ቅዱሳት መጻሕፍት
رفتن به کانال در Telegram
በዚህ ቻናል 👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ:: 👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ:: 👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ። ⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️ @Holy_scriptures
نمایش بیشتر7 823
مشترکین
+124 ساعت
+347 روز
+15330 روز
آرشیو پست ها
7 822
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ምክንያቱም የምንኖረው በእምነት እንጂ በማየት አይደለም።”
2ኛ ቆሮንቶስ 5፥7 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 822
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“እግዚአብሔር አምላክ የሚናገረውን እሰማለሁ፤ ሰላምን ለሕዝቡና ለቅዱሳኑ ልባቸውንም ወደ እርሱ ለሚመልሱ ይናገራልና።”
መዝሙር 85፥8
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 822
የእግዚአብሔርን ቃል የማንበብ ጥቅም
ክፍል-4
(የመጨረሻ ክፍል)
በመጀመሪያ የተከሰተው ኃጢአት የእግዚአብሔርን ቃል አለመታዘዝ ነበር፡፡ እግዚአብሔር በእኛ ላይ ያለውን ሥልጣን ግምት ውስጥ ሳናስገባ አንዳች ማድረግ ወይም እናደርገው ሲገባን ሳናደርገው ብንቀር ኃጢአት ይሆናል፡፡ ኃጢአት በ1ዮሐ.3፡4 "ዓመፅ" ተብሎ ተገልጾአል፡፡ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ሳንጠይቅ እንደፈቃዱ ሳይሆን በገዛ ፈቃዳችን የምንሠራው ሁሉ ኃጢአት ነው፡፡
ጌታችን ኢየሱስ መታዘዝን እንዴት እንዳሳየ እስኪ እንመልከት፡፡ በዕብራውያን 10፡7 ላይ ‹‹ፈቃድህን ላደርግ መጥቼአለሁ›› ይላል፡፡ ፈቃድን ለማድረግ ደግሞ መታዘዝን መማር ነበረበት (ዕብ.5፡6) እርሱ ዘላለማዊው አምላክ እንደመሆኑ መጠን መታዘዝ ለእርሱ እንግዳ ነበርና፡፡ በወልድነቱም በምድር በነበረበት ጊዜ ሁልጊዜ አብን ደስ የሚያሰኝ ሥራ ይሠራ ነበር፡፡ እንዲህም አለ፤ ‹‹የእኔስ መብል የላከኝን ፈቃድ አድርግ ዘንድ ሥራውንም እፈፅም ዘንድ ነው፡፡›› (ዮሐ.4፡35)
ሰው ሁሉ በየመንገዱ በሚሄድበትና ሁሉም የራሱን ፈቃድ በሚሠራበት በዚህች ምድር ይህ ሰው (ወልድ) ግን ፍጹም ቅዱስ ሆኖ ሳለ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ብቻ ሲፈፅም መታየቱ ለእግዚአብሔር ምንኛ ደስ ያሰኘዋል!
በአሁኑ ጊዜም እግዚአብሔርንና ፈቃዱን አውቀው ለማገልገል ደስተኞች የሆኑና ይህንንም ለመረዳት ቃሉን በትጋት የሚመረምሩ ሰዎች ሲገኙ እግዚአብሔር ምን ያህል ደስ ይሰኝ!
ቃሉን ለማወቅ በመፈለግ ስናጠና የሚሰጠንን ጥቅም ታላቅነት መገመት ይቻላል፡፡ በቃሉ ውስጥ የጌታን ክብርና ጌታ በፍቅሩ ያዘጋጀልንን በረከት ስናይ ልባችን በደስታ ይሞላል፡፡ ቃሉን በማወቅ የእግዚአብሔርን ሐሳብ በበለጠ መረዳት እንችላለን፡፡ ከሰይጣን ጥቃት የምንከላከልበትንና ራሳችንም መልሰን ለሌላው ሰው የነፍሱን ደኅንነት በመንገር ጠላትን የምናጠቃበት የጦር ዕቃችን ቃሉ ነው፡፡
እባክህ ተወኝ ጭንቅላቴ ወንፊት ነው ምንም መያዝ አይችልምና ማጥናቱ ይከበደኛል የሚል ሰው ሊኖር ይችላል፤ ነገር ግን ወንፊቱም ደጋግሞ ውኃ ሲያልፍበት ማቆር ባይችልም ራሱ ግን ይፀዳል፡፡ ውኃውም የወንፊቱን ቆሻሻነት ያስወግዳል፡፡ የእግዚአብሔር ቃልም ሰውን እንዲሁ ያነፃል፡፡ ማንበብ ብቻ ሳይሆን በቃሉ ላይ ጊዜ ወስዶ ማሰላሰል አስፈላጊ ነው፡፡ ጥሩ የሆኑ ማብራሪያዎችንም መጠቀም መልካም ነው፤ ሆኖም ማብራሪያውን ራሱንም በቃሉ ልንፈትነው የተገባ ነው፡፡ ማብራሪያው ቃሉን እንዲተካ ማድረግ የለብንም፤ ምክንያቱም ቃሉን የሚተካ ሌላ የአማራጭ አስተያየት ሊኖር አይገባምና እንደዚህ ማድረግም በራሱ ስሕተት ነው፡፡
‹‹ልጄ ሆይ ቃሌን ብትቀበል ትእዛዜንም በአንተ ዘንድ ሸሽገህ ብትይዛት ጆሮህ ጥበብን እንዲያደምጥ ታደርጋለህ፤ ልብህንም ወደ ማስተዋል ታዘነብላለህ፤ ረቂቅ እውቀትን ብትጠራት ለማስተዋልም ድምፅህን ብታነሳ እርስዋንም እንደ ብር ብታፈላልጋት እርስዋንም እንደ ተቀበረ ገንዘብ ብትሻት የዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን መፍራት ታውቃለህ፡፡››
(ምሳ.2፡1-5)፡፡
ምንጭ፦ gbv-online.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 822
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ስለዚህ እነርሱ ደግሞ በክርስቶስ ኢየሱስ ያለውን መዳን ከዘላለም ክብር ጋር እንዲያገኙ ስለ ተመረጡት በነገር ሁሉ እጸናለሁ።”
2ኛ ጢሞቴዎስ 2፥10
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 822
#አዲስ_ዓመት
የእግዚአብሔርን ቃል የማንበብ ጥቅም
ክፍል-3
የእግዚአብሔር ቃል ያነጻል
የእግዚአብሔር ቃል የምንፀዳበትና የምንቀደስበት ብቸኛ የእግዚአብሔር መንገድ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ክርስቶስ ለቤተክርስቲያን ያደረገላትን ሲገልጥ ‹‹በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ›› (ኤፌ.5፡25) ይላል፡፡ በዮሐ.17፡17ም እንዲሁ ‹‹በእውነትህ ቀድሳቸው ቃልህ እውነት ነው›› የሚል እናገኛለን፡፡
አዘውትረን የእግዚአብሔርን ቃል ለአካሄዳችንና ለመንገዳችን የምንጠቀም ከሆንን ሕይወታችን ነጽቶ ከክፉ ተለይተን መኖር እንችላለን፡፡ በአብ ዘንድ ያለው ጠበቃችን እግሮቻችንን በቃሉ ያጥባቸዋል (1ዮሐ.2፡2)፤ ነገር ግን እግሮቻችን እንዲታጠቡ መፍቀድ የእኛ ኃላፊነት ነው፡፡
መዝሙረኛውም አንተን እንዳልበድል ቃልህን በልቤ ሰወርሁ (መዝ.119፡11) ይላል፡፡ በሌላ ስፍራም ባሪያህ ደግሞ ይጠብቀዋል በመጠበቁም እጅግ ይጠቀማል ይላል(መዝ.19፡11)፡፡
ልምምድ እና ትምህርት ሁሉ በቃሉ ይመዘናል
አሁንም በመዝ.119፡168 ‹‹መንገዶቼ ሁሉ በፊትህ ናቸውና ትእዛዝህንና ምስክርህን ጠበቅሁ›› ሲል ‹‹መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ›› እያለ ደግሞ በራእይ 2 እና 3 የሚያሳስብ ቃል ተጽፎ እናገኛለን፡፡ በአብያተ ክርስቲያናት (በአማኞች ማኅበር) ውስጥ የሚደረጉ ነገሮችን ሁሉ መፈተን አለብን፡፡ የሚሰጠው ትምህርትና የሚደረገው ተግባር ሁሉ መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት ከሚለው አንፃር ታይቶ በቃሉ መፈተን አለበት፡፡ በሌላ ስፍራም እንዲህ ይላል ‹‹ነቢያትም ሁለት ወይም ሦስት ሆነው ይናገሩ ሌሎችም ይለዩአቸው›› (1ቆሮ.14፡29) አካሄዳችንንና ሐሳባችንንም በቃሉ መፈተን አለብን፡፡ ሐሳቦቻችን ምንም ጥቅም የላቸውም፡፡ ወሳኙ የእግዚአብሔር ቃል የሚለው ነገር ብቻ ነው፡፡
በሐዋ.17፡11 ስናይ በቤሪያ የነበሩት አይሁዳውያን በተሰሎንቄ ከነበሩት የሚሻሉበት ነበረ፡፡ ምክንያቱም የጳውሎስን ትምህርት ከቃሉ አንፃር እያስተያዩ ይመረምሩት ነበርና፡፡ ጳውሎስም የትምህርቱ መነሻ ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሆኑ በግልጥ ያሳየበት ተጽፎ ይገኛል (1ቆሮ.15፡3-4)፡፡
‹‹የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል፡፡››(2ጢሞ.3፡16-17)፡፡
መታዘዝና ለፈቃዱ መገዛት
‹‹ትእዛዛትህን እጅግ እንጠብቅ ዘንድ አንተ አዘዝህ›› (መዝ.119፡4) ‹‹ባሪያህ ደግሞ ይጠብቀዋል በመጠበቁም እጅግ ይጠቀማል›› (መዝ.19፡11) ‹‹እኔ የአባቴን ትእዛዝ እንደ ጠበቅሁ በፍቅሩም እንደምኖር ትእዛዜን ብትጠብቁ በፍቅሬ ትኖራላችሁ›› (ዮሐ.15፡10)፡፡ ‹‹የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል አባቴም ይወደዋል ወደ እርሱም እንመጣለን በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን›› (ዮሐ.14፡23)፡፡ ‹‹ትእዛዛቱን ልንጠብቅ የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ ነውና ትእዛዛቱም ከባዶች አይደሉም›› (1ዮሐ.5፡3)፡፡
ከእነዚህም ንባቦች ሰው ቃሉን አውቆ መታዘዝ እንዳለበት እግዚአብሔር ለመታዘዝ ምን ያህል ዋጋ እንደሰጠ መገመት ይቻላል፡፡ ምን አድርግ ዘንድ ትወዳለህ? ለሚለው ጥያቄ የሚሰጠን መልስ ትእዛዜን ጠብቅ የሚል ይሆናል፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ gbv-online.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 822
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“አራተኛውም ወንዝ ኤፍራጥስ ነው። እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ወስዶ ያበጃትም ይጠብቃትም ዘንድ በዔድን ገነት አኖረው።”
ዘፍጥረት 2፥15
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 822
#አዲስ_ዓመት
የእግዚአብሔርን ቃል የማንበብ ጥቅም
ክፍል-2
የእግዚአብሔር ቃል መሪያችን ነው
መዝሙረኛው በመዝ.119፡9 ‹‹ጎልማሳ መንገዱን በምን ያነጻል? ቃልህን በመጠበቅ ነው›› ይላል፡፡ ወረድ ብሎም በቊጥር 11 ላይ ‹‹አንተን እንዳልበድል ቃልህን በልቤ ሰወርሁ›› ሲል በቁ.105 ላይ ደግሞ ‹‹ሕግህ ለእግሬ መብራት ለመንገዴ ብርሃን ነው›› ይላል፡፡
እግዚአብሔር ለኢያሱ እንደዚህ አለው ‹‹ነገር ግን ጽና እጅግ በርታ ባሪያዬ ሙሴ ያዘዘህን ሕግ ሁሉ ጠብቅ አድርገውም፤ በምትሄድበትም ሁሉ እንዲከናወንልህ ወደ ቀኝም ወደ ግራም አትበል፡፡ የዚህ ሕግ መጸሐፍ ከአፍህ አይለይ፡፡ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው፡፡ የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም›› (ኢያ.1፡7-8)፡፡
አስቸጋሪ ሁኔታ በነበረበት ጊዜ ጳውሎስ ለኤፌሶን ሽማግሌዎች ‹‹ለጸጋው ቃል አደራ ሰጥቻችኋለሁ›› (ሐዋ.20፡32) ሲል ለጢሞቴዎስ ደግሞ ‹‹መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳት መጻሕፍትን አውቀሃል›› (2ጢሞ.3፡15) ይለዋል፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል የማናውቅ ከሆነ ኃጢአት ምን መሆኑን እንዴት እናውቃለን? ነገር ግን አለማወቃችን ነፃ ሊያወጣን አይችልም (ዘሌ.5፡17) እግዚአብሔር ስለሁሉም ነገር የተናገረበትን ቃሉን ካላጠናን ማድረግ የሚገባንንና እንደ እግዚአብሔር ሐሳብ የሆነውንስ እንዴት ልናውቅ እንችላለን? ቃሉን የማናውቅ ከሆንን አንዳንድ አስፈላጊ በሆኑ ነገሮች እንዴት ልንወሰንና የምንሄድበትንም መንገድ እንዴት ልንመርጥ እንችላለን?
‹‹ትእዛዝህ ከጠላቶቼ ይልቅ አስተዋይ አደረገኝ፡፡ ምስክርህ ትዝታዬ ነውና ካስተማሩኝ ሁሉ ይልቅ አስተዋልሁ፡፡ ትእዛዝህን ፈልጌአለሁና ከሽማግሌዎች ይልቅ አስተዋልሁ፡፡ ... የቃልህ ፍቺ ያበራል ሕፃናትንም አስተዋዮች ያደርጋል፡፡›› (መዝ.119፡98-100፣130)
ቃሉ የጦር ዕቃችን ነው
‹‹የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ፤ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡›› (ኤፌ.6፡17) ‹‹በቃልህ ታምኛለሁና ለሚሰድቡኝ በነገር እመልስላቸዋለሁ፡፡››(መዝ.119፡42)
ይህን ሰይፍ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዴት እንደተጠቀመበት እንመልከት፡፡ ከሰይጣን የሚመጣበትን ጥያቄ ሁሉ ተጽፎአል እያለ ይመክት ነበር (ማቴ.4፡4፣7፣10) ውጤቱም ሰይጣንን እንዲሸሽ አስገድዶታል፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔርን ቃል መቋቋም የሚችል ኃይል አልነበረውምና ነው፡፡
ጌታችን ቃሉን በቀጥታ ሰይጣንን ለማሸነፍ ብቻ ሳይሆን የሰዎችንም ሐሳብ ለማክሸፍ ተጠቅሞበታል፤ በሉቃስ 20፡17 ለሚያስተምራቸው ሕዝብ ‹‹... ተብሎ የተጻፈው ይህ ምንድር ነው?›› ብሎ ሲያሳስብ ይታያል፡፡ በዮሐ.10፡34 ደግሞ ‹‹... ተብሎ በሕጋችሁ የተጻፈ አይደለምን?›› ሲል ይጠይቃል፡፡
‹‹የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና የሚሠራም ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፡፡ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፡፡ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል እኛን በሚቆጣጠር በእርሱ ዓይኖቹ ፊት ሁሉ ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው እንጂ በእርሱ ፊት የተሰወረ ፍጥረት የለም፡፡›› (ዕብ.4፡12-13)
ሰይጣንና ዓለምን ለመከላከልና ለማጥቃትም ልንጠቀምበት የምንችለው ብቸኛ መሣሪያ የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ የሕያው እግዚአብሔር ቃል በመሆኑ በውስጡ ኃይል እንዳለው ልንረሳ አይገባንም፡፡ ስንጠቀምበት ቃሉን የምንሰነዝርበት ሰው ሁሉ የቃሉን ኃይል ያውቃል፡፡ በቃሉ የምናነጋግረው ግለሰብ ቢቀበለውም ባይቀበለውም ወይም ያልተሰማው በመምሰል የተረጋጋ ለመምሰል ቢሞክር ወይም ተቃውሞው ቢቀጥልም እንኳን ሕሊናውን ግን ይወቅሰዋል፡፡ የተባለው ነገር እውነት እንደሆነም ያውቃል፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ gbv-online.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 822
በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ነህምያ የኢየሩሳሌምን ቅጥር እንደገና ለመገንባት ከየትኛው ከተማ በመነሳት ወደ ኢየሩሳሌም ተጓዘ?
7 822
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ዮሴፍ ትንሹ የፍሬ ዛፍ ነው፥ በምንጭ አጠገብ የሚያፈራ የፍሬ ዛፍ፤ አረጎቹ በቅጥር ላይ ያድጋሉ።”
ዘፍጥረት 49፥22
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 822
#አዲስ_ዓመት
የእግዚአብሔርን ቃል የማንበብ ጥቅም
ክፍል-1
መጽሐፍ ቅዱሳችሁን በማዘውተር ታነቡ እንደሆነ ልጠይቃችሁ እወዳለሁ፡፡ ቤተሰብ በገበታ ሲሰበሰብ ወይም በተለምዶ እንደሚደረግ ማለቴ ሳይሆን ለራሳችሁ ብላችሁ ብቻችሁን ስትሆኑ ታነቡ እንደሆነ ልጠይቅ ፈልጌ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ማዘውተሩ ትልቅ ጠቀሜታ አለው፡፡ አማኝ የእግዚአብሔርን ቃል የማያነብ ከሆነ ከእግዚአብሔር ጋር የቅርብ ኅብረት አይኖረውም፤ ደስታውም የተሟላ አይሆንም፡፡
እንደዚህ ማለታችንም የመጽሐፍ ቅዱስን ጥቅም ማጋነን አይሆንም፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቃል ስለሆነና እግዚአብሔርንና ሐሳቡንም ማወቅ የምንችለው ደግሞ በቃሉ ብቻ ስለሆነ ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ዘመን እግዚአብሔር በቃሉ ራሱን ገለጠ፤ ቃሉንም እንዲጻፍ አደረገው፡፡ በዚህ ቃሉም ማንነቱን ገለጠ፡፡ ያደረገውን፣ ሊያደርገው ያለውንና ሰው እንዴት ሊያገለግለው እንደሚገባም በቃሉ ተናገረ፡፡ ከዚያም ወልድ ወደ ምድር መጣና እግዚአብሔርን ተረከው (ዮሐ.1፡18) እንደዚሁም ስለወልድ ሕይወት ማለትም ስለ ልደቱ፣ ኑሮውና ሞቱ ስለ ተናገረውና ስለ ሥራውም ማወቅ የምንችለው በቃሉ ብቻ ነው፡፡ አሁን በምድር ላይ በአማንያን የሚያድር እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም በቃሉ በኩል ሁሉን ነገር ይገልጽልናል፡፡
ስለሆነም መጽሐፍ ቅዱስን የማይወድ አማኝ ካለ አሳዛኝ ነው፡፡ በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና እውቀት ማደግም ለቃሉ ካለን ፍቅርና ከቃሉ አጠቃቀም ጋር የተያያዘ ነው፡፡
አዲሱ ልደት- በእግዚአብሔር ቃል
ለምሳሌ መዝ.119ን ስንመለከት የዘማሪው እያንዳንዱ መንፈሳዊ ደረጃ ከቃሉ ጋር የተያያዘ ሆኖ እናገኛለን፡፡ በዚሁ መዝሙር ቁ.93ን ስናይ ‹‹በእርሱ ሕያው አድርገኸኛልና ፍርድህን ለዘላለም አልረሳም›› በማለት አዲሱ ሕይወት ከቃሉ እንደሚገኝ ይናገራል፡፡ እንደዚሁም በሌሎች ቁጥሮች ማለትም ቁጥር 25፣ 37፣ 41፣ 50፣ 88፣ 107፣ 116፣ 144፣ 149፣ 154፣ 156፣ 159 እና 175ን መመልከት ይቻላል፡፡ ይህ ሐሳብ በሌሎች በርካታ ምንባቦችም በግልጥ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ‹‹ለፍጥረቱ የበኩራት ዓይነት እንሆን ዘንድ በእውነት ቃል አስቦ ወለደን›› (ያዕ.1፡18) የሚል እናያለን፡፡ በሌላ ስፍራም ‹‹ዳግመኛ የተወለዳችሁት ከሚጠፋ ዘር አይደለም፤ በሕያውና ለዘላለም በሚኖር በእግዚአብሔር ቃል ከማይጠፋ ዘር ነው እንጂ›› (1ጴጥ.1፡23) ይላል፡፡
የእግዚአብሔር ቃል የኃጢአተኛን ሰው ኅሊና ወደ እግዚአብሔር ብርሃን እንዲመጣ ያደርገዋል፡፡ በዚህም ሰው ማን መሆኑን አይቶ ራሱን ያወግዛል፤ ወደ እግዚአብሔርም ይናዘዛል፤ ይህም መለወጥ ማለት ነው፡፡ ራስን መመርመርና በራስ መፍረድም የሰውን ልብ ያነፃል፤ መንፈስ ቅዱስም በቃሉ በኩል አዲስ ሕይወትን በሰውዬው ውስጥ ይሠራል፡፡
ስለዚህ ለማያምኑት ሰዎች ወንጌልን ስንነግር የእግዚአብሔርን ቃል ማወቅ አለብን፡፡ የራሳችን ቃል ሰውን ወደ እምነት ሊያመጣ አይችልም፡፡ ሰውን መለወጥ የሚችለው የእግዚአብሔር ቃል ብቻ ነው፡፡ ‹‹እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡›› (ሮሜ.10፡17)፡፡
የአዲሱ ሕይወት ምግብ
በተጨማሪም መዝሙረኛው ስለ እግዚአብሔር ቃል ሲናገር ‹‹ቃልህ ለጉሮሮዬ ጣፋጭ ነው ከማርና ከወለላ ይልቅ ለአፌ ጣፈጠኝ፤››(መዝ.119፡103) ‹‹ከማርና ከማር ወለላም ይጣፍጣል››(መዝ.19፡10) በማለት የቃሉን ጣፋጭነትና ምግብነት በማድነቅ ተናግሯል፡፡ ይህም ጣፋጭ ምግብ ደግሞ ለአዲስ ሕይወት ምግብ ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስም ሰው ‹‹ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም›› በማለት ቃሉ በሕይወት የምንኖርበት ምግብ እንደሆነ ተናግሯል (ማቴ.4፡4፣ ዕብ.5፡12-14፣ 1ጴጥ1፡25-2፡2)፡፡
በቃሉ የተገኘው አዲሱ ሕይወታችን የሚስማማውን ምግብ ማግኘት አለበት፡፡ ይህም ምግብ አዳኛችንና የሞተልን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤(ዮሐ.6፡56) እርሱ በምድር ቅዱስ ሰው ሆኖ የተመላለሰና በሰማይ ደግሞ የከበረ ጌታ ሆኖ የተቀመጠ የአማኞች ምግብ ነው፡፡ እርሱ የምድረ በዳውን መና የተካ፣ የከነዓን የምድር ፍሬ፣ እንደዚሁም ለአማኞች የዘወትር መብል የሆነ ከሰማይ የወረደ አማናዊ መና ነው (ኢያ.5፡11-13) ይህንንም ምግብ የምናገኘው በቃሉ ውስጥ ብቻ ነው፡፡ ጌታ በብሉይ ኪዳን በጥላዎችና በምሳሌዎች እየሆነ በትንቢቶች እና በነቢያት ይታያል፡፡ በአዲስ ኪዳን ደግሞ በሕይወቱ በሞቱና በክብሩ ከወንጌላት እስከ ራእይ በተጻፈው ይታያል፡፡
ታዲያ ብዙዎች መንፈሳዊ ሕይወታቸው ደክሞ አቅመቢስ ሆነው ጠንካራ ምግብ መውሰድ ተስኖአቸው ወተት ብቻ የሚያስፈልጋቸው (ዕብ.5፡12-14) ወደ ጉባኤ ስለማይመጡ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ስለማይከታተሉ ራሳቸውም ቃሉን ስለማያነቡ አይደለምን? ልናድግና ጤናማ የሆነ መንፈሳዊ ሕይወት ሊኖረን የሚችለው ዕለት ዕለት ያለማቋረጥ ቃሉን ስንመገብ ብቻ ነው፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ gbv-online.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 822
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ለተጠሩት ግን፥ አይሁድ ቢሆኑ የግሪክ ሰዎችም ቢሆኑ፥ የእግዚአብሔር ኃይልና የእግዚአብሔር ጥበብ የሆነው ክርስቶስ ነው።”
1ኛ ቆሮንቶስ 1፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 822
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።”
ኤርምያስ 29፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 822
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የኤፌሶን ከተማ አገልግሎቱን ከፈጸመ በኋላ የቤተክርስቲያን ሽማግሌዎችን ምክርና ሐሰተኞች እንደሚመጡ ያስጠነቀቃቸው የት ከተማ ነበር?
7 822
#እራሳችንን_እንመርምር
ስብከት ምንድነው? ጠቀሜታው ላላመነ ወይስ ላመነም ጭምር?
“በእግዚአብሔር ጥበብ ምክንያት ዓለም እግዚአብሔርን በጥበብዋ ስላላወቀች፥ በስብከት ሞኝነት የሚያምኑትን ሊያድን የእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ሆኖአልና።”
1ኛ ቆሮንቶስ 1፥21
“አንተ ግን ነገርን ሁሉ በልክ አድርግ፥ መከራን ተቀበል፥ የወንጌል ሰባኪነትን ሥራ አድርግ፥ አገልግሎትህን ፈጽም።”
2ኛ ጢሞቴዎስ 4፥5
“እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል? ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ?”
ሮሜ 10፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 822
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
"እግዚአብሔር የልመናዬን ድምፅ ሰምቶአልና ወደድሁት። ጆሮውን ወደ እኔ አዘንብሎአልና በዘመኔ ሁሉ እጠራዋለሁ።"
መዝሙር 116፥1-2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
