fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 539 مشترک است و جایگاه 8 340 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 161 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 539 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 28 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 1 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -4 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 24.98% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.34% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 882 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 539 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 8 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 29 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 539
مشترکین
-424 ساعت
-147 روز
+130 روز
آرشیو پست ها
ኢትዮ ኤሌክትሪክ ወሳኝ ድል አስመዝግቧል ........///...... በ11ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ውድድር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሞጆ ከተማን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል። ትናንት በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም በተከናወነው ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከጨዋታ የበላይነት ጋር ሁለት ለባዶ አሸንፏል። የመጀመሪያውን ጎል አጥቂው አቤል ሀብታሙ ከርቀት አክርሮ በመምታት ሲያስቆጥር  ሁለተኛውን ጎል ደግሞ ናትናኤል ሰለሞን በባከነ ሰዓት በ92ኛው ደቂቃ አስቆጥሯል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ ኳስ መስርቶ በመጫወት እንዲሁም በተደጋጋሚ የተቃራኒ ግብ ክልል ላይ በመድረስ የተሻለ እንቅስቃሴ ማድረግ ችሏል። ሞጆ ከተማ በበኩሉ አብዛኛውን የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በጥልቀት በመከላከል ላይ የተመሠረተ አጨዋወት የተከተለ ሲሆን አልፎ አልፎ መልሶ በማጥቃት ጎል ለማስቆጠር ቢጥርም ሳይሳካለት ቀርቷል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ በመጪው እሁድ በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ከወራቤ ከተማ ጋር 12ኛ ጨዋታውን የሚያከናውን ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ጥር  02 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

በተቋሙ ዘመናዊ የመረጃ አያያዝ ሥርዓት ለመዘርጋት የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ..........///........... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዘመናዊ የመረጃ አያያዝ ሥርዓት ለመትከል የሚያስችል የሰነድ አያያዝና አስተዳደር መመሪያ እያዘጋጀ መሆኑን በተቋሙ የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ዘርፍ አስታወቀ። የዘርፉ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ስመኝ አያሌው እንደገለፁት ተቋሙ ከተመሰረተ ጊዜ ጀምሮ የሰነድ አያያዝና አስተዳደር መመሪያ ባለመኖሩ ሰነዶችን በማጣራት አደራጅቶ የመያዝባ የማስወገድ ችግር ነበረ። የቆዩ የተቋሙ ሰነዶች ተጣርተው ባለመደራጀታቸው እና ጊዜ ያለፈባቸው ሰነዶች ባለመወገዳቸው መረጃዎች በቀላሉ እንዳይገኙ አድርጎ መቆየቱን ኃላፊዋ አስታውሰዋል፡፡ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና የተቋሙን ሰነዶች በዘመናዊ መልኩ ለማደራጀት የሚያስችሉ አሰራሮች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑንም ሥራ አስፈጻሚዋ ገልፀዋል፡፡ እንደ ሥራ አስፈጻሚዋ ገለፃ ለቀጣይ ትውልድ የሚተላለፍ ዘመናዊ የመረጃ አያያዝ ሥርዓት በተቋሙ ለመትከል የሚያስችል የሰነድ አያያዝና አስተዳደር መመሪያ እየተዘጋጀ ነው፡፡ በተቋሙ ከ100 ሺህ በላይ የተለያዩ ሰነዶች እንደሚገኙና ሰነዶቹን ለይቶ ለማደራጀት የሰነድ አያያዝ ልምድ ያላቸው ባለሙያዎችን ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች በማዋቀር ወደ ሥራ መገባቱን አስታውቀዋል፡፡ ሥራውን በአግባቡ ለማከናወን ከብሄራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተመፃህፍት ኤጀንሲ በሰነድ አያያዝና አደረጃጀት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና እና ተሞክሮ በመውሰድ በመጀመሪያው ዙር የሰነድ መረጣና ምዘና ሥራዎች መሰራታቸውን ነው ሥራ አስፈፃሚዋ ያብራሩት፡፡ በዚህም 19 ሺህ 740 ፋይል አቃፊዎችና ጥራዞችን የማጣራት ሥራ የተሰራ ሲሆን ከተጣሩት ፋይሎች መካከል 11 ሺህ 788 ቦክስ ፋይልና ጥራዞች እንዲወገዱ መለየቱን ሥራ አስፈፃሚዋ ገልፀዋል፡፡ 127 ታሪካዊ ፋይሎች ደግሞ ወደ ኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመፃህፍት ኤጀንሲ አርካይቭ እንዲገቡ መለየታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት የሰነዶች ልየታ፣ ማደራጀትና የማስወገድ ሥራዎች በበጀት ዓመቱ ይጠናቀቃል ያሉት ወ/ሮ ስመኝ በቀጣይ በሪጅኖችና በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ተመሳሳይ ሥራ ይከናወናል ብለዋል፡፡ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የሰነድ ልየታና ማደራጀት ሥራ ሲጠናቀቅ ቀደም ሲል የነበሩ መረጃዎችን አደራጅቶ በመያዝ እንደተቋም ለሚፈለግ ዓላማ ለማዋል ከማስቻሉም በላይ ታሪካዊ ፋይዳ ያላቸውን ሰነዶች ከጥፋት በማዳን ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ እንደሚጠቅም ወ/ሮ ስመኝ ገልፀዋል፡፡ የተጀመረው ሥራ ሰነዶችን በማስተዳደር ሂደት የሚፈጠሩ የቦታና የጊዜ ብክነትን በማስቀረት ተቋሙን ከአላስፈላጊ ወጪዎች ይታደጋል ተብሎ ይታመናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 01 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

ቋሚ ኮሚቴው በምስራቅ ሪጅን በሚገኙ ማከፋፊያ ጣቢያዎች የመስክ ምልከታ አደረገ --------///---------- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምስራቅ ሪጅን ለሁርሶ ማከፋፊያ ጣቢያ ልዩ ጥበቃ እንዲያደርግ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ። ቋሚ ኮሚቴው ባለፈው ሳምንት በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮች እና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ በምስራቅ ሪጅን የመስክ ምልከታ አድርጓል፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሀመድ እንደገለፁት ቋሚ ኮሚቴው በሁርሶ ማከፋፊያ ጣቢያ እና በሐረር ቁጥር ሦስት ማከፋፊያ ጣቢያ በመገኘት የኦፕሬሽን ሥራዎችን ተመልክቷል፡፡ የሁርሶ ማከፋፈያ ጣቢያ ለምስራቁ የሀገራችን ክፍል ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት እና ለጅቡቲ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቀርብበት ጣቢያ መሆኑ ለቋሚ ኮሚቴ አባላቱ ተገልጾላቸዋል፡፡ የሐረር ቁጥር ሦስት ማከፋፊያ ጣቢያም ለሀረር ከተማና ለአጎራባች የኦሮሚያና የሶማሌ ክልል አካባቢዎች አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ ስለመሆኑ ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል፡፡ የቋሚ ኮሚቴው አስተባባሪ ዶ/ር ዘውዱ ታደሰ በበኩላቸው የሁርሶ ማከፋፈያ ጣቢያ ካለው አስተዋጽኦ አንፃር በሲሲቲቪ ካሜራ የታገዘ ልዩ ጥበቃ እንዲደረግለት፣ አስተማማኝ አጥር እንዲገነባለት እና ተጨማሪ ጥበቃዎች እንዲመደቡለት ጠይቀዋል፡፡ የሐረር ቁጥር 3 ማከፋፊያ ጣቢያም የኃይል አቅርቦቱን የሚያሳድግ ሥራ እንዲሰራለት የኮሚቴው አስተባባሪ አሳስበዋል፡፡ የሁርሶ ማከፋፈያ ጣቢያ በሁርሶ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ማዕከል አቅራቢያ የሚገኝ በመሆኑ ከመደበኛ ጥበቃው የተለየ ጥበቃ እንደማያስፈልገው፣ በሪጅኑ የሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኃይል አቅርቦት የሚያሳድግ የማስፋፊያ እና የአቅም ማሳደግ ሥራ እየተሰራ ስለመሆኑ ለቋሚ ኮሚቴው መገለፁን ዳይሬክተሩ አቶ ወርዲ መሀመድ ገልፀዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 29 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

የገና በዓል ያለምንም የኃይል እጥረት ተከብሯል ……..///…….. በገና በዓል ምንም ዓይነት የኃይል እጥረት አለማጋጠሙን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ፡፡ የማዕከሉ ዳይሬክተሩ አቶ የማነ ኢሳያስ እንደገለፁት ተቋሙ ለበዓሉ ከ3 ሺህ ሰባት መቶ ሜጋ ዋት በላይ ኃይል ለማቅረብ ዝግጅት የተደረገ ቢሆንም በበዓሉ ዋዜማና ዕለት የተመዘገበው ከፍተኛ የኃይል ጭነት 3 ሺህ 331 ነበር፡፡ የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች እና የኤክስፖርት ኃይል ሳይቋረጥ ለበዓሉ ያለምንም ችግር የሚፈለገውን ኃይል ማቅረብ መቻሉ በተቋሙ የተደረገውን ዝግጅት ያሳያል ብለዋል፡፡ ከኃይል እጥረት ጋር ተያይዞ ያጋጠመ የኃይል መቋረጥ አለመኖሩን የገለፁት ዳይሬክተሩ በመቀሌና አካባቢው ግን በዋዜማው ዕለት ለተወሰኑ ሰዓታት ኃይል ተቋርጦ እንደነበር አስታውቀዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ሪጅን የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ዳይሬክተር ሮቤል ገ/እግዚአብሔር እንደተናገሩት በመቀሌና አካባቢው ኃይል የተቋረጠው በመቀሌ ማከፋፈያ ጣቢያ የፊደር መቆጣጠሪያ ላይ በደረሰ የቴክኒክ ችግር ምክንያት ነው፡፡ የ2016 የገና በዓል የኃይል አጠቃቀሙ 3 ሺህ 331 ሜጋ ዋት ሲሆን የአምናው ከፍተኛው የኃይል አጠቃቀም 3 ሺህ 55 ሜጋ ዋት ሆኖ እንደነበር መግለፃችን ይታወሳል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 29 ቀን 2015 ዓ.ም

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን! አደረሳችሁ! መልካም የገና በዓል!
እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን! አደረሳችሁ! መልካም የገና በዓል!

photo content
+5

ለገና በዓል ከ 3 ሺህ ሰባት መቶ ሜጋ ዋት በላይ ኃይል ለማቅረብ ዝግጅት ተጠናቋል ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለገና በዓል በቂ ኃይል ለማቅረብ ዝግጅት ማጠናቀቁን በተቋሙ የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ዳይሬክተር አስታወቁ፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ የማነ ኢሳያስ እንደገለፁት ተቋሙ በዋናነት ኃይል አመንጭቶ የሚያቀርብ እንደመሆኑ መጠን ለገና በዓል የኃይል አቅርቦት ችግር እንዳያጋጥም አስፈላጊውን ዝግጅት አጠናቋል፡፡ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ሁሉም ዩኒቶች ፍተሻ ተደርጎላቸው ዝግጁ የተደረጉ ሲሆን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎችም ፍተሻ መጠናቀቁን ገልፃዋል፡፡ ዘንድሮ ዝግጁ ማድረግ የተቻለው ኃይል ከአምናው ተመሳሳይ የገና በዓል የኃይል አቅርቦት ጋር ሲነፃፀር በሁለት መቶ ሜጋ ዋት ከፍ ያለ መሆኑን ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡ በ2015 የገና በዓል የኃይል አጠቃቀሙ 3 ሺህ ሃምሳ አምስት ሜጋ ዋት በመድረስ በተቋሙ የኃይል አቅርቦት ታሪክ ሪከርድ ሆኖ የተመዘገበ ቢሆንም ዘንድሮ ከበዓሉ አስቀድሞ እስከ 3 ሺህ 536 ሜጋ ዋት የደረሰ የኃይል አጠቃቀም መመዝገቡን አስታውቀዋል፡፡ እንደ አቶ የማነ ገለፃ የገና በዓል የኃይል አጠቃቀም ከሌሎች በዓላት ከፍ የማለት አዝማሚያ ስለሚያሳይ የኃይል እጥረት እንዳያጋጥም ዝግጅት ተደርጓል፡፡ በመሆኑም ህብረተሰቡም ሆነ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች ያለምንም ችግር ኃይል መጠቀም የሚችሉበት ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል፡፡ በኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ የሚመራ እና ከዘርፉ ሁሉም ሪጅኖች የተወከሉበት ኮማንድ ፖስት መዋቀሩን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ ኮማንድ ፖስቱ በማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ችግር ቢያጋጥም አስቸኳይ ጥገና ለማድረግ የሚያስችል ቁጥጥርና ስምሪት የሚሰጥ መሆኑ ታውቋል፡፡ ከሪጅን ማዕከሎች ራቅ ባሉ አካባቢዎችም ከኃይል መሰረተልማቶች ጋር በተያያዘ የሚያጋጥም ችግር ቢኖር አስቸኳይ ጥገና የሚያከናውን ተጠባባቂ የባለሙያዎች ቡድን በየደረጃው ተዋቅሯል ብለዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 27 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+5

ኢትዮ- ኤሌክትሪክ በሊጉ ነጥብ ተጋራ ...........///........ በ10ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ውድድር ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ከቤንች ማጂ ቡና ጋር ያለምንም ጎል ተለያይቷል። በዛሬው ዕለት በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም በተካሄደው መርሐ ግብር ሁለቱም ቡድኖች ተመጣጣኝ የጨዋታ ፉክክር አሳይተዋል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ኳስን መስርቶ በአጭር የኳስ ቅብብል ወደ ሜዳ ቢደርስም በርካታ ያለቀላቸው ኳሶችን አምክኗል። ቤንች ማጂ ቡና በበኩሉ ረጃጅም ኳሶች ቶሎ ቶሎ በተቃራኒው ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ግብ ክልል መድረስ የቻለ ቢሆንም ጠንካራውን የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የተከላካይ ክፍል ግን ማለፍ ሳይችል ቀርቷል። በዛሬው ጨዋታ ነጥብ ተጋርቶ የወጣው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ22 ነጥብ እና በስምንት ንፁህ ጎል ሊጉን እየመራ ይገኛል። ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በመጪው ረቡዕ ጥር 01 ቀን 2016 ዓ.ም ከሞጆ ከነማ ጋር በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም የሚጫወት ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 26 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+8

የተቋሙ ክሊኒክ አገልግሎት አሰጣጥ የሚያሻሽል ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቷል .........///.......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሠራተኞችና ለሥራ መሪዎች አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘውን ክሊኒክ አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የሚያስችል ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱን በተቋሙ የጤና አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡ ሥራ አስኪያጇ ወ/ሮ መሰረት ሙሉጌታ እንደገለፁት በተቋሙ ዋና መ/ቤት በሚገኘው ክሊኒክ የሚሰጠው የህክምና አገልግሎት ሠራተኛው ጤናውን ጠብቆ የተሰጠውን ተልዕኮ እንዲወጣ እያገዘው ነው፡፡ ቀደም ሲል የተቋሙ ሠራተኛ የተሻለ የጤና አገልግሎት እንዲያገኝ ለማድረግ ወደተለያዩ የህክምና ተቋማት ይላክ የነበረ በመሆኑ ሠራተኛው ለእንግልት ተቋሙ ደግሞ ለተጨማሪ ወጪ ሲዳረጉ መቆየታቸውን ወ/ሮ መሰረት አስታውሰዋል፡፡ አዲስ የተገነባው ክሊኒክ የተደራጀ ላብራቶሪ እና መድኃኒት ቤት ያለው በመሆኑ ለሪፈራል እና ለመድኃኒት ግዢ ተቋሙ ያወጣ የነበረውን ከፍተኛ ወጪ ከመቀነሱም ባሻገር ሁሉም ሠራተኛ የህክምና አገልግሎቱን በአንድ መስኮት እንዲያገኝ አድርጎታል ብለዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጇ ገለጻ የጤና አገልግሎቱን በሁሉም የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ተደራሽ ለማድረግ ሠፊ ሥራ ተሰርቷል፡፡ የአምስት ዓመት ፍኖተ ካርታ ዝግጅት ተጠናቆ ለሚመለከተው አካል መቅረቡን ሥራ አስኪያጇ ጠቁመዋል፡፡ የተዘጋጀው ፍኖተ ካርታ የክሊኒኩን አደረጃጀትና የሰው ኃይልን ጨምሮ የህክምና መሳሪያዎች፣ የመድኃኒት ግዥ እና አቅርቦት ለማሻሻል የሚያስችል አቅጣጫ በግልጽ መቀመጡን ሥራ አስኪያጇ አብራርተዋል፡፡ ክሊኒኩ ለሠራተኛው ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት እንዲሰጥና ተቋሙን ካላስፈላጊ ወጪዎች እንዲታደግ አመራሩ ፍኖተ ካርታውን ገምግሞ እንዲያጸድቅ ሥራ አስኪያጇ ጠይቀዋል፡፡ ሠራተኛውም የተቋሙ የጤና አገልግሎት ያወጣቸውን መመሪያ እና ደንቦችን በማክበር አላግባብ የሚወጡ የህክምና ወጪዎችን ለመቀነስ አገልግሎቱን በባለቤትነት ስሜት እንዲጠቀም አሳስበዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 26 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

በማመንጫ ጣቢያው ላይ በተከናወነው የጥገና ሥራ ወጪን ማዳን ተችሏል ………///………. በመልካ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በራስ ኃይል የተከናወነው የኢንስፔክሽን እና የጥገና ሥራ ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ እንዳዳነው የኃይል ማመንጫ ጣቢዎች ኦፐሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የክላስተር 1 ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ እሸቱ ዱባለ እንዳስታወቁት በኃይል ማመንጫ ጣቢያው ብልሽት ደርሶባቸው ለነበሩ ሦስት ጀነሬተሮች ማቀዝቀዣ ሥርዐት እና የፓምፕ አካል የሆኑትን ሻፍት እና ፍላንጅ በተቋሙ ባለሙያዎች መጠገን ተችሏል፡፡ የጥገና ሥራው ሊቆሙ የነበሩ ጀኔሬተሮችን የማቀዝቀዣ ፓምፕ አካል የሆኑትን ስድስት ሻፍት እና ስድስት ፍላንጅ በራስ ኃይል በመጠገን እስከ ግማሽ ሚሊየን ብር ወጪ ማዳን እንደተቻለ አስታውቀዋል፡፡ ሥራው በውጭ አካላት ይሰራ ቢባል ለአንድ ሻፍት እስከ 50 ሺህ ብር እንዲሁም ለአንድ ፍላንጅ ደግሞ እስከ 35 ሺህ ብር ይጠይቅ ነበር ብለዋል። በጣቢያው መካኒካል ዎርክሾፕ የሚገኙ የተለያዩ ማሽኖችን በመጠገን ወደ ሥራ ማስገባት በመቻሉ ወጪን ከመቀነስ ባለፈ የተሳከ የክህሎትና ቴክኖሎጂ ዕውቀት ሽግግር እየተደረገ መሆኑን እንደሚያሳይ አቶ እሸቱ ተናግረዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 24 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

ፕሮጀክቱ ለሀገር በቀል የሥራ ተቋራጮችና ለአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ዕድል ፈጥሯል …....///......... የቡታጅራ - ወራቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ለሀገር በቀል የሥራ ተቋራጮች እና ለአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ዕድል መፍጠሩን የፕሮጀክቱ የሳይት አስተባባሪ አስታወቁ። አስተባባሪው አቶ ደረጀ ክፍሌ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ ለአምስት የተለያዩ ሀገር በቀል የሥራ ተቋራጮች እና ከ500 በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ፈጥሯል። በፕሮጀክቱ ግንባታ ላይ ተሳትፎ ሲያደርጉ የቆዩት ፕራይም ኢንጂነሪንግ፣ አብዲ ቦሩ ኤሌክትሮ ሜካኒካልና ሲቪል ኢንጂነሪንግ፣ ኢምፓየር ንግድና ኢንጂነሪንግ፣ ኢ.ኤ.ኤም.ቢ የህንፃ ሥራ ተቋራጭ እና ቢራራ ኢንጂነሪንግ የተባሉ ሀገር በቀል የሥራ ተቋራጮች መሆናቸውን አቶ ደረጀ ተናግረዋል። የፕራይም ኢንጅነሪንግ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሔኖክ ዘሪሁን እንደገለፁት በፕሮጀክቱ ግንባታ ላይ ተሳትፎ ማድረጋቸው በዘርፉ የተሰማሩ የሀገር በቀል ሥራ ተቋራጮች አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱ ማሳያ ነው። ድርጅታቸው በፕሮጀክቱ የመቆጣጠሪያ ክፍል፣ የስዊችያርድ፣ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች፣ የአፈር መሸርሸር መከላከያ፣ የውሃ ፍሳሽና የአጥር ሥራዎችን ማከናወኑን ተናግረዋል። አካባቢው ለበርካታ ዓመታት የኤሌክትሪክ ኃይል ጥያቄ ሲቀርብበት የነበረበት መሆኑን የገለፁት አቶ ሔኖክ የፕሮጀክቱ መጠናቀቅ ለማህበረሰቡ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል። በፕሮጀክቱ ግንባታ ላይ ያገኙት ዕውቀትና ልምድ የተቋማቸውን የማኔጅመንት አቅም ለማጠናከር እንዳገዛቸውም ነው አቶ ሔኖክ ያስታወቁት። የአብዲ ቦሩ ኤሌክትሮ ሜካኒካልና ሲቪል ኢንጅነሪንግ ተወካይ አቶ በለጠ አሻግሬ በበኩላቸው በፕሮጀክቱ የኦፕሬሽን ሠራተኞች መኖሪያ ቤትና የመቆጣጠሪያ ክፍሎች ግንባታ ላይ መሳተፋቸውን ገልፀዋል። የፕሮጀክቱን ግንባታ አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ ሁሉም የሥራ ተቋራጮች በቅንጅት ሲሰሩ መቆየታቸውንም ጠቅሰዋል። በማከፋፈያ ጣቢያው ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች መካከል ወ/ሮ ኑሪያ መሐመድ እና አቶ ሙከሚል ፈረጃ እንደገለፁት ደግሞ ፕሮጀክቱ ወጣቱ ተወልዶ ባደገበት መንደር የሥራ ዕድል መፍጠሩ ሥራ ለማግኘት ወደ ሌላ አካባቢ መጓዝን ያስቀራል። ፕሮጀክቱ ከተጠናቀቀ በኋላም ከ18 በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ወጣቶች ቋሚ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር አቶ ደረጄ ጠቁመዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 23 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3