fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 538 مشترک است و جایگاه 8 326 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 176 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 538 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 04 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 26 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -7 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 26.64% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.41% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 4 139 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 395 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 9 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 05 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 538
مشترکین
-724 ساعت
-77 روز
+2630 روز
آرشیو پست ها
የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ የምናደርገውን ድጋፍ እንቀጥላለን - የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች …………////………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች ኢትዮጵያ የገጠማትን የህልውና ፈተና ለመመከት በተለያየ መልኩ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋገጡ፡፡ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች "ደማችን ለሀገራችን" በሚል መሪ ሀሳብ ነሐሴ 5 ቀን 2013 ዓ.ም ለሀገር መከላከያ ሠራዊትና ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ለተውጣጡ ህዝባዊ የጸጥታ ኃይሎች የሚውል ደም ለግሰዋል፡፡ አመራርና ሠራተኞቹ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ እየተካሄደ ላለው የህልውና ዘመቻ አጋርነታቸውን ለማሳየት ሐምሌ 29 ቀን 2013 ዓ.ም ባካሄዱት ውይይት መነሻነት ከ40 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ለማድረግ ቃል የገቡ ሲሆን ተቋሙም 25 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ለማድረግ ቃል ወስኗል፡፡ በደም ልገሳ ፕሮግራሙ ላይ የተሳተፉት የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት በአሁኑ ወቅት የሕወኃት አሸባሪ ቡድን ከውጭ ጠላቶች ጋር በመቀናጀት ሀገሪቱን ለመበታተን የከፈተውን ጥቃት በጋራ መመከት ይገባል፡፡ የደም ልገሳው መርሃ ግብርም የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ሕይወቱን እየሰዋ ለሚገኘው ለሀገር መከላከያ ሰራዊትና ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ለተውጣጣው ህዝባዊ የጸጥታ ኃይል ያለንን አጋርነት ለማሳየት የተካሄደ ነው ብለዋል፡፡ ዋና ሥራ አስፈፃሚው እንደገለፁት የደም ልገሳው በጦርነቱ አደጋ ለሚደርሰባቸው የሠራዊቱ አባላትና ደም ለሚፈልጉ ለሌሎች ዜጎችም የሚውል በመሆኑ ሀገርን ለማዳን ሁሉም ህዝብ ከሠራዊቱና ከህዝባዊ የጸጥታ ኃይሉ ጎን በመሆን በተለያየ መልኩ ድጋፉን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል፡፡ ደም ሲለግሱ ያገኘናቸው በተቋሙ የፋይናንስ ስራ አስፈጻሚ አቶ ደመረ አሰፋ፣ አቶ ልብሰወርቅ አስፋው፣ አቶ መለሰ ፋርስ እና ሌሎች የተቋሙ ሠራተኞችም ለህልውና ዘመቻው በተለያየ መልኩ ድጋፍ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡ ግንባር ላይ ደሙን እያፈሰሰ ለሚገኝ የሠራዊት አባል ደም መለገስ "ሀገር የማዳን" አንዱ አካል ነው ብለዋል ሠራተኞቹ፡፡ የተካሄደው የደም ልገሳ መርሀ ግብር ለሀገር የሚከፈል ዋጋን መደገፍ ነው ያሉት ሠራተኞቹ በአሁኑ ሰዓት ሀገሪቱ የገጠማትን የህልውና ፈተና ለመመከት ሁሉም ሰው በሚችለው መንገድ ድጋፉን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚኖርበት አንስተዋል፡፡ ሀገር ከሌለ ምንም ነገር የለም ያሉት አመራርና ሠራተኞቹ እየተደረገ ያለው የህልውና ዘመቻ ድጋፍ የሀገር ህልውና ቀጣይነትን የሚወስን በመሆኑ በተለያየ መንገድ የሚደረገው ድጋፍ እንደተጠበቀ ሆኖ በተመደብንበት ሥራ ላይም በኃላፊነት ስሜት የተሰጠንን ሥራ እንፈጽማለን ብለዋል፡፡ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ እየተዋደቀ ላለ ሠራዊት ደም መለገስ ትንሹ ነገር ነው ያሉት የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች በቀጣይ በተለያየ መልኩ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል፡፡ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ኢትዮጵያን ከገጠማት ፈተና ለማዳን ከሀገር መከላከያ ሠራዊት እና ከሌሎች ህዝባዊ የጸጥታ ኃይሎች ጎን የትም፣ መቼም፣ በምንም እንቆማለን የሚለውን ሀገራዊ ንቅናቄ በመቀበል ለእናት ሀገር ከገንዘብ ድጋፍ ባለፈ ግንባር ድረስ በመዝመት እስከ ሕይወት መስዋት ድረስ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 5 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content

photo content
+9

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች ደም በመለገስ ላይ ናቸው። የደም ልገሳው የተቋሙ አመራሮችና ሰራተኞች ከመደበኛ ስራቸው በተጓዳኝ ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጎን አብሮ ለመቆም ያላቸውን ቁርጠኝነት ለማሳየት ያለመ ነው። የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ለሀገር ህልውና ዘመቻ ከ40 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ ለማድረግ መወሰናቸው ይታወሳል። ነሐሴ 5 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content
+3

ጣቢያው በበጀት ዓመቱ 3248 ጊጋዋት ሰዓት ለማመንጨት አቅዷል ………….///…………… የጣና በለስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በበጀት ዓመቱ 3248 ጊጋዋት ሰዓት ለማመንጨት ማቀዱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ቢምረው ዳኜ ገለፁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ እንደገለፁት የጣቢያው አራቱም ዩኒቶች በጥሩ ሁኔታ ላይ ስለሚገኙ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከተከናወነው የሚልቅ ኃይል ለማምረት ታቅዷል፡፡ የጥገና ባለሙያዎች አቅም እያደገ መምጣቱና ከሀገር ውጪም ሆነ ከማዕከል የጥገና ባለሙያ እስኪመጣ ሳይጠበቅ የሚሰራ ባለሙያ መፈጠሩ፣ ዩኒቶች በጥገና ምክንያት ከሥራ ውጪ የሚሆኑበት ጊዜ መቀነሱና የተሻለ የውሃ መጠን በክረምቱ እንደሚኖር ታሳቢ መደረጉ እቅዱን ከፍ አድርጎ ለማቀድ መነሻ ሆኗል ብለዋል፡፡ ጣቢያው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 2773 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ በማምረት የዕቅዱን 90 በመቶ ያሳካ ሲሆን በዓመቱ ከተመረተው ኢነርጂ ውስጥ የ17 ነጥብ 5 በመቶ ድርሻ ነበረው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 03 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+3

የተቋሙ ጋራዥ ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳኑን አሰታወቀ ..............////............. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋራዥ ለድርጅቱ ተሸከርካሪዎች ቀላል፣ መካከለኛ እና ከባድ ጥገ
+4
የተቋሙ ጋራዥ ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳኑን አሰታወቀ ..............////............. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋራዥ ለድርጅቱ ተሸከርካሪዎች ቀላል፣ መካከለኛ እና ከባድ ጥገናዎች በመስጠት ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳኑን የተሽከርካሪ ጥገና ከፍተኛ ኦፊሰር አቶ ብሩክ እንዳለ አስታወቁ፡፡ በበጀት ዓመቱ ጋራዡ የሰጠው የጥገና አገልግሎት በውጪ ድርጅቶች ቢከናወንላቸው ኖሮ ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ይደረግባቸው እንደነበር የጠቀሱት አቶ ብሩክ ጥገናው በተቋሙ ጋራዥ ከ6 ሚሊዮን ብር ባልበለጠ ዋጋ በመከናወኑ ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ማዳን ተችሏል ብለዋል፡፡ እንደ ከፍተኛ ኦፊሰሩ ገለፃ በበጀት ዓመቱ ለ801 የድርጅቱ ተሽከርካሪዎች የቀላል ጥገና ወይም ሰርቪስ አገልግሎት በመስጠት ወጪ ከማዳን ባሻገር ተሽከርካሪዎችን በፍጥነት በመጠገን ጊዜ መቆጠብ ተችሏል፡፡ በተጨማሪም ለ305 ተሽከርካሪዎች የመካከለኛና ከባድ ጥገና አገልግሎት እንዲሁም ለ10 ተሽከርካሪዎች የሞተር ዕድሳት መደረጉንም ነው አቶ ብሩክ የተናገሩት፡፡ የኤሌክትሪክ ኃይል ጋራዥ የሞተር ዕድሳት፣የቦዲ ዕድሳትና የቀላል ጥገና አገልግሎቶች እየሰጠ እንደሚገኝ አቶ ብሩክ አስታውቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 01 ቀን 2013

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም የነበራቸው የሥራ ክፍሎች ዕውቅና እንዲሰጣቸው ተወስኗል ............../////.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የማኔጅመንት ቡድን በ2013 በጀት ዓመት መልካም አፈፃፀም የነበራቸው የሥራ ክፍሎች ዕውቅና እንዲሰጣቸው ወስኗል። ማኔጅመንቱ ከሐምሌ22 - 24 ቀን ያካሄደውን ግምገማ ተከትሎ የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን፣ የኃይል ማስተላለፊያዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን፣ የሰው ኃይል እና የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት የሥራ ክፍሎች መልካም አፈፃፀም በማስመዝገባቸው እውቅና እንዲሰጣቸው ተወስኗል። የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ በውጤታማነት እንዲፈፀምም የሁሉም ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ማኔጅመንቱ አሳስቧል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 01 ቀን 2013 ዓ.ም

አገልግሎት ከማይሰጡ ንብረቶች ከ72 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ …………////……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2013 በጀት ዓመት አገልግሎት የማይሰጡ የተለያዩ ንብረቶችን በማስወገድ 72 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የተቋሙ የንብረት አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ አበበ ጉዲሳ እንዳስታወቁት ገቢው የተገኘው አገልግሎት የማይሰጡ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች፣ መዳብ፣ አልሙኒየም፣ ዘይት የመጣባቸው በርሜሎች፣ ሽቦዎች፣ የተሸከርካሪ ጎማዎች፣ የዕቃ ማሸጊያ ጣውላዎች እና የመሳሰሉትን ንብረቶች በማስወገድ ነው፡፡ በበጀት ዓመቱ አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን በማስወገድ 40 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 72 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ይህም ከእቅዱ የ32 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር ወይም የ80 ነጥብ 2 በመቶ ብልጫ እንዳለው እና ከ2012 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ41 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር ወይም 138 በመቶ ብልጫ እንዳለው ነው አቶ አበበ የገለጹት፡፡ አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን የማስወገዱ ሥራ የመንግስት ንብረት አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 9/2003 መሰረት በማድረግ ተቋሙ ባወጣው የንብረት ማስወገድ መመሪያ መሰረት በግልጽ ጨረታ መከናወኑን እንደነበር አቶ አበበ ተናግረዋል፡፡ የስራ ክፍሎች አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶች እንዲወገድላቸው በሚያቀርቡት ጥያቄ መሰረት በተቋቋመው የንብረት አስወጋጅ ኮሚቴ ታይቶ በግልጽ ጨረታ ሽያጩ ሲከናወን እንደነበርም ተገልጿል፡፡ በበጀት ዓመቱ ለነበረዉ የገቢ አሰባሰብ እድገት እንዲወገዱ የተጠየቁ ንብረቶች መጠን ከፍተኛ መሆን፣ በማስወገድ ሂደቱ ውስጥ በኮሚቴነት የተሳተፉ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ጥንካሬ እና ለስራው ያደረጉት ትብብርና በተቋሙ እየተፈጠረ ባለው የንብረት ማስወገድ ስራ ግንዛቤ ማደጉ በምክንያትነት ይጠቀሳሉ፡፡ አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን ህጋዊ በሆነ መንገድ በጨረታ ለማስወገድ በሚሰራበት ወቅት አንዳንድ የፕሮጀክት እና የኦፕሬሽን ኃላፊዎች ለስራው ቀና ትብብር አለማድረጋቸው እና በሶስተኛ ወገን የሚወገዱ ንብረቶችን ያለ ምንም ሕጋዊ ማስረጃ ለመውሰድ ፍላጎት መታየታቸው በበጀት ዓመቱ ቢሮው ያጋጠሙት ተግዳሮቶች መሆናቸውን አቶ አበበ ጠቁመዋል፡፡ እንደ አቶ አበበ ገለፃ በቴክኖሎጂ የታገዘ የንብረት ማደራጀት ስራው ሲጠናቀቅ፤ የተቋሙን ንብረቶች መረጃ በየጊዜው ወቅታዊ ለማድረግ፣ ለመቆጣጠር፣ በአግባቡ ለመጠቀም የሚያግዙ የተለያዩ የአሰራር ዘዴዎችን ለመተግበር በሂደት ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡ በተቋሙ የንብረት አያያዝ እና አስተዳደር ላይ የሚታየውን ክፍተት በዘላቂነት ለመሙላት ዘመናዊ የዕቃ ግምጃ ቤት ለመገንባት፣ የአይ. ኤፍ. አር. ኤስ፣ የንብረት ዋጋ ክለሳ እንዲሁም የኢ. አር. ፒ (Enterprise Resource planning) ሲስተም የመዘርጋት ሥራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 30 ቀን 2013 ዓ.ም

የአሉቶ ጂኦተርማል የማስፋፊያ ፕሮጀክት የእንፋሎት ፍለጋ ቁፋሮው 138 ሜትር ደርሷል ……..//………… ግንቦት 21 ቀን 2013 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው የአሉቶ ላንጋኖ የከርሰ ምድር እንፋሎት የማስፋ
+3
የአሉቶ ጂኦተርማል የማስፋፊያ ፕሮጀክት የእንፋሎት ፍለጋ ቁፋሮው 138 ሜትር ደርሷል ……..//………… ግንቦት 21 ቀን 2013 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው የአሉቶ ላንጋኖ የከርሰ ምድር እንፋሎት የማስፋፊያ ፕሮጀክት የእንፋሎት ፍለጋ የጉድጓድ ቁፋሮ 138 ሜትር መድረሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአሉቶ ጂኦተርማል ፕሮጀክት አስታወቀ። የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ መሳይ ፈቃዱ እንደገለፁት ከደህንነት (safety) ጋር በተያያዘ ቁፋሮው ለሳምንታት እንዲቆም ተደርጎ ነበር፡፡ አሁን ላይ ከደህንነት ጋር የተያያዙ መስፈርቶች ስለተሟሉ ቁፋሮው ዛሬ እንዲቀጥል ተደርጓል። እንደ አቶ መሳይ ገለፃ የእንፋሎት ፍለጋ የጉድጓድ ቁፋሮው ወደ ከርሰ ምድር እስከ 2 ሺህ 700 ሜትር ጥልቀት የሚኖረው ሲሆን እስከ 70 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ለማመንጨት ታስቦ እየተሰራ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 29 ቀን 2013 ዓ.ም

ሪጅኑ ዓመታዊ የስራ አፈፃፀሙን ዛሬ ገምግሟል …………///…………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዓመታዊ የስራ አፈፃፀሙን ዛሬ ገምግሟል፡፡ በግምገማው መጀመሪያ ላይ ለሀገር ሰላምና ሉዓላዊነት ለተሰው የመከላከያና የፀጥታ አካላት የ1 ደቂቃ የህሊና ፀሎት የተደረገ ሲሆን በሪጅኑ የሚገኙ የ12ቱም ሰብስቴሽን ኃላፊዎች፣ የጅግጅጋ እና ድሬዳዋ ንዑስ ሪጅን ኃላፊዎች የአፈፃፀም ሪፖርቶች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ ሪጅኑ በመደበኛና አስቸካይ ጥገናዎች የያዘውን ዕቅድ ሙሉ በሙሉ ማሳካቱና ለሌሎች ሪጅኖች መልካም ተሞክሮ ሊሆን የሚችል ቢሮዎችን ለሥራ ምቹ የማድረግ ሥራ መከናወኑም ተገልጿል፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድርያስ በግምገማው ላይ እንደተናገሩት የዓመቱ አፈፃፀም በመልካም የሚጠቀስ ቢሆንም ከዚህም የተሻለ ለማከናወን ሁሉም በትጋት እንዲሰራ አሳስበዋል፡፡ በአዲሱ በጀት ዓመት ጉድለቶችን በመሙላት ለላቀ ሥራ እንዲነሳሱ በማሳሰብ የስራ አፈፃፀም ግምገማ ስርዓትና የእድገት ውድድርን በተመለከተ ከሠራተኞች ለተነሱ ጥያቄዎችም ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ከፍተኛ የአፈፃፀም ውጤት ላመጡ 2 ወንድና 1 ሴት ሰራተኞች እንዲሁም በጡረታ ለተገለሉ አንድ ሰራተኛ የዕውቅና ምስክር ወረቀት ተሰጥቷል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 29 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+7

የሀገራችንን ሰላም ለማስጠበቅ ሁላችንም በአንድነት እንቆማለን - የኢ.ኤ.ኃ አመራርና ሠራተኞች ………..////………….. የኢትዮጵያን ህልውና ለማረጋገጥ ሁሉም ዜጋ በአንድነት መቆም እንዳለበት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮች እና ሠራተኞች አስታወቁ፡፡ የተቋሙ የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በዛሬው ዕለት ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱ ላይ የተገኙት የተቋሙ የሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደተናገሩት በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ ላይ ከውስጥም ከውጭም የተቃጣውን ፈተና ለመታደግ ሁሉም ዜጋ በአንድነት ሊቆም ይገባል፡፡ የህወኃት አሸባሪ ቡድን በሥልጣን ዘመኑ ሀገሪቱን መቀመቅ አውርዷት እንደነበር ያነሱት አቶ ሙላት ከመንበረ ሥልጣኑ ከተወገደ በኋላም የባንዳነት ስራ በመስራት ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡ አሸባሪ ቡድኑን በጋራ መመከት እንደሚገባም ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡ የተቋሙ ሠራተኞች በበኩላቸው በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል እየተካሄደ ባለው የህልውና ዘመቻ እየተሳተፉ ለሚገኙት ለሀገር መከላከያ ሠራዊት እና ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ለተውጣጡት ህዝባዊ የጸጥታ ኃይሎች አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ "ሁሉን ነገር ማድረግ የሚቻለው ሀገር ስትኖር ነው" ያሉት ሠራተኞቹ፤ ለእናት ሀገር ኢትዮጵያ ከገንዘብ ድጋፍ ባለፈ ግንባር ድረስ በመዝመት እስከ ሕይወት መስዋዕት ድረስ በመክፈል አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብተዋል፡፡ በተለያዩ አፍራሽ ፕሮፖጋንዳዎች በመሳተፍ ለአሸባሪው ቡድን ድጋፍ በማድረግ ላይ የሚገኙ አካላትን በማጋለጥ ሁሉም የበኩሉን መወጣት እንዳለበትም ሠራተኞች አሳስበዋል፡፡ ኢትዮጵያን እናፈርሳታለን እያሉ የሚዝቱ አካላት ራሳቸው ይፈርሱ ይሆናል እንጅ ኢትዮጵያን ማፍረስ እንደማይችሉ ሊገነዘቡ ይገባልም ብለዋል ሠራተኞቹ፡፡ በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ የተቋሙ የሰው ኃይል ስራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ እንደገለፁት ሠራተኛው ለህልውና ዘመቻው ከሚያደርገው ድጋፍ ጎን ለጎን የተጣለበትን ኃላፊነት በአግባቡ በመወጣት ለሀገር አለኝታነቱን ማሳየት አለበት ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 29 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+7

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የካይዘን ትግበራ የመግባቢያ ሰነድ ተፈረመ …………///………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ ካይዘን ኢንስቲትዩት ጋር በትናትናው ዕለት የካይዘን ትግበራ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ፡፡ የመግባቢያ ሰነዱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የኢትዮጵያ ካይዘን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ተወካይ አቶ አስናቀ ጉዲሳ ተፈራርመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ በፊርማ ሥነ - ሥርዓቱ ላይ ተቋሙ ከ381 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት አጠቃላይ ሀብት እንዳለው ገልፀው ይህን ሀብት በአግባቡ ለመጠበቅ እና ለመጠቀም የካይዘን ትግበራ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ ገልፀዋል፡፡ የተቋሙን የሥራ ብቃት እና አፈጻጸም መዘመንና ማደግ ሀገሪቱ በምታካሄደው ሁለተናዊ ዕድገት ላይ የሚጫወተውን ሚና የላቀ እንደሚያደርገው ዋና ሥራ አስፈጻሚው ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ኃይል ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ በበኩላቸው ተቋሙ ባደረገው የዳሰሳ ጥናት እና በተወሰኑ ቦታዎች በተካሄደው የካይዘን ትግበራ ድርጅቱን ወጪ ቆጣቢ በማድረግ ውጤታማና አበረታች ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል፡፡ በቀጣይም ተቋሙ ባሉት 189 ማከፋፈያ ጠቢያዎች እና በ22 ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ የካይዘን ፍልስፍና ትግበራን ለማስፋፋት እና ለመተግበር ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ አቶ አታላይ ጠቁመዋል፡፡ የሚከናወኑትን የካይዘን ሥራዎች ለመምራት እና ለመተግበር የማኔጅመንቱን ቁርጠኝነት ገልፀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ካይዘን ኢንስቲቱት የዋና ዳይሬክተር ተወካይ አቶ አስናቀ ጉዲሳ እንደተናገሩት ካይዘን ማለት ጥራትና ምርታማነትን በቀጣይነት በማሻሻል ውጤታማ መሆን ማለት ነው፡፡ በመሆኑም ኢንስቲቱ የተቋሙን ሠራተኞች በማሰልጠን እና ትግበራው ላይ በመገኘት የማመከር እና ድጋፍ በመስጠት ትግበራው ዘላቂነት እንዲኖረው ክትትል እና ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ ሃብት ከሚንቀሳቀስባቸው የሃገሪቱ ግዙፍ ተቋማት መካከል አንዱ እንደመሆኑ በትንሽ የካይዘን ሥራ ትርጉም ያለው ለውጥ ለማምጣት እንደሚቻል አቶ አስናቀ ጠቁመዋል ፡፡ የፊርማ ሥነ-ስርዓቱ አሁን በይፋ ይካሄድ እንጂ ካለፉት ሶስት እና አራት ወራት አንስቶ ለሚመለካታቸው የተቋሙ ሠራተኞች ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ ባለፈው አንድ ወር ደግሞ በኮተቤ የንብረት ማከማቻ መጋዘን የትግበራ ሥራ ተጀምሯል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 29 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+4

ጣቢያው ዩኒት ሊያስቆሙ የሚችሉ ብልሽቶችን በራስ አቅም እየጠገንኩ ነው አለ ………….///…………… የጣና በለስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ዩኒቶችን ሊያስቆሙ የሚችሉ ብልሽቶችን በራስ አቅም እየጠገነ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ቢምረው ዳኜ ገለፁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ እንደገለፁት በዘይት የሚሰራው የውሃ መቆጣጠሪያ ቀለበት (Operating ring) የመሰንጠቅ አደጋ ገጥሞት የነበረ ቢሆንም በተቋሙ የጥገና ባለሙያዎች ሞደፊክ ተደርጎ በመስራት ተጠግኗል፡፡ በዚህም ዩኒቱ ሳይሰራ ለረጅም ጊዜ እንዳይቆም በማድረግ፣ የጥገና ባለሙያ ከውጪ ሀገር ሳይጠብቅና የውጭ ምንዛሪ ሳይወጣበት ብልሽቱን መጠገን አስችሏል፡፡ በተመሳሳይም በማቀዝቀዣ ስርዓቱ ውስጥ ፓምፕና ሞተርን የሚገናኘው (capler) ሞደፊክ ተደርጎ ከፕላስቲክ ቁስ ተሰርቶ በስራ ላይ እንዲውል ተደርጓል፡፡ ውሃ ከፓምፕ ገፍቶ ከወጣ በኋላ ወደኋላ እንዳይመለስ የሚያደርገው አካል (Non Return Valve) በዝገት ምክንያት በመበላሸቱ የተበላሸውን ብረት መልሶ ቅርጽ በማውጣትና በሌላ በመተካት የማስተካከል ስራ ተሰርቷል፡፡ በፓምፕ ውስጥ ውሃ በተገቢው እንዲዘዋወር የሚያደርገው የፕላስቲክ ቀለበት(ጋስኬት) በሰበቃ ምክንያት በማለቁ በሌላ የመተካት ስራ ተሰርቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 29 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+4

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማኔጅመንት አባላት ዛሬ ከሰዓት በኋላ ባደረጉት ስብሰባ ለሀገር ማዳን የህልውና ዘመቻ የአንድ ወር ደመወዛቸውን ለመለገስ ተስማሙ። ሠራተኞችም በፍላጎታቸውና በአቅማቸው የህልውና ዘመቻውን መደገፍ በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ለመምከር መድረክ እንዲመቻች ውሳኔ አሳልፏል። ሐምሌ 28 ቀን 2013 ዓ/ም