fa
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

رفتن به کانال در Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

کانال ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 13 369 مشترک است و جایگاه 1 753 را در دسته حمل و نقل و رتبه 2 530 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 13 369 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 20 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 129 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 8 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 38.47% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.24% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 143 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 037 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 11 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 21 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته حمل و نقل تبدیل کرده‌اند.

13 369
مشترکین
+824 ساعت
+697 روز
+12930 روز
آرشیو پست ها
መልካአ ምድራዊ አቀማመጡ አስቸጋሪ የሆነው የሞጣ-ጃራጌዶ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ወደ አስፋልንት ንጣፍ ስራ ተሸጋገረ ። እስካሁን በተሰራው ስራም 22 ኬሎሜትሩ ሙሉ ለሙሉ በአሰፋልት ንጣፍ ስራ ተሸፍኗል ። እንዲሁም የተራራ እና የአፈር ቆረጣ ስራዎች የመሬት ጠረጋ ድልዳሎ ፣የሰብ ቤዝ፣የቤዝ ኮርስ፣የውሀ ማፋሰሻ መስመር ትቦዎች ቀበራ ተከናውኗል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ 58.ኪሎ ሜትር እርዝመት ያለው ሲሆን በወረዳ 14 ሜትር እና በገጠር 7 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል፡፡ ከአጠቃላይ ስራው ውስጥ 69 በመቶው የሚሆነው ግንባታ የተጠናቀቀው የመንገድ ፕሮጀክቱ ከሞጣ ከተማ ተነስቶ ጃራጌዶ ከተማ ላይ የሚያበቃ ነው፡፡ በመንግስት በተመደበ አንድ ቢሊየን 640ሚሊየን ብር በላይ ነው ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘው ። በተለይም ፕሮጀክቱ በአባይ ወንዝ ላይ የሚገነባ ድልድይ አካቶ የያዘ በመሆኑ የድልድዩ ቋሚ ተሸካሚ የመሰረት ቁፋሮ (pile foundation excavation) እየተሰራ ነው። ድልደዩ ተገንብቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ እንደአማራጭ መሸጋገሪያ የሚያገለግል ጊዜያዊ ድልድይ ተሰርቶ ተጠናቋል፡፡ የመንገዱን ግንባታ እያከናወነ የሚገኘው ዞሆንግሚ ጄቲኢጂሲ ኮንሶርቲየም (Zhongmi-JTEGC Consortium) የተባለ አለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃ.የተ.የግ.ማ እየተከታተለው ይገኛል፡፡ የሞጣ-ጃራጌዶ የመንገድ ፕሮጀክት ተሰርቶ ሲጠናቀቅ ምስራቅ ጎጃም ዞን የሚገኘውን ሁለት እጁ እነሴ ወረዳን ከደቡብ ጎንደር ዞን ከሚገኘው አንዳቤት ወረዳ ያገናኛል፡፡ እንዲሁም በክልሉ የሚመረቱትን የጤፍ፣የበቆሎ እና የበርበሬ ምርቶችን በተቀላጠፈ መልኩ በማጓጓዝ የአካባቢው አርሶ አደር ካመረተው ምርት ተጠቃሚ እንዲሆን ያስችለዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም መንገዱ ከዚህ ቀደም ያልነበረና አዲስ እየተሰራ የሚገኝ በመሆኑ የመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽነትን በማስፋት የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ወደላቀ ደረጃ ያሸጋግራል፡፡

የጌዶ - መነቤኛ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+2
የጌዶ - መነቤኛ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

የጌዶ-መነቤኛ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመልካም አፈጻጸም ላይ ነው። 80 ኪ. ሜትር የሚረዝመው ይህው ፕሮጀከት በእስካሁኑ ክንውን 32 ኪ. ሜትሩ በአስፋልት ንጣፍ ስራ ተሸፍኗል። ቀሪ ስራዎችም ለአሰፋልት ንጣፍ ዝግጁ እየሆኑ ሲሆን በቀጣይ አመት ዋና ዋና የመንገድ ግንባታ ስራዎችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናል። የአፈር ሙሌትና፣ ድልዳሎ፣የውሃ መፋሰሻ ቱቦ ቀበራ የሰብ ቤዝ ስራ እንዲሁም የቤዝ ኮርስ ማምረት ስራዎች በመካሄድ ላይ ይገኛል። የጌዶ -መነበኛ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት በዘጠኝ መቶ አርባ ሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተገነባ ያለ መንገድ ነው። ግንባታውን የሚያካሂደው ሲኖሃይድሮ ኮርፖሬሽን የተባለ የቻይና አለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ ድርጅት ሲሆን ፤ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ሀዪውይ ኢንጂነሪንግ እና ኮንሰልቲንግ እየሰሩ ነው። በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ እና ሆሮ ጉድሩ ዞኖች ውስጥ የሚገኘው የጌዶ-መነቤኛ መንገድ ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ የነበረና ለትራንስፖርት ምልልስ አሰቸጋሪ የነበረ ነው። አካባቢው ያሉት ልዩ ልዩ ጸጋዎች ከማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ አኳያ እንዲሁም ከከተማው ቀጣይ አድገት አንጻር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ነው። ይኸው የመንገድ ፕሮጀክት የጎን ስፋት በከተማ እና በወረዳ 16 ሜትር፣ በቀበሌ 15.9 ሜትር ሲሆን በገጠር 10 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተሰራ ነው። በተጨማሪም ግንባታው በውስጡ የመንገድ አካፋይ ፣ የእግረኛ መሄጃ እና የመንገድ አቃፊ ትከሻ በግራ እና በቀኝ ያካተተም ይሆናል ፡፡ ከአዲስ አበባ -ነቀምቴ-አሶሳ ዋና መንገድ በመገንጠል በግብርና ምርት የሚታወቀውን ምዕራባዊ የኢትዮጵያ ክፍልን ተጠቃሚ የሚያደርገው የጌዶ-መነቤኛ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ሲጠናቀቅ፦ በአካባቢው በስፋት የሚገኘውን ከፍተኛ የሰብል ምርቶች ጤፍ ፣ ድንች ፣ ስንዴ ፣ባቄላ በተጨማሪም እንስሳትንና የእንስሳት ተዋጽኦችን ወደ ማዕከላዊ ገበያ በተሻለ ዋጋ በመሸጥ አምራች እና ሸማቹን ተጠቃሚ ያደርጋቸዋል። የፊንጫ የስኳር ፋብሪካ ምርትን ምቹ የሆነ ትራንስፖርትን ተጠቅሞ ወደ መሀል ከተማ ገበያ በማድረስ የስኳር ኢንደስትሪውን እንዲያድግ ከፍተኛ ሚናን ይጫወታል ። በአሁን ሰዓት ከጌዶ - መነበኛ 80.5 ኪ. ሜትሩን መንገድ በተሸከርካሪ ለመጓዝ ከ 3 ሰዓት በላይ የሚጠይቅ ሲሆን ግንባታው በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ሲጠናቀቅ የትራንስፖርት ጊዜን በአማካኝ ከግማሽ በላይ ያሳጥረዋል።

በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ እንደሚሆን የሚጠበቀው የኢመባ የምርምር የልህቀት ማዕከል ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ ነው ። የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮችም የምርምር ማዕከሉን የግንባታ እንቅስቃሴ በመመለክት ቀጣይ የ
+1
በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ እንደሚሆን የሚጠበቀው የኢመባ የምርምር የልህቀት ማዕከል ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ ነው ። የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮችም የምርምር ማዕከሉን የግንባታ እንቅስቃሴ በመመለክት ቀጣይ የስራ አቅጣጫንም አስቀምጠዋል። ዓለም አቀፍ የምርምር ደረጃዎችን አሟልቶ እየተገነባ የሚገኘው ይህው የኢመባ የምርምር የልህቀት ማዕከል ዋና ዋና የግንባታ ስራዎቹ እየተጠናቀቁ ሲሆን ቀሪ ክንውኖችን ለመፈጸምም በትኩረት እየተሰራ ነው። በመስክ ምልከታውም የላቡራቶሪ የግንባታ ስፍራዎች የቢሮ እና የመሰበሰቢያ አዳራሽ ፣ የተመራማሪዎች የአፓርትመንት፣ የእንግዳ ማረፊያንና የሰራተኞች ሬሰቶራንት ግንባታ ተጠናቋል። ቅጥረ- ግቢውን የማስዋብ ፤ቀሪ ውጫዊ እና ውስጣዊ የህንጻ የማጠናቀቅ ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቁም ይጠበቃል። ይህ የምርምር ማዕከል በዘመናዊ መልኩ ይበልጥ መደራጀቱ የመንገድ ሀብትን ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ ለመምራት፤ ለመሰተዳደርና ለመገንባት የላቀ አበርክቶትን የሚችር ነው። የሀገራችን የመንገድ አውታር የታሰበላቸውን የአገልግሎት ጊዜ እንዲሰጡ ያስችል ዘንድ ማዕከሉ ሳይንሳዊ ጥናቶችን በማበርከት ሚናው የላቀ ነው። በቀጣይ ውስን በሆኑ አፍሪካ አገራት ብቻ የሚገኙ የምርምር መሳሪያዎችን የሚያሟላ ይሆናል። የፐርፎማንስ ግሬድ አማራጭ ዲዛይን ቴክኖሎጂን ለመጠቀም የሚያስችል ዘመናዊ የፍተሻ መሳሪያዎች የሚኖሩት በመሆኑ በብዙ አፍሪካ ሀገራትም ተመራጭ የምርምር ማዕከልም ያደረገዋል ። ማዕከሉ የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራን እንዲሁም ለግንባታ እና ለጥገና ፕሮጀክቶች ከመሬት መንሸራተት ጋር ተያይዞ ለሚከሰት ችግሮች የቴክኒክ ድጋፍ እና የግብአት ፍተሻ አገልግሎት ከመስጠቱም ባለፈ ለዩኒቨርስቲዎችና ለተቋማትም የማማከር አገልግሎት የመሰጠቱን ስራ አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ፡፡

የቱርሚ-ኦሞ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ስራ ተጠናቆ ሙሉ ለሙሉ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ሊጀምር ነው፡፡ 56.71 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ይህ መንገድ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የተገነባ ሲ
+3
የቱርሚ-ኦሞ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ስራ ተጠናቆ ሙሉ ለሙሉ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ሊጀምር ነው፡፡ 56.71 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ይህ መንገድ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የተገነባ ሲሆን በአሁኑ ወቅት 97 በመቶ የሚሆነው ስራ ተጠናቆ የማጠቃለያ ስራዎች እየተከናወኑ ነው ፡፡ በብር 897,005,974.6 ወጪ የተገነባው ይህ መንገድ በጀቱ በኢትየጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡ መንገዱ በገጠር 10 ሜትር እና በወረዳ 14 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ነው ፡፡ የግንባታ ስራውን ራማ እና አፍሮ ፂዮን ኮንስትራክሽን በጥምረት በመሆን ነው የገነቡት ፡፡ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ስታዲያ ኢንጅነሪንግ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ሰርቶታል፡፡ መንገዱ በዋናነት የቱርሚ ከተማን ከካንጋቴ ከተማ ጋር በማገናኘት ጊዜን የቆጠበ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲኖር ያደርጋል፡፡ ከዚህ ቀደም በአካባቢው ህብረተሰብ ላይ በክረምት እና በበጋ ወቅት በአቧራ እና በጭቃ ይደርስባቸው የነበረውን የጤና ችግር እንዲሁም ከፍተኛ የጉዞ እንግልት ያስቀራል፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው የሚገኝ የስኳር ፋብሪካ ምርቱን መንገዱን በመጠቀም በቀላሉ ወደ መሀል ሀገር መጓጓዝ እንዲችል በማድረግ እረገድ ሚናው የላቀ ነው። ከጎረቤት ሀገር ኬኒያ ጋር በማሰተሳሰር እረገድም ፋይዳው የጎላ ነው። እንዲሁም በአካባቢው የሚገኘውን የቱሪስት መዳረሻ ስፍራን ለማየት ለሚመጡ ቱሪስቶች የመንገዱ መሰራት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡

የሞጆ-መቂ-ባቱ የፍጥነት መንገድን እና በቀጣይ እውን የሚሆኑ ፕሮጀክቶች የምስራቅ አፍሪካን እና አካባቢውን የንግድ ትስስር በማቀላጠፍ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን የሚያረጋግጥ ነው አሉ የላፕሴት (LAPSSE
+6
የሞጆ-መቂ-ባቱ የፍጥነት መንገድን እና በቀጣይ እውን የሚሆኑ ፕሮጀክቶች የምስራቅ አፍሪካን እና አካባቢውን የንግድ ትስስር በማቀላጠፍ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን የሚያረጋግጥ ነው አሉ የላፕሴት (LAPSSET) አባል ሀገራት የልዑካን ብድን አባላት ። የየሀገራቱ የልዑካን ቡድን አባላት በቅርቡ ግንባታው የተጠናቀቀውን የምዕራፍ አንድ የሞጆ-መቂ-ባቱ የፍጥነት መንገድን ጎብኝተዋል። በመርሃ- ግብሩ ላይም የትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታዎች አቶ ካሳሁን ጎፌ እና አቶ የኋላሸት ጀመረ ፤የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኘ የየተቋማቱ አመራሮች ለልኡካን ቡድኑ ገለጻ እና ማብራሪያ ሰተዋል። የፍጥነት መንገዱ የአዲስ አበባ-ሞያሌ-ናይሮቢ-ሞምባሳ የመንገድ ኮሪደር አካል በመሆኑ የቀጠናውን ሁለተናዊ ትስስር በማጎለበት እረገድ የላቀ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል ። የአባል ሀገራቱን የኮሪደር ፕሮጀክቶች በመሠረተ ልማት ለማስተሳሰር በታቀደው መሰረት መተግበሩ ከተሞክሮነት በዘለለ የንግድ ትስስር በማቀላጠፍ ለሁለንተናዊ እድገት የሚኖረው ፋይዳ ትልቅ እንደሆነ አብራርተዋል ። በአፍሪካ ቀጠናዊ ነጻ የንግድ ስርዓት ለመፍጠር የተጀመረውን ጉዞ በእጅጉ ይደግፋልም ብለዋል፡፡ የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክንም የጎበኙት የልኡካን ብድን አባላቱ በፈጣን መንገድ መስመር ላይ የሚገኝ በመሆኑ ከኢትዮጵያ እስከ ሞያሌ ድረስ የመንገድ መሠረተ ልማት ግንባታ የተጠናቀቀ እና የሞያሌ የፍተሻ ጣቢያ (One Stop Boarder Post) አገልግሎት የጀመረ በመሆኑ ለሀገራቱ የኢኮኖሚ እድገት አሰተዋጾ የላቀ መሆኑን ተናግረዋል።

ነቀምት - ሶጌ - ካማሽ - ቆንጮ የመንገድ ፕሮጀክት አጠቃላይ መረጃ የፕሮጀክቱ ስም ኮንትራት 1 ኪ.ሜ. 00 – ኪ.ሜ. 104.8 ርዝመት 104.8 ኪ.ሜ. ግንባታውን የሚያከናውነው የስራ ተቋራጭ ገምሹ በየነ ኮንስትራክሽን ኃ/ የተ/የግ/ማ አማካሪ ድርጅት የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን እና ቁጥጥር ስራዎች ድርጅት ለግንባታው የተመደበው የገንዘብ መጠን 2,359,484,513.18 ብር ለግንባታው የሚውለው ወጪ የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ግንባታውን ለማከናወን የተሰጠው ጊዜ 3 ዓመት የመንገዱ የሚያልፍባቸው ከተማ፣ ወረዳ እና ቀበሌ » ከተማ ነቀምት » ወረዳ ሳሲጋ፣ ሶጌ » ቀበሌ ገባሰንበታ፣ ደንቢ ሰፈራ፣ ቢሎ፣ አንገር ደዲሳ፣ ሶስተኛ ካንፕ፣ አንገረ ሰፈራ፣ ሊኩ ኮንቢ ፣ ሁለተኛቤሎ ፣ ቢች ቢች ፣ ሃሙስ ገበያ እና ሃሮ ደዲሳ የመንገዱ የሚገነባበት መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ » ሜዳማ 39.92% » ወጣ ገባ 45.68% » ተራራማ 9.17% » ገደላማ 4.13% የፕሮጀክቱ ስም ኮንትራት 2 ኪ.ሜ. 104.8 – ኪ.ሜ. 160 ርዝመት 55.2 ኪ.ሜ. ግንባታውን የሚያከናውነው ስራ ተቋራጭ ገምሹ በየነ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማ አማካሪ ድርጅት የኢትዮጵያ አይ ዲ ኮን ኢንፍራስትራክቸር ዲቨሎፕመንት አማካሪዎች ኃ/የተ/የግ/ማ ለግንባታው የተመበደበው የገንዘብ መጠን 1,923,629,581.78 ብር ለግንባታ የሚውለው ወጪ የሚሸፍነው በኢትዮጵያ መንግስት ግንባታውን ለማከናወን የተሰጠው ጊዜ 3 ዓመት የመንገዱ የሚያልፍባቸው ወረዳ እና ቀበሌ » የወረዳ ከተማ ከማሺ » ቀበሌ ሄና፣ ጊልጊላ፣ ሚርሚታ፣ ጃዛለኩ፣ ሺመላኩኖ፣ አጋሎሜቲ እና አቴሜቲ የመንገዱ የሚገነባበት መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ » ወጣ ገባ 45.83% » ተራራማ 11.23% » ገደላማ 42.93% በመንገድ ግንባታ ወቅት የሚካተቱ ሥራዎች » የዲዛይን ሥራ » የዋና መንገድ ጠረጋ » የአፈር ቆረጣና ሙሌት ሥራ » የድልድይ እና አነስተኛ የውሃ መተላለፊያ/መፋሰሻ ቦይ ግንባታ/ » የመንገድ ዳር ትራፊክ ምልክቶች ተከላ ሥራ » የአፈር መከላትን መከላከያ ግንብ ስራ እና የጋቢዮን ስራ » የአነስተኛ እና መካከለኛ የውሀ መተላለፊያ /መፋሰሻ ቱቦች ስራ » በርካታ የስትራክቸር ስራዎች » በግንባታ ወቅት የትራንስፖርት መስተጓጎልን ለመቅረፍ ተለዋጭ መንገዶችን እንደአስፈላጊነቱ መገንባት » የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ንጣፍ ሥራ የግንባታው አንድምታዊ ጠቀሜታዎች? ከኢኮኖሚ ዕይታ » ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዋልታ የሆነው የቡና ምርት በስፋት አካባቢው ላይ ስለሚገኝ የመንገዱ መጠናቀቅ ይህንን ሀብት ወደ ማዕከላዊ ገበያም ሆነ ወደ ውጪ ልኮ የውጪ ምንዛሬን ከማስገኘት አኳያ መጠነ ሰፊ ፋይዳ አለው። » በግንባታው ወቅት ከሁለት ሺ በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ሕብረተሰብ ሰፊ የሥራ ዕድልን ይፈጥራል። » በመዓድን ቁፋሮ ለተሰማሩት የአካባቢው ነዋሪዎች መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ከአዲስ አበባ - ነቀምት - ጊምቢ - አሶሳ ጋር ስለሚያገናኝ አማራጭ መንገድን ተጠቅመው ያወጡትን ማዕድን በፍጥነት ወደ ማዕከላዊ ገበያም ሆነ ወደ ውጪ በማቅረብ የሀገር ኢኮኖሚው እንዲያድግ ጉልህ ሚና ይጫወታል። » በመንገዱ መጎዳት ሳቢያ ለተሸከርካሪ መለዋወጫ ይወጣ የነበረ አላስፈላጊ ወጪን ከመቀነሱም ባሻገር ይወስድ የነበረውን የነዳጅ ፍጆታ በመቀነስ የውጭ ምንዛሬን ማስቀረት ይቻላል ፡፡ » የአካባቢው አፈር ለም በመሆኑ የመንገድ ምቹ አለመሆን ይዞት የነበረውን ባለሀብት ቦታውን ለኢንቨስት ተመራጭ በማድረግ የሀገሪቱን እድገት ያፋጥናል። » የትራንስፖርት ጊዜን በማሳጠር የሁለቱን ክልሎች ህዝብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በይበልጥ ያረጋግጣል፡፡ » የመንገዱ መገንባት በመስመሩ ላሉ ትንንሽ መንደሮች ወደ ከተማ እንዲያድጉ ይበልጥ የኢኮኖሚ መነቃቃትን ይፈጥርላቸዋል፡፡ የትራንስፖርት ችግርን በመቅርፍ የሁለቱን ክልሎች ህዝብ ተሸከርካራዎችን ተጠቅመው በተመጣጣኝ ዋጋ ወደ ፈለጉት ቦታ የሚንቀሳቀሱበትን ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ የቱሪዝም ጸጋዎችን ከመጠቀም አንጻር » ነቀምት ውስጥ የሚገኘውን በ1870 የተገነባውን የደጃዝማች ኩምሳ ሞረዳ ቤተ-መንግስት ለማየት ለሚመጡት ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጭ ጎብኝዎች ምቹ ሁኔታን ከመፍጠሩም ባሻገር ለአካባቢው ወጣቶች ተጨማሪ የስራ ዕድል በመፍጠር የራሳቸውን ገቢ ማሳደግ ያስችላል። » የወለጋ ሙዚየምን ለመጎብኘት በመንገዱ መሰራት ምክንያት ተጨማሪ ቱሪስቶች ከሃገር ውስጥም ሆነ ከውጪ ምቹ በሆነ አስፋልት ኮንክሪት መነገድ እንዲመጣ ያስችላል። » በመንገድ እጦት ምክንያት ትኩረት ያልተሰጣቸውን በሳሲጋ ወረዳ ውስጥ የሚገኙትን ታሪካዊ ስፍራዎች እንደ የጊዳ ጊሊንዴ ዋሻ እና የሶሮጋ ግድብን የመንገዱ ግንባታ ሲጠናቀቅ የቱሪዝም ዘርፉን ያሳድገዋል። » በአጠቃላይ የሀገሪቱን ቱሪዝም እድገት በማፋጠን የውጭ ምንዛሬን ከማስገኘቱም ባለፈ በመንገዱ ዙሪያ ለሚገኙ ማህበረሰቦች የቱሪዝም መስህቦቸን ለማስጎብኘት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። ከማህበራዊ ዕይታ » የመንገዱ ግንባታ በሚጠናቀቅበት ወቅት በዋነኝነት የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልልን እና የኦሮሚያ ክልልን በአስፋልት ኮንክሪት መንገድ በማስተሳሰር የሁለቱን ክልል ህዝቦች ማህበራዊ መስተጋብር ያጠናክራል። » በመስመሩ የሚገኙ ዞኖች እና ወረዳዎች እንዲሁም ከ26 በላይ የሚሆኑ ቀበሌዎችን በአስፋልት ኮንክሪት መንገድ በቅርበት ያስተሳስራል። » መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የሁለቱን ክልል ህዝቦች በቀላሉ ትራንስፖርትን ተጠቅመው በአቅራቢያው ባሉት የጤና፣ የትምህርት እና ሌሎች ማህበራዊ ተቋዋማት ግልጋሎት ማግኘት ያስችላል። » አዳዲስ ትምህርትቤቶች የመገበያያ ቦታዎች የጤና ተቋማት እንዲሁም ሌሎች አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶችን ተደራሽነት በእጅጉ ያስፋፋል። » በመንገዱ ዙሪያ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በቀላሉ ምርታቸውን በአቅራቢያቸው ወደ ሚገኘው ከተማም ሆነ ክልል ወስደው በመሸጥ ገቢያቸውን ያሻሽላሉ። ከግብርና ዕይታ » በአካባቢው በስፋት የሚገኘውን የግብርና ምርቶች እንደ ጤፍ፣ ገብስ፣ በቆሎ ምርቶችን እንዲሁም የቀንድ ከብቶችን ትራንስፖርትን ተጠቅመው ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማድረስ ነዋሪው ከምርታቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል፡፡ » አርሶአደሩ ከገበያ ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ አጠናክሮ በማስተሳሰር የውጭ ምንዛሪ ማፍራትና የአምራቹንና የሸማቹን ህብረተሰብ ገበያ በማረጋጋት መንገዱ የምርትና ምርታማነት ዕድገት እንዲመጣ አስተዋጽኦ ያደርጋል። » የተለያዩ ዘመናዊ የግብርና ግብዓቶችን ትራንስፖርትን በተመጣጣኝ ዋጋ በመጠቀም ወደ አካባቢው በማድረስ የአከባቢውን የግብርና ሁኔታ ለማዘመን እድል ይፈጥራል። » መዳበሪያና ምርጥ ዘር ለገበሬው በቀላሉ ማድረስ ያስችላል። » ሁለቱን ክልሎች ከማገናኘቱ አንፃር በክልሎቹ መካከል የግብርና ልምድ ተሞክሮ ልውውጥ እንዲኖር ያስችላል።

ከ4.2 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ኦሮሚያ እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልልን የሚያስተሳስረው የነቀምት - ሶጌ-ካማሽ-ቆንጮ 160 ኪ.ሜ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ስራ ዛሬ ተጀመረ፡፡ በነቀምቴ ከተማ በተከናወነዉ፣ በዚሁ  የመንገድ ግንባታ ማስጀመር መርሀ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ምክትል ዋና የዳይሬክተር ኢንጅነር መሀመድ አቡድራማንጨምሮ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል ባለሥልጣናት ታድመዋል ። ፕሮጅክቱ የህዝቦቹን  የበርካታ አመታት የመሰረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ ከመስጠቱም ባሻገር በመንገድ መሰረት ልማት እጥረት ተራርቀው የሚገኙ  ሁለቱን ወንድማማች ህዝቦች ይበልጥ የሚያቀራርብ መሆኑን አቶ ሽመልስ  ተናግረዋል። የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊህ ሀሰን በበኩላቸው የመንገዱ መገንባት ለሁለቱም ክልሎች ያለውን ሁለንተናዊ ጠቀሜታን ገልጸዋል፣ አካባቢው ቡናን ጨምሮ በተለያዩ የተፈጥሮ ፀጋዎች የታደለ በመሆኑ የመንገዱ መገንባት በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የላቀ ድርሻ ይኖረዋልብለመዋል የስራ ሃላፊዎቹ ።  መንገዱ የሚገነባበት አካባቢ የወንዞች ተፋሰስ መገኛ በመሆኑ በቀጣይ ሜክናይዝድ ግብርና ለማካሄድ የመንገድ መገንባት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራልም ብለዋል። ክልሎቹን አቋርጦ የሚያልፍ በመሆኑም  የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻ ገጸ በረከቶችን የታደለ በመሆኑ የመንገዱ መገንባት ሀገሪቷ ከቱሪዝም ለምታገኘው ገቢ ፋይዳውን የላቀ ያደርገዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሃመድ አቡድራማን በበኩላቸው  ይህንን ወሳኝ ፕሮጀክት በተቀመጠለት  የጊዜ ገደብነና በተያዘለት የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቅ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በትኩረት እንደሚከታተለው አረጋግጠዋል ። ለፕሮጀክቱ መሳካት የማህበረሰቡ ትብብር ወሳኝ መሆኑን ገልፀው አስፈላጊውን  ድጋፍና ትብብር እንዲያደርግ አደራ ብለዋል የሰብል ምርት መገኛ የቡና እና የቅመማ ቅመም ሀብቶች ማብቀያ የማር የአትክልትና ፍራፍሬም ምርቶች በስፋት የሚመረትበት መሆኑን ጠቅሰው ይህን የላቀ ሃብት ወደ ማዕከላዊ እና አለምአቀፍ ገበያ በማድረስ የሀገሪቱን የወጪ ንግድ በማሳደግ በኩል አስተዋፅኦው የጎላ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪም አካባቢው በማዕድን ሀብት የበለፀገ በመሆኑ በዘርፉ ለተሰማሩት የማዕድን አውጭዎች እና ባለሀብቶች የመንገድ መገንባት የተለየ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብሐዋል ። የግንባታ ስራውን የሚያካሂደው ገምሹ በየነ ኮንስትራክሽን ኋ/የተ/የግ/ማ የተባለ አገር በቀል የስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው፡፡ የመንገዱን ጥራት ቁጥጥር እና የማማከር ስራዎችን የሚያከናውነው ደግሞ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን እና ቁጥጥር ስራዎች ድርጅት ነው። የግንባታዉ ወጪው የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡ ፕሮጀክቱ በሶስት አመታት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ። መንገዱ በገጠር ከ8-10 ሜትር ߹በቀበሌ 12 ሜትር፣በወረዳ የእግረኛ መንገድን አካቶ ከ19-24 ሜትር የጉን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ይገነባል።0

በ 672 ሚሊዮን ብር ወጪ የጅግጅጋ ባይባስ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ሥራ ዛሬ ተጀመረ። በጅግጅጋ ከተማ በተከናወነው የግንባታ ሥራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ላይ የኢመባ የስራ ሃላፊዎች የሱማሌ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድን ጨምሮ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል። የጅግጅጋ ባይፓስ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በከተማዋ የሚስተዋለውን የትራፊክ መጨናነቅ ከማስተንፈሱም ባሻገር የከተማዋን ዕድገት በማሳለጥ ረገድ ሚናው ከፍተኛ ነው። ፕሮጀክት 7 ኪ.ሜ ርዝማኔ ያለው እና የጎን ስፋቱ 30 ሜትር ሲሆን በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ይገነባል፡፡ ከዚህ ባለፈም የእግረኛ እና የብስክሌት መተላለፊያ፣ የአረንጓዴ ቦታ፤ የውሃ ማፋሰሻ ቱቦ ያካትታል። እንዲሁም 90ሜትር ርዝመት ያለው ዘመናዊ ድልድይም የግንባታው አካል ነው። ግንባታውን ከመንግስት በተመደበ 672,098,730,28 ብር ወጪ ይርጋለም ኮንስትራክሽን የተባለ ሀገር-በቀል የሥራ ተቋራጭ ድርጅት ያከናውነዋል። ፕሮጀክቱን የማማከር እና የመቆጣጠሩን ተግባር ደግሞ ELDA ኢንጅነሪንግ ይከውነዋል። ፡ የመንገድ ግንባታው በ18 ወራት ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናል ። ርዕሰ-መስተዳድሩ አቶ ሙስጠፌ መሀመድ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በክልሉ በርካታ የመንገድ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። በክልሉ ለሰፈነው ሰላም እና መረጋጋት የመንገዶቹ መገንባት አስተዋፆው የጎላ መሆኑንም አንስተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ  የኢትዮጵያ - ጁቡቲ የትራንስፖርት ኮሪደር  አካል የሆነውን  የአዳማ-አዋሽ ምዕራፍ አንድ አዳማ- ኪ.ሜ 60 የፍጥነት መንገድ ግንባታን ዛሬበይፋ አስጀመሩ ። በአዳማ ከተማ በተካሄደው መርሃ- ግብር ላይ ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ አደም ፋራ ፣  የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ   ፣ የሱማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ፣ የትራንስፖርት ሚንስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ በኢትዮጵያ ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱል ካማራ ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ ጨምሮ ፣  ከፍተኛ የፌዴራል እና የክልል ባለስልጣናት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ዕንግዶች ታድመዋል፡፡    ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትጵያን በአራቱም አቅጣጫ ካሉ የጎረቤት አገራት መንገድን ጨምሮ በሁሉም መስክ ለማስተሳሰር ትኩረት ተሰቶ እየተሰራ ለመሆኑ ይህ ፕሮጀክት ጉልህ ማሳያ ነው ብለዋል። በዛሬው ዕለት ግንባታው የተበሰረው የኢትዮ- ጅቡቲ የትራንስፖርት ኮሪደር  አካል ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ እንዳለውም አንስተዋል። የወጪ ገቢ ንግዳችንን የሚያሳልጡ የትራፊክ መጨናነቆችንም የሚቀርፉ የፍጥነት  መንገዶችን  የማስፋፋት ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። የትራንስፖርት ሚንስትሯ ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ  በበኩላቸው  የአዳማ አዋሽ ኮሪደር ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገት ወሳኝ ከሆኑ የመንገድ ኮሪደሮች መካከል አንዱ ቢሆንም  ነባሩ መንገድ የትራንስፖርት ፍሰቱን የሚመጥን እና ደረጃውን የጠበቀ ያልነበረ በመሆኑ ፣ በመንገዱ ተጠቃሚዎች እንዲሁም በንብረት እና በህይወት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያደርስ ቆይቷል ብለዋል ፡፡ ይህ የፍጥነት መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ  ፣ እነዚህን ችግሮች በመቅረፍ ፣ የትራንስፖርት ፍሰቱን የተሳለጠ በማድረግ እና በትራፊክ መስተጓጎል  ሳቢያ ኢኮኖሚው ላይ የሚፈጥረውን ጫና በማቃለል የተሳለጠ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጥ እንደሚያደርገውም ገልፀዋል፡፡ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የፕሮጀክቱ ግንባታ የሚካሄድበት አዳማና ዙርያው  የትላልቅ ፣ መካከለኛና ቀላል ማኑፋክቸሪንግ ፣ የአግሮ ፕሮሰሲንግ ፋብሪካዎች እና የኢንዱስትሪዎች መገኛ እንደመሆኑ  እነዚህ ኢንዱስትሪዎች እና ፋብሪካዎች ኢትዮጵያ  ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ በመሸጋገር  ከበለፀጉት ሀገራት ተርታ ትሰለፍ ዘንድ  የፍጥነት መንገድ ፕሮጀክቱ  ትልቅ አበርክቶ ይኖረዋል ብለዋል። የአዳማ አዋሽ መንገድ  ግንባታ   በተገቢው የጥራት ደረጃ እና የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ የክልሉ መንግስት ከሚመለከታቸው የመስተዳድር አካላት ፣ ከአካባቢው ሕብረተሰብ እንዲሁም ከባለስልጣኑ መ/ቤት ጋር በመሆን ለፕሮጀክቶች መዘግየት ምክንያት እየሆነ የመጣውን  ከወሰን ማስከበር ጋር የተያይዙ ችግሮችን እንዳይከሰቱ አስፈላጊውን ድጋፍ ክትትል እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የአፍሪካ ልማት በኢትዮጵያ ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱል ካማራ በመርሀግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት የአፍሪካ ልማት ባንክ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ባለው የመንገድ ዘርፍ ልማት በተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች ከ1000 ኪሜ በላይ እርዝማኔ ያላቸው ፕሮጀክቶችን እውን ለማድረግ ከ1.4 ቢሊዮን ዶላር በላይ ወጪ እንዳደረገ ገልጸዋል። በቀጣይም የአፍሪካ ልማት ባንክ ኢትዮጵያን ከጎረቤት ሀገራት ጋር በመንገድ ለማስተሳሰር እያደረገችው ላለው ጥረት ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ በበኩላቸው የወደብ መዳረሻ በሆነው እና የሀገራችንን የገቢ ወጪ ንግድ በስፋት በሚካሄድበት ኮሪደር ዘመናዊ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት አንዲቻል  እና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለማሳደግ የፍጥነት መንገዶችን መገንባት እጅግ ወሰኝ ስለመሆኑ ገልጸዋል ፡፡ በቀጣይም የአዳማ - አዋሽ የፍጥነት መንገድ ፕሮጀክት  ቀጣይ ምዕራፍ የሆነውን ከኪሜ 60    እስከ  አዋሽ እና ከአዋሽ - ድሬዳዋ ያለውን  ቀጣዩ የጅቡቲ ኮሪደር መንገድ በፍጥነት መንገድ ደረጃ ለመገንባት በሂደት ላይ ላይ እንደሚገኘ አንስተዋል፡፡ በዚህም  ኢትዮጵያ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ጅቡቲ ድንበር ደወሌ ድረስ  የተዘረጋ   የዘመናዊ መንገድ ባለቤት ያደርጋታል ሲሉም ኢ/ር ሃብታሙ ተገኘ ተናግረዋል፡፡ ዛሬ የግንባታ ስራው  በይፋ የየተጀመረው  የአዳማ -አዋሽ -ሚኤሶ ድሬዳዋ ፕሮጀክት ምዕራፍ አንድ አዳማ -አዋሽ ኮንትራት አንድ አዳማ - ኪ.ሜ  60 የፍጥነት መንገድ ሲሆን 60  ኪሜ እርዝማኔ አለው ፡፡ የፍጥነት መንገዱን ለመገንባት  6,688, 456, 565.74 ብር ጨረታውን በማሸነፍ ግንባታው የሚካሄደው ጄ ኤም ሲ እና ኤል አር ቢ ሲ ኤል የተባሉ ዓለም አቀፍ የስራ ተቋራጮች በጥምረት በመሆን ነው፡፡ የግንባታው  ወጪው የማሸፈነውም   በአፍሪካ ልማት ባንክ እና በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡ የመንገዱን ጥራት በመቆጣጣር ረገድ የማማከር ስራውን የሚሰሩት  ሊ ኢንተርናሽናል ሊሚትድ እና ዩኒኮን በጋራ በመሆን ነው ፡፡ የፍጥነት መንገዱ ከነባሩ መንገድ ጋር የሚያገናኙ ሶስት  ማሳላጫዎች በአዳማ ፣  ኑራ ኤራ   እና በወለንጪቲ  ላይ የሚገነባለት ይሆናል ፡፡ የምዕራፍ አንድ አዳማ -አዋሽ ኮንትራት አንድ አዳማ - ኪ.ሜ  60 የፍጥነት መንገድ  34 ሜትር ስፋት አለው ፡፡ እያንዳንዱ የተሸከርካሪ መጓጓዣ መስመር 3.6 ሜትር ስፋትና 9 ሜትር ሜዲያን (የመንገድ አካፋይ) ያካተተ ነው ::  የመንገድ አካፋዩ በዚህ ደረጃ እንዲሰፋ የተደረገው በተቃራኒ አቅጣጫ ያለን ተሸከርካሪን በመለየት  አደጋን ለማስወገድ አልያም ለመቀንስ   ነው፡፡ የመንገዱ ትከሻ ስፋት  ከ1.5 ሜትር እስከ 3 ሜትር  ነው፡፡ አራት መኪኖችን በአንድ ጊዜ በግራና በቀኝ በኩል ያስተናግዳል፡፡  መንገዱ አጠቃላይ 90 ሜትር የወሰን ስፋት  ያካተተ ነው፡፡ ይህም በቀጣይ ለሚኖረው የማስፋፋት ስራ በቂ ቦታ እንዲኖር የሚያስችል ይሆናል፡፡ በተጨማሪም  የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂን መሰረት በማድረግ  ችግኞችን  በመትከል አካባቢውን  የማስዋብ ስራ ይሰራል፡፡ በፍጥነት መንገዱ ለመጠቀም የተቀመጠለት የፍጥነት ገደብ በሰዓት ከ100 እስከ 120 ኪ.ሜ  ነው፡፡ የፍጥነት መንገዱ ሲገነባ ከእንስሳት እና ከሰዎች እንቅስቃሴ ነጻ በመሆኑ ለአሽከርካሪ ፍጹም ምቹ የማሽከርከር እድል እና ነጻነትን  የሚያድል ከመሆኑም ባለፈ በነባሩ መንገድ  በተደጋጋሚ የንጹሃን ዜጎችን ህይወት  እየቀጠፈ ያለውን እና የንብረት ውድመት እያስከተለ የመጣውን የትራፊክ አደጋ በመቀነስ ረገድ ትልቅ ፋይዳ ያለው ነው ፡፡

የኢተያ – ሮቤ ምእራፍ አንድ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ስራ አፈጻጸም በመስክ ምልከታ ተቃኝቷል። የመንገድ ፕሮጀክቱ በትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ ፣ የኢመባ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን እንዲሁም የባለስልጣኑ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ነው ምስክ ምልከታ የተካሄደው። የትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ የመንገዱን አሁናዊ እንቅስቃሴ በተመለከቱበት ውቅት እንዳሉት አካባቢው በግብርና ምርቱ ታዋቂ ቢሆንም ከዚህ ቀደም ደረጃውን የጠበቀ መንገድ ባለመኖሩ አርሶ አደሩ ከምርቱ መጠቀም ሳይችል እንደቆየ አስታውሰው በቀጣይ መንገዱ ሲጠናቀቅ ምርቱን በፍጥነት ለማዕከላዊ ገበያ እውጥቶ በመሸጥ ተጠቃሚነታቸውን የሚጨምር ነው ብለዋል። አቶ ካሳሁን ጎፌ ጨምረውም የኢተያ – ሮቤ ምእራፍ አንድ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ስራ ተጠናቆ ተገቢውን ግልጋሎት መስጠት እንዲችል ካስፈለገ ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ በተለይም ኢትያ፣ ሁሩታ፣ ዲክሲስ እና ሮቤ ከተሞች ላይ ያጋጠመውን ዩቲሊቲ ተቋማት በሆኑት መብራት ፣ ቴሌ እና የመጠጥ ውሀ መስመሮች እንዲሁም የመኖሪያ ቤቶች በፍጥነት ከመንገድ ክልል አለመነሳት ጋር ተዳምሮ የሚስተዋሉ ችግሮችን በአስቸኳይ ሊቀረፉ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል ። የኢመባ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን በበኩላቸው 75.6 ኪሜ የሚረዝመው የኢተያ – ሮቤ ምእራፍ አንድ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ከዚህ ቀድም በተቋራጩ አቅም ማነስ ምክንያት በመጓተቱ የቅሬታ ምንጭ የፈጠረ ቢሆንም የባለስልጣኑ መ/ቤት ከተቋራጩ ጋር በገባው ውል መሰረት ግንባታውን እንዲያፋጥን ከጋራ መግባባት ላይ መድረስ በመቻሉ ነው የመንገድ ግንባታ እንቅስቃሴው ዳግም ሊነቃቃ የችለው ብለዋል። አሁንም ቢሆን ለፕሮጀክቱ በስኬት መጠናቀቅ የባለድርሻ አካላት ትብብር እና ድጋፍ ከምንም በላይ ወሳኝ እንደሆነ ገልጸው የባለስልጣኑ መ/ቤትም ጥብቅ ክትትል ያደርግልም ብለዋል ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን ። ኢተያ – ሮቤ ምእራፍ አንድ ምንገድን በ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ወጪ ግንባታውን የሚያከናውነው የስራ ተቋራጭ ቻይና ሬል ዌይ ቁጥር 3 የተባለው አለም አቀፉ የስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው ፡፡ ለመንገዱ ግንባታ ስራ የሚውለውን 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በኢትዮጵያ መንግሥት የሚሸፈን ይሆናል፡፡ በእስካሁኑ 15 ኪሜ የሚሸፍን የአስፋልት ንጣፍ ስራን ጨምሮ ን የአፈር ቆረጣና ሙሌት እንዲሁም የውሃ መፋሰሻ ቱቦ ቀበራ ስራም በመካሄድ ላይ ሲሆን በቀጣይ አመት ዋና ዋና የመንገድ ግንባታ ስራዎችን በማጠናቀቅ ለትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት እንደሚደረግ ይጠበቃል። ከአስፋልት ንጣፍ ስራው ጎን ለጎበቀጣይ የ6 ድልድዮች ግንባታ ስራን ጨምሮ የስትራክቸርና ሌሎች ተያያዥ ሥራዎች እየተከናወነ ይገኛል። የኢተያ ሮቤ መንገድ ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ ሆኖ ለትራንስፖርት በእጅጉ አሰቸጋሪ የነበረ ነው ፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅም በአካባቢው የሚመረቱ ከፍተኛ የግብርና ምርት ውጤቶችንና የቁም እንስሳትን በቀጥታ ወደ ማእከላዊ ገበያ በፍጥነት በማድረስ አምራች ሸማቹን ተጠቃሚ ያደርጋል። በመንገዱ ብልሽት ሳቢያ በተለይም በክረምት ወቅት የሚከሰተውን ከፍተኛ የትራንስፖርት መስተጓጎል በማስቀረት ምቹ የትራንስፖርት ፍሰትን ይፈጥራል ፡፡ የኢተያ – ሮቤ የመንገድ ግንባታ ኘሮጀክት የስራውን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር እየተሳተፈ የሚገኘው አገር በቀሉ ሃይ ዌይ ኢንጅነርስ ኤንድ ኮንሰልታንትስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ድርጅት ነው ፡፡ የመስክ ስራ ቅኝቱ ከኢተያ ሮቤ ፕሮጀክት በመቀጠል 92.6 ኪ.ሜ የሚረዝመው የአርሲነገሌ _ቢላሎ - ቀርሳ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ስራ እንቅስቃሴ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት እንዲሁ ምልከታ ተደርጓል። በዚህም የፕሮጀክቱን አፈጻጸም አሁን ካለበት በበለጠ ማሳካት እንዲቻል የሁሉም አካላት ትብብር ውሳኝ መሆኑ ተነስቷል።

የደባርቅ - ዛሪማ ሊማለሞ ተለዋጭ መንገድ
+4
የደባርቅ - ዛሪማ ሊማለሞ ተለዋጭ መንገድ

መልካ ምድራዊ አቀማመጡ አሰቸጋሪ የሆነውን የሊማሊሞ መንገድን የሚያቋርጥ አዲስ ተለዋጭ የመንገድ ግንባታ ስራው እየተፋጠነ ነው። ፕሮጀክቱ የደባርቅ - ዛሪማ ሊማለሞ ተለዋጭ መንገድ ሲሆን 68.62 ኪ.ሜ ርዝመት አለው፡፡ እስካሁኑ ከተከናወኑ ስራዎች መካከል የአፈር ጠረጋ ፣ድልዳሎ እና ሙሌት ስራዎች አንዲሁም እስከ 20 ሜትር እርዝመት ያለው የአፈር የቆረጣ ስራ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም የሶስት ትልልቅ ድልድዮች ግንባታ ስራ ፣ የውሃ መፋሰሻ ቱቦዎች እና ቦዮች ምርት ስራም እየተከናወነ ነው ፡፡ በቀጣዩ አመት የአስፋልት ንጣፍ ስራ ለመጀመር የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተጠናቀቀ ይገኛል፡፡ የደባርቅ - ዛሪማ ሊማለሞ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት ስራን በሚፈለገው ፍጥነት ለማካሄድ እክል የነበሩትን የሲሚንቶ እጥረት እና በከተሞች አካባቢ የሚስተዋሉ ወሰን ማሰከበር ችግሮችን ለመቅረፍ ኢመባ ከሚመለከታቸው ባለድርሻዎች ጋር በትብብር እየሰራ ነው። የደባርቅ - ዛሪማ መንገድ ዲዛይን እና ግንባታን ባካተተ መልኩ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው የሚገነባው ፡፡ የመንገዱ ጎን ስፋት በወረዳ 21 እና በገጠር 10 ሜትር ስፋት አለው ፡፡ የግንባታ ስራውን 2.14 ቢሊዮን ብር በሆነ ወጪ እያካሄደ የሚገኝው ቤይጂንግ ኧርባን ኮንስትራክሽን ግሩፕ የተባለ የቻይናው አለም አቀፍ ተቋራጭ ነው፡፡ የማማከር ስራው ደግሞ በባንግላዲሹ ቢ ሲ ኤል ከአገር በቀሉ አይኮን ጋር በትብብር ያካሂዱታል፡፡ የመንገዱ መገንባት ከአዲስ አበባ ፣ ባህርዳር ፣ ጎንደር አድርጎ ሽሬ የሚዘልቀው ዋና መንገድ አካል ከመሆኑም ባሻገር ከጎረቤት አገር ኤርትራ ጋር ደረጃውን በጠበቀ አስፋልት መንገድ የሚያገናኝ ስለሚሆን ጠቀሜታው ከፍ ያለ ነው፡፡ ከዚህ ቀደም ከደባርቅ አድርጎ ዛሪማ ለመሄድ የነበረውን ነባሩን የሊማሊሞ አደገኛ መንገድ ከትራፊክ አደጋ፣ ከመሬት መንሸራተት እና በክረምት ወቅት ሊከሰት ከሚችል መንገድ መዘጋት በማስቀረት የተሳለጠ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ነው፡፡ በተጨማሪም ደረጃውን የጠበቀ መንገድ ተጠቃሚ ያልነበረውን የአካባቢውን ነዋሪ በዘመናዊ መንገድ እንዲገለግል በማድረግ እንዲሁም በመስመሩ የሚመረቱትን የሰብል ውጤቶች በቀላሉ ወደገበያ በማቅረብ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ይጠበቃል ፡፡ ወደ ሰሜን ተራሮች ለሚሄዱ ቱሪስቶች ምቹ መንገድ ከማቅረብ አንጻር ለቱሪዘም ሴከተሩም የበኩሉን ሚና ያበረከታል ። የመንገድ ፕሮጀክቱ ከነባሩ ሊማሊሞ መንገድ በስተግራ በኩል እየተሰራ ሲሆን መነሻውን ደባርቅ መሃል ከተማ ያደርግና የዘበና፣ የቢጢቆ፣ የጫንቅ፣ የአደማራ ጊዮርጊስ፣ የአብረሃም፣ የአዳጋት፣ የጥርሃይና የማይጥምቀት እና አምበራ ትናንሽ የቀበሌ አስተዳደር መቀመጫዎችን አቋርጦ ዛሪማ ከተማ ላይ ያበቃል፡፡ ከተገነባ 82 ዓመታትን የተሻገረው ታሪካዊው የሊማሊሞ መንገድ በቀጣይ የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ አካል በመሆን እራሱን የቻለ የቱሪስት መዳረሻ እና ሳይክል ጉዞ ለሚያደርጉ የሀገር ውስጥና የውጭ አገር ቱሪስቶች አይነተኛ መዳረሻ ቦታ ይሆናል ተበሎም ታቅዷል ፡፡

የሶዶ-ኦሞ ወንዝ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+4
የሶዶ-ኦሞ ወንዝ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት