Pdf All grade ethiopian or books
رفتن به کانال در Telegram
Reading for great full 🗞 EDUCATIONAL NEWS &INFO 📚 FICTION BOOKS 🌠 📚 STUDENT TEXTBOOK 📚 TEACHER GUIDE 👥 JOIN GROUP 👉 @ABPDF44
نمایش بیشتر2 864
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-67 روز
-330 روز
آرشیو پست ها
#AddisAbaba
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በበይነ መረብ (ኦንላይን) ከሚሰጥባቸው ከተሞች አንዱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስለመሆኑ ተሰምቷል።
ይህን ተከትሎ የፈተና ቅድመ ዝግጅት ተግባራት ላይ ያተኮረ ውይይት ዛሬ ሲካሄድ ውሏል።
የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ኃላፊው ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ፤ " የ2016 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በከተማው በኦንላይን ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ነው " ብለዋል።
ለፈተናው ኮምፒዩተሮች፣ ላፕቶፖችና ታብሌቶችን ጨምሮ ሌሎች ግብአቶችን የማሟላት ስራ ተጀምሯል ተብሏል።
የግል ትምህርት ቤቶች ለፈተናው የሚያስፈልጉ ግብአቶችን ከወዲሁ እንዲጀምሩ ጥሪ ቀርቧል።
ትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ.ም 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን እንደሚሰጥ ማሳወቁ ይታወሳል።
ሙሉ በሙሉ ፈተናው በኦንላይን ባይሰጥም በተመረጡ ከተሞች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የቀሩት ተማሪዎች በተለመደው ሁኔታ ዩኒቨርሲቲ ገብተው በወረቀት ይፈተናሉ።
እስካሁን በየትኞቹ ከተሞች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች ፈተናውን በኦንላይን ይወስዳሉ የሚለው አይታወቅም። በምን አግባብ ተማሪዎቹ እንደሚመረጡም ለጊዜው በይፋ የሚታወቅ ነገር የለም።
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ፤ ከሐምሌ 9 እስከ ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (ኦንላይን) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል።
@gread10pdf
የ2016 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል)ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሐምሌ 3-5 ለማህበራዊ ሳይንስ ሐምሌ 9-11/2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል። በወረቀት ላይ የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ሰኔ 30-ሐምሌ 01/2016 ዓ/ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ሐምሌ 6-7/2016 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ይሆናል።
ስለሆነም ተፈታኞች እና የሚመለከታቸው ሁሉ ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ እናሳስባለን።
የፈተና ስርቆትንና ኩረጃን በጋራ እንከላከል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
@gread10pdf
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለሆሳዕና በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡
@gread10pdf
@gread10pdf
ለተማሪዎች የሚጥቅሙ የAI ቱሎች
🌟Academic Help
https://academichelp.net/ = Assists students and writers in creating high-quality essays
🌟Wisdolia
https://www.wisdolia.com/ = Generate flashcards and multiple choice questions in seconds.
🌟Grammarly
https://www.grammarly.com/
Real-time grammar, tone, and plagiarism checker
🌟Smodin
https://smodin.io/
Elevate writing, research, and homework with AI, multilingual
🌟POE
https://poe.com/
Enhance user interactions with adaptable, intelligent
@gread10pdf
⭐️የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የሞዴል ፈተና የጊዜ ለውጥ
✅የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ፕርግራም ለውጥ የተደረገ ሲሆን ከ21/8/2016 ጀምሮ የሚሰጥ ይሆናል::
✅የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ፕሮግራም ግን ቀድሞ በወጠው ፕሮግራም መሰረት ይቀጥላል(የተለወጠ ነገር የለም)::
Join us
@gread10pdf
⭐️የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የሞዴል ፈተና የጊዜ ለውጥ
✅የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ፕርግራም ለውጥ የተደረገ ሲሆን ከ21/8/2016 ጀምሮ የሚሰጥ ይሆናል::
✅የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ፕሮግራም ግን ቀድሞ በወጠው ፕሮግራም መሰረት ይቀጥላል(የተለወጠ ነገር የለም)::
Join us
@gread10pdf
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መቼ ይሰጣል?
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና መቼ እንደሚሰጥ በርካቶች ጥያቄ አድርሰውናል።
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወቃል።
በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ምዝገባ እንዳደረጉ መገለፁም ይታወሳል፡፡
ለሦስተኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተናው፤ ዘንድሮ ለተፈጥሮ ሳይንስ እና ለማኅበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስኮች ለእያንዳንዳቸው በስድስት የትምህርት አይነቶች እንዲሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰኑ አይዘነጋም፡፡
Credit :- Tikvah University
Join us
@gread10pdf
#ረመዳን #ዐቢይ ፆም
የሁለቱ ታላላቅ ሃይማኖቶች የተከበሩ የፆም ወቅቶች በአንድ ቀን ነገ ሰኞ መጋቢት 02/2016 ይጀምራል።
ይህን መሰል ግጥምጥሞሽ ከ33 ዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ሊከሰት የሚችል ድንቅ ግጥምጥሞሽ ነው።
ፈጣሪ ፀሎታችንን ይስም፤ምድራችንን ሰላም ያድርግልን 🤲
@gread10pdf
#MoE
ትምህርት ሚኒስቴር ፤ የ2016 ዓ .ም አጋማሽ የመውጫ ፈተና ውጤት ከየካቲት 18/2016 ዓ/ም ጀምሮ መለቀቁን አሳውቋል።
ሚኒስቴሩ ይህን ያሳወቀው ፤ ለሁሉም የግልና የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሙሉ ባስተላለፈው መልዕክት ነው።
ተፈታኞች ውጤታቸውን በ https://result.ethernet.edu.et ሊንክ ማየት ይችላሉ ተብሏል።
@gread10pdf
ለ 8ኛ ክፍል ተማሪዎች የ 2016 ዓ.ም ሰኔ ወር ላይ የምትፈተኑት ዋናው ፈተናችሁ የሚወጣው ከ8ኛ ክፍል ብቻ ነው የ 7ኛ ክፍልን አይጨምርም።
የ6ተኛ ክፍልም በተመሳሳይ የ5ኛ ክፍልን አያካትትም
Join
@gread10pdf
