይቸ አፈቀርኳት ብል?! ሃሃሃሃሃሃ …. ‹‹እውነት ነው ?››…አለ ጠያቂው ወደሷ ዙሮ ‹‹አዎ !›› አለች እየተሸኮረመመች ! ምን አሽኮረመማት በሰገሌ ጊዜ ለነበረ ፍቅር ? ‹‹አንችስ ›› ‹‹…ይገርምሃል እኔ ደግሞ ከኋላየ ሁኖ ሲያንጎራጉር ድምፁ ይስበኝ ነበር… በቃ ዙሬ እንዳላየው እፈራለሁ … ግን ወድጀው ነበር ...ስንት ወር ሙሉ ….›› ህዝቡ በሳቅና በጭብጨባ አጀባት ! ትክዝ ብየ …. ሪሞትኮንትሮሉን ተጫንኩና ቲቪውን አጠፋሁት ! እዚች አገር ላይ ከራዕይ ይልቅ ትዝታ ትልቅ ቦታ አለው ! ‹‹ወደፊት ›› ያለ ሁሉ ወይ ይሞታል ወይ ያብዳል አልያም ይሰደዳል ወይም እንደእኔ ….! ብቻ ወደኋላ መዞር ያልቻለ እጣ ፋንታው መበላት ነው! ለምንድነው እኛ ኢትዮጵያዊያን ፍቅራችንም ፀባችንም እንደግመል ሽንት ወደኋላ የሚሄደው?? … አልኩ በትካዜ! #Share #AlexAbreham @AlexAbreham
نمایش همه...