fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 544 مشترک است و جایگاه 8 333 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 158 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 544 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 27 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 10 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -16 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 25.06% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.33% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 895 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 539 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 7 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 28 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 544
مشترکین
-1624 ساعت
-97 روز
+1030 روز
آرشیو پست ها
አዲስ የተቋቋመው የተቋሙ ክበብ የሥራ አመራር ቦርድ ኃላፊነቱን ተረከበ ………..///………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሠራተኞች ክበብ አዲስ የመተዳደሪያ ደንብ ፀድቆ ወደ ተግባር መገባቱን የተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አስታወቁ። ኃላፊው አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደተናገሩት እንደ አዲስ የተቋቋመው የሥራ አመራር ቦርድ ለሠራተኛው በቂ እና ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲያገኝ የሚያስችል አሰራር መዘርጋት ይጠበቅበታል፡፡ ቦርዱ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ በመወጣት የሠራተኛውን ፍላጎት ለማርካት በርትቶ እንዲሠራ የተቋሙ ማኔጅመንት ሁለንተናዊ ድጋፍ እንደሚያደርግ አቶ ሙላት አረጋግጠዋል፡፡ የተቋሙ መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር ሊቀ መንበር አቶ መኮንን ክፍሌ በበኩላቸው ሠራተኛው ከሚያነሳቸው ቅሬታዎች አንዱ የካፍቴሪያ አገልግሎት መሆኑን ገልፀው ችግሩን ለመፍታት አዲስ አደረጃጀት መዋቀሩን አስታውቀዋል። የተቋሙ የሰው ኃይል ስራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ እንደተናገሩት ኃላፊነቱ በዋናነት የተሰጠው ለመሰረታዊ የሠራተኛ ማህበሩ ቢሆንም የክበብ አገልግሎቱ እንዲጠናከር ተቋሙ ሁለንተናዊ ድጋፍ ያደርጋል፡፡ ሠራተኛውን ማርካት፣የአሠራር ግልፀኝነት ማስፈንና ተራማጅ አሠራሮችን መተግበር ከቦርዱ እንደሚጠበቅ ያነሱት ደግሞ በዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የአስተዳደራዊ ጉዳዮች እና ዶክመንቴሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ ናቸው፡፡ አዲስ የተሰየሙት የክበቡ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሌንሴ ኤድኤ በበኩላቸው አባላቱ የተጣለባቸው ኃላፊነት ከባድ መሆኑን ተረድተው በቁርጠኝነት እንዲሰሩ አሳስበዋል። የክበቡ ሥራ አመራር ቦርድ ሰባት አባላት ያሉት ሲሆን የቦርድ ሰብሳቢዋ ሆነው የተሰየሙት ወ/ሮ ሌንሴ ኤደኤ የክበቡን የመተዳደሪያ ደንብ ከተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ እጅ ተረክበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ አካውንት | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content
+1

photo content
+9

በበጀት ዓመቱ ከሙስና እና ብልሹ አሰራር ጋር የተያያዙ አስራ ስድስት ጥቆማዎች ቀርበዋል ……....//……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተገባደደው በጀት ዓመት ከግዢ ሂደት፣ ከፕሮጀክት አመራር፣ ከጥቅም ግጭት እና ከካሳ ክፍያ አፈፀፀም ጋር የተያያዙ አስራ ስድስት ጥቆማዎች መቅረባቸውን በተቋሙ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ሥራ አስፈጻሚ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስፈጻሚው አቶ መርጋ ተረፈ እንደገለጹት ከቀረቡት ጥቆማዎች መካከል በአስራ አራቱ ላይ አስፈላጊው የማጣራት ሥራ ተከናውኖ ለሚመለከተው አካል የውሳኔ ሀሳብ ቀርቧል፡፡ የተቀሩት ሁለቱ ጥቆማዎችም በማጣራት ሂደት ላይ እንደሚገኙ ሥራ አስፈፃሚው ገልጸዋል፡፡ የአሰራር ሥርዓቶች ግልጽና ተጠያቂነት ያለባቸው እንዲሆኑ ለማድረግና የሕግ ተገዥነት ለማሳደግ በበጀት ዓመቱ ከ1 ሺህ 6 መቶ በላይ ለሚሆኑ የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች በሥነ-ምግባር ግንባታ ላይ ያተኮሩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎች መሰጠታቸውንም ተናግረዋል፡፡ የተሰጡት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞችን የአገልጋይነት አመለካከት እንዲያዳብሩ፣ ከአድሎና ሙሰኝነት የፀዱ እንዲሆኑ፣ የመንግስት ሀብትና ንብረትን በአግባቡ እንዲጠቀሙ በማድረግ ተቋሙ የተጣለበትን ሀገራዊ ተልዕኮ በብቃት ለመወጣት የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል፡፡ የሥራ ክፍሉ የሚቀርቡለትን ጥቆማዎችና ቅሬታዎች ከማጣራትና ድንገተኛ ፍተሻ ከማድረግ ጎን ለጎን ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ወደ ዲሲፕሊን ችግሮች እንዳይገቡ የሚከላከል የሥነ-ምግባር መመሪያ መሰራጨቱንም ገልፀዋል፡፡ እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በበጀት ዓመቱ ሀብታቸውን እንዲያስመዘግቡ በህግ ግዴታ ከተጣለባቸው ኃላፊዎች በተጨማሪ ለሙስና ተጋላጭ የሆኑ 210 ሠራተኞችም ሀብታቸውን እንዲያስመዘግቡ ተደርጓል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ አካውንት | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content

የታወር ስርቆትን ለመከላከል የሚያስችሉ አሰራሮች ለመተግበር ታቅዷል …….///…… ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣውን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ስርቆት ለመከላከል የሚያስችሉ ስልቶችን ለመተግበር መታቀዱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት አስታወቀ። በጽ/ቤቱ የአስተዳደራዊ ጉዳዮችና ዶኩመንቴሽን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለፁት የስርቆት ተግባሩ በተቋሙ ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ከማድረሱም ባሻገር ለኃይል መቆራረጥ ምክንያት እየሆነ መጥቷል፡፡ ተቋሙ የሚያስተዳድራቸው ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች በመላው ሀገሪቱ የተዘረጉ በመሆናቸው ከክልል ርዕሰ መስተዳደሮች ጀምሮ እስከ ቀበሌ አመራሮች የሚደርስ ቋሚ የግንኙነት እና የውይይት መድረኮች ለመፍጠር እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ስርቆት በተደጋጋሚ በሚከሰትባቸው አካባቢዎች ከሚገኙ የአስተዳደር አካላት እና የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር በመሆን ችግሩን ከመሰረቱ ለማመፍታት የሚያስችሉ ሥራዎች እንደሚሰሩም ነው ያስታወቁት፡፡ እንደ አቶ ዋለ ገለፃ ከአስተዳደራዊ ሥራዎች ባሻገር ችግር በዘላቂነት ለመፍታት በቴክኖሎጂ የተደገፉ የተለያዩ አሰራሮችን ለመተግበር ታቅዷል፡፡ ከእነዚህ መካከል የታወር ስርቆትን ለመከላከል የሚያግዙ የታወር መቃኛ ሴንሰር (Tower Surviellance System) እና የኤሌክትሪክ ትራንስሚሽን መከታተያ ሴንሰር ተግባራዊ ለማድረግ መታቀዱን ጠቁመዋል፡፡ የፊዚካል ሴኪዩሪቲ አቅምን ለማጎልበት የሚያስችሉ የአደረጃጀት እና የማዘመን ሥራዎች እንደሚከናወኑም ገልፀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2015 ዓ.ም ብቻ በኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት ሥርቆት ከ100 ሚሊየን ብር በላይ ኪሳራ እንዳጋጠመው መዘገባችን ይታወሳል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሰኔ 25 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ አካውንት | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content
+3

በትራንስፎርመር ላይ ባጋጠመ ችግር የኃይል መቋረጥ አጋጥሟል ........///.......... በመቀሌ ማከፋፈያ ጣቢያ ባለ 33 ኪሎ ቮልት ፓወር ትራንስፎርመር ላይ ባጋጠመ ችግር የተነሳ ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፋ የሰሜን ሪጀን የኦፕሬሽንና ጥገና መምርያ ዳይሬክተር አቶ ሮቤል ገ/እግዚአብሔር እንደገለፁት በትራንስፎርመሩ ላይ በገጠመው ችግር የተነሳ በመቀሌ ኢንዲስትሪ ፓርክ እና 70 ካሬ አካባቢ ኃይል ተቋርጧል። በተጨማሪም በሀገረ ሠላም እና በህንጣሎ ዋጀራት ወረዳዎችና በዙሪያቸው ባሉ ቀበሌዎች እንዲሁም በኢታካ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ኃይል መቋረጡን ኃላፊው ገልፀዋል። ይሁንና ከማከፋፈያ ጣቢያው በ15 ኪሎ ቮልት ኃይል ሲያገኙ የነበሩ አካባቢዎች ኃይል እንዳልተቋረጠባቸው አስረድተዋል። ትራንስፎርመሩ ላይ የገጠመውን ችግር ለማወቅ የሚያስችሉ ሥራዎች መጀመራቸውን ተናግረዋል። ችግሩ የትራንስፎርመር ዋይንዲንግ ላይ የተከሰተ ከሆነ ሌላ ትራንስፎርመር መቀየር ሊያስፈልግ እንደሚችል ጠቁመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሰኔ 24 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ አካውንት | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content

በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎቹ ሲከናወን የቆየው የጥገና ሥራ ተጠናቀቀ ...///... የአዋሽ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የተንሸራታች መሬት መከላከያ ግንብና የመንገድ ጥገና ሥራዎች መጠናቀቃቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኮንስትራክሽን የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ አስታወቀ፡፡ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎቹ ውስጥ ሲከናወኑ የቆዩት የአፈር መናድ መከላከያና የመንገድ ጥገና ሥራዎች መጠናቀቃቸውን አስመልክቶ የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች የመስክ ጉብኝት አካሂደዋል። በመስክ ጉብኝቱ ወቅት ገለፃ ያደረጉት በመምሪያው የሲቪል ሥራዎች ጥገና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ግርማ መንገሻ እንደገለፁት በጣቢያው የተገነባው የተንሸታራች መሬት መከላከያ ግንብ ሥራ 110 ሜትር ርዝመትና 10 ሜትር ከፍታ አለው፡፡ በጣቢያዎች ውስጥ 125 ሜትር የሚሸፍን የመንገድ ጥገና ሥራ መከናወኑንም ነው ሥራ አስኪያጁ በጉብኝቱ ወቅት የገለፁት። የግንባታ ሥራውን በሰባት ወራት ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለማስረከብ ከኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ጽ/ቤት ጋር ኮንትራት ተፈርሞ ሥራው ቢጀመርም በተለያዩ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ምክንያቶች በታሰበው ፍጥነት ግንባታውን ማከናወን እንዳልተቻለ ጠቁመዋል። ግንባታው የሚከናወንበት ቦታ ዐለታማ መሆኑና የተለያዩ ከባድ ማሽነሪዎችን መጠቀም የግድ ሆኖ መገኘቱ ፕሮጀክቱን ፈታኝ አድርጎት እንደነበር ነው ኢንጅነር ግርማ የገለፁት። የአዋሽ ወንዝ በፈጠረው የመሬት መንሸራተት ሳቢያ የጣቢያው ሠራተኞች ከመኖሪያ ቤት ወደ ኃይል ማመንጫ ቤት ተንቀሳቅሰው ለመስራት ተቸግረው እንደነበር ነው የጠቀሱት። ለፕሮጀክቱ መጠናቀቅ የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽ እና የኢንጅነሪንግ ዘርፎች ለነበራቸው ቀና ትብብርና ቅንጅት ምስጋና ያቀረቡት ኢንጂነር ግርማ ፕሮጀክቱ የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ በኃይል ማመንጫዎች እያከናወናቸው ከሚገኙ የጥገና ሥራዎች ውስጥ ትልቁ መሆኑን ለጎብኚዎች አስረድተዋል። የፕሮጀክቱ ሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘውዱ ሸንቁጤ በበኩላቸው በወቅቱ የነበረው የግንባታ ዕቃዎች ዋጋ መናርና የግንባታ ማሽነሪዎች ተደጋጋሚ ብልሽት ሥራውን በተያዘው የጊዜ ገደብ አጠናቆ ለማስረከብ ማነቆ ሆነው መቆየታቸውን ተናግረዋል። በኃይል ማመንጫ ጣቢያው የተንሸራታች መሬት መከላከያ ግንብና የመንገድ ጥገና ሥራዎችን ለማከናወን ከ4 ሺህ 500 በላይ ኩንታል ሲሚንቶ መጠቀማቸውንም ነው የገለፁት። እንደ አቶ ዘውዱ ገለፃ ፕሮጀክቱን አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ ከ36 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ጠቅሰዋል። ከአዲስ አበባ በደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ 125 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኙት የአዋሽ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እያንዳንዳቸው 32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም አላቸው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሰኔ 24 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ አካውንት | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content
+1

photo content
+9

ዘርፉ በራስ አቅም ባከናወነው ሥራ ከ63 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳኑን አስታወቀ …..…///……… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን የሲቪል ጥገና ሱፐርቪዥን ቢሮ በራስ አቅም ባከናወነው የመንገድ ሥራ ከ63 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳኑን አስታወቀ፡፡ የቢሮው ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ደበላ እንደገለጹት በጊቤ አንድ እና በጊቤ ሁለት የሚገኙት የጠጠር መንገዶች በመጎዳታቸው የዕለት ከዕለት የኦፕሬሽን ሥራዎች ላይ ጫና ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡ በጊቤ አንድ የ11 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር እና በጊቤ ሁለት የውሃ መቀበያ ወይም ኢን ቴክ መግቢያ 5 ኪሎ ሜትር የሚሆኑ የጠጠር መንገዶቹን ለመጠገን በ98 ሚሊዮን ብር ለኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ተሰጥቶ ነበር ብለዋል፡፡ ይሁን እንጂ ኮርፖሬሽኑ ከስምምነቱ በኋላ የዋጋ ማሻሽያ ማድረግ በመፈለጉ የቀጥታ ግዢው እንዲሰረዝ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ የቀጥታ ግዥው ከተሰረዘ በኋላ የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስፈላጊ ማሽነሪዎችን በመከራየት ሥራው በሲቪል ጥገናና ሱፐርቪዥን ቢሮ ባለሙያዎች እንዲሰራ በመወሰን ወደ ሥራ መገባቱን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ በሲቪል ጥገና ሱፕርቪዥን ቢሮ እየተከናወነ ያለው የሁለቱ መንገዶች አፈጻጸም አሁን ላይ ከ98 በመቶ በላይ መድረሱን አቶ ብርሃኑ ጠቁመዋል፡፡ እንደ አቶ ብርሃኑ ገለጻ የመንገድ ሥራው በክፍሉ ሠራተኞች መከናወኑ የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን አቅርቦት ከነበረው ከ63 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ከማዳኑም በተጨማሪ ተቋሙ የባለሙያዎቹን አቅም እንዲጠቀም እና የዕውቀት ሽግግር እንዲኖር ዕድል መፍጠሩን አብራርተዋል፡፡ ቀሪ ሥራዎችን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የተናገሩት አቶ ብርሃኑ የመንገዶቹ መጠናቀቅ የጣቢያዎችን የየዕለት ኦፕሬሽን ሥራዎች የተሳለጡ እንዲሆኑና ለሰራተኛው ምቹ የሥራ ከባቢን የሚፈጥር መሆኑን ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 20 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+8

ከፍተኛ ጭነት በሚበዛባቸው ሰዓታት እስከ 10 በመቶ የኃይል መቋረጥ ሊያጋጥም ይችላል .......///........ በግሪድ ላይ ባጋጠመ የሲስተም ችግር የተነሳ ከፍተኛ ጭነት በሚበዛበባቸው ሰዓታት እስከ 10 በመቶ የሚደርስ የኃይል መቋረጥ ሊያጋጥም እንደሚችል በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ። በማዕከሉ የሪል ታይም ኦፕሬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ጉልላት እንግዳ እንዳስታወቁት ያጋጠመውን የቴክኒክ ችግር በፍጥነት ለመቅረፍ የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው። በመሆኑም የተጀመረው ሥራ እስኪጠናቀቅ ድረስ ህብረተሰቡና ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ ሥራ አስኪያጁ ጠይቀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ሰኔ 19 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የተቋሙ የሥራ አመራር አባላት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሚዲያ ኮምፕሌክስን ጎበኙ ……..///……... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻና የሥራ አመራር አባላት ትናንት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሚዲያ ኮምፕሌክስን ተዟዙረው ጎብኝተዋል። ጉብኝቱ በተቋማቱ መካከል የተጀመሩ የትብብር ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ያለመ ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር አባላት የኮርፖሬሽኑን የተለያዩ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ስቱዲዮች እና መቆጣጠሪያ ክፍሎች እንዲሁም የቤተ-መፅሐፍትና የአውደ- ርዕይ ማሳያ ቦታዎችን ጎብኝተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 19 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

ተቋሙ ከኢቢሲ ጋር የነበረውን የሥራ ግንኙነት የሚያድስ ስምምነት ተፈራረመ ......///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እያከናወናቸው ያሉ ሥራዎችን ለህብረተሰቡ የበለጠ ለማስተዋወቅ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ ለመስራት ተስማማ፡፡ ስምምነቱ ተቋሙ እያከናወናቸው ያሉ ሥራዎችን በዜና፣ በመደበኛ ፕሮግራሞች እና በዶኩመንታሪ ዝግጅት እንዲሁም በአጫጭር መልዕክቶች ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ቀደም ሲል የነበረውን ስምምነት ለማደስ መሆኑ በፊርማ ሥነ ስርዓቱ ላይ ተገልጿል፡፡ ሥምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጌትነት ታደሰ ተፈራርመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በፊርማ ስነ-ሥነሥርዓቱ ወቅት እንደተናገሩት የተፈረመው ስምምነት በሁለቱ ተቋማት መካከል የነበረውን የሥራ ግንኙነት ለማጠናከር እና ካለፈው ተሞክሮ በመውሰድ የበለጠ ሥራ ለመሥራት ያግዛል። ሥምምነቱ ተቋሙ እያከናወናቸው ያሉ የኃይል መሰረተ ልማት ግንባታዎችን በቴሌቪዥንና በሬዲዮ ቻናሎች እንዲሁም በኢቢሲ ዲጂታል ሚዲያ ለህብረተሰቡ በማድረስ የተቋሙን መልካም ገጽታ ለመገንባት ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልፀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አንጋፋ የኃይል አቅራቢ ተቋም በመሆኑ በህግ የተሰጠውን ተግባርና ኃላፊነት በህብረተሰቡ ዘንድ የበለጠ እንዲታወቅ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ተቋሙ ቀፈም ሲል ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር በመተባበር ሲሠራቸው የነበሩ የገፅታ ግንባታ ሥራዎች ተቋሙን በማስተዋወቅ  ረገድ ለውጥ ማሳየት ጀምረዋል። ይሁንና ተቋሙን እየፈተኑት የሚገኙት የካሳ ክፍያ፣ የወሰን ማስከበር እና የኃይል መሠረተ ልማት ስርቆት ለህብረተሰቡ አስተማማኝ ኃይል እንዳይቀርብ ከማድረጋቸውም ባሻገር በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ትልቅ ጫና እያሳደሩ በመሆኑን በስፋት ሊሰራባቸው እነወደሚገባ አሳስበዋል። በተጨማሪም የተቋሙን ብራንድ በማስተዋወቅ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መካከል ያለውን ልዩነት ህብረተሰቡ እንዲገነዘብ ለማድረግ እንዲሰራ ሥራ አስፈፃሚው ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጌትነት ታደሰ በበኩላቸዉ የተደረገው ስምምነት ሁለቱ ተቋማት የጀመሩትን የትብብር ሥራ ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን አንስተዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ታላቁ የህዳሴ ግድብን ጨምሮ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን የሚገነባ ተቋም መሆኑን የጠቀሱት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ሚዲያ በተቋም ገፅታ ግንባታ ሥራ ውስጥ የሚኖረውን ፋይዳ በመረዳት ተቋሙ እየሰራ ያለውን ሥራ በብሔራዊ ሚዲያው ለማስተዋወቅ ኢቢሲን በመምረጡ  ደስተኛ ነን ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ለሀገር እሴት የሚጨምሩና ለዕድገት ትልቅ ፋይዳ ያላቸው ፕሮጀክቶችን በማስተዋወቅ በመሠረተ ልማቶች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ህብረተሰቡ እንዲከላከልና እንዲጠብቅ የማስገንዘብ ሥራ በትኩረት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። ተቋማቸው ሀገሪቱ በኤሌክትሪክ ኃይል ልማት የምታደርገውን እንቅስቃሴ እና ወደፊት የያዘችውን ዕቅድ ለማህበረሰቡ የማሳወቅ ሥራ እንደሚሰራ ገልፀዋል። የኮሙዩኒኬሽን ሥራ ውጤት በሂደት የሚታይ ቢሆንም በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ለማምጣት ተቋማቸው ይሠራል ብለዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ሰኔ 18 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9