fa
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

رفتن به کانال در Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

کانال ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 13 331 مشترک است و جایگاه 1 756 را در دسته حمل و نقل و رتبه 2 541 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 13 331 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 16 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 90 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 8 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 40.85% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.40% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 439 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 050 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 17 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 17 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته حمل و نقل تبدیل کرده‌اند.

13 323
مشترکین
+824 ساعت
+217 روز
+9030 روز
آرشیو پست ها
በአማራ ክልል እየተከናወኑ ያሉ የፌደራል የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን አስመልክቶ ውይይት ተካሄደ አዲስ አበባ ፣ ታኅሣሥ 14 ፣ 2017 (ኢ መ አ):- በአማራ ክልል እየተከናወኑ ያሉ የፌዴራል የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች አፈጻጸምን አስመልክቶ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደርና የአማራ ክልል ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ውይይት አካሂደዋል፡፡ በዕለቱም የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ እና የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን የተገኙ ሲሆን በግንባታ ላይ ያሉ የመንገድ ፕሮጀክቶች ያሉበትን አሁናዊ ሁኔታ የሚያመላክት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ በክልሉ በአንዳንድ ፕሮጀክቶች ከጸጥታ፣ ከወሰን ማስከበር ፣ የተቋራጮች አቅም ውስንነት እና ግንባታቸው ከተጀመረ በኋላ የሚስተዋሉ የዲዛይን ማሻሻያ ስራዎች ጋር የተያያዙ ችግሮች በፕሮጀክቶቹ አፈጻጸም ሂደት ላይ ተፅዕኖ ስለማሳደራቸው ተገልጿል፡፡ በመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶቹ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮቹን ለመፍታት የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር እና የክልሉ መንግሥት በጋራ በመስራት አፋጣኝ መፍትሄ መስጠት እንዳለበት አጽንኦት ተሰጥቷል፡፡ ለፕሮጀክቶቹ መዘግየት ምክንያት የሆኑ ችግሮችን በመቅረፍ ፕሮጀክቶችን በተቀመጠላቸው የግንባታ ጊዜ እንዲጠናቀቁ የቅርብ ክትትል የሚያደርግ ከሁለቱም አካላት የተውጣጣ ኮሚቴ ተቋቁሟል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የነጌሌ ቦረና - ኪሎሜትር 64 ነጥብ 5 መንገድ ፕሮጀክት በጥሩ አፈጻጸም ላይ ይገኛል ነጌሌ ቦረና፣ ታኅሣሥ 08፣ 2017 (ኢ መ አ):- በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ቦረና ዞን'ን ከሶማሌ ክልል ሊበን ዞን ጋር የሚያገናኘው ምዕራፍ አንድ የነጌሌ ቦረና - ኪሎሜትር 64 ነጥብ 5 መንገድ ፕሮጀክት በጥሩ አፈጻጸም ላይ ይገኛል። የመንገድ ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያን ከሱማሊያ እና ኬንያ ጋር የሚያስተሳስረው የነገሌ ቦረና - ዶሎ አዶ - መልካሱፍቱ ግዙፍ ፕሮጀክት አካል ሲኾን፥ የመጀመሪያው ምዕራፍ 64 ነጥብ 5 ኪሎሜትር ይሸፍናል። ከዚህ ቀደም በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረው ይህ መንገድ፣ ካለው በርካታ ሀገራዊ ፋይዳ አንፃር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል። የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም አሁን ላይ 74 ነጥብ 4 በመቶ ደርሷል። ግንባታውን በጣምራ የሚያከናውኑት ሀገር በቀሎች ኤም ሲ ጂ ኮንስትራክሽን እና ዓለማየሁ ከተማ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ፣ በአሁኑ ወቅት የ36 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ሥራ አጠናቅቀዋል። በተጨማሪም የ96 በመቶ የጠረጋ፣ የ69 በመቶ የፍሳሽ ማስወገጃ፣ የ97 በመቶ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የ50 ኪሎሜትር ሰብቤዝ እና የ37 ኪሎሜትር ቤዝኮርስ ሥራዎች ተሠርተዋል። የአንድ ድልድይ ግንባታም ተጠናቅቋል። ፕሮጀክቱን በዚህ ዓመት ለማጠናቀቅ የሚያስችሉ በማሽነሪ እና በቁሳቁስ አቅርቦት በኩል አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን በሥፍራው ባደረግነው ቅኝት ተመልክተናል። በተቋማችን በኩልም ከመስተዳድር አካላት ጋር በመቀናጀት ተገቢው ድጋፍ እና ክትትል እየተደረገ ይገኛል። ለፕሮጀክቱ የተመደበው 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በፌደራል መንግስት በጀት የሚሸፈን ሲኾን፣ ኤስ ጂ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ፕሮጀክቱን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራ ይሠራል። የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ ከዚህ ቀደም ከነጌሌ ቦረና ከተማ አንስቶ እስከ ፕሮጀክቱ መዳረሻ ድረስ የሚወስደውን 2 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 50 ደቂቃ ያሳጥረዋል። የሁለቱን ክልሎች የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር በማጠናከርም የነገሌ፣ ዴካሱፍቱ፣ ሀይሱፍቱ እና መሰል ከተሞችን በቅርበት ያገናኛል። በአካባቢው በስፋት የሚገኙትን ስንዴ፣ ጤፍ እንዲሁም የቁም እንስሳት ንግዱን ያቀላጥፋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የያቤሎ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክትን በተያዘው ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው ያቤሎ፣ ታኅሣሥ 03፣ 2017 ዓ.ም (ኢ መ አ):- በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ቦረና ዞን በ304 ሚሊዮን ብር ወጪ እየተገነባ የሚገኘውን የያቤሎ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት በተያዘው ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ 7 ነጥብ 44 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ የዞኑ መቀመጫ ለኾነችው ያቤሎ ከተማ ተጨማሪ አማራጭ ኾኖ የሚያገለግል ነው። በተለይም በያቤሎ -ኬላ ነባር መንገድ ላይ የሚስተዋለውን የትራፊክ ጭንቅንቅ ያስቀራል፡፡ ከዚህም ባለፈ በአቅራቢያ ከሚገኙ የጎሮቤት ሀገራት ጋር ያለውን የወጪ እና የገቢ ንግድን በማቀላጠፍ በኩልም አዎንታዊ ሚና ይጫወታል፡፡ አሁን ላይ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም 91 ነጥብ 43 በመቶ ደርሷል። እየተከናወኑ ከሚገኙ የግንባታ ሥራዎች መካከል የ87 በመቶ የፍሳሽ ማስወገጃ፣ የ99 በመቶ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የ7 ኪሎሜትር ሰብቤዝ፣ የ6 ኪሎሜትር ቤዝኮርስ እና የ5 ኪሎሜትር አስፋልት ሥራዎች ተከናውነዋል። በተጨማሪም የአንድ ድልድይ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቋል። ግንባታው በታቀደለት ጊዜ እንዲጠናቀቅም በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኩል አስፈላጊው ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል እየተደረገ ይገኛል። መንግስታዊው የልማት ድርጅት የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ግንባታውን ያከናውናል። ቤስት ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ፕሮጀክቱን የመቆጣጠር እና የማማከር ሥራ ይሠራል። የግንባታው ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት ይሸፈናል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

በመንገድ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም የባለድርሻ አካላት ሚና ላይ ትኩረቱን ያደረገ ውይይት ተካሄደ አዲስ አበባ፣ ህዳር 30/2017 ዓ.ም(ኢመአ)፡ የፌዴራል መንግስት የሚያስተዳድራቸው የመንገድ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም የባለድርሻ አካላት ሚና ላይ ትኩረቱን ያደረገ ውይይት በአዲስ አበባ ከተማ ተካሄደ፡፡ በውይይት መድረኩ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር፣ የገንዘብ ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን፣ የፕሮጀክቶች ወቅታዊ ሁኔታን የሚያሳይ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ የፕሮጀክቶቹ አፈጻጸም ውጤታማ እንዲሆን ከፌደራል እስከታችኛው እርከን የሚገኝ የመንግስት መዋቅር እንዲሁም ወሳኝ የሚባሉት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን መወጣት በሚችሉበት አግባብ ላይ ውይይት ተካሂዷል። ለፕሮጀክቶቹ መጓተትና መቋረጥ ምክንያቶች ናቸው ተብለው የተነሱ ጉዳዮች የጸጥታ ችግር፣ የካሳ ክፍያ፣ ወቅታዊ የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ እና የግብዓት አቅርቦት በተለይ ሲሚንቶ፣ ነዳጅና የመሳሰሉት ናቸው፡፡ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶችም ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ የውይይት መድረኩን የመሩት የከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ የትምጌታ አስራት የመንገድ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ ማጠናቀቅ እንዲቻል በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን በአጽንኦት ገልፀዋል፡፡ እነዚህን ተግዳሮቶች ጊዜ ሳይሰጣቸው በወቅቱ ለመፍታት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት እንዲፈታ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ ድጋፍ እንደሚያደርግም ሚኒስቴር ዴኤታው ገልጸዋል፡፡ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሰመረታ ሰዋሰው በመድረኩ ተግዳሮት ናቸው ተብለው የተነሱ ጉዳዮችን በሚመለከት እንደ ገንዘብ ሚኒስቴር የሚያስፈልግ ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን መድረኩ ትልቅ ግብዓት የተገኘበት መሆኑን ገልጸው፣ በተነሱ ጉዳዮች ዙሪያ የባለድርሻ አካላት ዝርዝር ድጋፍ ተለይቶ የሚደርሳቸው እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የሆሳዕና ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ እየተከናወነለት ነው ሆሳዕና፣ ታኅሣሥ 01፣ 2017 (ኢ መ አ):- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ554 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚገነባው የሆሳዕና ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ እየተከናወነለት ነው። ተለዋጭ መንገዱ 5 ነጥብ 125 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፣ ከናራሞ የወልቂጤ መውጫ እስከ መካነ ኢየሱስ እና ከመብራት ኅይል ሰብ ስቴሽን እስከ ወላይታ ሶዶ መውጫ ባለው መስመር እየተገነባ ይገኛል። ግንባታው ከዚህ ቀደም ሲካሄድ ቆይቶ በገጠሙት የተለያዩ ችግሮች ምክንያት መዘግየቱ ይታወቃል። በአሁኑ ወቅቱ የግንባታውን ቀሪ ሥራዎች ለማጠናቀቅ እንዲቻል በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የዓለምገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ፕሮጀክቱን ተረክቦ በራስ-ኅይል እያከናወነ ይገኛል። ፕሮሚነንት ኢንጅነሪንግ ሶሉሽን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራ ይሠራል። አሁን ላይ የ1 ኪሎሜትር አስፋልት ንጣፍ፣ የ87 በመቶ አፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የ5 ኪሎሜትር የውኃ መፋሰሻ ቱቦ፣ የ4 ነጥብ 6 ኪሎሜትር የሰብቤዝ ሥራዎች ተሠርተዋል። አጠቃላይ አፈጻጸሙ 29 ነጥብ 96 በመቶ ደርሷል። ግንባታው በራስ-ኃይል መከናወን ከጀመረ ወዲህ በመልካም የአፈጻጸም ደረጃ ላይ ማድረስ የተቻለ ሲኾን፥ እስከ ሰኔ ወር 2017 ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ እየተሠራ ይገኛል። ከተማዋ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት መቀመጫ እንደመኾኗ መጠን ለከተማው አማራጭ መንገድ ይሆናል፡፡ የመንገድ ትራፊክ መጨናነቅን ከመቀነሱም ባለፈ የከተማዋን ሁለንተናዊ ዕድገት ያፋጥናል። መንገዱ የእግረኛ እና የመንገድ አካፋይን ጨምሮ በክልል መቀመጫ ስታንዳርድ 22 ነጥብ 5 ሜትር የጎን ስፋት አለው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

Calls for workshop (Virtual)
Calls for workshop (Virtual)

የተቋማችን የመንገድ ምርምር ማዕከል ከጃፓን ድርጅት/ JICA/ ጋር በመተባበር አውደ ጥናት አካሄደ አዲስ አበባ፣ ህዳር 27/2017 ዓ.ም (ኢመአ) ፦ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ምርምር ማዕከል ከጃፓኑ አለም አቀፍ የልማት ድርጅት /JICA/ ጋር “Establishing competence in Geotechnics and landslides management towards mitigating landslide hazards in road infrastructures” በሚል አርዕስት አውደ ጥናት አካሄደ። JICA ለኢትዮጵያ የመንገድ ዘርፍ ልማት በተለያየ መልኩ አስተዋጽዖ ከሚያደርጉ የልማት አጋሮች መካከል አንዱ ነው። የአውደ ጥናቱ ዋና አላማ በመሬት መንሸራተት እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን አስመልክቶ ለመወያየት የሚያስችል መድረኮችን መፍጠር ነው። በመረሃ ግብሩ ላይ በቁጥር ስድስት የሚሆኑ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበዋል ። እነዚህ ጥናታዊ ጽሁፎች በፌደራል መንገድ መሰረተ ልማት ላይ በየጊዜው እያጋጠሙ ላሉ የመሬት መንሸራተት መንስኤዎች ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ በመድረኩ ላይ የቀረበዉን ጥናት በተመለከተ ተሳታፊ ከሆኑ ባለድርሻ አካላት ለተነሱ የተለያዩ ጥያቄዎች በጥናቱ አቅራቢዎች ምላሽ ተሰጥቶበታል። ከዚህም በተጨማሪ በዘርፉ ሊያጋጥሙ የሚችሉ የመሬት መንሸራተትን ለመቀነስ የሚያስችሉ እርምጃዎች እና የወደፊት ተግባራትን አስመልክቶ በቡድን በመከፋፈል ተወያይተዋል፡፡ የኢመአ የጂኦቴክንክ እና የመሬት መንሸራተት ጥናት ቡድን ከJICA ጋር በመተባበር የመሬት መንሸራተት መቆጣጠሪያ መመሪያዎችን አስመልክቶ በዘርፉ ላሉ ባለሙያዎች እያደረገ ያለው የአቅም ግንባታ እና ልምድ ልውውጥ ስራ አመርቂ ውጤቶችን አሳይቷል። በአውደ ጥናቱ ላይ ከተለያዩ ዩንቨርስቲ የተውጣጡ ባለሙያዎች ፣ አማካሪ ድርጅቶች እና በዘርፉ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል።