fa
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

رفتن به کانال در Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

کانال ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 13 361 مشترک است و جایگاه 1 755 را در دسته حمل و نقل و رتبه 2 537 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 13 361 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 18 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 91 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 11 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 41.16% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.44% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 491 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 060 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 11 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 20 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته حمل و نقل تبدیل کرده‌اند.

13 351
مشترکین
+1124 ساعت
+477 روز
+9130 روز
آرشیو پست ها
በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ከምክር ቤቱ አባላት በመንገድ መሰረተ ልማት ዙሪያ የተነሱ ጥያቄዎች እና በክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ የተሰጡ ማብራሪያዎች

የባሕር ዳር ዓባይ ወንዝ ድልድይ አፈፃፀም 94.56 በመቶ ላይ ደርሷል አዲስ አበባ፣ መጋቢት 18 ቀን 2015 ዓም (ኢመአ)፡ በባሕር ዳር ዓባይ ወንዝ ላይ እየተሰራ ያለው ድልድይ በዚህ ዓመት ሙሉ
+3
የባሕር ዳር ዓባይ ወንዝ ድልድይ አፈፃፀም 94.56 በመቶ ላይ ደርሷል አዲስ አበባ፣ መጋቢት 18 ቀን 2015 ዓም (ኢመአ)፡ በባሕር ዳር ዓባይ ወንዝ ላይ እየተሰራ ያለው ድልድይ በዚህ ዓመት ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለአግልግሎት ክፍት እንደሚሆን ይጠበቃል ፡፡ ድልድዩ 380 ሜትር ርዝማኔ እና 43 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ሲሆን፣ መንገዱ 4.7 ኪ.ሜ. ርዝማኔ አለው፡፡ በአሁኑ ሰዓት ከዓባይ ወንዝ በሁለቱም አቅጣጫ ሲሠራ የቆየውን ድልድይ የመጨረሻ የማገናኘት የሙሊት(key segment) ሥራ ተከናውኗል፡፡ ከሁለቱም አቅጣጫ ሲሠራ የቆየው ድልድይ የመጨረሻ የማገናኘት በመከናወኑ የድልድዩን የላይኛውን 380 ሜትር አካል (super structure) እንዲጠናቀቅ አስችሎታል፡፡ ለግንባታው የሚያስፈልገው 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡ ግንባታውን የቻይናው ሲ ሲ ሲ ( CCCC) የኮንስትራክሽን ድርጅት እያከናወነ ይገኛል፡፡ የመቆጣጠርና እና የማማከር ሥራውን የቱርኩ ቦቴክ እና የሃገር ውስጥ አማካሪው እስታዲያ እየተወጡ ይገኛሉ፡፡ የድልድዩ ግንባታ አጠቃላይ አፈጻጸም 94.56 በመቶ ላይ ደርሷል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከአማካሪ ድርጅቶች ጋር የውይይት መድረከ አካሄደ:: አዲስ አበባ፣ መጋቢት 14፣ 2015 (ኢመአ)፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በመንገድ ግንባታዎች ላይ እየተሳተፉ ከሚገኙ የማማከርና የቁጥጥር ስራን ከሚሰሩ የተለያዩ ድርጅቶች ጋር የውይይት መድረከ አካሄደ:: ውይይቱ ተቋሙ የኮንስትራክሽን ዘርፉን በማሻሻል እና ትኩረት በማድረግ በመንገድ ግንባታና ቁጥጥር ስራዎች ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን በመለየት የተሻለ አፈፃፀም እንዲመጣ ለማስቻል ያለመ ነው፡፡ በመድረኩ የተገኙት የኢመአ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን ከአማካሪ ድርጅቶች ጋር በመንገድ ግንባታ ማማከርና ቁጥጥር ዙሪያ የተደረገው ምክክር ዘርፉን ወደተሻለ ደረጃ ለማሻገር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም በዘርፉ የተሠማሩ አማካሪ ድርጅቶች ከተቋሙ ጋር ትስስር በመፍጠር በየጊዜው በመገናኘትና በመመካከር አማራጭ መፍትሄዎችን በማቅረብ በተለይ በሙያዊ ስነምግባር፣ በፋይናንስ፣ በቅንጅታዊ አሰራር ግልጽነትና ተጠያቂነት ማስፈን እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ተሳታፊ የሆኑ የተለያዩ አማካሪ ድርጅቶችም በስራ ላይ ያጋጠሟቸውን ችግሮች እና መሻሻል አለባቸው ያሉትን ሀሳቦችን አንስተው የጋራ ውይይት ተከናውኗል:: አሁን ላይ የአማካሪ ድርጅቶቹ ማህበር ያለውን ቁመና በማጠናከር በሚገጥሟቸው ተግዳሮቶችና መፍትሄ በሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ከተቋሙ ጋር በቅርበት ለመስራት የተስማሙ ሲሆን ማህበሩን በማጠናከር ክፍተቶችን ለማጥበብ እና በቀጣይ የአገልግሎት ጥራት በሚመጣበት አግባብ ዙሪያ መክረዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ አማካሪ ድርጅቶች የኮንስትራክሽን ዘርፉን የተሻለ ለማድረግ የሚገነቡ መንገዶች ጥራታቸውን የጠበቁና ዘመናዊ ለማድረግ ትኩረት ሰጥተው ተግባራዊና ውጤታማ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባቸው እና ሴክተሩን ማነቃቃት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ አማካሪ ድርጅቶቹም ተቋሙ የጣለባቸውን ሃላፊነት በአግባቡ በመወጣት የሚስተዋሉ የአፈፃፀም ውስንነቶችንና የተነሱ ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን አጠናክሮ ለመቀጠል ስምምነት ፈጥረዋል፡፡ አማካሪ ድርጅቶቹ የኢመአ አሰራርን በትክክል ተረድተዉ ሊታይ በሚችል ትርጉም ያለው ለውጥ በሚያመጣ መልኩ ለተሻለ አፈፃፀም በጋራ ትኩረት በመስጠት እየተመካከሩ ለጋራ ግብ መስራት እንዳለባቸውም በመረዳት በመተጋገዝና በመነጋገር መፍትሄ ለማምጣት የሚያስችሉ ስራዎችን ለመስራት መግባባት ላይ ተደርሷል:: በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

Call for Company Owners and General Managers Training

የሞምባሳ - ናይሮቢ - አዲስ አበባ ኮሪደር አካል የሆነው የሀዋሳ - አገረማሪያም - ሞያሌ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የሚመለከት ጥናታዊ ፅሁፍ ቀረበ:: የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገዶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ለመገምገም በተመረጡ መንገዶች ላይ የዳሰሳ ጥናት የሚያካሂዱ አማካሪ ድርጅቶች በመቅጠር የሚያስጠና መሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት በሀገር በቀሉ ኢትዮ-ኢንፍራ ኢንጅነሪንግ እና አሰፋ አዲሱ ዴቨሎፕመንት ኮንሰልታንት በተባሉ ድርጅቶች በሞጆ-ሐዋሳ-ሃገረማርያም-ሞያሌ የመንገድ ኘሮጀክት ዙሪያ የሚኖራቸውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ለመዳስስ የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት ሲካሄድ ቆይቶ ለግምገማ ቀርቧል፡፡ በእለቱ በቀረበው ጽሁፍ ላይ ጥናቱን ለማካሄድ ጥቅም ላይ በዋሉ ዘዴዎች፣ ተግባራት እና የተገኙ ውጤቶች ዙሪያ የማማከር ስራዉን ባከናወነው ድርጅት በኩል ማብራሪያ ቀርቦ ውይይት ተካሄዷል፡፡ በውውይቱም ከጥናቱ በዋናነት ምን ማግኘት እንደተቻለ እና ከዚሁም ጋር በተያያዘ ቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ ጥናቱን በሚገባ ለማጠናቀቅ የሚያስችሉ ግብዓቶች የተሰጡ ሲሆን አቅጣጫዎች ተለይተው ምክረ ሃሳብ ተሰጥቶበታል፡፡ የቀረበው ጥናት በዋናነት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ለታለመለት አላማ በአግባቡ ጥቅም ላይ መዋሉን ለማረጋገጥና በአሁኑ ወቅት እየሰጠ የሚገኘው አገልግሎት እንዲሻሻል በማገዝና ስለመንገዱ የተሻሉ መረጃዎችን ለማግኘት የሚረዳ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ከዚሁም ጎን ለጎን የመንገዱ መገንባት በግብርና፣ በትምህርት፣ በጤናዉ ዘርፍ እና ተጨማሪ የስራ እድል በመፍጠር እንዲሁም በአካባቢው ሌሎች የማህበራዊ አገልግሎት እንዲስፋፋ ከማድረግና የትራንስፖርት እንቅስቃሴን በማሳለጥ ረገድ የሚኖረው ፋይዳ የላቀ እንደሚሆን ተጠቁሟል:: ይህ የመንገድ ኮሪደር በአገሪቷ ከሚገኙ የወጪና ገቢ ንግድ መስመሮች አንዱና ዋነኛው በመሆኑ ከፍተኛ የትራፊክ እንቅስቃሴ የሚካሄድበት እና በኬንያ በኩል ወደ አገር ዉስጥ በሚገቡ የሸቀጥ ምርቶችን ወደመሀል አገር ለማጓጓዝ ብሎም ከጎረቤት አገር ጋር ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር እና ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑ በጥናቱ ተመላክቷል፡፡ ጥናቱ በአፍሪካ ልማት ባንክና በኢትዮጵያ መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ የሚካሄድ ሲሆን ተጨማሪ ግብዓቶችን አካቶ በቅርቡ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡

ሚኒስትር ካውንስለሩ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደርን ጎበኙ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6 ቀን 2015 ዓም (ኢመአ)፡ በኢትዮጵያ የቻይና ኢኮኖሚክና ኮሜርሻል ሚኒስትር ካውንስለር የሆኑት ክቡር ሚስተር ያንግ ይሃንግ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደርን ጎበኙ። ክቡር ሚኒስትር ካውንስለሩ ከልዑካን ቡድናቸው እና በኢትዮጵያ በመንገድ ግንባታ ስራ ከተሰማሩ የቻይና የመንገድ ግንባታ ስራ ተቋራጮች ጋር በጋራ በመሆን ነው ፤ ኢመአን የጎበኙት። በወቅቱ ከነበረው የጉብኝት መርሃግብር ባሻገር በቻይና የስራ ተቋራጮች ግንባታቸው በመካሄድ ላይ የሚገኙ የመንገድ ፕሮጀክቶችን አስመልክቶ የምክክር ወርክ ሾፕ ተካሂዷል። በቻይና የስራ ተቋራጮች አማካኝነት ግንባታቸው በመካሄድ ላይ የሚገኙ የመንገድ ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ያጋጠሙ ችግሮችን እና መልካም ተሞክሮዎችን አስመልክቶ በኢመአ በኩል ለእንግዶቹ ሰፊ ገለፃ ተደርጎላቸዋል። የሥራ ተቋራጮቹ እያጋጠማቸው የሚገኙ ችግሮችን በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን በተለይም የወሰን ማስከበር፤ እንደ ሲሚንቶ ፣ ነዳጅ፣ ብረት እና ለግንባታ ግብአት ማምረቻ የሚውል ፈንጅ (explosive) እጥረት፣ የክፍያ መዘግየት (በተለይም የውጭ ምንዛሪ ክፍያ) እንዲሁም በአንዳንድ አካባቢዎች የሚስተዋሉ የፀጥታ ችግሮች እንዲፈቱላቸው ጠይቀዋል። ከመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶቹ ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ የማኔጅመንት አባላት ፣ እና በእንግዶቹ መካከል ሰፊ ውይይት ተካሂዶ አፈፃፀሙን ለማሻሻልና ግንኙነታቸውን ለማጠናከር የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

ባቱ - አርሲ ነገሌ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+3
ባቱ - አርሲ ነገሌ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

የባቱ - አርሲ ነገሌ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ አፈጻጸም ላይ ይገኛል ሃዋሳ፣ መጋቢት 6 ቀን 2015 ዓም (ኢመአ) ፡ የሞጆ - ሐዋሳ የፍጥነት መንገድ አካል የሆነውና የ 57 ኪ.ሜ ርዝማኔ ያለው የባቱ - አርሲ ነገሌ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ይገኛል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ ከኢመአ የተለያዩ ዲስትሪክቶች በመጡ መሃንዲሶች መሐንዲሶች የተጎበኘ ሲሆን የመንገድ ግንባታው በአሁኑ ወቅት ወደ 31 .7 ኪ .ሜ ያህል የአስፋልት ንጣፍ ተካሂዶለታል ፤ ይህም ከአጠቃላዩ ሲታይ የ 55 . 57 በመቶ ስራው እየተጠናቀቀ ይገኛል ፡፡ የባቱ - አርሲ ነጌሌ የፍጥነት መንገድ ግንባታን እያከናወነ የሚገኘው የእስራኤሉ SBI international holdings A.G /ኤስ ቢ አይ ኢንተርናሽናል ሆልዲንግስ ኤ.ጂ የስራ ተቋራጭ / ነው፡፡ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ኩንውሀ ኢንጂነሪንግ እና ኮንሰልቲንግ ከኮሪያ ኤክስፕረስ ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ እያከናወኑት ይገኛሉ፡፡ ለፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ አገልግሎት ላይ የሚውለው ብር 3308243 (ሶስት ቢሊየን ሶሰት መቶ ስምንት ሚሊየን ሁለት መቶ አርባ ሶስት ሺህ ብር) ከአለምባንክ በተገኘ ድጋፍ የተሸፈነ ነው፡፡ የፍጥነት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ የጎበኙት የየዲስትሪክቶቹ መሃንዲሶች ባገኙት ቴክኖሎጂያዊ የልምድ ልውውጥ እና ግንዛቤ መደሰታቸውን ገልጸዋል ፡፡ የሞጆ - ሀዋሳ የፍጥነት መንገድ አካል የሆኑት ኮንትራት አንድ ሞጆ - መቂ እንዲሁም ኮንትራት ሁለት መቂ - ባቱ ከዚህ ቀደም ግንባታቸው ተጠናቅቆ ለትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት መደረጋቸው የሚታወስ ነው ፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የፊቅ -ሐመሮ - ኢሚ ባሌ ምዕራፍ 2 አስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+4
የፊቅ -ሐመሮ - ኢሚ ባሌ ምዕራፍ 2 አስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

የፊቅ -ሐመሮ - ኢሚ ባሌ ምዕራፍ 2 አስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ተጠናቀቀ አዲስ አበባ፣መጋቢት 1 ፣ 2015(ኢመአ)፦ በሶማሌ ክልል የሚገኘው የፊቅ - ሐመሮ - ኢሚ ባሌ ምዕራፍ 2 (ኪ.ሜ 81 እስከ ኪ.ሜ 216) አስፋልት መንገድ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቀቀ። የመንገድ ፕሮጀክቱ፥135 ነጥብ 7 ኪ.ሜ ርዝማኔ ያለው ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት ደረጃውን በጠበቀ መልኩ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል። በግንባታው ከአስፋልት ንጣፍ፣ የፉካ ና የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ሥራዎች በተጨማሪ የአምስት ድልድይ መልሶ ግንባታ እና የስምንት ድልድዮች አነስተኛ ጥገና ሥራ ተከናውኗል። ግንባታውን ዓለም አቀፉ 'ቻይና ኮሙኒኬሽንስ ኮንስትራክሽን ካምፓኒ' አከናውኖታል። ለግንባታው የዋለው 1,540,036,614.16(አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ አርባ ሚሊዮን ሠላሳ ሥድስት ሺህ) ብር ወጪ በፌደራል መንግስት በጀት ነው የተሸፈነው። 'ቤስት ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ' ደግሞ የግንባታውን ጥራት በመቆጣጠርና በማማከር በኩል ተሳትፏል። የፕሮጀክቱ መጠናቀቅ የክልሉን የመንገድ መሠረተ-ልማት አውታር ከማስፋቱም ባሻገር ማኅበራዊ እና ኢኮሚያዊ ጠቀሜታው ከፍተኛ ነው። በዋናነትም ቀደም ሲል ከጅግጅጋ ኢሚ በጎዴ በኩል የነበረውን የ726 ኪ.ሜ የጉዞ ርቀት ወደ 418 ኪ.ሜ በማሳጠር፣ የኅብረተሰቡን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ በእጅጉ ያቀላል። በተጨማሪም የፊቅ፣ ሐመሮ እና ኢሚ አካባቢዎችን በቅርበት በማገናኘት፥ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን ያጠናክራል። በመስመሩ የሚገኙ ትንንሽ መንደሮችም ወደ ከተማነት የሚያድጉበትን ምቹ ዕድል ይፈጥራል። ፕሮጀክቱ መነሻውን ከአዲስ አበባ 741 ኪ.ሜ ርቀት ሐመሮ ወረዳ ላይ በማድረግ ኢሚ ወረዳ ድረስ ይዘልቃል። መንገዱ፥ በገጠር 10 ሜትር፣ በቀበሌ 14.8 ሜትር እንዲሁም በወረዳ 19 ሜትር የጎን ስፋት አለው። የዚሁ ፕሮጀክት ትስስር አካል የሆነው የፊቅ-ሐመሮ-ኢሚ ባሌ ምዕራፍ-1 ፊቅ-ኪ.ሜ 81 አስፋልት መንገድ ግንባታ በማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ የሚገኘ ሲሆን፥ ቀሪ ውስን የግንባታ ሥራዎችን በአንድ ወር ውስጥ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ነው። መንገዶቹ ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ ኅብረተሰቡ እና የየአካባቢው መስተዳድር አካላት የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ኢ.መ.አ ያሳስባል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኦሮሚያ ክልልን ከአማራ ክልል ጋር በመንገድ መሰረተ ልማት የሚያስተሳስረዉ የሙከጡሪ-ኮከብ መስክ አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት የግንባታዉ ዋና ዋና ስራዎች እየተገባደዱ ሲሆን ፣ የማጠቃለያ ስራዎችን ለመፈጸም በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። የሙከጡሪ-ኮከብ መስክ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ከአዲስ አበባ ጎጃም ከሚወስደዉ ዋና አዉራ ጎዳና ጋር የሚያገናኝ መንገድ ነው፡፡ መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ለአካባቢዉን ህብረተሰብ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ከፍተኛ የሆነ ፋይዳ ይኖረዋል፡፡ አካባቢው በጤፍ ፣ ማሽላ እና ስንዴ አምራችነቱ የሚታወቅ ሲሆን ፣ የአካባቢው አርሶ አደሮች እና ነጋዴዎች ይህን ምርት በፍጥነት ወደ ገበያ ለማቅረብ ያስችላቸዋል ተብሎ ይታመናል፡፡ ቀደም ሲል የነበረዉ የመንገዱ ገፅታ በጠጠር ደረጃ የነበር ሲሆን ፣ ለትራንስፖርት አስቸጋሪ የነበር እና ህብረተሰቡን ለበርካታ እንግልት የዳረገ ነበር፡፡ አሁን ላይ ይህ ፕሮጀክት በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል፡፡ የመንገዱ አጠቃላይ ርዝማኔ 58 ኪሜ ሲሆን፣ 53 ኪሜ አስፋልት ንጣፍ ስራው ተጠናቋል፡፡ የተቀረዉ 5 ኪሎሜትር አስፋልት ንጣፍ ስራም በቅርቡ ይጠናቀቃል፡፡ የዚህ መንገድ ግንባታ የመንገድ ትከሻን ጨምሮ በገጠር 10 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር እና በወረዳ 21 ሜትር የጎን ስፋት አለዉ፡፡ ለግንባታው የተመደበው በጀት ብር 768,622,711.45 ሲሆን ፣ ወጪውም ሙሉ በሙሉ የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው። መንገዱን እየገነባ የሚገኘዉ ቻይና ሬይልዌይ ቁጥር ሶስት ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ሲሆን ፣ የማማከርና ቁጥጥር ስራዉን ደግሞ ኤልዳ ኢንጂነሪንግ እና ዳምራ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ በጣምራ እያከናወኑት ይገኛሉ። ከዚህም ባሻገር በአካባቢው የመሃልሜዳ-አቡስ እና የአቡስ-አለም ከተማ አስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪም ከዚሁ የሙከጡሪ-ኮከብ መስክ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ባሻገር የኮከብ መስክ ዓለም ከተማ ፣ የአለም ከተማ-ደጎሎ እና የደብረብርሃን-ጅሁር-ደነባ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች እየተካሄዱ ነው፡፡ የእነዚህ መንገዶች መገንባት ከዚህ ቀደም በአካባቢው ይስተዋል የነበረውን የትራንስፖርት ችግር የሚቀርፍ ከመሆንም ባሻገር ከአካባቢው ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ አገልግሎት ይሰጥ ለነበረው የሙከጡሪ መስመር እንደ አማራጭ ሆኖ ያገለግላል፡፡

የጎዴ-ቀላፎ-ፈረፈር ሎት-1 አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+3
የጎዴ-ቀላፎ-ፈረፈር ሎት-1 አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

የጎዴ-ቀላፎ-ፈረፈር ሎት-1 አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ አፈጻጸም 46 ነጥብ 5 በመቶ ላይ ደርሷል! ጎዴ፣ የካቲት 24፣ 2015(ኢመአ):- በሶማሌ ክልል ሸበሌ ዞን እየተገነባ የሚገኘው የጎዴ-ቀላፎ-ፈረፈር ሎት-1 94 ነጥብ 8 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ አፈጻጸም 46 ነጥብ 5 በመቶ ላይ ደርሷል፡፡ በአንድ ወር ውስጥም ወደ አስፋልት የማንጠፍ ምዕራፍ ለመሸጋገር የሚያስችል የአስፋልት ፕላንት ተተክሎ ዝግጅት እየተደረገ ነው። ከግንባታ ሥራው መካከልም የጠጠር መፍጫ ማሽን በመትከል ለግንባታ ግብዓትነት የሚውሉ ምርቶች እንደ የአርማታ ጠጠር፣ ቤዝ ኮርስ እና የአስፋልት ጠጠር የማምረት ስራ፣ የአፈር ቆረጣና ሙሌት ስራዎች ፣ የሰብ ቤዝ ስራ፣ የአነስተኛ የውኃ መተላለፊያ ቱቦዎች፣ ስላብ ከልቨርቶች እና የድልድይ ግንባታዎች በመካሔድ ላይ ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪም የግንባታ ሥራው የትራፊክ እንቅስቃሴውን እንዳያውክ የተለዋጭ መንገድ ተገንብቶ አገልግሎት እየሰጠ ነው። ኢ መ አ በግንባታው ወቅት የሚገጥሙ ውስንነቶችን በመለየት አስፋላጊውን ድጋፍ እና ክትትል እያደረገ ይገኛል። ግንባታውን በማከናወን ላይ የሚገኘው ዓለም-አቀፉ ቻይና ሬይል ዌይ ሰቨንዝ ግሩፕ ነው። ለግንባታው የሚውለው 1,530,000,000.00 (አንድ ቢልዮን አምስት መቶ ሰላሳ ሚሊዮን) ብር ወጪ በፌደራል መንግስት በጀት ነው የተሸፈነው። ፕሮጀክቱን በማማከር እና በመቆጣጠር በኩል ስታድያ የምህንድስና ሥራዎች አማካሪ ኃላ/የተ/ የግል ማኅበር ከንዑስ አማካሪ ጂ እና ዋይ ኢንጂነሪንግ ኮንሰልት ኃላ/የተ/ የግል ማኅበር በጣምራ እየሰሩ ነው። ፕሮጀክቱ እውን ሲሆን የክልሉን የመንገድ መሠረተ ልማት አውታር ከማስፋቱም ባሻገር በመስመሩ የሚገኙትን የጎዴ እና ቀላፎ ከተሞች ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ያሳልጣል። በመንገድ ክልል ውስጥ የሚገኙትን አነስተኛ መንደሮች ወደ ከተማ የሚያድጉበትን ምቹ አጋጣሚን ይፈጥራል። የሸበሌን ወንዝ ተከትለው የሚመረቱትን የግብርና ምርቶች በጥራትና ፍጥነት ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማድረስ የአርሶ አደሩን ተጥቃሚነት ያሰፋል። እንዲሁም በፍየል፣ ግመል እንዲሁም በመሰል የቁም እንስሳት ንግድ ላይ ለተሰማሩ ግለሰቦች ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። መንገዱ በቀበሌ 12 ሜትር ፣ በወረዳ ከተማ 19 ሜትር እና በዞን ከተማ 21.5 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

በወልዲያ ከተማ እየተሰራ በሚገኘው የመንገድ ግንባታ ዙሪያ ከማህበረሰቡ ጋር ውይይት ተካሄደ። በውይይቱ መድረኩ የወልዲያ ከተማ ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራር ፣ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮምቦልቻ
+6
በወልዲያ ከተማ እየተሰራ በሚገኘው የመንገድ ግንባታ ዙሪያ ከማህበረሰቡ ጋር ውይይት ተካሄደ። በውይይቱ መድረኩ የወልዲያ ከተማ ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራር ፣ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮምቦልቻ እና አካባቢው ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ፅ/ቤት ሃላፊ ኢንጂነር ተስፋዬ አንተንይስሙ ፣ አማካሪ ማህንዲሶች ፣ የከተማው ነዋሪዎች እና የአገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል። በውይይቱ ወቅት የመንገዱ ግንባታ ሂደት መዘግየት የከተማዋን ነዋሪዎች ለበርካታ ችግሮች እንደዳረጋቸው በተሳታፊዎቹ በኩል ተገልጿል። የወልዲያ ከተማ ተለዋጭ የመንገድ ግንባታ በወሰን ማስከበር ችግር እና በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በነበረው ጦርነት ምክንያት የግንባታ ሂደቱ መስተጓጎሉ ይታወቃል። በቅርቡ የተደረገውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ በአሁኑ ወቅት የግንባታ እንቅስቃሴው ተጀምሯል። በእስካሁኑ የግንባታ እንቅስቃሴ የስትራክቸር ፣ የመንገድ አካፋይ ፣ የቆረጣ እና የአፈር ሙሌት ስራዎች የተከናወኑ ሲሆን ፣ የቤዝ ኮርስ ማንጠፍ ስራም ተጀምሯል። በተጨማሪ የአስፋልት ንጣፍ ስራ በቅርቡ ይጀመራል። መንገዱ በአጠቃላይ 7.3 ኪ.ሜ ርዝማኔ ያለው ሲሆን ፣ የመንገድ ትከሻን ጨምሮ የጎን ስፋቱ 30 ሜትር ነው። ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በወልዲያ ከተማ የሚስተዋለውን የትራፊክ መጨናነቅ ከመቅረፍ ባሻገር ለከተማዋ ልዩ ውበትን ያጎናፅፋል። በአሁኑ ወቅት የመንገዱን ግንባታ በማካሄድ ላይ የሚገኘው በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮምቦልቻ ዲስትሪክት ነው። መንገዱ በፍጥነት እና በተገቢው የጥራት ደረጃ ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ ለማስቻል አስፈላጊውን ትብብር እንደሚያደርጉ በወቅቱ ያነጋገርናቸው የከተማው ነዋሪዎች ገልፀዋል።