fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 537 مشترک است و جایگاه 8 357 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 176 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 537 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 01 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 22 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 4 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 25.24% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.50% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 921 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 563 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 9 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 02 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 537
مشترکین
+424 ساعت
-357 روز
+2230 روز
آرشیو پست ها
#የፕሮግራም ጥቆማ# የኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ ምክንያቶች ሊቋረጥ ይችላል። ከዋንኞቹ ምክንያቶች መካከል አንዱ ስርቆት ነው። ስርቆት በተቋሙ ላይ ብቻ ሳይሆን ኤሌክትሪክ በሚጠቀሙ ግዙፍ ኢንደስትሪዎ
#የፕሮግራም ጥቆማ# የኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ ምክንያቶች ሊቋረጥ ይችላል። ከዋንኞቹ ምክንያቶች መካከል አንዱ ስርቆት ነው። ስርቆት በተቋሙ ላይ ብቻ ሳይሆን ኤሌክትሪክ በሚጠቀሙ ግዙፍ ኢንደስትሪዎች ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ሊያደርስ ይችላል። የጥቂት ሰዓታት ኃይል መቋረጥ በሚሊየን ብሮች ኪሳራ በተቋማት ላይ እንደሚያደርስ ስንቶቻችን እናውቅ ይሆን? ድርጊቱን መከላከል የሁላችንም ኃላፊነት መሆኑን ስንቶቻችን እንረዳለን? ዛሬ ምሽት ከ3:30 ጀምሮ በኢቲቪ ዜና ቻናል በሚተላለፈው ፍኖተ ብርሃን ፕሮግራም ላይ ዝርዝር መረጃዎችን ያገኛሉ። እንዲታደሙ ጋብዘናል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 29 ቀን 2015 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኤሌከትሪክ ኃይል ከምስረታው አሁን እስካለበት ዘመን ያሉት ታሪካዊ ሂደቶች ቅኝት በሀገራችን ኤሌክትሪክ አገልግሎት መስጠት የጀመረው በናፍጣ በሚሰራ ጀነሬተር ነበር፡፡ ከዚያን ጊዜ በኋላ የተለያዩ ፋብሪካዎች መቋቋም ሲጀምሩ በናፍጧ የሚሰሩ ጀነሬተሮችም እየተስፋፉ መጡ፡፡ በዚህ ዓይነት መንገድ በአዲስ አበባ በተለይም በምኒሊክ ቤተመንግስት ጀመረው አገልግሎት ቀስ በቀስ ወደሌሎች ከተሞች መስፋፋት ጀመረ፡፡ በነገራችን ላይ ኤሌክትሪክን ለህብረተሰቡ መሸጥ የተጀመረው መች እንደሆነ ያውቁ ይሆን? ተቋሙ የጠላት መስሪያ ቤት በሚል ስያሜ አገልግሎት መስጠት የጀመረበትን ምክንያትንስ? እንዲህ ዓይነት አዳዲስ መረጃዎች በፕሮግራሙ ተካተዋል፤ እንዲከታተሉት ጋብዘናል፡፡ https://studio.youtube.com/video/uX6HcfZX1q4/edit “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 28 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

በቡታጅራ - ቡኢ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በ32 ምሰሶዎች ላይ 1 ሺህ 911 ብረቶች በዘራፊዎች ተወስደዋል ………///…….. በቡታጅራ - ቡኢ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ላይ ከሚገኙት 78 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች መካከል በ32ቱ ላይ ከፍተኛ ስርቆት መፈፀሙን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሪጅን 3 አስታወቀ፡፡ በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ከበደ ፉፋ እንደገለፁት እስከ ጥር 2015 ድረስ ስርቆት ከተፈፀመባቸው 32 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዋች 1 ሺህ 911 ብረቶች በዘራፊዋች ተወስደዋል። ከአዳሚ ቱሉ - ቡታጅራ ከሚገኙት 123 ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዋች መካከል ደግሞ በ19 ምሰሶዋች ላይ 1 ሺህ 311 ብረቶች መስረቃቸውን ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል። በሁለቱ መስመሮች ላይ የተፈፀመው ስርቆት በገንዘብ ሲሰላ የተሰረቁ ብረቶችን መልሶ ለመተካት የሚወጣውን ወጪ ሳይጨምር ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚደርስ ገልፀዋል። ከብረቶች በተጨማሪ በኦፕቲካል ግራውን ፋይበር (OPGW) መስመሩ ላይ በስርቆት ምክንያት ጉዳት በመድረሱ የመረጃ ልውውጥ ሥርዓቱን ከመረበሽ ባለፈ ከፋይበር ኪራይ የሚገኘውን ገቢ እንዲቀንስ ያደርጋል ብለዋል። በየጊዜው በስርቆት ወንጀል እጅ ከፍንጅ የተያዙ ሌቦች ቢኖሩም ተመጣጣኝ የቅጣት ውሳኔ እየተሰጣቸው ባለመሆኑ ችግሩ አለመቀነሱን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት እየደረሰ ለሚገኘው ሀገራዊ ችግር የህግ ማዕቀፉን መፈተሸና አፈጻፀሙንም መከታተል እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። በተቋሙ የማዕከላዊ ሪጅን 3 ቴክኒሻን የሆኑት አቶ ሙሉቀን ወልደ ማርያም በበኩላቸው በአካባቢው የሚፈፀመው ከፍተኛ ስርቆት ህብረተሰቡ የሚያነሳውን የኃይል አቅርቦት ጥያቄ ለመመለስ ትልቅ ችግር መፍጠሩን ገልፀዋል። በተለይ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን አዳሚ ቱሉ፣ ባቱና ጊዶ ወረዳዎች እንዲሁም በደቡብ ክልል ቡታጅራና ቡኢ አካባቢዎች ተደጋጋሚ ስርቆት እንደሚፈፀም እና በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በአማካይ ከሁለት በላይ ስርቆቶች እንደሚፈፀሙ ጠቁመዋል። ድርጊቱን ለመከላከል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ጨምሮ የተለያዩ አማራጮች እየተወሰዱ ቢሆንም የሚፈለገውን ውጤት ለማምጣት ብዙ መሰራት እንዳለበት አስተያየት ሰጥተዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 25 ቀን 2015 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሰጠውን ዋንኛ ተልዕኮ ለማሳካት ከተለያዩ ታዳሽ የኃይል ምንጮች ኃይል እያመነጨ ይገኛል፡፡ ለዚህም የተለያዩ የኃይል ማመንጫዎችን፣ ማስተላለፊያ መስመሮችንና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ ተቋሙ ዋንኛ ተልዕኮውን ለማሳካት የያዛቸው ዕቅዶች ምን ይመስላሉ? ምን እየሰራ ነው? ዕቅዶቹን ለመተግበር ፈተና ይሆናሉ ተብለው የሚታሰቡት ጉዳዮችስ? በዚህ እና በተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ቃለመጠይቅ ሰጥተው ነበር፡፡ ቃለመጠይቁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር በመተባበር በሚያቀርበው ሳምንታዊው “ፍኖተ ብርሃን” የቴሌቪዥን ፕሮግራም ላይ ቀርቦ ነበር፡፡ ፕሮግራሙን በተቋማችን ዩትዩብ ቻናል ላይ እንድትከታተሉት ጋብዘናል፡፡ https://www.youtube.com/watch?v=msHi9usO91Q ሌሎች የማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችንን በመከተል ተቋሙን የሚመለከቱ አዳዲስ መረጃዎችን እንደምታገኙ ልንጠቁማችሁ እንወዳለን፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 24 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

የሳፕ ቴክኖሎጂ ትግበራ የተቋሙን የአሰራር ሥርዓት ወደ ዲጂታል እያሸጋገረው መሆኑ ተገለፀ ……..///………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሳፕ ቴክኖሎጂዎች በሥራ ላይ መዋላቸው የአገልግሎት አሰጣጡንና አሰራሩን ወደ ዲጂታል የሚያሸጋግሩ መሆናቸው ተገለፀ። በመጀመሪያው ምዕራፍ የሳፕ ሲስተም አተገባበር እና ያጋጠሙ ችግሮችን ለማረም የተቋሙ ማኔጅመንት አባላት ከአማካሪው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል። በኢትዮጵያ አየር መንገድ ቺፍ ኢንፎርሜሽን ኦፊሰር አቶ ጌትነት ታደሰ እንደገለፁት በመጀመሪያው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ ወቅት በሁለቱም ተቋማት በኩል ከሰው ኃይል፣ ከፋይናንስ፣ ከሥልጠና ዝግጅት፣ ከዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም ከመረጃ አደረጃጀት ጋር የተያያዙ የአፈፃፀም ችግሮች ታይተዋል። በመጀመሪያው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ ወቅት የታዩ ችግሮችን ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ እንዳይሻገሩ ለማድረግ ተቋማቸው መጠነ-ሰፊ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል። እንደ አቶ ጌትነት ገለፃ በመጀመሪያው ምዕራፍ የታዩ ችግሮችን በመቅረፍና መታረም ያለባቸውን ሞጁሎች በማስተካከል ሁለተኛውን ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ በተቀመጠለት ዕቅድና የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ ተቋማቸው ይሰራል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማኔጅመንት አባላት በበኩላቸው የሳፕ ሲስተም በተቋሙ ላይ መተግበር ከጀመረ ወዲህ ውስብስብ የፋይናንስ እና የሰው ኃይል አደረጃጀት አሰራሮችን እያቀለለ መምጣቱንም አብራርተዋል። ከፋይናንስ፣ ከሎጅስቲክስ፣ ከቅጥር፣ ከውጤት ተኮር ምዘና፣ ከሰው ሀብት አስተዳደር እና ከሌሎች የአገልግሎት ትግበራዎች ጋር ተያይዘው የተፈጠሩትን ችግሮች ከአማካሪው ተቋም ጋር በጋራ ለመቅረፍ ቁርጠኛ መሆናቸውንም ገልፀዋል። በመጀመሪያው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ ወቅት የታዩ ክፍተቶችንና የአሰራር ግድፈቶችን ቅድሚያ በመስጠት ለማስተካከል የድርጊት መርሃ-ግብር መዘጋጀት እንዳለበት የማኔጅመንት አባላቱ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። በሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ እንደ ትሬዠሪ፣ የዕቅድ ዝግጅት፣ ግዢ፣ ሳይበር ሴኪዩሪቲ፣ የሰው ኃይል፣ የውስጥ ኦዲት፣ የኢንተርፕራይዝ አሴት፣ የፈንድ እና የንብረት አስተዳደር እንዲሁም ሌሎች የአገልግሎት አሰጣጥ ሞጅሎች ተግባራዊ ይደረጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ነው በውይይቱ ላይ የተነሳው። በአሁኑ ሰዓት ከሁሉም የሥራ ዘርፎች የተውጣጡ የተቋሙ ባለሙያዎች ከአማካሪው ጋር በጋራ በመሆን በሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ሲስተም ትግበራ ላይ እየተሳተፉ ናቸው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 21 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

ከያቤሎ እስከ ሞያሌ ኃይል ተቋርጧል ………////……… ከያቤሎ ወደ ቡኩሉ ጉማ የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ መሰረቱ በጎርፍ ተሸርሽሮ በመውደቁ የተነሳ ከለሊት 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በአካባቢው ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የደቡብ ሪጅን 1 ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ንጉሴ እንዳስታወቁት በአካባቢው ከረጅም ጊዜ በኋላ እየጣለ ያለው ዝናብ ሦስት የብረት ምሰሶዎች መሰረት እንዲሸረሸር አድርጓል፡፡ ይህን ተከትሎ ለሁለቱ የብረት ምሰሶዎች የአፈር መሸርሸር መከላከያ ግንብ የተሰራ ሲሆን የአንደኛው ምሰሶ የአፈር መሸርሸር መከላከያ ግንብ ግንባታ እየጣለ በነበረው ዝናብ ምክንያት አለመጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ዛሬ ለሊት 8፡00 ላይ ከያቤሎ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት አካባቢ አንደኛው ምሰሶ በመውደቁ ወደ ቡኩሉ ጉማ ማከፋፈያ ጣቢያ ይሄድ የነበረው ኃይል ሙሉ በሙሉ መቋረጡን አቶ ምትኩ ገልፀዋል፡፡ በዚህ የተነሳ ቡኩሉ ጉማ፣ ሜጋ እና ሞያሌ ከተሞችን ጨምሮ በኬንያ ድንበር አካባቢ ያሉ ከተሞችና መንደሮች ኃይል ተቋርጧል ብለዋል፡፡ የኃይል መቋረጡን በጊዜያዊነት የእንጨት ምሰሶዎችን በመትከል ለማስተካከል ጥረት መጀመሩን የገለፁት ዳይሬክተሩ አካባቢው ሌላ አማራጭ መስመር ስለሌለው ችግሩ እስኪቀረፍ የአካባቢው ነዋሪዎች በትዕግስት እንዲጠብቁ ጠይቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 21 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

የጽሑፍ ፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአይቲ አፕሊኬሽን 1ኛ የስራ መደብ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ግንቦት 05 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ሜክሲኮ ኬኬር ህንጻ በሚገኘው በተቋሙ ዋና መ/ቤት 20ኛ ፎቅ የጽሁፍ ፈተና ስለሚሰጥ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

photo content
+2

ተቋሙ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት የሚያስችሉ ፕሮጀክቶችን እየገነባ ነው ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ20 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን ለሶዶ ዙሪያ ወረዳ ማህበረሰብ የሚያገለግል የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ እየገነባ እንደሚገኝ የግንባታው ተቆጣጣሪ መሐንዲስ ገለፁ። በኢትዮ - ኬንያ ኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያ ሲቪል መሐንዲስና የማቀነባበሪያ ፋብሪካው የግንባታ ተቆጣጣሪ አቶ ያዕቆብ አለማየሁ እንደገለጹት በህዳር ወር 2015 ዓ.ም የተጀመረውን የግንባታ ሥራ በአጭር ጊዜ አጠናቆ ለማስረከብ እየተሠራ ይገኛል። ፋብሪካው ሲጠናቀቅ የሞላሰስና የእህል ዘሮችን ግብዓት በመጠቀም ተፈላጊ የሆኑ የመኖ ዓይነቶችን እንደሚያቀነባብር እና የከብትና የዶሮ እርባታ ለሚጀምሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ትልቅ ጥቅም እንደሚሰጥ ገልጸዋል። የኢትዮ - ኬንያ ኢንተርኮኔክሽን ፕሮጀክት የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ አያሌው በበኩላቸው ተቋሙ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በሚገባ ለመወጣት የሚያስችሉ ሌሎች ፕሮጀክቶችንም እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ ለሶዶ ዙሪያ ወረዳ ማህበረሰብ ከመኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካው በተጨማሪ በ125 ሚሊዮን ብር ወጪ ነዋሪዎቹ የመብራት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ስምምነት ተፈራርሟል። በሥምምነቱ መሠረት ፕሮጀክቱን በፍጥነት አጠናቆ ለአካባቢው ማህበረሰብ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከሚያናውነው የኃይል መሠረተ ልማት ግንባታ በተጓዳኝ ለህብረተሰቡ ጥቅም የሚሰጡ የመንገድ፣ የጤና፣ የውሃና መብራት አገልግሎቶችን በማሟላት ማህበራዊ ኃላፊነቱን በሚገባ እየተወጣ እንደሚገኝ ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ ህብረተሰቡም በአካባቢው የሚገኙ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች የራሱ ሀብት መሆናቸውን ተገንዝቦ በአግባቡ እንዲጠብቅ አሳስበዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 16 ቀን 2015 ዓ.ም

የኘሮግራም ጥቆማ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር በመተባበር ሳምንታዊ የሬድዮና የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች በማዘጋጀት ወደእናንተ ማድረስ መጀመሩ ይታወቃል፡፡ ዛሬ ከም
የኘሮግራም ጥቆማ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር በመተባበር ሳምንታዊ የሬድዮና የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች በማዘጋጀት ወደእናንተ ማድረስ መጀመሩ ይታወቃል፡፡ ዛሬ ከምሽቱ 12፡10 በኢቢሲ የኦሮምኛ ቋንቋ ቻናል እንዲሁም ምሽት 3፡30 በኢቲቪ ዜና ቻናል የሚቀርቡ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞቻችንን እንድትከታተሉ በአክብሮት እንጋብዛለን።

ከወር በላይ ተቋርጦ የቆየው የዳውሮ ዞን ኤሌክትሪክ ማግኘት ጀምሯል ......///......... በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በዳውሮና ኮንታ ዞኖች ከአንድ ወር በላይ ተቋርጦ የቆየው የኤሌክትሪክ
+7
ከወር በላይ ተቋርጦ የቆየው የዳውሮ ዞን ኤሌክትሪክ ማግኘት ጀምሯል ......///......... በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በዳውሮና ኮንታ ዞኖች ከአንድ ወር በላይ ተቋርጦ የቆየው የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት መጀመሩን በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የደቡብ ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንደገለፁት በዳውሮ ዞን አባ ቀበሌ የሚገኘው 132/33 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ የማከፋፈያ ጣቢያ ላይ በደረሰ የቴክኒክ ብልሽት ምክንያት ከጣቢያው ኃይል ሲያገኙ በነበሩት የሁለቱ ዞኖች ወረዳዎችና ቀበሌዎች ከመጋቢት ስድስት ጀምሮ ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ቆይቷል። በማከፋፈያ ጣቢያው ላይ ተከስቶ የነበረውን የቴክኒክ ብልሽት ጠግኖ ሥራ ለማስጀመር ትራንስፎርመር ከአዲስ አበባ ወደ ሥፍራው በማጓጓዝ ችግሩን ለመፍታት መቻሉን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ማከፋፈያ ጣቢያው ከትናንት ሚያዚያ 12 ቀን 2015 ዓ.ም ምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ መደበኛ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል:: ከአንድ ወር በላይ የቆየውን ችግር ለመፍታት ተቋሙ ሲያደርግ የነበረውን ጥረት በመረዳት በትዕግስት ለጠበቁ የዞኖቹ ነዋሪዎች በተቋሙ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et ታህሳስ 13 ቀን 2015 ዓ.ም

የምስራቅ ኢትዮጵያ አካባቢ ኃይል አግኝቷል ..........///.......... በከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ በተፈፀመ ስርቆት ኃይል የተቋረጠበት የምስራቅ ኢትዮጵያ
የምስራቅ ኢትዮጵያ አካባቢ ኃይል አግኝቷል ..........///.......... በከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ በተፈፀመ ስርቆት ኃይል የተቋረጠበት የምስራቅ ኢትዮጵያ አካባቢ በአማራጭ መስመር ኃይል አግኝቷል። በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የምስራቅ ሪጅን 1 መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሐመድ እንደገለፁት ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ከቆቃ በአማራጭ ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ የተደረገው ጥረት ውጤት በማስገኘቱ የምስራቅ ኢትዮጵያ ከተሞችና ጅቡቲ ኃይል ማግኘት ችለዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1444ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላም፣ የደስታ፣ የፍቅር እና የጤና እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ! አሸብር ባልቻ፣ የኢትዮ
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1444ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላም፣ የደስታ፣ የፍቅር እና የጤና እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ! አሸብር ባልቻ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ

በስርቆት የተነሳ በምስራቅ ኢትዮጵያ ሙሉ በሙሉ ኃይል ተቋርጧል ..........///.......... ከአዋሽ ወደ ድሬዳዋ በተዘረጋው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ ሁ
በስርቆት የተነሳ በምስራቅ ኢትዮጵያ ሙሉ በሙሉ ኃይል ተቋርጧል ..........///.......... ከአዋሽ ወደ ድሬዳዋ በተዘረጋው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ ሁርሶ አካባቢ በተፈፀመ ስርቆት የምስራቅ ኢትዮጵያ ትልልቅ ከተሞችና አካባቢያቸው ሙሉ በሙሉ ኃይል መቋረጡን በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የምስራቅ ሪጅን 1 መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሐመድ እንደገለፁት በተፈፀመው ስርቆት የተነሳ ድሬዳዋ፣ ሐረር፣ ጅግጅጋና ሌሎች የምስራቅ ኢትዮጵያ ከተሞችን ጨምሮ ወደ ጅቡቲ ኤክስፖርት የሚደረግበት መስመር ኃይል ተቋርጧል። የተቋረጠውን መስመር ለመጠገን የቴክኒክ ባለሙያዎች ቡድን መሰማራቱን የገለፁት ዳይሬክተሩ ኃይል ለተቋረጠባቸው አካባቢዎች ከቆቃ በሌላ አማራጭ ኃይል ለመስጠት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል። የኃይል መቋረጡ የረመዳን ፆም ፍቺ ላይ ተፅዕኖ እንዳያሳድር በምስራቅና በማዕከላዊ ሪጅን የጥገና ባለሙያዎች በቆቃና በሁርሶ አካባቢ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም አስታውቀዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ2015 ዓ.ም የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ መልካም
እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ2015 ዓ.ም የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ፡፡  በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የፍቅር እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለሁ፡፡   አሸብር ባልቻ፣ ዋና ሥራ አስፈፃሚ