fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 537 مشترک است و جایگاه 8 357 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 176 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 537 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 01 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 22 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 4 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 25.24% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.50% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 921 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 563 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 9 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 02 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 537
مشترکین
+424 ساعت
-357 روز
+2230 روز
آرشیو پست ها
ተቋሙ አዲስ የግንባታ ማኑዋል ተግባራዊ በማድረጉ ለውጦች እየታዩ መሆናቸው ተገለፀ ………///……… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ አዲስ የግንባታና ክትትል የአሰራር ማኑዋል ተግባራዊ በማድረጉ በሥራ ጥራትና ቅልጥፍና ላይ ተስፋ ሰጪ ለውጦች መታየታቸውን በዘርፉ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የደብረታቦር ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ከፈለኝ እንደገለፁት የአደረጃጀት እና አሰራር ማኑዋሉ ተግባራዊ በመደረጉ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅ የሚያስችሉ አበረታች ለውጦች ታይተዋል፡፡ ቀደም ሲል በነበረው አሰራር ግዢ በማዕከል ስለሚፈፀም የግንባታ ግብዓቶች በጊዜው እንደማይቀርቡ የተናገሩት አቶ ቴዎድሮስ በአዲሱ ማኑዋል መሠረት መምሪያው የራሱን የግዥ ክፍል አቋቁሞ ወደ ሥራ በመግባቱ ለግንባታ የሚውሉ ዕቃዎች በወቅቱ ማቅረብ ተጀምሯል፡፡ ለግንባታ ሥራ የሚውሉ የፌሮ ብረቶች፣ የመጋዘን ግንባታ ዕቃዎች እና ማሽነሪዎች በወቅቱ በመቅረባቸው የደብረታቦር ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ መጀመር በተበሰረበት ዕለት ሥራ መጀመራቸውን እንደአብነት ጠቅሰዋል፡፡ እንደ አቶ ቴዎድሮስ ገለፃ በአዲሱ የአሰራር ማኑዋል መሰረት ፕሮጀክቶችን በጥራትና በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ በማከናወን በምስራቅ አፍሪካ ብሎም በአፍሪካ ብቁና ተወዳዳሪ ኮንትራክተር ለመሆን እየተሰራ ነው፡፡ የግንባታ ሥራ ከመጀመሩ በፊት የዲዛይን ስራዎችን በማጠናቀቅ፣ የግንባታ ዋጋ በማውጣት እና የዶክመንቴሽን ሥራዎች በማከናወን ዓለም አቀፍ የኮንትራክተር ስታንዳርድ የሚያሟላ የኃይል ግንባታ ተቋም ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ ዘርፍ የደብረታቦር ማከፋፈያ ጣቢያ የአማካሪ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አቶ እሸቱ ፋንቱ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ እና ጥራት እየተገነባ መሆኑን በየዕለቱ በመከታተልና የማስተካከያ እርምጃዎች በመውሰድ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡ ምንም እንኳ ተቋራጩ እና አማካሪው ከአንድ ተቋም ቢሆኑም ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜና ጥራት መሰረት እንዲከናወን ከወትሮው በተለየ መንገድ በሥራ ላይ ክትትል እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡ የፕሮጀክቱን ግንባታ መቆጣጠር ብቻ ሳይሆን የጥራትም ሆነ የግንባታ ጊዜውን የሚያጓትቱ ሁኔታዎች ሲፈጠሩ ለግንባታ ተቋራጩ ወቅቱን የጠበቀ ምክረሃሳብ በማቅረብ ችግሮች በአፋጣኝ እንዲፈቱ ይደረጋልም ብለዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 01 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም በአይ ሲ ቲ አፕሊኬሽን ኦፊሰር 1ኛ የስራ መደብ በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል ባለን ክፍት ቦታ መሰረት የስም ዝርዝራችሁ ከ1 – 10 (አንድ እስከ አስር) የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍ ፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከግንቦት 29 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ሜክሲኮ ኬኬር ህንጻ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት 2ኛ ፎቅ የሰራተኛ ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡

photo content
+4

የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን የኃይል ማከፋፈያ ግንባታ በተያዘለት መርሐግብር በመከናወን ላይ ነው …….///…… በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ በመገንባት ላይ የሚገኘው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን የኃይል ማከፋፈያ ፕሮጀክት ግንባታን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የግንባታው ፕሮጀክት ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ የፕሮጀክቱ ሳይት መሐንዲስ አቶ ገ/ፃዲቅ ገ/ህይወት እንደገለፁት የፕሮጀክቱ ሥራ ከተጀመረ ሁለት ወራት ቢጠጋውም የሰራተኞች መኖሪያና የቢሮ ግንባታ የመሰረት ቁፋሮ በማጠናቀቅ የኮለን ማቆም ሥራዎች ተጀምረዋል፡፡ የኃይል ማከፋፈያውን ቦታ የአፈር ቆረጣ ሥራ መጀመሩን እና በቀጣይ የመሰረት ቁፋሮ እና የአርማታ ሥራዎች ለማከናወን ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን አስታውቀዋል፡፡ የግንባታ ሥራው በተቋሙ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ እንደሚከናወን እና በአሁኑ ጊዜ ከ70 በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች የስራ ዕድል መፍጠሩን ገልፀዋል፡፡ አጠቃላይ ሥራው 15 በመቶ መድረሱን የገለፁት መሐንዲሱ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ረገድ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡ ስድስት ሔክታር መሬት ላይ የሚያርፈውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት እስከ ጥቅምት 2017 ዓ.ም ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዟል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 29 ቀን 2015 ዓ.ም

ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም በፕሮኪዩርመንት 1ኛ የስራ መደብ በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት
ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም በፕሮኪዩርመንት 1ኛ የስራ መደብ በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍ ፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከግንቦት 29 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ሜክሲኮ ኬኬር ህንጻ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት 2ኛ ፎቅ የሰራተኛ ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡

photo content
+5

የሥርዓተ ፆታ ጉዳይን በሁሉም ዘርፎች አካቶ መስራት ይገባል ተባለ ……..///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥርዓተ ፆታ ጉዳይን በሁሉም ዘርፎች አካቶ መስራት እንደሚገባ በተቋሙ የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች መምሪያ አሳሰበ፡፡ ከተቋሙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ ባለሙያዎች በሥርዓተ ፆታ እና ልማት እንዲሁም በስርዓተ ፆታ ማካተት ዙሪያ በኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ በሥልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች መምሪያ ዳይሬክተር በተወካያቸው አማካይነት ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት ሥልጠናው የስርዓተ ፆታ ባለሙያዎች የዕውቀትና ክህሎት ክፍተታቸውን በመሙላት በተቋሙ ስርዓተ ፆታን አካቶ ለመስራት ያግዛል፡፡ በተቋሙ የሴቶች ፎረም ሰብሳቢ ወ/ሮ ምዕራብ ጋሹ በበኩላቸው በስርዓተ ፆታ ልማት እና አካቶ ዙሪያ የተሰጠው ሥልጠና ለሚሰሩት ሥራ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርላቸው ገልፀዋል፡፡ በስልጠናው የተሳተፉ ሰልጣኞችም ሥልጠናው ግንዛቤያቸውን እንደጨመረና ለሚሰሩት ሥራ ትልቅ ስንቅ እንደሚሆነላቸው ገልፀዋል፡፡ በኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ለ3 ቀናት የተሰጠው ስልጠና ሲጠናቀቅ ለተሳታፊዎች የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 28 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

በተቋሙ እየተከናወኑ ያሉ የማዘመን ሥራዎች ውጤት እየተገኘባቸው ነው ……..///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እየተከናወኑ ያሉ አሰራርን የማዘመን ሥራዎች ውጤት እየተገኘባቸው መሆኑን በተቋሙ የሞደርናይዜሽን መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ገነቱ ደሳለኝ እንደተናገሩት ተቋሙ በርካታ ሀብት የሚያንቀሳቅስ ቢሆንም የንብረት አያያዙ ግን በቴክኖሎጂ የተደገፈ አልነበረም፡፡ የተቋሙን አሰራሮች በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የሥራ ሂደቶች አሰራር ወጪ ቆጣቢ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ እንዲሆን የሚያግዙ የተለያዩ ሞጁሎች ተቀርጸው እየተገበሩ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክት ሲስተም፣ የግዥና ንብረት አስተዳደር፣ የፋይናንሻል ሪፖርቲንግ እንዲሁም የኢአርፒ ሞጁሎች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ አቶ ገነቱ እንዳሉት በተቋሙ ውስጥ ከሰው ኃይል አስተዳደር፣ ከፋይናንስ ሪፖርት ስርዓት፣ ከግዥና ከንብረት አስተዳደር እንዲሁም ከፕሮጀክት አስተዳደር ጋር የተያያዙ አሰራርን የማዘመኛ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ እየተደረጉ ይገኛሉ፡፡ የፕሮጀክቶቹ መተግበር የሥራ ቅልጥፍናን በማምጣት፤ ወጪን፣ ጊዜንና የመረጃ ክፍተትን በመቀነስ ተቋሙ ውጤታማ እንዲሆን እያገዙት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከንብረት አስተዳደር ጋር በተያየዘ ከዚህ በፊት በርካታ ችግሮች እንደነበሩ የጠቆሙት ዳይሬክተሩ የማዘመን ሥራው በእያንዳንዱ አካባቢ የሚገኙ የተቋሙ ንብረቶችን በመረጃ ቋት እንዲገቡ በማድረግ ሀብቱን ወጪ ቆጣቢና በሚመች መልኩ ለማስተዳደር ተችሏል ብለዋል፡፡ ከሰው ሀይል እና ፋይናንስ አስተዳደር ጋር ተያይዞ በተሰሩት ሥራዎችም የመረጃ አያያዝ ክፍተቶችን በመቅረፍ ዘመናዊ የመረጃ አያያዝ እና ወጥ የሆነ የፋይናንስ ሪፖርት ስርዓት እንዲኖር መደረጉን አቶ ገነቱ አስረድተዋል፡፡ እየተተገበሩ ባሉ የማዘመን ሥራዎች ላይ በርካታ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎች የተሰጡ ሲሆን አሰራሮችም በየሥራ ዘርፉ ባሉ አመራሮች ለሠራተኞች በየደረጃው ስለመተዋወቃቸው ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ በትግበራ ወቅት የሥራ ዘርፎች ለሚያጋጥማቸው ችግር ሙያዊ ድጋፎች እየተደረጉ እንደሆነም ገልፀዋል፡፡ የሥራ ክፍሎች አሰራሮችን ተግባራዊ እያደረጉ መሆናቸውንና አለመሆናቸውን ለመከታተልና ለማረጋገጥ፤ ሠራተኛው በአሰራሩ ላይ ያለውን የእርካታ ግብረ መልስ ለማወቅ እና የድጋፍ ጥያቄ የሚቀርብበት "ዞፍ" የሚባል አሰራር ተዘርግቶ ተግባራዊ እየተደረገ እንደሆነም አቶ ገነቱ አመልክተዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 28 ቀን 2015 ዓ.ም

የፕሮግራም ጥቆማ የአዳማ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ 51 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው፤ የንፋስ ኃይል ማመንጫው እያንዳንዳቸው አንድ ነጥብ አምስት ሜጋ ዋት ኃይል ማመንጨት የሚችሉ 34 የ
የፕሮግራም ጥቆማ የአዳማ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ 51 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው፤ የንፋስ ኃይል ማመንጫው እያንዳንዳቸው አንድ ነጥብ አምስት ሜጋ ዋት ኃይል ማመንጨት የሚችሉ 34 የንፋስ ማመንጫ ተርባይኖች አሉት፡፡ 117 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወጪ የተደረገበት የአዳማ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የንፋስ ኃይል ማመንጫ ሲሆን የአዲስ አባባ ዩኒቨርስቲ በአማካሪነት፤ የቻይና ኩባንያ ደግሞ በተቋራጭነት ተሳትፈዋል፡፡ የዚህን የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራ የሚያከናውኑት ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ሲሆኑ ከ65 እስከ 70 ሜትር ከፍታ በመሰላል በመውጣት አስቸጋሪ የሚባለውን የንፋስ ተርባይን የመፈተሸና መጠገን ሥራ ያከናውናሉ፡፡ በተለይ ወጣት ሴት ኢንጂነሮች በሥራው ላይ ከፍተኛ ተሳትፎ እያደረጉ መሆናቸው ትልቅ ስሜት ይፈጥራል፡፡ በዚህ ላይ የተዘጋጁትን ፕሮግራሞች በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የኦሮምኛ ቋንቋ ቻናል ዛሬ ምሽቱ ከ12፡10 ጀምሮ እንዲሁም በአማርኛ ቋንቋ በኢቲቪ የዜና ቻናል ከምሽቱ 3፡30 ጀምሮ እንድትከታተሉ በአክብሮት እንጋብዛለን፡፡ ከዚህ ቀደም የተላለፉትን ፕሮግራሞች ለመመልከት ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ፡፡ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower

photo content
+9

የደጀን ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ 75 በመቶ ደርሷል ……..///……. የደጀን ባለ 230 ኪ.ቮ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ከሁለት ወራት በኋላ የፍተሻ እና ሙከራ ስራ እንደሚጀመር ፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አስታወቀ፡፡ የፕሮጀክቱ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች አስተባባሪ አቶ ኃይለሚካኤል አሰፋ እንደገለፁት አብዛኛዎቹ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች እየተገባደዱ ነው፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው አንድ ባለ 63 እና አንድ ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ፓወር ትራንስፈርመሮች ተከላ ስራ በመጠናቀቁ የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ 75 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል፡፡ አቶ ኃይለሚካኤል እንደገለፁት የዕቃ አቅራቢው ኩባንያ አስፈላጊ ዕቃዎችን በወቅቱ የሚያቀርብ ከሆነ ቀሪ ሥራዎችን በማጠናቀቅ የፍተሻ እና የሙከራ ሥራ በሐምሌ ወር የሚጀመር ይሆናል፡፡ የፕሮጀክቱ ሲቪል ሥራዎች አስተባባሪ አቶ ሚሊዮን ታምራት በበኩላቸው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ሥራዎች በአብዛኛው ተጠናቀው የጠጠር ንጣፍ፣ የአጥር እና የውሃ ማፋሰሻ ቦዮች ግንባታ በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራት መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ የዘንድሮ የበልግ ዝናብ መራዘሙና የሲሚንቶ እጥረት ማጋጠሙ ለግንባታው መዘግየት አስተዋጽኦ የነበራቸው ቢሆንም የሲሚንቶ እጥረቱ መፍትሔ በማግኘቱ ግንባታው መፋጠኑን ገልፀዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የዚሁ ፕሮጀክት አካል በሆነው የደብረ ማርቆስ - ደጀን ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የኤሌክትሪክ ገመድ ዝርጋታ ተጀምሯል፡፡ የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ እንዳለ ላቀው እንደገለፁት የዝናብ ሁኔታው ከተስተካከለ አጠቃላይ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታውን በአንድ ወር ውስጥ በማጠናቀቅ የፍተሻ እና የሙከራ ሥራዎችን መጀመር ይቻላል፡፡ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ የግንባታ ሥራ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ እየተከናወነ ሲሆን የማማከር ሥራውን ደግሞ የተቋሙ የኢንጂነሪንግ ዘርፍ እየተሳተፈበት ይገኛል፡፡ ለ330 የአካባቢው ወጣቶች ጊዜያዊ የስራ ዕድል የፈጠረው ይህ ፕሮጀክት ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለአካባቢው ማህበረሰብና በዙሪያው ለሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 24 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

ሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ ውጤታማ እንዲሆን በትኩረት እየተሰራ ነው .........///.......... ሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ሲስተም ፕሮጀክት ውጤታማ እንዲሆን ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሚገኝ በተቋሙ የሞደርናይዜሽን መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ገነቱ ደሳለኝ እንዳስታወቁት ፕሮጀክቱን ውጤታማ ለማድረግ በመጀመሪያው ምዕራፍ የተስተዋሉ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመገምገም ወደ ሥራ ተገብቷል። ፕሮጀክቱ ውጤታማ እንዲሆን በሁለተኛው ምዕራፍ በሚተገበሩ ሞጁሎች ላይ የሚካተቱ ጉዳዮችን ለመለየት እና ወሰኑን ለመወሰን የሚያስችል አውደ ጥናት ተካሂዷል። በመጀመሪያው ምዕራፍ ትግበራ ላይ ሞጁሎችን ወሰን በመለየት እና የሥራ ክፍሎች ድርሻቸውን አውቀው በመስራት በኩል ክፍተቶች በመኖራቸው በትግበራ ሥራው  ላይ የተለያዩ ችግሮች አጋጥመው እንደነበር አቶ ገነቱ አስታውሰዋል። እየተካሄደ ያለው አውደ ጥናት በየሥራ ክፍሎች የሚተገበሩ ሞጁሎችን ወሰን ለመለየት እና በትግበራው ላይ የሚሳተፉ አካላትን ኃላፊነት በአግባቡ ለማስቀመጥ እንደሚያግዝ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። ለሳፕ ትግበራ ውጤታማነት አውደ ጥናቱ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ጠቁመው የሚመለከታቸው አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡና በቁርጠኝነት እንዲወጡም አሳስበዋል። በኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢአርፒ ሳፕ ሲስተም ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አቶ ማቱሳላ ዘውዴ በበኩላቸው የሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ሲስተም በስድስት ደረጃዎች እንደሚተገበር እና በፕሮጀክቱ ላይ 15 ሞጁሎች ተግባራዊ እንደሚደረጉ ተናግረዋል። የሞጁሎቹን ወሰን በተቋማቸው በኩል ከቀረቡት ስታንዳርዶች በተጨማሪ ሲስተሙን በሚጠቀመው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል እንዲካተቱ የሚፈለጉ ይዘቶች በመነጋገር እንደሚጨመሩ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜና በጀት መሠረት እየተከናወነ እንደሚገኝ ያነሱት ሥራ አስኪያጁ ፕሮጀክቱን በተቀመጠለት መርሃ ግብርና ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ለማጠናቀቅ በየደረጃው የሚገኙ የተቋማቸው አመራሮችና በፕሮጀክቱ ሥራ ላይ የተመደቡ ባለሙያዎች በቁርጠኝነት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ እንደተናገሩት አውደ ጥናቱ በየሥራ ክፍሉ በሚተግበሩ ሞጁሎች ላይ መካተት ያለባቸውን ጉዳዮች በአግባቡ ለይቶ ለማስቀመጥ ይረዳል። በአውደ ጥናቱ ላይ የሳፕ መለኪያ ምን እንደሚመስል በተግባር እየታየ እንደሆነ ገልፀው ይህም የተቋሙን ፍላጎት ከሳፕ ሲስተም  መለኪያዎች ጋር በማገናኘት የሲስተሙ ወሰን በምን መልኩ መቀረፅ እንዳለበት ለማሳየት ያግዛል ነው ያሉት። በሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ሲስተም ትግበራ ላይ ከሰው ሀብት አስተዳደር ጋር በተያያዘ ሰባት ንዑሳን ሞጁሎች እንደሚተገብሩ ጠቁመው ሞጁሎቹ በተቀመጠው አሰራር መሠረት ተግባራዊ እንዲሆኑ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩም አቶ አታላይ ተናግረዋል። በአውደ ጥናቱ ላይ የሁለተኛው ምዕራፍ ከሚተገበርባቸው የሥራ ክፍሎች የተውጣጡ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ተሳትፈዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 23 ቀን 2015 ዓ.ም

ኢትዮጵያ ካሏት ወንዞች መካከል በአግባቡ የተጠቀመች የአዋሽ ወንዝን ነው፡፡ የአዋሽ ወንዝ ለመስኖ፣ ለንፁህ መጠጥ ውሃ፣ ለኃይል ማመንጫና ለቱሪዝም በመዋል ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡ በቀዳሚነት ከሚጠቀሱት የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች መካከል ሦስቱ የሚገኙት በአዋሽ ወንዝ ላይ ነው፡፡ በወንዙ ላይ የቆቃ፣ የአዋሽ 2ኛ እና 3ኛ የውሃ ኃይል ማመንጫዎች ይገኛሉ፡፡ በዚህ ላይ የተዘጋጀውን ፕሮግራም ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ፡፡ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower

photo content
+7

ፕሮጀክቱ የከተማዋን እና የአካባቢውን የኤሌክትሪክ ኃይል ጥያቄ የሚመልስ ነው ተባለ ……….///………. የበቆጂ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የከተማዋን እና የአካባቢውን ነዋሪ የዘመናት የኤሌክትሪክ ኃይል ጥያቄ እንደሚመልስ የበቆጂ ከተማ ከንቲባ እና ነዋሪዎች ገለፁ። የከተማዋ ከንቲባ አቶ ሁሲያ አሚን እንደገለፁት የበቆጂ ከተማ ኢትዮጵያን በዓለም ያስተዋወቁ አንጋፋ አትሌቶችን ያፈራች ቢሆንም በከተማዋ እና በአካባቢው ባለው የኃይል እጥረት ምክንያት ታሪኳን የሚመጥን የልማት ሥራ አልተከናወነላትም። በመሆኑም የማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት በአካባቢው ላለው የኤሌክትሪክ ጥያቄ ምላሽ እንደሚሰጥ እና የህብረተሰቡን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እንደሚፈታ ከንቲባው ገልፀዋል፡፡ የፕሮጀክቱ መጀመር ከተማዋን የኢንቨስትመንት እና የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ እየተሰራ ያለውን ሥራ በመደገፋ በኩል ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረውም ጠቁመዋል። ከአካባቢው ነዋሪዎች መካከል አቶ ጎበና ሀጂ ሮባ እና አቶ ፈንታዬ ደለሉ በበኩላቸው በአካባቢው በሚያጋጥመው የኃይል መቆራረጥ የተነሳ ለተለያዩ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እንደሚጋለጡ ተናግረው ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ለአገልግሎት ሲበቃ የአካባቢው ኢኮኖሚ እንደሚያነቃቃ ገልፀዋል። የፕሮጀክቱ መጀመር በከተማዋ እና በአጎራባች ወረዳዎችና ቀበሌዎች ለሚገኙ ወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ ይፈጥራል ያሉት ነዋሪዎቹ ፕሮጀክቱ ውጤታማ እንዲሆን በሚችሉት አቅም አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል። የበቆጂ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ወጣት ታሪኩ ዓለሙ እና ሲሳይ ነጋሽ በበኩላቸው ከዚህ በፊት ለወራት ሥራ አጥ ሆነው እንደቆዩ ገልፀው በአሁኑ ወቅት በፕሮጀክቱ ግንባታ ላይ የሥራ ዕድል ስለተፈጠረላቸው ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። የበቆጂ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ ግንቦት 5 ቀን 2015 ዓ. ም በይፋ መጀመሩ ይታወሳል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 21 ቀን 2015 ዓ.ም

የፕሮግራም ጥቆማ ኢትዮጵያ ካሏት ወንዞች መካከል በአግባቡ የተጠቀመች የአዋሽ ወንዝን ነው፡፡ የአዋሽ ወንዝ ለመስኖ፣ ለንፁህ መጠጥ ውሃ፣ ለኃይል ማመንጫና ለቱሪዝም በመዋል ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክቷ
የፕሮግራም ጥቆማ ኢትዮጵያ ካሏት ወንዞች መካከል በአግባቡ የተጠቀመች የአዋሽ ወንዝን ነው፡፡ የአዋሽ ወንዝ ለመስኖ፣ ለንፁህ መጠጥ ውሃ፣ ለኃይል ማመንጫና ለቱሪዝም በመዋል ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡ በቀዳሚነት ከሚጠቀሱት የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች መካከል ሦስቱ የሚገኙት በአዋሽ ወንዝ ላይ ነው፡፡ በወንዙ ላይ የቆቃ፣ የአዋሽ 1ኛ እና 2ኛ የውሃ ኃይል ማመንጫዎች ይገኛሉ፡፡ በዚህ ላይ የተዘጋጁትን ፕሮግራሞች በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የኦሮምኛ ቋንቋ ቻናል ዛሬ ምሽቱ ከ12፡10 ጀምሮ እንዲሁም በአማርኛ ቋንቋ በኢቲቪ የዜና ቻናል ከምሽቱ 3፡30 ጀምሮ እንድትከታተሉ በአክብሮት እንጋብዛለን፡፡ ከዚህ ቀደም የተላለፉትን ፕሮግራሞች ለመመልከት ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ፡፡ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 20 ቀን 2015 ዓ.ም